Sunday, November 30, 2014

በህዳር 27ቱ ሠላማዊ ሰልፍ እንሳተፋለን !!! ከኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሠማ ኮሚቴ የተላለፈ የአጋርነት መግለጫ

ሠማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች የአንድነት መድረክ በመፍጠር ሰላማዊ ሰልፍ ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ/ም ለማድረግ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልፀው የሐገሪቱ ህዝብ በቦታው በመገኘት ድምፁን እንዲያሠማ ባሳወቁት መሠረት የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሠማ ጊዜያዊ ኮሚቴ እና የማህበሩ አባላት በሠላማዊ ሠልፉ ላይ ከሌላው የሐገራችን ህዝብ ጋር በመሆን ድምፃችንን እንደምናሠማ እየገለፅን ለሠላማዊ ሠልፉ መሣካት የበኩላችንን ደርሻም ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን ስንገልጽ በዚህ በጨለማ ዘመን ኃላፊነት ወስደው ይህንን ታላቅ ሠለማዊ ሠልፍ ላዘጋጁት የሠለማዊ ሠልፉ አዘጋጆች ምስጋናችንን በማቅረብ ነው፡፡
እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያን እያስተዳደሩ ሳይሆን እየገዙ ያሉት ብዙሀኑ ባለስልጣናት ከትምህርት አለም እር

ኩማ ደመቅሳ በዋሽንግተን ዲሲ ሆስፒታል ተኝተዋል

(ኢየሩሳሌም አርአያ)

አቶ ኩማ ደመቅሳ በዋሽንግተን ዲሲ ሆስፒታል ተኝተው እንደሚገኙ ታማኝ ምንጮ አስታወቁ።

ኩማ በጭንቅላት እጢ (ቲዩመር) በሽታ ምክንያት ለከፍተኛ ህክምና ዲሲ መምጣታቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የመዳን ተሳፋቸው 90 በመቶ የተመናመነ መሆኑን ከሃኪሞች እንደተገለፀላቸው አስታውቀዋል።

ከባለቤታቸው ጋር የመጡት ኩማ ሆስፒታል ከመግባታቸው በፊት ባለፈው ሳምንት ማርዮት ሆቴል አርፈው እንደነበረ ሲታወቅ ሁለት ኢትዮጵያውያንን በሆቴሉ መተላለፊያ ላይ ሲያገኙ ክፉኛ ደንግጠው እንደነበረ ማወቅ ተችሏል። አሜሪካ -ዲሲ መምጣታቸው እንዳይታወቅባቸው የሚጠነቀቁትና ፍርሃት የሚታይባቸው ኩማ የስጋታቸው ምንጭ እንደሌሎች ባለስልጣናት ተቃውሞ ይገጥመኛል በሚል እንደሆነ ሲታወቅ የማያውቁትን ስልክ እንደማያነሱ ማረጋገጥ ተችሏል።

በተለይ የመዳን ተስፋ እንደሌላቸው ከተነገራቸው በኋላ ከኢትዮጵያ የሚደወልላቸውን ስልክ እንደማያነሱ ታውቋል። ኩማ ደመቅሳ ከ1993ዓ.ም በፊት ሙስና ውስጥ እንዳልገቡና ነገር ግን የአዲስ አበባ ከንቲባ ከሆኑ በኋላ በከፍተኛ ሙስና ከተዘፈቁት ባለስልጣናት ተርታ እንደተመደቡ ይታወቃል።


Saturday, November 29, 2014

የሕወሓት ሰዎች በብአዴን እና በኦሕዴድ ባለስልጣናት ላይ በአዲስ መልክ ሽብር እየፈጠሩ ነው::

ምንሊክ ሳልሳዊ
- የሕወሓት ስጋት ውስጥ ውስጡን ክሻእቢያ ጋር ግንኙነቱን እንዲያጠናክር አድርጎታል::
- የኢትዮጵያ ሕዝብ ውስኝ የለውጥ ወቅት ላይ መሆኑን አውቆ አደባባይ በመውጣትወያኔን ሊያስወግድ ይገባል::ከፊታችን አደጋ አለ በሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የገቡት እና በመፍትሄፍለጋ ስብሰባዎች የተወጠሩት የሕወሃት ሰዎች ክከፍተኛ ባለስልጣናት ጀምሮ እንከ በታች ሹሞች ድረስ በብአዴንና በኦህዴድ ባለስልጣናት ላይ ክፍተኛ የማስፈራራት እና የማዋከብ ሽብር እየፈጸሙ መሆኑን አንድ ከፍተኛ የኢሚግሬሽን እና ደህንነት ባለስልጣን ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል::በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ የሚገኙ የብአዴን እና የኦሕዴድ አባላት በግል እንዳይገናኙ እንዲሁም ከመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች ጋር እንዳይገናኙ ከፍተኛ የሆነ ክትትል እየተደረገባቸው ሲሆን በባለስልጣናት ደረጃ እያንዳንዱ እንቅስቃሴ የሚያጠና የደህንነት ቡድን የተመደበባቸው ሲሆን ስልኮቻቸውም እየተጠለፉ መሆኑን እኚሁ ባለስልጣን ተናግረዋል::

የብአዴንና የኦሕዴድ ሰዎችን ከፍተኛ አነስተኛ እና ጥቃቅን በሚል ተከፍለው በሕወሓት እየተሰለሉ ስልካቸው እየተጠለፈ ሲሆን እንደ በግ የሚታዘዝላቸው የደቡብ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ውስጥ ዘልቀው እንዳይገቡ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑ ታውቋል::ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የሆኑ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት መቀራረብ እና አብሮ መዋል የሕወሓት ሰዎችን ማሳሰቡን እና የደህንነት ክትትል እያደረጉባቸው እንደነበረና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከደመቀ መኮንን እና ከሙክታር ከድር ጀምሮ እስከ በታች የፌዴራል ባለስልጣኖች ላይ ከፍተኛ ስለላ እየተካሄደ ምንጮች መረጃ ሰተው እንደነበር ሲታወቅ ይህ በአሁኑ ወቅት በእጥፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ታውቋል::ሁኔታዎች መልካም አይደሉም ከፊታችን አደጋ ተደቅኗል::ለውጥ ያስፈልጋል::የሚሉ የተቆጡ ድምጾች በስፋት በኢሕኣዴግ አባላት እየተሰሙ ያለበት አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው ሕወሓት በግል እና በጋራ ባለስልጣናቱ ላይ ከፍተኛ ማስፈራራት እና ዛቻ እያደረገባቸው መሆኑን የተናገሩት ምንጮቹ ኢሕአዴግን ለመናድ ብትሞክሩ ሃገሪቷ ትበታተናለች::እንደ ሱማሊያ መንግስት አልባ ሆና እንደ ሩዋንዳ ትበጠበጣለች እያሉ ከማስፈራራትም አልፎ በግል የተነከራችሁበት ሙስና አደባባይ እናወጣዋለን:: እኛን ማንም ሊጠይቀን አይችልም ቁልፉ እኛ ጋር ነው የሚሉ በኣደገኛ መርዞች የተሞሉ ማስፈራሪያዎች መሰንዘር ክጀመሩ እንደቆዩ ተገልጿል::የኢትዮጵያን ህዝብ እንደ ሶማሌ እና ሩዋንዳ ማስብ ጅልነት ነው::የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ እንጂ ፍጅት ስለማይፈልግ ኢሕ አዴግ ሲፈርስ ሕወሓት እንደሚያስበው ሳይሆን ትልቅ ሰላም በሃገሪቱ ላይ ይሰፍናል ያሉት ምንጩ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ባለስልጣናት የየቀን ሪፖርት እና ግንኙነት በተመለከተ ማን ከማን ጋር እንደዋለ ማን እነማን ቤት እንደሄደ በመከታተል እየቀረበ ሲሆን የሃገሪቱን የደህንነት ቢሮ በጋራ የሚመሩት ጸጋዬ:ጌታቸውና ደብረጺሆን በየቀኑ ለትግሪኛ ተናጋሪ ደህንነቶች በአጫጭር ስብሰባዎች መመሪያ እያወረዱ ከመሆኑም በላይ አደጋ ውስጥ መሆናቸውን እየደጋገሙ እንደሚናገሩ ምንጮቹ አክለዋል::በአሁን ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ ወሳኝ የትግል ወቅት ላይ መሆኑን በማወቅ የበሰበሰውን የወያኔ አምባገነን ስርአት ለመጣል በጋራ አደባባይ በመውጣት የሚያካሂደውን አብዮት የመከላከያ ሰራዊት የፖሊሱ እና የብአዴን እንዲሁም የኦሕዴድ ፓርቲ ለውጡን እንደሚደግፉት የህዝቡን መነሳሳት እየጠበቁ መሆኑን እና ሕወሓት ከመስጋቱ የመጣ ከሻእቢያ ጋር በውስጥ ግንኙነቱን አጠናክሮ መቀጠሉን እንዲሁም ለተመረጡ የኤርትራ ስደተኞች የደህንነት ትምህርት የተሰጠ እንደሚገኝ እኚሁ ባለስልጣን መረጃ አድርሰውኛል:

Unipolar power in decline, new cold war & EPRDF in fear

By Robele Ababya, 28/11/2014I would like to start writing this piece, centered on respect for basic human rights, with this quote derived from the address to the European Parliament by His Holiness Pope Francis on 25 November 2014:- “Promoting the dignity of the person means recognizing that he or she possesses inalienable rights which no one may take away arbitrarily, much less for the sake of economic interests.” These are immortal words delivered to the August EU Parliament received with standing ovation and warm applause of the distinguished audience.It is needless to elaborate that genuine fighters for freedom, unity, equality, democracy and prosperity under the supreme rule of law should understand the alignment of global powers at play in terms of politics,

Court hands down prison sentence for an Eritrean trained terror convict

The Federal High Court 19th Bench handed Gashaw Shibabaw, a member of the outlawed Ethiopian People Patriotic Front (EPPF), a prison sentence of four years and eight months without probation.

The convict received shelter, training and logistical assistance from the Eritrean regime under the auspices of the terrorist group EPPF, before crossing into Ethiopia with his full military gear to launch terrorist attacks in the country.

In a statement the convict gave to police, he admitted to joining EPPF, a terrorist group supported by the notorious regime in Asmara and received military and political training in a place called Erena.

Two years ago, the convict crossed into Ethiopia with a small insurgent group to mount terrorist attacks in the country and was involved in several skirmishes with local security personnel, before being arrested in May, 2013.

The Federal Prosecutor brought terrorism charges against the individual and the convict admitted to joining an outlawed terrorist organization, to receiving military and political training in Eritrea, tirelessly working to carry out the group’s missions, illegally crossing into Ethiopia through River Tekeze with his full military gear, forcefully recruiting farmers to join the terrorist group, engaging Ethiopian security forces militarily and attempting to attack government institutions.

As such, the court sentenced the convict to serve a prison term of four years and eight months without probation.

በሚሰሩት መንገዶች ደስተኞች አይደለንም ሲሉ የባህርዳር ነዋሪዎች ገለጹ

ኢሳት ዜና :- የገዢው መንግስት በምርጫ 2007 ያለውን ተቀባይነት ለማጠናከር በማሰብ የተለያዩ የህብረተሰቡን ክፍሎች በየክፍለ ከተማው በማሰባሰብ የተሰሩ ስራዎችን በማቅረብ ለመመስገን ሙከራ ቢያደርግም፤ተሰብሳቢዎች ግን ምንም እንዳልተሰራና ተሰራ የተባለውም ችግር ያለበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የመንገዶች መበላሸት ያሳሰባቸው ነዋሪዎች በአካባቢው ላሉ አመራሮች የስራውን የጥራት ጉድለት ቢያሳውቁም የተስተካከለ ነገር እንደሌለ ገልጸዋል፡፡ “በ2006 የተሰራው ስራ በሙሉ ዜሮ ነው፡፡ በየክፍለ ከተማው ያለው የሰራተኛ ቁጥር ከ 8 ወደ 102 እንዳደገ ብትነግሩንም ለኛ የተረፈን የባለስልጣን ጋጋታ እንጅ የህዝቡን ስራ የሚሰሩት በሳምንት ሁለት ቀን ብቻ ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜየችሁን በስብሰባና የፖለቲካ ስራ በመስራት ታሳልፋልችሁ ” በማለት የተሰራው ስራ ለፖለቲካ ትረፍነት እንጅ ለህዝብ ተብሎ እንዳልሆነ የተናገሩ ወገኖች አሉ፡፡ ሌላው ቅሬታ አቅራቢ በአሁኑ ሰዓት ያሉ የኮብል ስቶን ስራዎች የመኪና ጎማ የሚደበድቡ ጥራት የሌላቸው በመሆናቸው በመንገዶች ዙሪያ የሚሰሩት የተፋሰስ ስራዎች ሁሉ ጥራታቸውን ያልጠበቁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

Friday, November 28, 2014

የእስክንድር ነጋ ያገባኛል ባይነት!

በላይ ማናዬ
‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል!››

ይህን ያለው ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ነው፡፡ እስክንድር ነጋን ካወኩት ወዲህ እንደዛሬ በኃይለ ቃል ሲናገር ሰምቼው አላውቅም፤ ወይም ትዝ አይለኝም፡፡ ዛሬ (ህዳር 19/2007 ዓ.ም) እኩለ ቀን ላይ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሆኖም ሁኔታው ሁሉ እንደማንኛውም ቀን አልነበረም፡፡ በር ላይ ስደርስ በርከት ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት ሰሞኑን እያካሄዱት ያለውን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ በማስመልከት እስክንድር ነጋን፣ አንዱዓለም አራጌን እና ሌሎችንም ሊጠይቁ በቦታው ተገኝተው ነበር፡፡

በጠዋት ቂሊንጦ የሚገኙ ወዳጆቼን ጠይቄ አብረውኝ ከነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጋር ነበር ወደ ቃሊቲ ያመራሁት፡፡ ቃሊቲ የተገኘው ሰው ሁሉ መጠየቅ የሚፈልገውን ሰው እና ሙሉ አድራሻውን እያስመዘገበ ሳለ በመሐል እኔም እስክንድርን መጠየቅ እንደምፈልግ ነግሬ ተመዘገብኩ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ግን ስማችሁ ከዚህ ቀደም ያልተመዘገባችሁ አሁን መግባት አትችሉም መባሉን መዝጋቢ ፖሊሱ አረዳን፡፡ እኔ እና ትንሽ ሰዎች መግባት ስንችል አብዛኛው ሰው ግን መግባት እንደማይችል ተነገረን፡፡

በዚህ ሁኔታ እስክንድር ጋር ደርሰን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ አንድ የአንድነት ፓርቲ አባል ሰሞኑን ፓርቲያቸው እስረኞችን በተመለከተ በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ እየተሰራ ያለውን ስራ ለእስክንድር ያብራራለት ጀመር፡፡ እስክንድር በተለመደ ጥሞናው ሲያዳምጠው ቆይቶ፣ በግሉ የተሰማውን እና መሆን ቢችል ያለውን ነጥብ ተናገረ፡፡ በመሐል ወጣቱ የአንድነት አባል ወደ እስክንድር ጠጋ ብሎ ሌሎች ተጨማሪ ጉዳዮችን ሲነግረው ድንገት አንድ የፖሊስ አዛዥ ጨዋታቸውን እንዲያቆሙና እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እንዲገባ፣ ወጣቱ የአንድነት አባል ደግሞ ወደ ውጪ እንዲወጣ በትዕዛዝ ማጣደፍ ያዘ፡፡

ይህኔ እስክንድር ለስለስ ባለ አነጋገር ምንም እንዳላጠፋን በመግለጽ ፖሊሱ መረጋጋት እንዳለበት አስረዳ፡፡ የፖሊስ አዛዡ ግን ጭራሽ ብሶበት ወጣቱ በቶሎ እንዲወጣ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹ፖለቲካ ማውራት አቁሙ› የሚል ሆነ፡፡ ይህን ተከትሎ እስክንድር ድንገት በኃይለ ቃል ተናገረ፡፡ ‹‹መብቴን አሳልፌ አልሰጥም፤ የትም ብሆን ስለመብቴና ሀገሬ ያገባኛል፡፡ እዚህ ከሚጠይቁኝ ሰዎች ጋር የፈለኩትን ማውራት እችላለሁ፡፡ እናንተ ከፈለጋችሁ በር ላይ መልሷቸው እንጂ እኔ ጋር ከመጡ በኋላ ስለሀገሬ ከእነሱ ጋር መነጋገር መብቴ ነው፡፡ አዎ የትም ቦታ ብሆን፣ መቼም ቢሆን ስለ ሀገሬ ያገባኛል! የማወራው ስለ ሰላማዊ ትግል፣ ስለህጋዊ ትግል ነው!›› አለ እስክንድር በስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡

በግሌ እስክንድር እንዲረጋጋ፣ ሁኔታው ግን ያልተገባ እንደሆነ ገለጽኩ፡፡ ፖሊሱ ግን ሊረጋጋ አልቻለም፡፡ እስክንድርን ይዞት ሄደ፡፡ ‹‹በርቱ! እንቅስቃሴያችሁ ህጋዊና ሰላማዊ ይሁን እንጂ ትግላችሁን ቀጥሉ!›› ሲል እስክንድር ወደ እስር ቤቱ እየገባ ተናገረ፡፡ የፖሊስ አዛዡም ከእስክንድር ጋር የነበረንን ቆይታ ሰዓቱ ሳይደርስ ገታው፡፡ የእስክንድር ያገባኛል ባይነት አስደመመኝ፡፡ እስር ቤት ሆኖም፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም እስክንድር ስለ ሀገሩ እንደሚያገባው በስሜት ተናገረ፡፡ መብቱን መቼም ቢሆን አሳልፎ እንደማይሰጥ አስረገጠ፡፡

