Tuesday, February 23, 2016

በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ አድማሱን እያሰፋ ነው ተባለ

ኢሳት (የካቲት 15 ፥ 2008)
ሰሞኑን  በተለያዩ የኦሮሚያ ክልሎች ዳግም ያገረሸው ተቃውሞ ከሳምንቱ መገባደጃ ጀምሮ በምስራቅና ምዕራብ ሃረርጌ አካባቢዎች በሚገኙ የገጠር ከተሞች መቀጠሉን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል።
ምዕራብ ወለጋን ጨምሮ በተለያዩ የክልሉ ከተሞች እየተካሄደ ባለው ተቃውሞ በጸጥታ ሃይሎች በሚገደሉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ በመሄድ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በስፍራው ያለው የጸጥታ ሁኔታ ባለመረጋጋቱም የሟቾችን ቁጥር በአግባቡ ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን፣ የተለያዩ አካላት እስከ 20 የሚደርሱ ሰዎች በሳምንቱ መገባደጃ ብቻ መገደላቸውን ይገልጻሉ።

No comments:

Post a Comment