ስለ ያገባኛል ባይነት ሳስብ በጠዋት ቂሊንጦ ያገኘኋቸውን የዞን 9 ጦማሪዎች አስታወስኩ፡፡ ‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!› ይላሉ ወጣቶቹ ጦማሪያን፡፡ ከአብርሃ ደስታ ጋር አብረው ያገኘኋቸው እነ በፍቃዱ ኃይሉ እና አጥናፍ ብርሃኔ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ አወጉኝ፡፡ ‹‹ህወሓት አንድ ወይም ሁለት ነባር የህወሓት ባለስልጣናትን በሽብር ከከሰሰ ስርዓቱ እንዳበቃለት እቆጥራለሁ፡፡ ምክንያቱም ሽብር ማታለያ መሆኑ ይቀራል›› አለኝ በፍቃዱ ኃይሉ፡፡ አብርሃ ደስታ ቀበል አድርጎ ‹‹እናት አልጋነሽ በሽብር ስትከሰስ በጣም ብዙ ሰው ተቃውሞ ነበር›› አለ፡፡ አጥናፍ በበኩሉ ‹‹ቄስና ሸህ ሽብርተኛ እየተባለ አይደለም እንዴ›› በማለት ጠየቀ፡፡

አብርሃ ደስታ አንድ ነገር በኃይል እንደሚቆጨው ተናገረ፡፡ ምን እንደሆነ ጠየቅሁት፡፡ ‹‹ብዙ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሳላደርግ መታሰሬ ይቆጨኛል!›› አለ፡፡ በፍቃዱ በበኩሉ፣ ‹‹እኔም የገባኝ ነገር ያለውን የሰላማዊና ህጋዊ የመስሪያ ልክ አለመስራታችን ነው፡፡ አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው እንዲህ ለሚያስሩን ስንት ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን እንኳ ሳናደርግ በትንሽ ነገር በርግገው እዚህ ሲያስገቡን ይቆጨኛል›› በማለት ሀሳቡን ቀጠለ፡፡ ‹‹በእርግጥ አንድ ሰው አሁን መጠንቀቅ ያለበት የሚሰራው ስራ ህጋዊ መሆን አለመሆኑን እንጂ፣ ይህን ካደረኩማ ያስሩኛል የሚለውን መሆን የለበትም፡፡ እነሱ ከፈለጉ ያስሩሃል፤ ስለዚህ መብትህን ተጠቅመህ መታሰሩ ይሻላል እንዲሁ ምንም ሳይሰሩ ከመግባት›› ሲል አብርሃ ሀሳቡን አካፈለ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች 8 ሺህ ብር ዋስትና ተጠየቀባቸው

ለህዝባዊ ስብሰባ ሲቀሰቅሱ በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ዮሴፍ ተሻገር እንዲሁም የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል የሆነው ሲሳይ በዳኔ ዛሬ ህዳር 19/2007 ዓ.ም ሾላ አካባቢ በሚገኘው ፍርድ ቤት ቀርበው 8 ሺህ ብር ዋስትና እንዲያስይዙ ተወስኖባቸዋል፡፡

መርማሪው ም/ሳጅን ዳንኤል ከበደ የምርመራ መዝገቡ እንዳለቀ ቢያምኑም ‹‹ተጠርጣሪዎቹ ከወጡ ተመሳሳይ ወንጀል ስለሚፈጽሙ ተጨማሪ ቀነ ቀጠሮ ይሰጥልን›› ብለው ተከራክረዋል፡፡ ከታሳሪዎቹ መካከል አቶ ዮሴፍ ‹‹በህጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ አመራሮች በመሆናችን ወጥተንም የምንሰራው ህጋዊ ስራ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች በመሆናችን የዋስትና መብታችን ሊጠበቅልን ይገባል›› ሲሉ ተከራክረዋል፡፡

አቶ ሲሳይ በዳኔ በበኩሉ ‹‹አሁንም በምርመራ ወንጀል መስራታችን የሚያሳይ ነገር አላገኙም፡፡ ምንም አይነት ወንጀል ሳንሰራ ነው የታሰርነው፡፡ ቋሚ መኖሪያ ያለን ሰዎች ነን፡፡ በመሆኑም ዋስትናችን ሊከበርልን ይገባል›› ሲል ተከራክሯል፡፡ በመጨረሻም ዳኛ አያሌው ደስታ ሁለቱ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እያንዳንዳቸው 4 ሺህ ብር የገንዘብ ማስያዢያ (ዋስ) እንዲያቀርቡ ወስነውባቸዋል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ ለእስር የተዳረጉት ሌሎች ሁለት የፓርቲው አባላት ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ ሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ እንደተሰጠባቸው የሚታወስ ነው፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ሰማያዊ ፓርቲ ባደረጋቸው ሰልፎች በፖሊስ የሚያዙ የፓርቲው አባላት በተደጋጋሚ የገንዘብ ዋስትና ሲጠየቅባቸው ቆይቷል፡፡

“Breaking the Cycle of Dysfunction in Ethiopians Institutions forum”

November 18, 2014. Washington, DC–. At the recent  in Washington D.C. on November 15, it was quite evident that Ethiopia does not lack for gifted people who possess the essential capabilities, virtue, and experience needed to build a New Ethiopia.

It was inspiring to hear from a wide array of speakers who portrayed the qualities of courage, strength, faith, wisdom, integrity, and an attitude of respect towards others, even when some differences of opinion emerged. This was a civil dialogue, meant to be a model for how Ethiopians with grievances against each other or simply of diverse backgrounds might come together to forge a better future. People came together as people first. Then, they came together around shared values—a desire to see a society where truth, freedom, justice, civility, opportunity, and harmony could prevail for all its people.Discussions both within the forum and outside the formal discussions were lively as people, most of whom had never met, shared opinions, ideas, and stories. New connections were made. The forum, Breaking the Cycle of Dysfunction in Ethiopians Institutions was unique in that it focused on providing a structured venue where Ethiopians could  It was broken into two sessions.

ቅኝ ግዛት እና ሕዝቡን ቢራ እንዲጠጣ ማበረታታ ምን እና ምን ነበሩ? ዳቦ ሳንጠግብ እና የምናነበውን ጋዜጣ ሁሉ ዘግተው አዕምሯችንን እያደነዘዙ የቢራ ፋብሪካ መደርደር ምን ይባላል?

በባዕዳን በቅኝ ግዛት ተይዘው የነበሩ ሀገሮች ሁለት ዋና ዋና ሀብታቸውን አጥተዋል።( በነገራችን ላይ በባዕዳን ቅኝ ግዛት የተያዙቱኑ ነው ያልኩት እንጂ ፕሬዝዳንት መሆን ያማረው ሁሉ ቅኝ ግዛት ነበርኩ እያለ የእራሱን እና የህዝቡን ክብር ገደል የሚጨምረውን አይመለከትም።)ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ካልተገዙ ጥቂት ሃገራት አንዷ ነች።ኢትዮጵያውያንን ቡና አትጠጡ ቢራ ብቻ ጠጡ ብሎ ያስገደዳቸው ቅኝ ገዢ አልነበረባቸውም።እድሜ በደማቸው ሀገራቸውን አስከብረው ለኖሩት አባቶቻችን እና እናቶቻችን።እኛ እንደ ብዙ የአፍሪካ ሃገራት ዋና ከተማችንን የቅኝ ገዢዎች አልመረጡልንም። አለመምረጥ ብቻ አይደለም የከተሞቻችን ህንፃዎች እና መንገዶች በአብዛኛው የተሰሩት በእራሳችን መሀንዲሶች ነው።የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃቤት ፕላን ሲቀርብ አንድ ፈረንሳዊ መሃንዲስ ባለ ብዙ ፎቅ እንዲሆን አድርጎ አቅርቦ ነበር።በኃላ ግን ኢትዮጵያዊው መሃንዲስ (ስማቸውን አላስታውስም) ወደ ንጉሡ ቀርበው ”ይህንን ያህል ፎቅ ብዙ ሕዝብ በእየለቱ በሚወጣበት እና በሚገባበት ህንፃ ላይ አይሆንም።ይህ ማለት ከሀገሩ ሊፍት እንድናስገባ ሊያደርገን ነው።ከእዝያ ይልቅ ወደጎን ነው መለጠጥ ያለበት” ብለው ባቀረቡት ሃሳብ መሰረት ማዘጋጃ ቤቱ ወደጎን እንዲሰፋ ተደረገ።በእዚህም ብዙ ሕዝብ ለጉዳዩ በቀላሉ ለመውጣት እና ለመግባት ቻለ።ቅኝ ገዢዎች መሰረተ ልማቱን እንዴት ለሀገራቸው ኢንዱስትሪዎች መጋቢ እንዲሆን አድርገው እንደሚቀርፁ የሚያመላክት አንዱ ማሳያ ነው የማዘጋጃ ቤቱ ህንፃ ጉዳይ።

የፓርቲዎች ትብብር ለአዳሩ ሰልፍ ቦታው መስቀል አደባባይ እንዲሆን ወስኗል

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለአዳሩ ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ አስገባ
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ.ም ለሚደረገው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የእውቅና ደብዳቤ አስገባ፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የገባው ደብዳቤ በሰማያዊ፣ መኢዴፓ እና ኢብአፓ ተፈርሞ የገባ ሲሆን የእውቅና ደብዳቤውንም ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ሊቀመንበርና የትብብብሩ ም/ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ፣ አቶ ግርማ በቀለ ከኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና የትብብሩ ፀኃፊ እና የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ አቶ ኑሪ ሙደሲር አስገብተዋል፡፡

የትብብሩ አመራሮች ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ በሄዱበት ወቅት የአቶ ማርቆስ ተወካይ ለሆኑት አቶ ፈለቀ አበበ ደብዳቤውን ለመስጠት ጥረት ቢያደርጉም ተወካዩ ‹‹የከንቲባ ጉዳዮች ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው የለም፡፡ እሱ ካልመራበት መቀበል አንችልም›› በሚል ደብዳቤውን አልቀበልም እንዳሏቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ወደ አቶ አሰግድ ቢሮ ቢያቀኑም እንዳላገኙዋቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ሆኖም የትብብሩ አመራሮች ደብዳቤ መስጠት እንጂ ደብዳቤ ማስመራት የሰራተኞቹ እንጂ የእነሱ ስራ እንዳልሆነ በመግለጽ ደብዳቤውን ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ታመዋል የተባሉት የአቶ ማርቆስ ተወካይ የሆኑት አቶ ፈለቀ ቢሮ በአራት ምስክሮች ፊት አስቀምጠው መምጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ አመራሮቹ የእውቅና ደብዳቤውን አቶ ፈለቀ ቢሮ አስቀምጠው ከመውጣታቸውም ባሻገር በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በፈጣን መልዕክት (ኢ ኤም ኤስ) በሪኮመንዴ ቁጥር eg157416502et መላካቸውን ገልጸዋል፡፡

የአዳር ሰላማዊ ሰልፉ ህዳር 27 ከጠዋቱ 3 ሰዓት ተጀምሮ ህዳር 28 ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቅ ሲሆን ቦታውም መስቀል አደባባይ ላይ እንደሚሆን መወሰኑ ታውቋል፡፡

የትብብሩ አመራሮች የእውቅና ደብዳቤውን ለማስገባት በሄዱበት ወቅት በቦታው የትብብሩ አመራሮች የሚያውቋቸው ደህንነቶች ባለ ጉዳይ በመምሰል ይመላለሱ እንደነበርና ፖሊሶችም ይከታተሉ እንደነበር ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

Thursday, November 27, 2014

ተማሪዎች፣ መምህራን እና የተቋማት ፕሬዚዳንቶች ለአመጽ ተነሱ!

ዘረኛውና አምባገነኑ የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከላትነት ለይቶ የማያይ ስለመሆኑ በተቋማቱ ውስጥ የሚደረጉ ተግባራት ማረጋገጫዎች ናቸው። ለዚህ ተግባሩ በሰነድ ደረጃ መቅረብ ከሚችሉት የቅርብ ጊዜ ማስረጃዎች ዋነኛው በህዳር 2007 ዓ.ም. በሥራ ላይ የዋለው “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል” የተሰኘው በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላለፈው ሰነድ ነው። ይህ ሰነድ፣ የህወሓት አሳፋሪ የትምህርት ፓሊሲ ባፈጠጠ መልኩ የተገለፀበት፤ የኢፌዴሪ መንግሥት ተብሎ በሚጠራው የህወሓት አገዛዝ ተቋም እና በህወሓት/ኢህአዴግ ፓርቲ መካከል ለይምሰል እንኳን ልዩነት አለመኖሩ በግላጭ የሚታይበት ሰነድ በመሆኑ በዚህ ርዕሰ አንቀሳችን በስፋት ልንዳስሰው ወስነናል።ሰነዱ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ መርዙን መርጨት የሚጀምረው ገና በመግቢያው ስለማንዋሉ አስፈላጊነት ሲገልጽ ነው። ማንዋሉ “ከምንም በላይየብጥብጥና የሁከት መንስኤ የሆነውን ተማሪ በኢህአዴግ አመራር አባላት እየታገዙ ለመያዝ የሚያስችል ነው” በማለት ህወሓት ተማሪውን የሚመለከተው “ከምንም በላይ በብጥብጥ መንስኤነት” መሆኑ፤ ለዚህ መድሀኒቱ ደግሞ ተማሪውን በኢህአዴግ አመራር አባላት “መያዝ” መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ይገልፃል። ቀጥሎም “በምርጫው ሊፈጠር የሚችለውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሁከትና ብጥብጥ ለማስቆም በማደራጀት መረጃ ለመጥለፍ አመችነቱ የላቀ እንደሚሆን ታምኖበታል” በማለት መረጃ መጥለፍ የዩኒቨርስቲዎችና የትምህርት ሚኒስቴር ሥራ እንደሆነ አድርጎ ያቀርባል።የማንዋሉን ዓላማዎች በሚገልፀው ክፍል ደግም “… የከፍተኛ ትምህርት የትምህርት የልማት ሰራዊት ግንባታን ወይም የፓለቲካ ሰራዊት ግንባታ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተደራጀና በተናቀጀ ሁኔታ በማቀጣጠ

ጋዜጠኛ መልካም ሞላ በድጋሚ ተከሰሰች!

የ‹‹ ቆንጆ ›› መፅሔት ዋና አዘጋጅና የ‹‹ ጃኖ›› መፅሔት ዓምደኛ የነበረችው መልካም ሞላ ሀምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ዜና እወጃ ላይ ‹‹ህገ-መንግሥቱን በኃይል ለመናድ በመንቀሳቀስ፣ ህዝቡን ለዓመፅ ማነሳሳትና የሽብር ስራን ለምስራት ማቀድ ›› በሚል የፍትህ ሚኒስቴር ክስ የመሰረተባት መሆኑን በዜና አቅራቢው ተመስገን በየነ በኩል የተከሰሰች መሆኑን የሰማችና ከዚያም ባሉት ተከታታይ ቀናት የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ለጥያቄ እንደሚፈልጋት ጥሪ ከደረሳት በኋላ የምትወዳትን ሀገሯን፣ ሙያዋንና ቤተሰቦቿን ትታ ዿግሜ 4 ቀን 2006 ዓ.ም ከሀገር መሰደዷ ይታወቃል ፡፡

ይሁን እንጂ የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቢሮ በያዝነው ህዳር ወር 2007 ዓ.ም ከሀገር ከመውጣቷ በፊት በዋና አዘጋጅነት ትሰራበት ለነበረው የ‹‹ቆንጆ›› መፅሔት ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ካሣን የወንጀል ምርመራ ቢሮ በማስቀረብ በጥር ወር 2006 ዓ.ም ማለትም ከአንድ ዓመት በፊት ‹‹ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መ/ቤት ምን እየሰራ ነው ? በሚል ርዕስ ሥር በኢትዮጵያ የግብረ ሰዶማዊነት መስፋፋትን በተመለከተ በፃፈችው ፁሁፍ ‹‹ ህዝቡ በመንግሥት ላይ እምነት እንዲያጣ አድርጋለች ›› በሚል ክስ እንደመሰረተባትና ለጥያቄ እንደሚፈልጋት በመግለፅ ሥራ አሥኪያጁ እንዲያቀርባት ታዟል፡፡ ይሁንና ጋዜጠኛ መልካም ሞላ በሀገር ውስጥ የሌለች በመሆኑ ከዚህ በፊት በሎሚ፣ በጃኖ ፣በአዲስ ጉዳይና በሌሎች የመፅሔት አሳታሚዎች ላይ እንደቀረበው የአሸባሪነት ክስ በቆንጆ መፅሔት አሳታሚ ላይም ይህ የክስ ፋይል እንደሚከፈት የታመነ ሲሆን ለጊዜው ግን ከአንድ ዓመት በፊት በፃፈችው ፁሑፍ ‹‹ ህዝቡን በመንግሥት ላይ እምነት እንዲያጣ አድርጋለች›› በሚል ክስ የቀረበባት ጋዜጠኛ መልካም ሞላን ካለችበት ቦታ አስሮ እንዲያቀርብ የፌደራል ፖሊስ የከባድ ወንጀል ምርመራ ክፍል የታዘዘ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በ21ኛው ክ/ዘመን መንግሥት አላባዋ ሀገር ፣መንግሥት አልባው ሕዝብ ።

የኢትዮጵያውያን ደም እንደውሻና እንደ ድመት በአረብ ሀገር አውራ ጎዳና ላይ መፍሰሱ የተለመደ በመሆኑ ዛሬ ዛሬ እንደዜና ለወሬም አልተመቸም አሰልች ሁኗል ።

ትላንት ውባለም የተባለች አንዲት ኢትዮጵያዊት  ቤይሩት ኢጀኑብ (ኢዘሪሂ) በሚባለው ከከተማው ወጣ ባለ አካባቢ ራሷን
ከሶስተኛ ፎቅ ላይ በመጣል ህይወታ ሊያልፍ ችልዋል።

በትላንትናው እለት የ20 አመት እድሜ ያላት ውባለም የተባለች አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ በደቡብባዊ ሊባኖን ከአሰሪዎቿ ቤት 2ኛ ፎቅ ላይ ወድቃ ህይወቷ ማለፉ ተነገረ፡፡

አንዳንድ አለምአቀፍ ድርጅቶች የቤት ሰራተኞች ሰብዓዊ መብቶች በስፋት በሚጣስባት ሊባኖን ሰራተኞች ጥቃት እዳይደርስባቸው ለመከላከል እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ዴይሊ ስታር ሲዘግብ

በአረብ ሀገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ጥቃት የሚደርስባቸው ቢሆንም በየአረብ ሀገራቱ የሚገኙት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ወይም ቆንፅላ ጽ/ቤቶች ችግሩን ለመቅረፍ የሚያደርጉት ጥረት እንደሌለ አንዳንድ በአረብ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተናግረዋል፡፡

የዜጎች መብትን ማስጠበቅ ካልተቻለ የኤምባሲዎቹና ቆንፅላ ጽ/ቤቶች እዛ መገኘት ፋይዳው ግልፅ አይደለም ይላሉ ችግሮቹን በቅርበት የሚመለከቱ ኢትዮጵያውያን፡፡


Wednesday, November 26, 2014

ቆንጆ መጽሔት ተከሰሰች

ከሁለት ሳምንት በፊት ከማዕከላዊ የምርመራ ቢሮ ከወዲያኛው ጫፍ የደወለው ሰው እንደነገረኝ ‹‹ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ነው›› ብሎ ደወለልኝ፡፡ ደዋዩ ቆንጆ መጽሔት መሆኑን ካጣራ በኋላ ዋና አዘጋጇ ስልክ ላይ ብደውል ዝግ ነው ፤ ጥር ወር ላይ ባወጣችሁት ዘገባ እኛ ጋ ክስ ተመስርቶባችኋል አለኝ፡፡ ስለሆነም ለዋና አዘጋጇ መልዕክት አድርሱ መጥታ ቃሏን ትስጥ አለኝ፡፡ ለጊዜው በቅርብ እንደሌለች ነገርኩት፡፡ ‹‹እሺ›› ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡ ድጋሚ ባለፈው ሳምንት አንድ ስልክ ተደወለ፡፡ በወቅቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለነበርኩ ስልኩን ማንሳት አልቻልኩም፡፡ ስወጣ ግን ደወልኩ፡፡ ስልኩን ያነሳችው ሴት ‹‹የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዋና (ማዞሪያ ስልክ)›› መሆኑን ነገረችኝ፡፡ እንግዲህ ይህ ስልክ ግቢ ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ የሚጠቀሙበት በመሆኑ እንደ እኔ ሞባይሉ ላይ ሚስድ ኮል አይቶ መልሶ ለደወለ ማን እንደደወለለት ገና ተጠያይቆ ነው የሚታወቀው፡፡

ርዮት አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንድቅ አላማ በላይዋ ላይ ለብሳ በክብር ከቃሊቲ ትወጣለች – ግርማ ካሳ

በሃይ ስኩል የእንግሊዘኛ አስተማሪ ነበረች። በሕገ መንግስቱ ላይ የተደነገገዉን መብት በመጠቀም፣ በተለያዩ አገር ውስጥ በሚታተሙ ሜዲያዎች ትጽፋለች። «እነርሱ እንዲጻፍ ከሚፈልጉት ዉጭ እንዲጻፍ የማይፈልጉ ባለስልጣናት፣ የሃሰት ክስ መሰርተዉ፣ ዳኛ ለተብዬዎች መመሪያ ሰጠዉ፣ መሰረተ ልማቶችን ለማፍረስ አሴራለች፣ ሽብርተኛ ናት» ብለዉ ፈረዱባት።

ይች እህት ርዮት አለሙ ትባላለች። ጡቷ አካባቢ ችግር ስላለበት ክትትል እንደሚያሰልጋት እየታወቅም ክትትል እንድታገኝ አልተደረገም። ወደ ሶስት አመት ገደማ ባላጠፋችዉ ጥፋት፣ ኢሕአዴግን ስለተቃወመች ብቻ፣ እየማቀቀች ነዉ። የርዮት ወንጀል አገሯ፣ ሕዝቧን መዉደዷ ነዉ።

ቦታ ጠበብኝ ( ሄኖክ የሺጥላ )

ታላቁ መንግስታችን የኢትዮጵያዊነት እሴቶች የሆኑት ነገሮች ሁሉ መደርመሱን ቀጥሎበታል። የነጻነት እና የማንነት ተምሳሌት የሆኑት አብይ ኩነቶችን ጭቃ ከመቀባት እስከ አፈር ማልበስ፣ ከማብጠልጠል እና ማናናቅ እስከ መቀበር፣ ከ መዝረፍ እና ማዘረፍ እስከ ፍጽሞ ማጥፋት እየሄደበት ያለውን መነገድ አስፋፍቶ ቀጥሎበት ትናንት ደሞ የ ታላቁን ወ-መዘክር መጻሕፍት ቤት ታሪካዊ መጽሐፍቶች ( የባለ ብዙ ዘመን እድሜ መጽሐፍቶች ) በኪሎ እንደሸጠው ሰምተናል። እነዚህ መጽሐፍቶች በውስጣቸው የያዙት ቁም ነገሮች ትውልድ የሚቀርሱ ፣ የማንነት መቅርጫዎች፣ የአእምሮ መሳያዎች ነበሩ። ዛሬ ግን ስኩዋርና እጣን መጠቅለያ ይሆኑ ዘንድ ተፈርዶባቸው በየ -ስርጡ ተወሽቀው ይገኛሉ። የሚገርመው እነዚህም መጽሐፍቶች ” ቦታ ጠበበኝ

Tuesday, November 25, 2014

በለገጣፎ ከተማ ከ32,000 ሺህ በላይ ዜጐች ቤት አልባ ሊሆኑ ነው

ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ለ12 ዓመታት በአካባቢው መኖሪያ ቀልሰው ኖረዋል፡፡ ሆኖም “የከተማ ሰው ወሮናል” የሚል ተቃውሞ በገበሬው እንዲነሳ ያደረጉ የከተማው ባለሥልጣኖች በ2 ቀናት ውስጥ ቤታችን ሊያፈርሱ ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ የካ ሰዴን ወረዳ የሚገኙት የጉራ፣ሰፈራ፣ድሬ፣ ዳሌ እና ቀርሳ የሚባሉ አካባቢዎች ውስጥ የሚገኙ ወደ 3000 ሺህ የሚጠጉ ቤቶች እንዲፈርሱ ምልክት ተደርጎባቸዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ቅዳሜ ህዳር 13 ቀን 2007ዓ.ም በከተማው በመሰባሰብ ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል፡፡ በነጋታው እሁድ ዕለትም ከ1000 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች በመሰባሰብ ባጋጠማቸው አደጋ ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የነዋሪዎቹን ችግር ለማዳመጥ ፈቃደኛ ያልሆኑት የከተማው የመንግስት ባለስልጣናት ግን በቅዳሜው በስብሰባው ላይ ባለመገኘታቸው ነዋሪዎቹ በነጋታው እሁድ ከ1000 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች በወረዳው ጽ/ቤት በመገኘት ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡ ሰኞ ህዳር 15 ቀን 2007 ዓ.ም በድጋሚ በመሰባሰብ 10 ተወካዮቻቸውን ወደ 4 ኪሎ ፓርላማ መላካቸውን በስፍራው የተገኘው የፍኖተ ነፃነት ዘጋቢ አረጋግጧል ፡፡


Monday, November 24, 2014

ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው


የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡

ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡

Sunday, November 23, 2014

በሰሜን ጎንደር የሕወሓት አማሳኞች ሰርገው የበመግባት ወጣቱን እያጋደሉ መሆኑ ተሰማ::

-ከከተማው ለስራ የሄዱ ወጣቶች ንብረታቸውን እና ገንዘባቸውን ሳይሰበስቡ አከባቢውን ለቀዋል
በኢትዮ ሱዳን ድንበር ላይ ለስራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን መንደር እየለዩ በመቧደን በከፍተኛ ጭፍጭፍ ውስጥ እንደሚገኙ ከአከባቢው የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል::

ከሱዳን ጋር በተያያዘው እና የታች አርማጮ መሬት ከሆነው ሰቲቱ ሁመራ ማይካድራ ሉግዲ አብዲራፍ አብድራሃጀር መተማ ሸዲ የተወሰነውን ጠገዴ ያሉት የጎንደር መሬቶች ላይ በኢንቨስትመንት ስራ ላይ የተማሩ የሕወሓት አባላት የሆኑት የጊዜው ባለሃብቶች በቀተሯቸው እና ከአማራው ክልል ጎንደር ጎጃም እና ወሎ የመጡ ወጣት ገበሬዎችን እርሲ በራስ በመንደር እና በጎጥ በመከፋፈል እንዲተራረዱ እንዲጨራረሱ የሰሩበትን ገንዘብ ሳይሰበስቡ አከባቢውን በፍርሃት ለቀው እንዲሄዱ እያደረጉ መሆኑን መረጃዎቹ የሰሞኑን ከፍተኛ ግጭት አስመልክተው ጠቁመዋል::

በሉግዲ አከባቢ በዚህ ሰሞን ብቻ በጎንደር እና በጎጃም በወሎ እና በሸዋ በሚል የተቧደኑ ሰዎች በሕወሓት ኢንቨስተሮች ነገር አስፋፊነት ከፍተኛ ግጭት በመከሰቱ በርካታ ወጣቶች የተገደሉ ሲሆን ቀሪዎቹ ንብረታቸውን እና ገንዘባቸውን ሳይሰበስቡ ድንገት ግጭቱን ሸሽተው ወደ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የሄዱ መሆናቸው ታውቋል::

የሕወሓት አማሳኞች እና ሰላዮች በወጣቶቹ መካከል ሰርገው በመግባት እሪስ በ እርስ ጎጥና መንደር እንዲለይ አድርገው በማቧደን እርስ በ እርስ ሕዝቡ እንዲተራረድ አድርገዋል ሲሉ ምንጮቹ በላኩት መረጃ ተናግረዋል::በዚህ ሳምንት ብቻ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ ሬሳዎች ወደ ሉግዲ ከተማ የተጓጓዙ ሲሆን ይህ የሕወሓት ሰላዮች/አማሳኞች የሚቀሰቅሱት የሰርጎ ገብነት ዝሴራ እስከ ማይካድራ ድረስ ተስፋፍቶ ከፍተኛ የደም መፋሰስ እና የዘር መጠፋፋት እየተደረገ መሆኑን አክለው ገልጸዋል::

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

በአለማችን በተለይ አፍሪካ ዉስጥ የአገርን ብሄራዊ ኃብት የሚዘርፉ፤የህዝብን መብት የሚረግጡና አገርን እነሱ ባሰኛቸዉ አቅጣጫ ብቻ ይዘዉ የሚነጉዱ አያሌ ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት አሉ። እነዚህ ህዝብን የሚበድሉ መንግስታት ሁሉም በጥቅሉ አምባገነን ይባሉ እንጂ በመካከላቸዉ ጎላ ብሎ የሚታይ ትልቅ ልዩነት አለ። ሀኖም የቱንም ያክል ልዩነት ቢኖርም እንደ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች እንመራዋለን የሚሉትን ህዝብ የሚንቁና የኛ ነዉ የሚሉትን አገር የሚጠሉ አምባገነን መንግስታት የሉም፤ በታሪክም ኖረዉ አያዉቁም። አምባገነን መንግስታት የስልጣን ዘመናቸዉን ለማራዘምና ከስልጣን ጋር ተያይዞ የሚመጣዉን ክብር፤ ዝናና ጥቅማ ጥቅም እንዳይቋረጥ ሲሉ የሚቃወማቸዉንና ለስልጣን ዘመናቸዉ አደጋ ነዉ የሚሉትን ሁሉ ያስራሉ፤ ይደበድባሉ ወይም ይገድላሉ።

ሰበር ዜና የበይነ መረብ ዘመቻው ኢህአዴግን አሳስቦታል

አንድነት ፓርቲ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚያካሂድ ይፋ ያደረገው የበይነ መረብ ዘመቻ ግቡን እንዳይመታ በቅርቡ አሰልጥኖ ባሰማራቸው የፌስ ቡክ ተጠቃሚዎች ብሄርን፤እምነትን እና የአንዱ ፓርቲ ደጋፊና የሌላው ፓርቲ ነቃፊ በመሆን አጀንዳዎን በማንሳት የፌስ ቡክ ተጠቃሚዎችን ትኩረት ለመሳብና የፌስ ቡክ ተጠቃሚዎች ወደ ጋራ አጀንዳ እንዳይሰባሰቡ ሳምንቱን ሙሉ በንቃትና በጥንቃቄ መስራት እንዳለባቸው በኢህአዴግ ጽ/ቤት በኩል በዛሬው እለት ማስጠንቀቂያዊ ትዕዛዝ መተላለፉን ማስጠንቀቂያው የደረሳቸው ተሳታፊ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገልፀዋል ፡፡እንደ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገለፃ ምን አልባትም ዘመቻው ትኩረት እየሳበ የሚሄድ ከሆነ በቴሌ አማካኝነት የኔት ወርክ መስተጓጎል እና ማቋረጥ ለመፍጠርም መታሰቡን አያይዘው ገልፀዋል፡፡አንድነት ፓርቲ የበይነ መረብ ዘመቻ በቀጣይ ሳምንት እንደሚያደርግ በትላንትናው እለት ለመገናኛ ብዙሀን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡


Friday, November 21, 2014

ፕሮፌሰር በየነ ጼጥሮስ ዲያስፖራውን ወቀሱ “ዲያስፖራው ገዥው ፓርቲ የሚሰራው ሥራ ሁሉ ጥፋት ነው ብሎ ራሱን አሳምኖ ቁጭ ያለ ነው”

ከአንድ ዓመት ላላነሰ ጊዜ በአሜሪካን ሀገር በቺካጎ ከተማ በሚገኝ አንድ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሲያስተምሩ ቆይተው በቅርቡ ወደሀገር ቤት መመለሳቸውን የተናገሩት የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ዲያስፖራውን ወቅሰዋል።

ፕሮፌሰሩ በዛሬው ዕለት ለንባብ ከበቃው መንግስታዊው ዘመን መጽሄት የጥቅምት 2007 ዕትም ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ “ዲያስፖራው ተስፋ የቆረጠና የተናደደ ነው፡፡ ተስፋ ስለቆረጠና ስለተናደደ ገዥው ፓርቲ የሚሰራው ሥራ ሁሉ ጥፋት ነው ብሎ ራሱን አሳምኖ ቁጭ ያለ ነው፡፡ በዚህም የሚናደድና የሚንቦገቦግ ነው፡፡

እናም ከእነዚህ ጋር ውይይት ማድረግ አይቻልም፡፡» ብለዋል። ፕሮፌሰር በየነ በዚሁ ቃለምልልሳቸው “ዲያስፖራውን ለመምከር እንሞክራለን» ካሉ በኃላ በአሜሪካ ቆይታቸው ወቅት እርሳቸው ንግግር እንዲያደርጉ የተጋበዙ ሰዎች እንዲበተኑ እንደተደረገ ተናግረዋል።

መጽሄቱ በእሳቸው ላይ ይህ ለምን እንደተደረገ ጠይቆአቸው በሰጡት ምላሽ “እኔ እውነቱን ስለማወጣ ነው» የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ኢህአዴግ በአንድ በኩል እኛን ትክክል ባልሆነ ምስል ያስቀምጠናል ያሉት የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ዲያስፖራው ደግሞ የባሰ በመሆኑ መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡


አንድነት ፓርቲ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች” የሚል ዘመቻ ማዘጋጀቱን ይፋ አደረገ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ ከህዳር 14 እስከ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚቆይ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች” የሚል የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ አዘጋጅቷል። በዚህ ዘመቻ ለመንግስት ባለስልጣናት፣ ለታዋቂ ግለሰቦች፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማትና ለልዩ ልዩ የሚዲያ ድርጅቶች በኢንተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በኩል መልዕክት በመላክ በሀገራችን ያሉት የፖለቲካ እስረኞች ሁኔታና አያያዝ በተመለከተ መረጃ በመስጠት ተገቢ የሆነ አያያዝ እንዲኖራቸው፤ ከእስር እንዲፈቱ፣ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉትን ማሰርና ማዋከብ እንዲቆም በመንግስት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ፓርቲው አስታውቋል። በዚህ ዘመቻ ላይ ሁሉም የዘመቻው ደጋፊና በሀገሪቱ ዴሞክራሲያው ስርዓት እንዲመሰረትና የዜጎች ሰብዓዊ መብት እንዲከበር የሚሹ ሁሉ ከላይ ለተጠቀሱት ግልሰቦችና ተቋማትን ጨምሮ ሚሊዮኖች ለሚያውቁትና ተፅዕኖ ማሳደር ይችላል ለሚሉት ሰው ሁሉ መልዕክት በኢንተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በመላክ ድምፃቸውን ያሰሙ ዘንድ ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም. አዲስ አበባ በሚገኘው ዋና ጽህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

ፓርቲው ከዚህ በፊት ከህዝቢ ከፍተኛ ድፍ ያስገኘለትን “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” እና “…ለመሬት ባለቤትነት” የሚሉ የተለያዩ ህዝባዊ ስብሰባዎችን እና የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎችን አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ማድረጉ ይታወቃል፡፡  የዛሬውን ሙሉ ዝርዝር መግለጫ ከታች ይመልከቱ፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል
 ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ()  ጋዜጣዊ መግለጫ

በሀገራችን ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚደረግ በመንግስት በኩል በከፍተኛ ደረጃ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት የተከናወኑት አራት ምርጫዎች ያየን እንደሆነ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ወደፊት ሊወስዱ እንዳልቻሉ እሙን ነው፡፡ ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተለያየ መንገድ ሲገልፅ ቆይቷል፡፡ በተቃራኒው መንግስትና ገዢው ፓርቲ በፍፁም መለየት በሚያስቸግር ሁኔታ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሆነው ተቀናጅተው ለአንድ ለአውራ ፓርቲ ግንባታ እየሰሩ እንደሆነ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህ የመንግሥትና የገዢው ፓርቲ ተግባር ምርጫን ያለ አማራጭ እንዲሆነ እያደረገው እንደሆነ ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ አባላት ላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ዘመቻ በሚባል ደረጃ እየተካሄደ ያለው አፈናና እስር፤ ከዚህም ባሻገር ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ ክልከላውና ወከባው ተጠናከሮ መቀጠሉ፤ ገዥው ቡድን የምር ተቃዋሚ ፓርቲ ናቸው ብሎ የሚያስባቸው ፓርቲዎች ለማዳከምና ከምርጫው ውድድር ውጪ ለማድረግ ያለው ቁርጥ አቋም የሚያሳይ ነው። ይህ የገዢው ቡድን አካሄድ በሀገራችን ዴሞክራሲያዊ የሆነ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲመሰረት ፍላጎት እንደሌለው በደንብ የሚያረጋግጥ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ፍትሐዊ በሆነ ምርጫ የሚፈልገውን ፓርቲ እንዲመርጥ እድል ሊጠሰው ሲገባ በሥርዓቱ በእኩል ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳያካሄድ የተለያዩ ጫናዎች እየተደረጉበት የሚካሄዱት ምርጫዎች ሁሉ ትርጉም አልባ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ የገዢው ቡድን ሀላፊነት የጎደለው እንቅስቃሴ በተግባር የሚደግፈው ከሠላማዊ ትግል ይልቅ የኃይልና የአመፅ መንገድ እንደሚሆን የተረዳ አይመስልም፤ ይልቁንም በሠላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉትን ፓርቲዎች ወደ አላስፈላጊ መስመር በመግፋት ሀገራችን ወደ ብጥብጥና ወደ እርስ በእርስ ጦርነት እንድትገባ የሚያደርግ ሁኔታ እየተከተለ ነው የሚገኘው። በሥልጣን ላይ ያሉት ወገኖች ይህ አሳሳቢ ሁኔታ በትክክል እንዳያዩ ጭፍን የሥልጣን ጥም ጋርዷቸዋል፡፡

በቀጣይ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚደረገው ምርጫም በመንግስት በኩል የመድበለ ፓርቲን ስርዓት ለማጎልበት ምንም ዓይነት ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠር ከአሁኑ የተለያዩ እንቅፋቶችን በመደርደር ላይ ነው። የአንድነት አመራሮችና አባላት በግፍ በማሰር ፓርቲው በምርጫው እንዳይሳተፍ ከፍተኛ የሆነ ጫና እየተደረገ ቢሆንም አንድነት ፓርቲ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሆኖ ህዝቡ እንዲሳተፍ በመቀስቀስና በማበረታታት የተዘጋውን የዴሞክራሲ በር በምርጫ ካርዱ ሊያስከፍት እንደሚችል ከፍተኛ እምነት አለው፡፡

ከሁሉም በላይ ደግሞ እንደከዚህ ቀደሙ ኢህአዴግ ደጋፊዎቼ የሚላቸውን ብቻ በመራጭነት አስመዝግቦ ምርጫ የሚያደርግበት ሁኔታ ማብቃት ይኖርበታል ብለን እናምናለን፡፡ ይህ ተግባራዊ እንዲሆን በእኛ በኩል ደጋፊዎቻችን በመራጭነት እንዲመዘገቡ ከማበረታት ጀምሮ የህዝብና የፓርቲ ታዛቢ በመሆን የምርጫ ሂደቱን በሙሉ በንቃት እንዲከታተል እንዲሳተፍ የበኩላችንን ጥረት በማድረግ የ2007 ሀገራዊ ምርጫ ከጅማሮው ህዝባዊ እንዲሆን ትግላችንን እንቀጥላለን፡፡ ይህ እርምጃም ህዝቡን የስልጣን ባለቤት ለማድረግ ወሳኝ እርምጃ ነው የሚል እምነት አለን፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ በገዥው ቡድን መልካም ፍቃድ ወይም በማንኛውም ውጫዊ ተፅዕኖ የፖለቲካ ምህዳሩን እንደማይሰፋ ሊገነዘብ ይገባል። ምህዳሩ የሚሰፋውና ትክክለኛ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ የሚኖረው ህዝቡ በጠቅላላ ከፍርሀት ቆፈን ተላቆ በሙሉ ልብ ለመብቱ ሲቆም፣ ለፓርቲዎች ተገቢው ድጋፍ ሲሰጥ፤ ከፍ ሲልም ወደ ትግሉ ሲቀላቀል መሆኑ መገንዘብ ያስፈልጋል።

በዚህ አጋጣሚ አንድነት ፓርቲ ከህዳር 14 እስከ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚቆይ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች” የሚል የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ አዘጋጅቷል። በዚህ ዘመቻ ለመንግስት ባለስልጣናት፣ ለታዋቂ ግለሰቦች፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማትና ለልዩ ልዩ የሚዲያ ድርጅቶች በኢንተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በእኩል መልዕክት በመላክ በሀገራችን ያሉት የፖለቲካ እስረኞች ሁኔታና አያያዝ በተመለከተ መረጃ በመስጠት ተገቢ የሆነ አያያዝ እንዲኖራቸው፤ ከእስር እንዲፈቱ፣ በሰላማዊ መንገድ የሚታሉትን ማሰርና ማዋከብ እንዲቆም በመንግስት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለመፍጠር ያለመ ነው። በዚህ ዘመቻ ላይ ሚሊዮኖች ለሚያውቁትና ተፅዕኖ ማሳደር ይችላል ለሚሉት ሰው ሁሉ መልዕክት በኢተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በመላክ ድምፃቸውን ያሰሙ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)
ህዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ


እነ ሀብታሙ አያሌው ዋስትና ተከለከሉ-አቃቤ ህግ ማስረጃ አሟልቶ እንዲቀርብ ታዝዟል

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው አራቱ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እና በተመሳሳይ መዝገብ የተከሰሱት ሌሎች ስድስት ተከሳሾች ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡

ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ እና ዳንኤል ሺበሽ በሚገኙበት የክስ መዝገብ የተከሰሱት አስሩም ተከሳሾች ዛሬ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት፣ ተከሳሾቹ ህገ መንግስቱን በመጥቀስ ያቀረቡትን የዋስትና መብት ጥያቄ ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ የጸረ ሽብር አዋጁን በመጥቀስ ዋስትናው እንዳይፈቀድ ያቀረበውን መከራከሪያ በመቀበል የዋስትና ጥያቄውን አልተቀበለውም፡፡ በመሆኑም ተከሳሾች ፍርድ ቤቱ ክሱን መርምሮ በሂደት ውሳኔ እስኪያሳልፍ ድረስ በእስር ላይ ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ወስኗል፡፡

በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ጠበቆች የቀረበውን ማስረጃ አለመሟላት በመመርመር አቃቤ ህግ ለህዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም ማስረጃዎችን አሟልቶ እንዲቀርብ በሚል አጭር ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በዛሬው ዕለት ተከሳሾች ከላይ ሙሉ ነጭ ሸሚዝ ለብሰው ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ነጭ ማድረጋቸውም ‹ሰላማዊ ነን› የሚለውን መልዕክት ለማስተላለፍ በማለም እንደሆነ መረዳት ተችሏል፡፡


ከ400 በላይ ህዝብ የተፈናቀለበት መሬት በሙስና ተቸበቸበ

በደቡብ ወሎ ዞን በኮምቦልቻ ወረዳ ቀበሌ 11 በተለምዶ ጋሪሳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ይኖሩ የነበሩ 470 ሰዎች ቦታው ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል ተብሎ ሰብአዊ መብታቸው ተጥሶ እንዲፈናቀሉ ከተደረገ በሁዋላ፣ በካሬ ሜትር 1 ብር ከ46 ሳንቲም መሬታቸው እንሸጥ ተደርጓል።

ጉዳዩ የህዝብ መነጋገሪያ ሆኖ ከቆየ በሁዋላ ሰሞኑን ከህዝቡ እየጨመረ የመጣውን ግፊት ተከትሎ በተደረገ ህዝባዊ ስብሰባና የካቢኔ አባላት ስብሰባ፣ የወረዳው አዛዦች ከተፈናቃዩ ደሃ ህዝብ የወሰዱትን መሬት በሙስና መቸብቸባቸውን እርስ በርስ እየተገላለጡ ይፋ አድርገዋል።

የወረዳው ላይዘን ኦፊሰር አቶ ሃብቶም የተባሉ ግለሰብ፣ አስተዳዳሪውን አቶ አበራ አበረን በአዲስ አበባና በባህርዳር መሬት ገዝተው ቤት መስራታቸውንና ቡልዶዘሮችን ገዝተው እያከራዩ መሆኑን ሲያጋልጡ፣ ምክትል ከንቲባው ደግሞ በባንክ ሂሳባቸው 8 ሚሊዮን ብር እንደተገኘባቸው እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች ቤቶችን መገንባታቸውን አጋልጠዋል። አጋላጩ አቶ ሀብቶምም በከተማዋ ሁለት ቦታ ገዝተው ቤት መስራታቸውን መቀሌ ላይ ተጨማሪ ቦታ መግዛታቸው በሌሎች ባልደረቦቻቸው ተጋልጧል።

ሶስቱም ባለስልጣኖች ለጊዜው ከስራቸው ቢታገዱም እስካሁን የተወሰደባቸው እርምጃ የለም።

አንዳንድ ተፈናቃይ አርሶደአሮች ለኢሳት እንደገለጹት አቤቱታ ቢያቀርቡም ሰሚ በማጣታቸው ለስደትና ለረሃብ መዳረጋቸውን ለኢሳት ገልጸዋል ።

ሰዎቹ ከስራ ቢሰናበቱም ወደ ሌላ ቦታ ተዛውረው መስራታቸው አይቀርም ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ በደቡብ ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ከ100 በላይ አርሶደሮች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። አርሶ አደሮቹ የመሬት ዋስትና ወረቀት እንዲሰጣችሁ በነፍስ ወከፍ 4 ሺ 500 ብር ክፈሉ ተብለው የተጠየቁ ቢሆንም፣ አርሶአደሮች ግን እስከዛሬ ግብር እየከፈልን ኖረናል፣ አሁን ተጨማሪ አንከፍልም በማለት ተቃውመዋል። ይህ ተከትሎ መሬታቸውን እየተቀሙ መሬቱ ለኢንቨስተር እየተባለ እየተቸበቸበ ነው።

አብዛኞቹ ባለስልጣኖች ከኢንቨስተሮች ጋር አክሲዎን እንዳላቸው መንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። በአካባቢው የሚታየው ተደጋጋሚ ግጭት ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ።


መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን ያጣል

ታሪክ ለሰው ልጅ ስሩና መሠረቱ ነው።ታሪኩንና መምጫውን የማያውቅ ህዝብ መድርሻውን የማያውቅና ራሱንም ለባርነት አሳልፎ የሰጠ ይሆናል፡፡ ለክብሩ ለእርሱነቱ ለህብረቱና ለነፃነቱ ፀንቶ መቆየት እና የጥንካሬውና ተሳስሮ የመዝለቂያው ሰንሰለት ታሪኩ መሆኑ ይታወቃል፡፡የአሜሪካ ባርያ ፈንጋዮች ትናንት በገፍ ከአፍሪካ በባርነት ያመጡዋቸው አፍሪካውያን አንድ ቀን በአንድ ቆመውና በህብረታቸው ጠንክረው ራሳቸውን ነፃ ለማውጣት እንዳይነሱ ሀ ብለው የነጠቋቸው ማንነታቸውን፤ ታሪካቸውንና መገኛቸውን ነበር፡፡ እንደ እቅዳቸውም እነሆ ዛሬ አብዛኛው ጥቁር አሜሪካዊ እኔ ማን ነኝ? መምጫዬስ ከወደየት ነው? በሚሉና በመሳሰሉ ጥያቄዎች ተተብትቦ ለምላሹ ሲውተረተር መገኘቱ፤ እንዲሁም ዛሬም ከተገዢነት መንፈስ ራሱን አላቆ በሁለት እግሩ ለመቆም ሲታትር ይገኛል፡፡ሌላው የኢጣልያ ወራሪን ሀይል ቅስም የሰበረውና በአለም አቀፍ ደረጃ ቅሌት ያከናነበው የአድዋ ጦርነት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ቅሌት በደም አጥቦ ሀያልነቱን ለአለም ለማሳየት በሞከረበት ሁለተኛው ወረራ ወቅት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የአድዋ ጦርነት የመሩት የአፄ ሚንሊክ ሀውልትን ከጥልቅ ጉድጓድ መቅበር እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ባጠቃላይ አንድ ህዝብ እንደ ህዝብና ሀገር ጠንክሮና በነፃነት ኮርቶ ለመኖር ብሎም ከትውልድ ትውልድ መሸጋገር መቻል ከማረጋገጫው አንዱ የትናንት ማንነቱና የመገኛ ታሪኩ መሆኑን ከላይ በምሳሌነት ያነሳናቸው ነጥቦች ያረጋግጣሉ፡፡ታሪክ ለአንድ ህዝብ የማንነቱ መገኛ፤ የመገኛው ምንጩና መምጫውን የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን የነገ መዳረሻውን የመመልከቻ መነፅርና ጠንክሮ የመንቀሳቀሻው ጉልበቱ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ መሳሪያ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ አንድ ህዝብ ታሪኩ ከጠፋ ሊገጥመው የሚችለው ችግርና ፈተና እንዲህ በቀላሉ የሚገመት ያለመሆኑንና እንደ ህዝብ እንደ ሀገር ቀጣይነቱን በቀላሉ መፍትሄ ከማይገኝለት ፈተና ውስጥ ይከተዋል ማለት ነው፡፡ኢትዮጵያችን ዛሬ ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ህልውናዋ አደጋ ላይ የወደቀበት መሆኑ ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ባለፉት 23 አመታት በዘረኞቹ የወያኔ ጉጅሌዎች እጅ ከወደቀችበት እለት ጀምሮ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆኑ የታሪካችንና የባህልችን ዋና ዋና እሴቶች ዋነኛ ኢላማ ሆነዋል፡፡ ይህንንም በተደጋጋሚና በግልፅ ከወያኔው መሪ እስከ ተራ ደጋፊው የሚወረወረው በትር ያረጋግጣል፡፡ ጉጅሌዎቹ የነፃነት ምልክት የሆነውንና በዕልፍ አዕላፋት ደም መሥዋዕትነት ፀንቶ የቆየውን ሰንደቅ ዓላማ በሶ መጠቅለያ ጨርቅ ከማድረግ ጀምረው ዛሬ በምሁራን ጥረትና በእያንዳንዱ ዜጋ ድጋፍ የተሰባሰቡት የታሪኮቻችን መዛግብት በጥንቃቄ ከተቀመጡበት (ቤተ-መዛግብት) እያወጡ ከማውደምና ለስኳር መጠቅለያነት እስከ መሸጥ ደርሰዋል፡፡ታሪካዊ ገዳማት ፈርሰዋል፤ ታሪካዊ ቅርሶች ለባእዳን አልፈው ተሽጠዋል፤ የነፃነት ታሪካችን እየተደለዘ በወያኔያዊ ዘረኛ የፈጠራ ታሪክ መተካቱ ቀጥሏል፤ ታሪካዊ ጀግኖቻችንን ማዋረድና ማውገዝ የእለት ተእለት ስራቸው ሁኗል። ወ ያኔዎች ኢትዮጵያዊነት ቅዝት ሆኖባቸዋል፤ ስለዚህም ቀንደኛ ጠላታቸው አድርገው ፈርጀውታል፡፡ ይህ የዘረኝነትና የዘረፋ ስርዓታቸው ውሎ ማደር የሚረጋገጠው ኢትዮጵያዊነት መመታት ሲችል ብቻ ነው ብለውም በፅኑ ያምናሉ፡፡ ለዚህም ነው ኢትዮጵያዊነታችንን ሊያዳክም ብሎም ሊያጠፋ ይችላል ብለው የገመቱትን ሁሉ ከመፈፀም የማይመለሱት፡፡ ለዚህም ነው በስንት ጥረትና በብዙዎች ድካም ተሰባስቦና ተደራጅቶ የቆየውን የታሪክ መዛግብትና መፅሀፍት ከቤተ-መዘክር አውጥቶ በኪሎ ለመቸብቸብ የበቁት፡፡ታዲያ ኢትዮጵዊ ነን የምንል ሁሉ ዘሬም እንደትናንቱ ይህን በማንነታችን ላይ የሚደረግ የጥፋት ዘመቻ ለማስቆም መነሳት ግድ ይለናል። እየተፈፀመ ያለው የታሪክ ማጥፋት ዘመቻ ለነፃነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ከምናደርገው ትግል እኩል ጎን ለጎን ለታሪካዊ ቅርሶቻችንና መዛግብቶቻችን ከጥፋት የመከላከልና የማዳን ስራ የመስራት የትውልድ ኃላፊነት አለብን፡፡ አለበለዚያ መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን አያውቅምና የምናደርገው የነፃነት ትግል የተሟላ ውጤት ማስገኘቱ ጥያቄ ውስጥ መግባቱ አይቀሬ መሆኑን መገንዘብ ይገባናል፡፡ ተገንዝበንም ወያኔን በቃህ ልንለው ይገባል፡፡በመጨረሻም ጂኦርጅ ኦርዌል ‘The most effective way to destroy people is to deny and obliterate their understanding of their own history” ብሎ ጽፎ ነበር። ህወሃቶች የዚህ ፍልስፍና ተከታዮች መሆንን በመምረጥ ለራሳቸው ውረደትን ፤ለአገራቸውም ውደቀትን ተመኝተዋል። ኢትዮጵያችን መንግስት በጠላትነት ተሰልፎ ከአገራችን ከህዝብና ለአገሪቷ እሴቶች ጋር የሚዋጋበት አገር ሁናለች። ህወሃት በብዙ መልኩ ሲታይ የኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላት መሆንን የመረጠ ቡድን ነው። የህወሃት በኢትዮጵያ ላይ በጠላትነት መቆሙ ያስቆጣቸው ወጣቶች እምቢ ለአገሬ፤ እምቢ ለክብሬ ብለው ተነስተው ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ተሠማርተዋል።ግዜው ከእነዚህ ወጣቶች ጎን የምንቆምበትም ጭምር ነውና ተነሱና ለነፃነታችንና ለአገራችን ዝና ለህዝባችን ክብር አብረን ታግለን ጠላትን የመረጠውን ህወሃትን እናስወግድ እና ንፁህ አገር እንፍጠር።ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

የባዮሎጂ ምሩቁ ዶክተር ቴድሮስ አድሓኖም ለሕክምናው ሞያ ያለውን ባይተዋርነትና ንቀት በድጋሚ አረጋገጠ!

ዶ/ር ቴድሮስ ከአንድ አለማቀፍ የሚድያ ተቋም ጋር አደረገው በተባለው ቃለ መጠይቅ “ኢቦላ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢገባ በቀላሉ ቁጥር ላይ እናውለዋለን፤ ምክንያቱም በደምብ የተደራጀ የጤና ልማት ሰራዊትና የኤክስቴንሽን ፓኬጅ አሰራር ስላለን” ማለቱን ተነግሯል፡፡
እግዚሀር ይይላችሁ፡፡ ዐለምን ሁሉ ያስጨነቀው ኢቦላ በጤና ኤክስተንሽን ሰራተኞች ሊቆጣጠር!

ዶ/ር ቴድሮስ የባዮሎጂና የፐብሊክ ሀልዝ ባለሙያ በመሆኑ ማስመሰልና ደፍረት እንጂ ይህ ነው የሚባል የሕክምና እውቀት ያለው ሰው ሆኖ አያውቅም፡፡ በሀገሪቱ ያለውን የሕክምና ትምህርት ጥራት እንዲሞት ቀጥተኛ ተሳትፎ ሲያደርግ የነበረና በኢትዮጵያ ሐኪሞች ዘንድ እጅግ የሚወቀስ አስመሳይ ሰው ነው፡፡

ወያኔ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱ ታወቀ • የኢህአዴግ አመራሮች መካከል ልዩነት ተፈጥሯል

(ነገረ ኢትዮጵያ) ገዥው ፓርቲ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን ለማሰር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ታማኝ ምንጮች ገለጹ፡፡ ሰሞኑን የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ባደረጉት ስብሰባ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃልን ወይንስ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን ማሰር ያዋጣል በሚል ልዩነት እንደተፈጠረ የገለጹት ምንጮቻችን በስተመጨረሻም የኢንጅነር ይልቃል መታሰር ትኩረት የሚስብ በመሆኑ ንቁ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን ማሰር አዋጭ ነው የሚለው ቡድን ተደማጭነት እንዳገኘ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ የሰማያዊና ሌሎች ፓርቲዎች አመራሮችን ‹‹ከኢሳት ጋር ግንኙነት ያደርጋሉ›› በሚል በሽብር ስም ለመክሰስ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችንም ሆነ ሌሎችን ‹‹ከኢሳት ጋር ግንኙነት አላቸው›› በሚል ይከሰሳሉ የተባሉት እስከህዳር ወር መጨረሻ ሊታሰሩ ይችላሉ ሲሉ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡በሌላ በኩል በዚሁ ስብሰባ ኢንጅነር ይልቃል ወይንም ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችን በማሰር ከተፈጠረው ልዩነት በተጨማሪ አመራሮችን በተለያዩ ሰበቦች ለማሰር በተዘጋጀውና ‹‹በዚህ መንገድ መሄዱ እስከመቼ ያዋጣናል?›› የሚሉ ጥያቄ በሚያነሱ ከፍተኛ የኢህአዴግ አመራሮች ልዩነት መፈጠሩንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም ባሻገር በሌሎች የፓርቲው አካሄዶች ላይ ልዩነት በመፈጠሩ ፓርቲው ውስጥ አደጋ ተፈጥሯል ያሉት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች በአቶ አባይ ፀሐዬ የሚመራ ቡድን ‹‹ልዩነታችን ቢያንስ እስከ ምርጫው ድረስ ማቻቻል አለብን›› በሚል በሁለቱ ቡድን መካከል ያለውን ልዩነት ለመፍታት እየጣረ ነው ብለዋል፡፡ሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች 8 ፓርቲዎች ጋር በመተባበር የአዳር ሰልፍን ጨምሮ የአንድ ወር መርሃ ግብር ቀርጾ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን የወሩ የመጀመሪያ መርሃ ግብር የሆነው የአደባባይ ስብሰባ ለማድረግ ሲቀሰቅሱ የተገኙ የፓርቲው አራት አመራሮች መታሰራቸው ይታወቃል፡፡

ምርጫ 2007ን ለመዝረፍ በሕወሃት/ኢሕአዴግ በከፍተኛ የትምህርት ተቋሞች የተደረጉ ወንጀለኛ ዝግጅቶች – በፓርቲው ውስጣዊ መረጃ ላይ የተመሠረተ ትንታኔ

– “በተለይም በአሁኑ ሰዓት ፈተና ላይ የጣለን የምርጫ ጉዳይ እንደምናሸነፍ ቃል የተያዘበት ቢሆንም [ቃለ ጉባዔ/የፓርቲው ሊቀመንበር መመሪያ?]፤ ፈተናዎች የሚፈጠሩት በሕዝብ እና በራሱ ታማኝ ባልሆኑ ሃይሎች ማለትም በመንግሥት ክንፍ አይቀለበስም ብሎ ማሰብ አይቻልም፡፡ በዚህም ቀድሞ መዘጋጀት ያለበት እና ለሁከት እና ለብጥብጥ መሳሪያ ሊሆን የሚችለው የሕዝብ ክንፍ የተማረው ሃይል ሊሆን ስለሚችል ሊታሰብ ይገባል ብለዋል [የፓርቲው ሊቀመንበር?]፡፡”

ምንጭ፡ በትምህርት ሚኒስትሩ ሽፈራው ሽጉጤ አስተባባሪነት የተዘጋጀው:

“የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢሕአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሠራዊት ግንባታ አድረጃጀት ማንዋል – ለምርጫ 2007”

ማጠቃለያ

ራሱ ሕወሃት/ኢሕአዴግም እንዳመነው፡ በከፍተኛ ፍርሃት እየራደ ያለ ባለአራት-ግንባሮችና ሌሎች አናሳ ቡድኖች ስብስብ ዋናው ሥልጣን በሕወሃት እጅ ሆኖ በኃይልና በከፍተኛ ጭቆና ሃገራችንን የሚያስተዳድር የፖለቲካ ድርጅት ነው። ከባህሪው የድርጅቱ ትልቁ ችግርም፡ ሣር ቅጠሉ ሳይቀር፡ ከዛሬ ነገ ሥልጣን ያሳጡኛል ብሎ በሥጋት የሚኖር በመሆኑ፡ ሣሩ፡ ቅጠሉንና ጎመኑም ጠላቶቹ እየመሰሉት፡ በእስር ቤት የሚያጉራቸው ወገኖቻችንን ብዛት ቤቶቻቸው ይቁጠሯቸው ብሎ ማለፉ፡ በቆጠራ ብቻ ጊዜ ከማባከን ያድናል።

የአውሮፓ ህብረት ምርጫ 2007ን እንደማይታዘብ ታወቀ

የአውሮፓ ህብረት ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በምርጫው ጉዳይ አነጋገረ• ጠቅላይ ሚኒስትሩንም ምሽቱን ያነጋግራል ተብሎ ይጠበቃል• ህብረቱ ምርጫውን አይታዘብም ተብሏልየአውሮፓ ህብረት ልዑክ ዛሬ ህዳር 11/2007 ዓ.ም ሶስት የተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎችን ያነጋገረ ሲሆን፣ በኢህአዴግ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን ለማነጋገር ምሽቱን ቀጠሮ መያዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡በአውሮፓ ህብረት የልዑል መሪ ሻንታል ሔቤሬት የተመራው የልዑካን ቡድን የሰማያዊ ፓርቲና የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነትን፣ እንዲሁም የመኢአድና የመድረክን አመራሮች ማነጋገራቸው ታውቋል፡፡የአውሮፓ ህብረት ሶስቱን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያነጋገረበት ዋነኛው አላማ ከምርጫ 2007 በፊት ያሉትን ችግሮች ለማወቅ የሚል ሲሆን በተቃዋሚዎቹ በኩል ያሉትን ችግሮች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል፡፡የሰማያዊና የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል የአውሮፓ ህብረት ላቀረበው ጥያቄ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን በማመልከት፣ ‹‹የምርጫው ችግር ከአጠቃላይ የኢትዮጵያ ችግር የመነጨ ነው፡፡ በተለይ ከ1997 ዓ.ም በኋላ ሚዲያውን፣ ሲቪክ ተቋማቱንና ተቃዋሚዎችን ለማፈን መሳሪያ የሆኑ አዋጆች የአገሪቱን ፖለቲካ አበላሽተዋል፡፡ በምርጫው ላይ የተፈጠረው ችግር የዚህ ሁሉ ድምር ነው›› በማለት መሰረታዊ የአገሪቱ ችግሮች ካልተፈቱ ምርጫው ላይ የተደቀነው ችግርም ሊፈታ እንደማይችል እንደገለጹላቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡በሌላ በኩል ከአሁን ቀደም የተደረጉትን ምርጫዎች የታዘበውና በምርጫዎች ሂደት ነበሩ የተባሉትን ችግሮች በሪፖርቱ በማካተት የሚታወቀው የአውሮፓ ህብረት ስለ ምርጫው ሁኔታ በቅርቡ ስላወቀና ቀድሞ ስላልተጋበዘ ምርጫውን እንደማይታዘብ የተወቀ ሲሆን በአንጻሩ የአፍሪካ ህብረት ምርጫውን እንደሚታዘብ ከወዲሁ ለመረዳት ተችሏል፡፡

Thursday, November 20, 2014

የጅማ ህዝብ ባገዛዙ መማረሩን ገለጸ

 ኢሳት ዜና :-የኦሮምያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሙክታር ከድር፣ የገንዝብ ሚኒስትሩ ሶፍያን አህመድና የኦሮምያ የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊው ከጅማ ዞን የተውጣጡ የተለያዩ ድርጅት ተወካዮችን በጊዜ አዳራሽ ሰብስበው ባነጋገሩበት ወቅት፣ ህዝቡ በአስተዳደሩ ተስፋ መቁረጡንና ለውጥ የሚፈልግ መሆኑን ተናግሯል።
የምርጫ ቅስቀሳ በሚመስለው መድረክ ፣ አቶ ሙክታር ተሰብሳቢው የሚሰማውን እንዲናገር ፈቅደዋል። ነዋሪዎቹ በዞኑ ልማት የሚባል ነገር እንደሌለ፣ ከጅማ አጋሮ የተሰራው የአስፋል መንገድ ፈራርሶ ህዝቡ ከመቸገሩም በላይ በተለይም ወላዶች ወደ ጅማ ሆስፒታል በሚሄዱበት ጊዜ መንገድ ላይ እንደሚሞቱ ተግልጿል።
በከተማው የሚገኙ ወታደሮች ነዋሪውን እየገደሉና እያሰቃዩ መሆኑን በቅርቡ የተፈጸሙ አሰቃቂ ግድያዎችን በማንሳት አቤቱታዎችን አሰምተዋል።
በዞኑ የተስፋፋው ሙስና ከአቅማችን በላይ ሆኗል ያሉት ነዋሪዎች ባለስልጣኖች የሚሾሙት ግንዘብ ዘርፈው ፎቅ ለመስራት ወይም ድርጅት ለመክፈት ነው በማለት የመንግስት ባለስልጣናት በከተማው ውስጥ የሚቀሙዋቸውን ቤቶችና ቦታዎችን በዝርዝር በመግለጽ አቅርበዋል።
የህዝቡ ቁጣ ያስደነገጣቸው አቶ ሙክታር ከድር ከስብሰባው በሁዋላ የተለያዩ ባለስልጣኖችን ሴንትራል ሆቴል በመሰብሰብ፣ የህዝቡ ብሶት ከልክ ማለፉን እንደገለጹና አፋጣኝ እርምጃ ተወስዶ የማረጋጋት ስራ እንዲሰራ አዘዋል።
በቅርቡ በአካባቢው የሰፈሩ ወታደሮች አንድ ወጣት እስከ አያቱ በሌሊት በጥይት ደብድበው መግለደላቸው መዘገቡ ይታወሳል። አርቲስ ወንዴ የተባለ ድምጻዊም እንዲሁ በወታደሮች ተደብድቦ ሆስፒታል ተኝቶ ሲታከም ከቆየ በሁዋላ፣ በአሁኑ ጊዜ በውጭ ሆኖ በማገገም ላይ ይገኛል።
ኢሳት አርቲስቱን ያነጋገረው ቢሆንም፣ አርቲስቱ እርሱና ልጁ በከፍተኛ ሁኔታ መደብደባቸውን በመግለጽ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ያመራ በመሆኑ፣ ከፍርድ ውሳኔ በፊት ለመናገር እንደሚከብደው ገልጿል።
በተመሳሳይ መልኩም በሃረር የመልካም አስተዳደር ንቅናቄ በሚል አጀንዳ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ህዝቡ ተቃውሞውን አሰምቷል። መድረኩን የመሩት የክልሉ ፕሬዚዳንት እና ምክትላቸው ሲሆኑ ፣ ፕሬዚዳንቱ በያዝነው አመት ያጋጠሙ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ህዝቡ እንዲናገር በፈቀዱት መሰረት ተሰብሳቢው እድሉን
በመጠቀም ብሶቱን አሰምቷል። አንዳንድ ነዋሪዎች ” ልጆቻችን ስራ አጥ ሆነዋል፣ እዚህ አካባቢ ከ60 አመታት በላይ ብንኖርም አሁን ግን ስራ እንዳናገኝ ታግደናል፣ የት ሂዱ ነው የምትሉን?” በማለት በአካባቢው የሚታየው ዘረኝነት እንዳስመረራቸው ገልጸዋል።
ባድሜ ዘምተው በመቁሰላቸው በቦርድ የተሰናበቱ ወታደሮች ደግሞ መስተዳድሩ እውቅና እንደነፈጋቸውና መብቶቻቸው እንዳልተከበሩላቸው ተናግረዋል።
በከተማዋ ውስጥ ፍትሃዊ የልማት ስርጭት አለመኖሩን የገለጹት ነዋሪዎች፣ በተለይ መጤዎች በሚባሉት አካባቢዎች ምንም አይነት የመሰረተልማት አገልግሎት እንዳልተዘረጋላቸው በምሬት ገልጸዋል።
ህዝቡ በርካታ ጥያቄዎችን ቢያነሳም ፕሬዚዳንቱ ጥያቄዎችን በወረዳ ደረጃ ታገናላችሁ በማለታቸው ህዝቡ አዳራሹን እየለቀቀ ወጥቷል።


የትብብሩ ፓርቲዎች እነማን ናቸው? እንዴትስ ተሰባሰቡ?

- ወደ ዘጠኝ ዝቅ ያሉትስ በምን ሁናቴ ነው?

ዮናታን ተስፋዬ (የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ)

አንዳንዴ ነገሮች በተጨባጭ ሳይሆን በመሰለን ነገር ብቻ እየተመለከትን እውነታውን እንዘነጋውና ችግር ናቸው ለምንላቸው ነገሮች ሌላ መላ ለማምጣት ብዙ እንደክማለን፡፡ መድከማችን ግን የችግሮቹን ወይም የሁነቶቹን አነሳስና አካሄድ ካላገናዘበና ከግምት ካላስገባ ከንቱ ድካም ይሆንና በስህተት ላይ ሌላ ማረሚያ ስህተት እየፈጠርን ችግሩን የባሰ እናወሳስበዋለን፡፡

ይህን ታሳቢ በማድረግ ሰሞኑን በትብብሩ ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስም ማብራሪያም ይሆን ዘንድ አጀማመራቸውንና 9 ከመሆናቸው በፊት ስንት እንደነበሩ፣ እነማን በምን ምክንያት ትብብሩን እንዳልተቀላቀሉ ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡ በዚህ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን የማስተናግድ ሲሆን በተረፈ ግን ሊጠየቁ የሚገቡ አካላት በአግባቡ እንዲጠየቁ እና በማነሳቸው ነጥቦች ላይ አስተያየትና መልስ እንዲሰጡ እጋብዛለሁ፡፡

ተማሪዋ በተሳፈረችበት ታክሲ ታፍና ተወስዳ በደረሰባት አስገድዶ መድፈር ሕይወቷ አለፈ / Ethiopian girl dies after being gang-raped in Addis Ababa

በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቄራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ አየር ጤና አካባቢ አንዲት የአሥረኛ ክፍል ተማሪ በተሳፈረችበት ታክሲ ታፍና ከተወሰደች በኋላ በደረሰባት አስገድዶ መደፈር ጉዳት ሕይወቷ ማለፉን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

ሟቿ ተማሪ ሃና ላላንጎ ጥቅምት 21 ቀን 2007 ዓ.ም. አየር ጤና በተለምዶ ሳሚ ካፌ በሚባለው አካባቢ በአንድ ሚኒባስ ውስጥ ተሳፍራ ወደ ጦር ኃይሎች እየመጣች እንደነበር ምንጮቹ ተናግረዋል፡፡

ከትምህርት ቤት ወጥታ ወደ ቤተሰቦቿ በመጓዝ ላይ የነበረችው ሟች ተማሪ የተወሰነ ርቀት ከተጓዘች በኋላ መድረሷን ተናግራ ‹‹ወራጅ አለ›› ስትል፣ በሚኒባሱ ውስጥ የነበሩ አራት ወንዶችና ሾፌሩ ስለት በማውጣት አስፈራርተው እንዳገቷትም ተጠቁሟል፡፡

ሟች እንዳትናገር በማድረግ በሰዋራ ቦታ በታክሲው ውስጥ እንድታመሽ ከተደረገች በኋላ፣ ከተጠርጣሪዎቹ አንደኛው ቤት ወስደው ለአምስት እየተፈራረቁ እንደደፈሯት ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

አንደኛው ተጠርጣሪ በራሱ ቤት ውስጥ እንድትቆይ በማድረግ ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲደፍራት እንደከረመም ምንጮቹ አክለዋል፡፡

ሁለተኛ ተጠርጣሪ ነው የተባለው ግለሰብ ለአምስት ቀናት በተደጋጋሚ ሲደፍራት ከከረመ በኋላ፣ ከቤት አውጥቶ ጭር ባለ ቦታ ጥሏት መገኘቷንም ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

ሟች ከፍተኛ የሆነ የማሕፀንና የፊንጢጣ ጉዳት አጋጥሟት ስለነበር በተለያዩ ሆስፒታሎች ሕክምና ያደረገች ቢሆንም፣ በደረሰባት ከባድ ጉዳት በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል በመታከም ላይ እያለች ሕይወቷ ማለፉን ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡

ሟች በመሀል በአንደኛው ተጠርጣሪ ስልክ ወደ ቅርብ ጓደኛዋ በመደወል ስልኩን በመዝጋቷ ጓደኛዋ የደወለችበትን ስልክ ለቤተሰቦቿ ትሰጣለች፡፡

የሟች ቤተሰቦች የሞባይሉን ቁጥር ለፖሊስ አሳልፈው በመስጠታቸው ፖሊስ ባደረገው ከፍተኛ የክትትል ሥራ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ሁሉም ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው በአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ቀርበው በወንጀል መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 35 መሠረት የእምነት ክህደት ቃላቸውን መስጠታቸውንም ምንጮቹ ተናግረዋል፡፡

አሁንም በኦሮምያ ዜጎችን ማሰሩ እንደቀጠለ ነው

 ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ የሚታሰሩ ዜጎች ቁጥር መበራከት የአለምን የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ባገኘ ማግስት፣ አሁንም ዜጎችን በሰበብ አስባቡ እያሰሩ ለፍርድ አቅርቦ ማስፈረድ ቀጥሎአል።
አፍሪካ ቀንድ የሰብአዊ መብት ሊግ ያወጠው ሪፖርት እንደሚያሳየው ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአምቦ ከተማ እና በሚዳ ቀኒ ወረዳ ከ20 ያላነሱ ተማሪዎች፣ መምህራንና አርሶ አደሮች ታስረዋል። እስራቱ የተፈጸመው መንግስት የአካባቢውን መሬት ለኢንቨስተሮች መስጠቱን ተከትሎ በተነሳ ተቃውሞ ነው። ከታሰሩት መካከል
አርሶ አደር ኪጣጣ ረጋሳ፣ ተማሪ ቶሎሳ ተሾመ፣ ድሬ ማሾ፣ ታሪኩ ቡልሾ፣ ያለው ባንቲ፣ ቢንያሳ ኢባ፣ ተስፋይ ቢይነሳ እና ነጋዴ መግስቱ ሞሲሳ ይገኙበታል።
እንዲሁም ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የጅምላ እስራቶች እየተከናወነ ነው። ብዙዎቹ በህጋዊ መንገድ የሚታገለው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባላት በመሆናቸው ብቻ መታሰራቸውን የሚገልጸው ሊጉ፣ በጅማ የድርጅቱ አመራሮች የሆኑት አቶ አጀብ ሼክ ሙሃመድ፣ አቶ ሙሃመድ
አሚን ካልፋና አቶ ነቢብ ጀማል ታስረው 2 አመት ከስድስት ወር እንደተፈረደባቸው ጠቅሷል።
ተፈጸመ ስለተባለው እስራት ያነጋገርናቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ተጠሪ አቶ በቀለ ነገአ ሰዎቹ በሃሰት እንደተፈረደባቸው አረጋግጠዋል። መሳሪያ የሌላቸውን ህገወጥ መሳሪያ ደብቃችሁዋል በሚል በሃሰት ተመስክሮባቸው መታሰራቸውን አቶ በቀለ አስረድተዋል ከታሳሪዎች መካከል የአቶ አጀብ ሼክ ሙሃመድ
ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ አዳነች ለኢሳት እንደገለጹት ደግሞ ባለቤታቸው በሀሰት ተመስክሮባቸው ከታሰሩ ጀምሮ እርሳቸውም በሚደርስባቸው ማስፈራሪያ ከቤት ለመውጣት መቸገራቸውን ገልዋል። ወደ ጎረቤት ሄደው እሳት እንዳይጭሩ ከመከልከላቸውም ሌላ፣ ቤታቸው በደንጋይ የደበደባል። የባለቤታቸው ወንድም ተመሳሳይ ችግር ስላጋጠመው ስራውን ትቶ ወደ ከተማ መምጣቱንም ወ/ሮ አዳነች ተናግረዋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሰሞኑን እስር ቤቶች በኦሮሞ ተወላጆች መሞላቱን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ አለም የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ሰጥተውታል።


Wednesday, November 19, 2014

በአርባምንጭ ታስረው የሚገኙ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተፈረደባቸው

 ኢሳት ዜና :-በ2006 ዓም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ረብሻ አስነስታችሁዋላ በሚል ከታሰሩት መካከል 4 ተማሪዎች በ2 አመት ከ3 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላልፏል። ሁለቱ የ4ኛ 5ኛ አመት የህክምና ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ ድገሞ የ3ኛ አመት የነርሲንግ ተማሪዎች ናቸው።

በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚከተሉትን የአለባባስና የምግብ ስነስርአት መመሪያን ተግባራዊ ለማድረግ በዛሬው እለት በአዳማ ዩኒቨርስቲ እንቅስቃሴ መጀመሩ ታውቋል። መንግስት ያወጣውን ህግ ተግባራዊ ለማድረግ በሚንቀሳቀስበት ወቅት መጠነኛ የሆነ ግርግር በዩኒቨርስቲው በር ላይ ተፈጥሯል።

መንግስት በ2003 ባወጣው መመሪያ የእስልምና እምነት ተከታይ ሴትተማሪዎች “ሂጃብ” ማድረግ የሚችሉ ሲሆን “ኒቃብ” መልበስ ግን አይችሉም። መንግስት ለጸጥታና ደህንነት ሲባል የተወሰደ እርምጃ ነው ብሎአል። ሃይማኖታዊ በአላትና ዝግጅቶችን በትምህርት ተቋማት ማካሄድ፣ በቡድን ሰበካ ማካሄድ፣ በቡድን መዘመር፣ በቡድን መጸለይና በቡድን መስገድ እንዲሁም የሃይማኖት መቀስቀሻ የሆኑና ከሃይማኖት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ውጤቶችን በትምህርት ተቋማት ግቢ ማሰራጨትና በመቀስቀሻነት መጠቀም ተከልክሏል።  በምግብ አዳራሽ መመገቢያ ሰአት በግል የህሊና ጸሎት ማድረግ የሚቻል ሲሆን በቡድን ወይም ከአንድ በላይ በመሆን መጸለይ አይቻልም።


ሽመልስ ከማልና ፈትያ የሱፍ በፕሬስ ድርጅት እየተወዛገቡ ነው

‹ችግሮች በአስቸኳይ ካልተፈቱ ለበላይ አካል እናሳውቃለን›› ፈትያ የሱፍ
‹‹ችግሮቹ ውጫዊ ናቸው›› አቶ ሽመልስ ከማል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የባህልና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈትያ የሱፍ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዙሪያ እየተወዛገቡ እንደሚገኙ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች!

የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት አንዱ አካል የሆነው የህሊና እስረኞችን የሶሻል ሚዲያ ንቅናቄ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ዘመቻ ሲሆን ከሚቀጥለው ከእሁድ ከህዳር 14 እስከ 20/2007 የሚቀጥል ፕሮግራም ነው። በዚህ ዘመቻ ሚሊዮኖች የፖለቲካ ይሳተፋሉ፤ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፣ ተገቢ የሆነ አያያዝ እንዲኖራቸው፤ በሰላማዊ መንገድ የሚታሉትን ማሰርና ማዋከብ እንዲቆም ድምፃቸውን ያሰማሉ፤
ዘመቻው ለመንግስት ባለስልጣናት፣ ለመንግስት መስሪያቤቶች፣ ኤምባሲዎች፣ ለታዋቂ ግለሰቦች፣ ለአለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ተሟጓች ተቋማት፣ ለተለያዩ ሚዲያዎች፣ በE‐mail በsms፣ በinbox ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የህሊና እስረኞች አያያዝና የእስር ሁኔታ፣ የታሳሪዎች ማንነትና አሁን የሚገኙበት ሁኔታ ወዘተ በመግለፅ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ ማድረግ ነው።

Tuesday, November 18, 2014

‹‹ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል›› ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከቃሊቲ

ቀጥሎ ያለው አጭር መልዕክት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር በሚገኝበት ቃሊቲ ለተገኘው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የገለጸው መልዕክቱ ነው፤ እንዲህ ቀርቧል፡፡

‹‹ነገሮችን ማወሳሰቡ ለማናችንም አይጠቅምም፡፡ ደግሞ በማናቸውም መልኩ የተወሳሰበ ችግር በመካከላችን ያለ አይመስለኝም፤ የለምም፡፡ እኛ እንደ ሀገር እና ህዝብ ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል፡፡ ጥልቅ የሆነ ትስስሮሽ በመካከላችን አለ፡፡ በመነጣጠልና የህዝብ ተቆርቋሪዎችን በማሳደድ ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ የሚሮጡትን ወደጎን መግፋት ይኖርብናል፡፡ ከምንም በላይ ህዝብ እና ሀገር ይቀድማል፡፡

‹‹አሁን እዚህ እስር ቤት ውስጥ ስላለው ነገር ብነግርህ ብዙ ጊዜ ልወስድብህ እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ፈረንሳያውያን አንድ አባባል አላቸው፤ ‹ፊቴን፣ አካባቢየን ካየህ በቂ ነው፣ ነገሮችን ከእኔ እና አካባቢየ ላይ ማንበብ ትችላለህ› የሚል ነው አባባሉ፡፡ እዚህ ግቢ ስትገባ ያለው ሁኔታ ደስ እንደማይል ማንበብ አያቅትህም፡፡ ብዙ ነገሮች አሉ፣ ጊዜ ጠብቀው ይፋ ይሆናሉ፡፡

‹‹እንደ እናንተ ሁሉ ሰዎች መጥተው ሲጠይቁኝ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ለምሳሌ በዛሬው የእናንተ መምጣት ምክንያት ለ15 ቀናት ያህል ተረጋግቼ እሰነብታለሁ፡፡ ትልቅ የሞራል ስንቅ አለው፡፡ እንዳልኩህ ግን መሰረታዊው ጉዳይ በሀገር ደረጃ ያለውን ትስስሮሽ ከችግሮቻችን መውጫ መንገድ አድርጎ መጠቀም መቻሉ ላይ ነው፡፡ ይህ ነው የሁላችንንም ተስፋ ወደ እውነታ የሚለውጠው፡፡ ስለ ወደፊቱ ማሰብ ይኖርብናል፡፡ አሁን ያለንበት ሁኔታ ወደ ተሻለ ነገር መለወጥ አለበት፡፡››
Photo: ‹‹ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል›› ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከቃሊቲ

ቀጥሎ ያለው አጭር መልዕክት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር በሚገኝበት ቃሊቲ ለተገኘው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የገለጸው መልዕክቱ ነው፤ እንዲህ ቀርቧል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ

‹‹ነገሮችን ማወሳሰቡ ለማናችንም አይጠቅምም፡፡ ደግሞ በማናቸውም መልኩ የተወሳሰበ ችግር በመካከላችን ያለ አይመስለኝም፤ የለምም፡፡ እኛ እንደ ሀገር እና ህዝብ ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል፡፡ ጥልቅ የሆነ ትስስሮሽ በመካከላችን አለ፡፡ በመነጣጠልና የህዝብ ተቆርቋሪዎችን በማሳደድ ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ የሚሮጡትን ወደጎን መግፋት ይኖርብናል፡፡ ከምንም በላይ ህዝብ እና ሀገር ይቀድማል፡፡

‹‹አሁን እዚህ እስር ቤት ውስጥ ስላለው ነገር ብነግርህ ብዙ ጊዜ ልወስድብህ እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ፈረንሳያውያን አንድ አባባል አላቸው፤ ‹ፊቴን፣ አካባቢየን ካየህ በቂ ነው፣ ነገሮችን ከእኔ እና አካባቢየ ላይ ማንበብ ትችላለህ› የሚል ነው አባባሉ፡፡ እዚህ ግቢ ስትገባ ያለው ሁኔታ ደስ እንደማይል ማንበብ አያቅትህም፡፡ ብዙ ነገሮች አሉ፣ ጊዜ ጠብቀው ይፋ ይሆናሉ፡፡

‹‹እንደ እናንተ ሁሉ ሰዎች መጥተው ሲጠይቁኝ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ለምሳሌ በዛሬው የእናንተ መምጣት ምክንያት ለ15 ቀናት ያህል ተረጋግቼ እሰነብታለሁ፡፡ ትልቅ የሞራል ስንቅ አለው፡፡ እንዳልኩህ ግን መሰረታዊው ጉዳይ በሀገር ደረጃ ያለውን ትስስሮሽ ከችግሮቻችን መውጫ መንገድ አድርጎ መጠቀም መቻሉ ላይ ነው፡፡ ይህ ነው የሁላችንንም ተስፋ ወደ እውነታ የሚለውጠው፡፡ ስለ ወደፊቱ ማሰብ ይኖርብናል፡፡ አሁን ያለንበት ሁኔታ ወደ ተሻለ ነገር መለወጥ አለበት፡፡››

በኦሮምያ ዜጎችን ማሰሩ እንደቀጠለ ነው

 ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ የሚታሰሩ ዜጎች ቁጥር መበራከት የአለምን የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ባገኘ ማግስት፣ አሁንም ዜጎችን በሰበብ አስባቡ እያሰሩ ለፍርድ አቅርቦ ማስፈረድ ቀጥሎአል።
አፍሪካ ቀንድ የሰብአዊ መብት ሊግ ያወጠው ሪፖርት እንደሚያሳየው ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአምቦ ከተማ እና በሚዳ ቀኒ ወረዳ ከ20 ያላነሱ ተማሪዎች፣ መምህራንና አርሶ አደሮች ታስረዋል። እስራቱ የተፈጸመው መንግስት የአካባቢውን መሬት ለኢንቨስተሮች መስጠቱን ተከትሎ በተነሳ ተቃውሞ ነው። ከታሰሩት መካከል
አርሶ አደር ኪጣጣ ረጋሳ፣ ተማሪ ቶሎሳ ተሾመ፣ ድሬ ማሾ፣ ታሪኩ ቡልሾ፣ ያለው ባንቲ፣ ቢንያሳ ኢባ፣ ተስፋይ ቢይነሳ እና ነጋዴ መግስቱ ሞሲሳ ይገኙበታል።
እንዲሁም ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች የጅምላ እስራቶች እየተከናወነ ነው። ብዙዎቹ በህጋዊ መንገድ የሚታገለው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባላት በመሆናቸው ብቻ መታሰራቸውን የሚገልጸው ሊጉ፣ በጅማ የድርጅቱ አመራሮች የሆኑት አቶ አጀብ ሼክ ሙሃመድ፣ አቶ ሙሃመድ
አሚን ካልፋና አቶ ነቢብ ጀማል ታስረው 2 አመት ከስድስት ወር እንደተፈረደባቸው ጠቅሷል።
ተፈጸመ ስለተባለው እስራት ያነጋገርናቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ተጠሪ አቶ በቀለ ነገአ ሰዎቹ በሃሰት እንደተፈረደባቸው አረጋግጠዋል። መሳሪያ የሌላቸውን ህገወጥ መሳሪያ ደብቃችሁዋል በሚል በሃሰት ተመስክሮባቸው መታሰራቸውን አቶ በቀለ አስረድተዋል ከታሳሪዎች መካከል የአቶ አጀብ ሼክ ሙሃመድ
ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ አዳነች ለኢሳት እንደገለጹት ደግሞ ባለቤታቸው በሀሰት ተመስክሮባቸው ከታሰሩ ጀምሮ እርሳቸውም በሚደርስባቸው ማስፈራሪያ ከቤት ለመውጣት መቸገራቸውን ገልዋል። ወደ ጎረቤት ሄደው እሳት እንዳይጭሩ ከመከልከላቸውም ሌላ፣ ቤታቸው በደንጋይ የደበደባል። የባለቤታቸው ወንድም ተመሳሳይ ችግር ስላጋጠመው ስራውን ትቶ ወደ ከተማ መምጣቱንም ወ/ሮ አዳነች ተናግረዋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሰሞኑን እስር ቤቶች በኦሮሞ ተወላጆች መሞላቱን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ አለም የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን ሰጥተውታል።


መንግስት የ9ኙን ፓርቲዎች የአደባባይ ስብሰባ መከልከሉ ትግሉን እንደማያቆመው ፓርቲዎቹ ገለጹ

በሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪነት 9 የፖለቲካ ድርጅቶች በጋራ የጠሩት የአደባባይ ስብሰባ በገዢው ፓርቲ የጸጥታ ሃይሎች እንዲበተን ከተደረገ በሁዋላ ድርጅቶቹ ባወጡት መግለጫ ” መንግሥት ከገባበት ከፍተኛ የፍርኃት ስሜት ለመውጣት ያስቀመጠው የሴራ መፍትሄ መስዋዕትነቱን ይጨምር እንደሆን እንጂ፣ ትግሉን አያቆመውም” ብለዋል። ፓርቲዎቹ ለአንድ ወር ባወጡት የስራ መርሃ ግብር መሰረት ከአራት ኪሎ እና አካባቢው ህዝብ ጋር በአደባባይ በቤልኤር ሜዳ ለመገናኘትና በምርጫ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት ቢያቅድም ፖሊስ ስብሰባው እንዲካሄድ መፈቀዱን አላውቅም በማለት በትኖታል።

Monday, November 17, 2014

ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ከተመሠረቱባቸው ሁለት ክሶች አንዱ ተሰርዞ ሌላው እንዲሻሻል ትዕዛዝ ተሰጠ

በማረሚያ ቤት የተጠርጣሪዎች አያያዝ ጉዳይ አሁንም መፍትሔ አላገኘም
በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው ጋዜጠኞችና ጦማሪያን የተመሠረተባቸውን ክስ ተቃውመው ባቀረቡት መቃወሚያ መሠረት፣ ቀርበውባቸው ከነበሩት ሁለት ክሶች አንዱ ሙሉ በሙሉ ተሰርዞ ሌላኛው እንዲሻሻል ፍርድ ቤት ኅዳር 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ትዕዛዝ ሰጠ፡፡
የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የመሠረተውን ክስ በመርመር ላይ ለሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ የተመሠረተባቸውን ክስ የተቃወሙት ጋዜጠኞች ተስፋለም ወልደየስና አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ እንዲሁም ጦማሪያን፣ ማኅሌት ፋንታሁን፣ ኤዶም ካሣዬ፣ ዘላለም ክብረት፣ አቤል ዋበላ፣ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፍ ብርሃኔ ናቸው፡፡

የሰንደቅ አላማችን ጠላት ወያኔና ወያኔ ብቻ ነዉ!

ሰንደቅ አላማ ለአንድ አገር ህዝብ የኩራት፤ የአልበገር ባይነት፤ የአንድነትና የታሪክ ተከታታይነት ምልክት ነዉ። ሰንደቅ አላማ በአንድ በኩል የወደፊቱን ብሩህ ተስፋ ክወዲሁ እያሳየን እየዟችሁ የሚለን፤ በሌላ በኩል ደግሞ በምናብ ወደኋላ እየወሰደን የድልና የመስዋዕትነት ታሪላችንን የሚያስታዉሰን የነጻነት፤ የሠላምና የብሩህ ተስፋ ማህደር ነዉ። የአገራቸን የኢትዮጵያ አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ሰንደቅ አላማ ትናንትናና ከትናንት ወዲያ በተስፋፊዎች አለመደፈራችንን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ዘረኞች የጫኑብንን የመከራ ቀንበር በቆራጥነት ሰብረን ነገና ከነገ ወዲያ የነፃነት አየር እንድንተነፍስ አስረግጦ የሚነግረን የአንድነታችን፤ የተገጋድሏችንና የድላችን ልዩ ምልክት ነዉ። አንድን ኢትዮጵያዊ ሰንደቅ አላማ ላንተ ምንህ ነዉ ብለን ብንጠይቀዉ ጥያቄዉን ዕድሜህ ስንት ነዉ ተብሎ እንደሚጠየቅ አንድና ሁለት ቃል ብቻ ተናግሮ አይመልስም። ሰንደቅ አላማም በአንድና በሁለት ቃላት ምንነቱ የሚገለጽ ተራ ቃል አይደለም። ኢትዮጵያዉያን ተማሩ አልተማሩ፤ ደሃ ሆኑ ኃብታም ፤ወንጀለኛ ሆኑ ወይም ሠላማዊ ለአገራቸዉ ሰንደቅ አላማ የተለየ ቦታ አላቸዉ። ሰዎች የአገራቸዉን ሰንደቅ አላማ የሚወዱትና ለሰንደቅ አላማዉ በክብር መዉለብለብ የህይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉት ስለታዘዙ ወይም ስለ ሰንደቅ አላማዉ ተነግሯቸዉ አይደለም። በእርግጥም የሰንደቅ አላማ ክብርና የአገር ፍቅር ለሰዎች ሰንደቅ አላማዉን አክብሩ፤ አገራችሁን አፍቅሩ እየተባለ የሚነገር ነገር አይደለም። አገርንና ወገንን ማክበርና መዉደድ ሰንደቅ አላማን ከማክበርና ከማፍቀር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነዉ።የሰንደቅ አላማ ልዪ ክብርና የአገር ፍቅር ሰዎች ተወልደዉ ከሚያድጉበት ማህበረሰብ፤ ከቤተሰብ፤ ከጎረቤትና ከጓደኛ እንደ ምግብና እንደ ዉኃ እየበሉና እየጠጡ የሚያገኙት የሰዉነትና የዜግነት መገለጫ ታላቅ እሴት ነዉ።ለዚህም ነዉ የማንም አገር ዜጋ አገሩ ዉስጥ ቢኖር ወይም ካገሩ ዉጭ፤ ቢታሰር ባይታሰር፤ ሀብታም ቢሆን ወይም ደሃ፤ የኔ ነዉ የሚለዉን የእናት አገሩን ሰንደቅ አላማ በፍጹም የማይረሳዉ። ከአገራቸዉ ዉጭ የሚኖሩ ሰዎች ደግሞ በተለይም

እንግሊዝ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በተመለከተ ደብዳቤ መጻፏን ወያኔ አረጋገጠ

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በተመለከተ ለወያኔዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ደብዳቤ መጻፋቸውንና ወያኔም አቋሙን ግልጽ ማድረጓን የወያኔዉ ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን ተናገረ። ሬድዋን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባለፈዉ ማክሰኞ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ዴቪድ ካሜሩን ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደብዳቤ መጻፋቸውን የተለያዩ የውጭ ሚዲያዎች መዘገባቸውን ሰምቻለሁ ካለ በኋለ “ለምን ጻፉ ማለት አይቻልም፤ ጥያቄዉ መሆን ያለበት ምን መለሳችሁ ነው፤” በማለት የተለመደ የማጭበርበሪያ ቃላት ደርድሯል።የተለያዩ የእንግሊዝ ሚዲያዎች ኢትዮጵያ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ ቀደም ሲል የተፈረደውን የሞት ቅጣት እንዳትተገብር እንዲሁም ኢትዮጵያ ለሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ አቶ አንዳርጋቸውን የመጐብኘት ቋሚ ፈቃድ እንዲሰጥ በደብዳቤያቸው መጠየቃቸውንም ሬድዋን ሁሴን ተናግሯል።ለዴቪድ ካሜሮን ደብዳቤ መልስ መሰጠቱን ያረጋገጠዉ ሬድዋን፣ “በተጨባጭ የተፈረደበትን ግለሰብ ነው የያዝነው፤ እንዲህ ብታደርጉት ባታደርጉት ብሎ ማንሳት ይቻላል። ምክንያቱም እነሱም የሚመለከታቸው በመሆኑ። በዚህ ምክንያት ግን የእኛ መልስ በራሳችን ሕግ መሠረት ዓለም አቀፍ ሕጉም በሚለው መሠረት የምናደርገውን እናደርጋለን፤” ብሏል። ኢትዮጵያ የምትተገብረው የራሷን ሕግ መሆኑን የገለጹት አቶ ሬድዋን፣ “ከነጭም ከጥቁርም የሚመጣን ደብዳቤ ተንተርሰን ምንም አንተገብርም፤” ብሏል። ከዚህ በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን ደብዳቤ ጽፈው፣ በኢትዮጵያ በኩልም መልስ ተስጥቷል ያለዉ ሬድዋን ሁሴን በደብዳቤው የቀረቡ ጥያቄዎች ቅሬታ እንዳላስነሱ ሁሉ መልሱም ቅሬታ አያስነሳም የሚል ተስፋ በኢትዮጵያ በኩል መኖሩን ተናግረዋል።“እነሱ ዜጋዬ ነው ብለዋል፤ የእነሱ ዜጋ እንደ ቼ ጉቬራ ነፃ አውጣ ተብሎ ኢትዮጵያ ውስጥ አልተላከም። የእነሱ ዜጋ ከነበረ የእንግሊዝን ዴሞክራሲ ይበልጥ ለመጨመር መታገል ይችል ነበር። ነገር ግን በኢትዮጵያ በቅጥር ነብሰ ገዳይነት ካልተሰማራ በስተቀር ሌላ ሚና አልነበረውም፤” ብለዋል።

Friday, November 14, 2014

ሁሉም የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ውጤታቸው የሚሞላላቸው በምርጫው ለኢህአዴግ በሚያዘጋጁት የድጋፍ ሃይል መጠን ነው ተባለ

ኢሳት ዜና :- ትምህርት ሚኒስቴር ” የከፍተኛ ትምህርት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጃት ማንዋል፣ ለምርጫ 2007 የተሻሻለ” በሚል ርእስ ያዘጋጀውና ለኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣኖች የቀረበው ሰነድ እንደሚለው በአገሪቱ ያሉ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዚዳንቶች ውጤታቸው የሚሞላላቸው በምርጫው ለኢህአዴግ በሚያዘጋጁት የተማሪዎች የድጋፍ ሃይል መጠን ነው።

ሰነዱ የትምህርት ልማት ሰራዊትን በዩኒቨርስቲዎች ለማስፋፋት የተደረገው ስራ ብዙም ውጤት እንዳላስገኘ ጠቅሶ፣ ለዚህም ዋናው ምክንያት በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ያሉ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች በአደረጃጃቱ ላይ አመኔታ በመጣታቸው ነው ብሎአል። የትምህርት ልማት ሰራዊትን ማደራጀት የፖለቲካ እንጅ የቴክኒክ ጉዳይ ባለመሆኑ ፣ በትምህርት ልማት የሚታቀፉ መሪዎች፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ሰራተኞችና ድጋፍ ሰጪ ድርጅቶች የትምህርት ሴክተሩን እቅድ መተግበር ብቻ ሳይሆን፣ በፖለቲካ ስእብናቸው የተገነቡና ኢህአዴግን የሚቀበሉ ተማሪዎች አድርጎ ማውጣት ይጠበቅባቸዋል ሲል ሰነዱ ያመለክታል።

ህወሓት በ2007 ምርጫ ሊሸነፍ እንደሚችል አመነ (አብርሃ ደስታ ከትግራይ)

ዓረና ፓርቲ በትግራይ ክልል ወረዳዎች በመዘዋውር ባሰብሰበው መረጃ መሰረት በ2007 በሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ገዥው ፓርቲ የህዝብን ድምፅ ካከበረ ህወሓት በመላው ትግራይ ሙሉ በሙሉ ይሸነፋል። አንድ የህወሓት የስራ አስፈፃሚ አባል (ለግዜው ስሙ ይቅር) በዓዲግራት ከተማ ለተሰበሰቡ ከምስራቃዊ ዞን የተውጣጡ የህወሓት ካድሬዎች “እናንተ በምትፈፅሙት በደል ምክንያት በ2007 ምርጫ እንሸነፋለን። ግን አንዳንድ የምናደርጋቸው ነገሮች ስለሚኖሩ ሙሉ በሙሉ ተስፋ አትቁረጡ። ለራሳችሁ ዕጣ ፈንታ ስትሉ በደንብ ስሩ” ማለቱ ታውቋል። ካድሬዎቹም “በናንተ (የላይኞቹ አመራሮች) ችግር ነው የምንሸነፈው፤ ህዝብ የማይቀበለውን ነገር እንድናሳምን ታስገድዱናላቹ” የሚል መልስ በመስጠታቸው የእርስበርስ ንትርክ መከፈቱ ታውቋል። ከስብሰባው በኋላ ካድሬዎቹ የንትርኩ ነጥቦች ለዓረና አባላት አስረድተዋል።

የሶዶ ከተማ ጎዳና ተዳዳሪዎች በግዳጅ ካምፕ እንዲገቡ ተደረገ

ከህዳር 6/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 10/2007 ዓ.ም በሶዶ ከተማ የሚደረገውን የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክቶ ሶዶ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ጎዳና ተዳዳሪዎች በግዳጅ ወደ ካምፕ እንዲገቡ መደረጋቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡

በመቶዎቹ የሚቆጠሩ ሴት፣ አዛውንትና ህጻናት ጎዳና ተዳዳሪዎች ሶዶ ውስጥ አራዳ ክፍለ ከተማ ተብሎ በሚጠራውና አዲስ እየተሰራ በሚገኘው ገለሜ የተባለ እስር ቤት ውስጥ በግዳጅ እንዲገቡ መደረጉን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ካምፕ ውስጥ የገቡትን የጎዳና ተዳዳሪዎችም የቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ለሳምንት ቀለብ እንደሚያቀርብላቸውና ጉባዔው ካለቀ በኋላ ወደነበሩበት እንደሚመለሱም ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ለጉባኤው ሲባል ዜጎችን በግዳጅ ወደ ካምፕ ማስገባቱ ደኢህዴን በከተማዋ ልማት እንደተመዘገበና ህዝቡን ከድህነት እንዳላቀቀ ለማስመሰል ያደረገው አስነዋሪ ተግባር ነው›› ያሉት የሰማያዊ ፓርቲ የወላይታ ዞን የአደረጃጀት ኃላፊ አቶ ታደመ ፈቃዱ ‹‹እስካሁን ሶዶ ከተማ ውስጥ መብራት ስለማይኖር በርካቶች ተዘርፈዋል፡፡ የተገደሉም አሉ፡፡ የከተማዋ ውበትም እምብዛም የተጠበቀ አልነበረም፡፡ አሁን ግን ከተማዋን ለማጽዳት እየተሯሯጡ ነው፡፡ መብራት ባልነበረበት ከተማ መንገዱ ሁሉ ባውዛ ሆኗል›› ሲሉ ስለሁኔታው አስረድተዋል፡፡

ለደኢህአዴን ጉባዔ ተብሎ የከተማዋ ውበት እንዲጠበቅና የጠፉት አገልግሎቶች ለጊዜው እንዲስተካከሉ መደረጉም በህዝቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል ተብሏል፡፡ ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው አንድ የከተማዋ ነዋሪም ‹‹ህዝቡ በአገልግሎቶች መጥፋት ተማሯል፡፡ የከተማው ውበት ለሚኒስትሮቹ እንጅ ለእኛ አይደለም፡፡ እንዲህ ከሆነ ደኢህዴን በየ15 ቀኑ ጉባዔ ቢያደርግ ጥሩ ነበር›› ሲሉ ስለሁኔታው ገልጸውልናል፡፡

ለጉባዔው ሲባልም በጸጥታ ስም በተቃዋሚዎች ላይ ክትትል እየተጠናከረ ይገኛል ያሉት አቶ ታደመ ‹‹ከተማዋ በፖሊስ ተጥለቅልቃለች፡፡ ፖሊሶች በየ 10 ሜትሩ ቆመው ነው የሚታዩት፡፡›› ብለዋል፡፡

በጅማ አንድ እናት እስከነልጃቸው በአሰቃቂ ሁኔታ በፖሊሶች ተገደሉ

ኢሳት ዜና :- ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ በአካባቢው የሰፈሩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በህዝቡ ላይ የሚወስዱት እርምጃ እየተባባሰ መጥቶ ረቡዕ ሌሊት ለሃሙስ አጥቢያ ፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የፌደራል ፖሊሶች ወደ አንድ ወጣት መኖሪያ ቤት ሰብረው በመግባት እርሱንና እናቱን

ጅማ

በአምስት አምስት ጥይኦች በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለው ወደ ካምፓቸው አምርተዋል። የከተማው ህዝብ ተቃውሞውን ለማሰማት ሃሙስ ጠዋት ወደ አደባባይ ቢወጣም የጠበቀው የፖሊስ ዱላ ነው።

እማኞች ለኢሳት እንደገለጹት ወ/ሮ መንበረ የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ በሆቴል አገልግሎት ኑሮአቸውን የሚገፉና በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ የሚከበሩ ልጃቸው ዮናስም እንዲሁ በጸባዩ ምስጉን የሆነ የገዢው ፓርቲ ተቃዋሚ ነው። የፌደራል ፖሊሶች ወደ ወ/ሮ መንበረ ሆቴል ገብተው ሲጠጡ ከቆዩ በሁዋላ አንከፍልም

በማለት መውጣታቸው ያበሳጨው ልጃቸው ወጣት ዮናስ ” የዚህ መንግስት አገልጋዮች ስለሆናችሁ ነው” በሚል ተናግሮአቸዋል። ወታደሮቹ ምንም ሳይሉ ወደ ካምፓቸው ካመሩ በሁዋላ ፣ ሌሊት ላይ መሳሪያቸውን ይዘው በመምጣት የዮናስ እናትን ቤት በር ሰብረው በመግባት ዮናስን በ5 ጥይት ደብድበውታል።

እናቱ ወ/ሮ መንበረ ” እባካችሁ ልጄን አትገደሉብኝ” ሲሉዋቸው ፖሊሶቹ እርሳቸውንም በ5 ጥይቶች ገድለዋቸው ወደ ካምፓቸው ተመልሰዋል።

ድርጊቱ ያስቆጣቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ከቀበር በፊት የተቃውሞ ሰልፍ ቢያደርጉም፣ በፖሊሶች ዱላ ተደብድበው ተበታትነዋል። ጅማ ጧት አካባቢ በተኩስ ስትናወጥ መዋሉዋንም ነዋሪዎች ተናግረዋል። በጉዳዩ ዙሪያ አንድ የጅማ ነዋሪ አነጋግረናል

ከአንድ ሳምንት በፊት አንዋር የተባለ ወጣት በጩቤ በአሰቃቂ ሁኔታ ከተገደለ በሁዋላ ህዝብ ድርጊቱን ለመቃወም ወደ አደባባይ ቢወጣም በተመሳሳይ መልኩ በፖሊሶች ተደብድቦ ተባሯል።

ከአንድ ወር በፊት ደግሞ ኬኔዲ መንገሻ የሚባል አዲስ ቅጥር የመንግስት ሰራተኛ በፖሊሶች ተገድሏል። በአካባቢው የሰፈረው የፌደራል ፖሊስ በህዝቡ ላይ የሚወስደው እርምጃ መጨመሩ ህዝቡ በስጋት እንዲኖር አድርጎታል። ነዋሪዎች እንደሚሉት ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ እየሆነ ነው።

በጉዳዩ ዙሪያ የጅማ ፖሊስን ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

Thursday, November 13, 2014

ምርጫ 2007 እና የ‹‹ተመራጩ›› አምባገነን ጉዞ

ጌታቸው ሺፈራው

በየዘመኑ የመንግስት ስርዓቶች ይቀያየራሉ፡፡ የህዝብ አመለካከት አድማስና የሚፈልገው ስርዓትም እንዲሁ፡፡ ይህን ሁሉ በሚገባው መንገድ ለመምራት ደግሞ ገዥዎች ለወቅቱ  ሁኔታ የሚያወጣቸውን የአገዛዝ ስርዓት ይዘረጋሉ፡፡ በተለይ ከህዝብም ሆነ ከሌላ አካላት ስልጣንና ህይወታቸውንም እያጡ የሚገኙት አምባገነኖች ስልጣናቸውን ለማቆየት የሚደረግን ብልጣብልጥ መንገድ ሁሉ መከተላቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ በአሁኑ ወቅት ምርጫ ዘመናዊ ፖለቲካ መለኪያ ነው፡፡ ነገር ግን ምርጫ አምባገነኖችን ስልጣን የሚያሳጣ በመሆኑ በሙሉ ልባቸው ወደ ምርጫ መግባትን አይደፍሩም፡፡ ከዚህ ይልቅ በስመ ምርጫ፣ አምባገነንነታቸውን፣ አፋኝነታቸውን ያጠናክራሉ፡፡ እነዚህን አብዛኛዎቹ ብልጣብልጦች ምርጫን እየጠሉ በስመ ምርጫ ስልጣናቸውን የሚያራዝሙ አምባገነኖች ‹‹ተመራጭ አምባገነኖች›› ይሏቸዋል፡፡

ይህ አይነት ስርዓት ከአፍሪካዎቹ ዚምባብዌ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣  ዩናጋዳ እስከ  ቱርክ ኢራንና ሩሲያ ድረስ ያለውን የብልጣብልጦች ‹‹መንግስት›› የሚያጠቃልል ነው፡፡ በእርግጥ በአፍሪካው በተለይም ደግሞ በኢትዮጵያ ገዥው ፓርቲ ደህንነትና መከላከያ ሰራዊቱን በቀኝ እጁ ምርጫን ደግሞ በግራው አንጠልጥሎ ወደ ‹‹ምረጡኝ›› የሚገባበትና ያልፈለገው ነገር ሲከሰት ‹‹ጨዋታ ፈረሰ!›› የሚልበት በመሆኑ ‹‹ተመራጭ አምባገነን/አፋኝ›› የሚባለውን መስፈርትም ብዙም የሚያሟላ አይደለም፡፡ ብልጣብልጥነትን ይልቅ ግትርነት፣ ማን አለብኝነት፣ አሊያም እኔ ከሞት ሰርዶ አይብቀል አይነት የአህያዋ አስተሳሰብ የተጠናወተው ነው ማለት ይቀላል፡፡

የዞን 9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች አስራአንደኛ የፍርድ ቤት ውሎ

በዛሬው እለት በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ 10 ተከሳሾቸን ጉዳይ ሊያይ የተሰየመው ችሎት በጦማርያኑ እና በጋዜጠኞቹ ላይ የቀረበውን ክስ አቃቤ ህግ አንዲያሻሽል ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡ባለፈው ሳምንት የክስ ፋይሉን አስመልክቶ የህግ እና የፍሬ ነገር ችግር አለበት በሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ያቀረቡትን የተከሳሾች ጠበቆች አንዲሁም መሻሻል የሚገባው ነገር የለውም ያለውን የአቃቤ ህግን መልስ ተከትሎ ብይን ለመስጠት ተቀጥሮ በዳኞች ለውጥ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶ የነበረው ችሎት ዛሬ ክሱ ላይ መሰረታዊ ማሻሻያ እንዲደረግ ብይን ሰጥቷል፡፡
ብይኑም በአጠቃላይ ሲታይ

ጊዜው የሕዝባዊ እምቢተኝነት ነው!!!

በአሁኑ ወቅት በአገራችን በከተሞችና በገጠሮች እየታዩ ያሉ ምልክቶችን በጥንቃቄ የመረመረ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መታዘቡ አይቀርም።በአንድ በኩል፣ ወያኔ የተወገደባት፣ ፍትህ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየት ተስፋችን እየለመለመ ነው። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም ዓመታት በሕዝብ ላይ ሰፍኖ የነበረው የፍርሀት ደመና እየገለጠ በመሆኑ ተዘግተው የቆዩ አንደበቶች መናገርና “ይኸ ሁሉ ግፍ ለምን?” ብለው መጠየቅ ጀምረዋል። ይህንን መነቃቃት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም፣ በኪነጥበብም እያየነው ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጥ በአገራችን ሊመጣ እንደሚችል ከማመን አልፎ ራሳቸውን በለውጥ አምጭ ኃይልነት መመልከት ጀምረዋል። በርካታ ወጣቶች ወያኔን በትጥቅ ለመገዳደር የወሰኑ ወገኖቻችንን እየተቀላቀሉ በዚህም ምክንያት ጉልበታቸውን እያፈረጠሙ ነው። የለውጡ እርሾ ከሲቪሉ አልፎ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ውስጥም እየተብሰለሰለ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፣ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ኃይል መሆኑ እያበቃ በአንፃሩ የትግሉ አጋር የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እየታዩ ነው። በሁሉም የሠራዊቱ ክፍሎች

ቤተክርስቲያን እንዳይፈርስ የተቃወሙት ዜጎች ታፍሰው የት እንደደረሱ አልታወቀም; “ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው”

ነገረ ኢትዮጵያ) ትናንት ህዳር 3/2007 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ የማሪያም ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ በመቃወማቸው የታፈኑት ዜጎች የት እንደደረሱ አልታወቀም ሲሉ በወቅቱ ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎችና የእምነቱ ተከታዮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
በወቅቱ 600 ያህል ዜጎች ተገኝተው ቤተ ክርስቲያኗ እንዳትፈርስ ሲቃወሙ እንደተመለከቱ የገለጹት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የቤተ ክርስቲያኗን መፍረስ የተቃወሙትን ጨምሮ ሌሎች በአካባቢው የተገኙ ዜጎችም በፖሊስ መታፈሳቸውን ገልጸዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ‹‹ህዝቡ በሰንደቅ አላማ አምላክ አታፍርሱብን እያለ ቢለምንም እነሱ ግን ጥይት ወደላይ በመተኩስ ህዝቡን ከማሸበራቸውም በላይ ያገኙትን እየደበደቡ በ9 የድንጋይ መጫኛ መኪና አስገድደው በመጫን ወዳልታወቀ ቦታ ውስደዋቸዋል፡፡ አድማ በታኝ ፖሊስ ቄስ፣ አዛውንት፣ ህጻንና ሴት ሳይል ያገኘውም አፍሶ ወስዷል፡፡ የኮብል ስቶን ጠራቢዎች ሳይቀሩ በአካባቢው በመገኘታቸው ታፍሰው ታስረዋል፡፡ አሁን የት እንዳሉ አይታወቅም፡፡›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራች ከሁለት አመት በላይ እንደሆነ የገለጹት አንድ የአካባቢው ነዋሪ ‹‹ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራችበት ጊዜ ጀምሮ እንድትፈርስ ጥያቄ እንደቀረበ ተገልጾልን አያውውም፡፡ አሁን ነው ደርሰው ያፈረሱት፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን አገልጋዮች ጨምሮ በጣም ብዙ ሰው በዱላ ተደብድቧል፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው፡፡›› ሲሉ ቅሬታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎችና አማኞች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ቤተ ክርስትያኗ እንዳትፈርስ እንደተቃወሙ፣ አድማ በታኝ ፖሊስ በአካባቢው ያገኘውን ሰው ካፈሰ በኋላ ቤተ ክርስቲያኗን በማፍረስ ቆርቆሮውን በመኪና ጭኖ እንደሄደ የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡


የህወሃቱን ፖለቲካ የአዋጁን በጀሮ!

ህወሃት በተፈጥሮው የፖለቲካ ብዙህነት ወይም ብዝሃነትን ማቻቻል የሚባል ነገር አያውቅም። ሌላው ቀርቶ በራሱ በድርጅቱ ውስጥ የሚነሱ የተለዩ ሃሳቦችን ሁሉ እንደጠላት ሃሳብ ፈርጆ ሰዎችን ደብዛቸውን ማጥፋት የተለመደ የህወሃት አሰራር ነው። ይህን የህወሃት ባህርይ በቅጡ ለመረዳት በቅርቡ የቀድሞው የህወሃት አመራር አባል የነበረው አቶ ገብሩ አስራት የጻፈው መጽሃፍ ጥቂት ገጾች በማየት መረዳት ይቻላል። ተቃዋሚ ፓርቲ ሰላማዊም ሆነ አልሆነ በህወሃት እንደጠላት ነው የሚቆጠረው።

ሰሞኑን ከትግራይ የህዝብና የመንግስት ግንኙነት ቢሮ ከሚባለው መስሪያ ቤት በትግረኛ ተጽፎ ለአባለት በሚስጥር የተሰራጨ ደብዳቤ ማንኛውምንም ተቃዋሚና ከህወሃት ውጭ የሚያስብና ህወሃትን የማይከተል ሁሉ “ፀላኢቲ” ጠላቶች ሲል ይፈርጃል። በዚህ ባለ 5 ገጽ ደብዳቤ ውስጥ እነዚህን “ፀላኢቲ” እንዴት እንደሚያሳድዱ፣ እንዴት እንደሚያዋክቡና እንደሚያጠፉ የሚመክር መመሪያ የሚሰጡ ሃሳቦች ተቀምጠዋል። በደብዳቤው ላይ ከአናቱ ሆነው የሚያስተዳደሩትን ወገናቸውን እንኳን አይለይም። በአጭሩ እኛ እንዳንመርጥ የሚፈልግ፣ የሚቀናቀንና ሌሎች ሰላማዊ ፓርቲወችን የሚመራና የሚደግፍ ሁሉ ፀላኢቲ ነው።

Wednesday, November 12, 2014

የገርጂ ኤሌክትሪክ ማሰራጫ ጣቢያ ቃጠሎ ደረሰበት

በታምራት ጌታቸው

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የገርጂ ማሰራጫ ጣቢያ ትናንትና ከሰዓት በኋላ 10፡30 ላይ የእሳት ቃጠሎ ደረሰበት፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ የተቃጠለው የገርጂ ማሰራጫ ጣቢያ፣ ከመገናኛ በኡራኤል እስከ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ ያለውን አካባቢ የሚሸፍን መሆኑም ታወቋል፡፡

ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባለመታወቁ፣ የዕለቱ ተረኛ ሠራተኞችን ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ በምርመራ ላይ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በተለይ በጥቅምት ወር መጨረሻ አካባቢ በተደጋጋሚ የኃይል ማቋረጥ ማጋጠሙም ይታወቃል፡፡ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና አገልግሎት ኃላፊዎች ጊዜያዊ ችግር ተፈጥሮበታል ወደተባለው የጣና በለስ የኃይል ማመንጫ መጓዛቸው ተነግሯል፡፡ የጣና ብልሽትም ሆነ በገርጂ ማሰራጫ ጣቢያ የደረሰውን አደጋ እንዲያብራሩ የመሥሪያ ቤቱን ኃላፊዎች ለማግኘት ቢሞከርም፣ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡

Tuesday, November 11, 2014

ግልጽ ደብዳቤ ”ለጠቅላይ ሚኒስትር” ኃይለማርያም ደሳለኝ : ከታሳሪ ዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስታችንን ያክብሩ!ሠላም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር!? እንዴት ነዎት? ያስታውሱ ከሆነ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢከፊሉ የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች  ‘ግልፅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ’“ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እባክዎትን የተለያዩ የመንግስት አካላት የሕገ መንግስታችንን ድንጋጌዎች እየጣሱ ነውና እርስዎም በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 74/13/ መሠረት ሕገ መንስቱን የማስከበርና የማክበር ግዴታ ስላለብዎት ሕገ መንግስቱን ያክብሩ” እኛም የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች የዚህ ‘ልማታዊ ርምጃ’ ሰለባ የሆንን ግለሰቦች ነን፡፡በርግጥ ከሁለት ዓመታት በፊት ‘ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስቱን’ ያስከብሩልን በማለት ጥያቄ ያቀረብንልዎት ግለሰቦች ‘ከ6 ወራትበፊት ሕገ መንግስቱን ለመናድ  ሞክራችኋል’ በማለት መንግስትዎ ሲያስረን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር ጠይቀን ሕገ መንግስቱን ለመናድ በመሞከር ወንጀል ተጠርጥረን ስንታሰር እስሩ በጣም ግራ አጋብቶን ነበር፡፡በዚህ ያልቆመው መንግስትዎ ክሱን ‘ሕብረተሰቡንና ሀገሪቱን ለማሸበር አቅዳችኋል ሞክራችኋል አሲራችኋል…’ በማለት ወደ ‘ሽብርተኝነት’ያሳደገው ሲሆን እርስዎም ከዚህ ጋር በተያያዘ ሃሳብዎትን ሲሰጡ ስለተመለከትንዎ ትንሽ ቅሬታ ይዘን መጣን፡፡በቅድሚያ አሁን ያለንበትን ሁኔታ በትንሹ ብናስረዳዎት ቅሬታችንን ለመረዳት ያስችልዎታልና አንዳንድ ጉዳዮችን እንንገርዎት፡፡ይሄን ማስታወሻ በምንፅፍልዎት ወቅት

አምሳሉ ገኪዳንና ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ታሰሩ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ ተጠይቆበት ወደ ማረፍያ ክፍል መግባቱ ታወቀ፡፡
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የጅማ ዩኒቨርሲቲ ባቀረበበት ክስ የፕሬስ ህጉን በሚፃረር መልኩ ለአራት ቀናት በማዕከላዊ ታስሮ የተለቀቀው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ክሱ እንደ አዲስ እንዲቀሰቀስበት ከተደረገ በኋላ ዛሬ በተለምዶ ገዳም ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ሁለተኛ የወንጀል ችሎት ከእንቁ መፅሔት አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን ጋር እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝም ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ እና የእንቁ አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን እያንዳንዳቸው የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ እንዲያቀርቡ እስከዛውም ወደ ማረፊያ እንዲሄዱ አዟል፡፡
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን በአሁኑ ሰዓት ችሎት መድኃኔዓለም አካባቢ በሚገኘው ወረዳ 8 ጣቢያ እንደሚገኝም ታውቋል


ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ።

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።




ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ አንጎላዊ ጋዜጠኛ ነው። በሙያው በሃገሩ አንጎላ በርካታ ክስ እና እስር እንደገጠመው ይነገራል። ባለፈው ወር በደቡብ አፍሪካ ዊትስ በተካሄደው የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥሰት በመፈጸም ከአፍሪካ ህብረት ህልም በተቃራኒ ቆማለች በማለት ተችቷል። ''የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በቀዳሚነት የመላ አፍሪካውያንን ህልም ይወክላል። የሰው ልጅ ክብር እና የሰብዓዊ መብት ክብር ደግሞ የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ህልም ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የሰዎችን ሰብዓዊ መብት በመጣስ በተቃራኒው መንገድ እየተጓዘች ነው። ይህ ደግሞ የአፍሪካውያንን ህልም አይወክልም። የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች በመፍታት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነትን እንዲያከብር እና ዜጎች እና ጋዜጠኞች ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በተግባር እንዲያውሉ እንዲፈቅድ የአፍሪካ ህብረት ጫና ማድረግ ይኖርበታል። ''

ራፋኤል በጉባኤው የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን እስር እና ክስ እንዲሁም የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝን የሶስት አመት ብያኔ በማሳያነት አንስቷል። አፍሪካውያን ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በቸልታ አልፈዋል ሲልም ተችቷል። ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ማክበር ካልቻለች የአፍሪካ ህብረት ከአዲስ አበባ መነሳት ይኖርበታል ብሎ ያምናል።

''የተወሰኑ ጋዜጠኞችን አውቃለሁ። በ2005 ተኩስ ሲጀመር እና ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ሲታሰሩ በአዲስ አበባ ነበርኩ። አሁን በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ በቂ ግንዛቤ አለኝ። ከኢትዮጵያውያን ምሁራን እና አሁን ባለው መንግስት የተለያየ ጫና የደረሰባቸውን ሰዎች አገኛለሁ። የአፍሪካ ህብረትን ለመወከል በመጀመሪያ ሰብዓዊ መብትን የሚያከብር ሃገር እንፈልጋለን። ኢትዮጵያ ይህንን ማድረግ ካልቻለች እንደ አፍሪካዊነታችን የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ዜጎች ራሳቸውን የመግለጽ እና ሰብዓዊ መብት ወደ ተከበረበት ሃገር እንዲዛወር መጠየቅ ይኖርብናል። ምክንያቱም ግለሰቦች የሚከበሩባት መንግስታት የህዝብ አገልጋይ እንጂ ከህግ በላይ ያልሆኑባት አጋርነት የጠነከረባት አፍሪካን እንሻለን። ኢትዮጵያ ደግሞ በአሁኑ ወቅት ይህን እያደረገች አይደለም። ''''

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ ባለፈው አመት ብቻ በኢትዮጵያ ስድስት የህትመት ውጤቶች ሲዘጉ ከ ሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች መሰደዳቸውን ይፋ አድርጓል። በምህጻሩ ሲፒጄ ተብሎ በሚጠራው የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ተቋም መሰረት ደግሞ ቢያንስ 17 ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ በእስር ላይ ይገኛሉ። ራፋኤል ማርኩዌዝ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ አፍሪካውያን ሊተባበሩ ይገባል ሲል ይናገራል።

''አፍሪካውያን በሙሉ በተለይም ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በትብብር ከሰራን የኢትዮጵያ መንግስት ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ ማድረግ እንችላለን። አላማችን ኢትዮጵያን ማግለል አይደለም። አላማችን ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን እንድታከብር ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩትንም እንድትፈታ ነው።''

Monday, November 10, 2014

ሌ/ጄነራል አበባው ታደሰ ወደ ውጭ ሊወጡ ሲሉ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በደህንነቶች ተመለሱ

(ከኢየሩሳሌም አርአያ)

ጄ/ል አበባው ታደሰ ወደ ውጭ ለመውጣት ሲሉ ከቦሌ አየር ማረፊያ በደህንነቶች እንዳይወጡ መደረጋቸውን ታማኝ ምንጮች ጠቁመዋል።

ከመከላከያ የጦር አዛዥነታቸው በጄ/ል ሳሞራ የኑስ እንዲነሱ የተደረጉት ጄ/ል አበባው ከአገር እንዳይወጡ የተደረገበት ምክንያት ግልፅ እንዳልሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ የተለያዩ ጥያቄዎች እንዳሉ በመግለፅ ለኢታማጆር ሹሙ ጄ/ል ሳሞራ ከረር ያለ ሪፖርት ያቀረቡት ጄ/ል ሰዓረ፣ ጄ/ል ሞላና ጄ/ል አበባው መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ በሳሞራ የተሰጠው መልስ ” የትምህክተኞች ጥያቄ ነው፤ ችግር የለም..» የሚሉና ጥያቄዎቹን የሚያጣጥሉ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

ሶስቱ ጄኔራሎች በሳሞራ ምላሽ በመበሳጨት ከስልጣናቸው ለማስነሳት በምስጢር ቢመክሩም መረጃው ባልታወቀ መንገድ አፈትልኰ ጄ/ል ሳሞራ ዘንድ በመድረሱ ጄ/ል ሰዓረ ከሰሜን ዕዝ አዛዥነታቸው፣ ጄ/ል ሞላ ከአየር ሃይል እንዲሁም ጄ/ል አበባው ከያዙት ስልጣን በሳሞራ በአስቸኳይ እንዲነሱ ሲደረግ በተለይ ጄ/ል አበባው ከ2 ወር በፊት ከመከላከያ እንዲባረሩ መደረጉን ምንጮቹ አስረድተዋል። በጄ/ል ሰዓረ ቦታ ጄ/ል ገብራት አየለ ሲተኩ በጄ/ል ሞላ ደግሞ የአግአዚ ክ/ሰራዊት አዛዥ ጄ/ል አደም መሐመድ መተከታቸውን አስታውቀዋል።

ሁለቱ ጄኔራሎች ዝቅ ባለ ደረጃ ተራ የመምሪያ ሃላፊ ተደርገው መሾማቸውን ምንጮቹ ገልፀዋል። ጄኔራል የመሾምና የመሻር ስልጣኑ የጠ/ሚ/ሩ እንደሆነ ህገመንግስቱ ቢደነግግም ነገር ግን የተጠቀሱት ጄኔራሎች የተነሱት በጄ/ል ሳሞራ ትእዛዝ፣ የተተኩትም በሳቸው ውሳኔ እንደሆነና ጠ/ሚ/ር ሃ/ማርያም ከወራቶች በኋላ እንዲያውቁ ተደርጐ ለተሾሙት ጄኔራሎች የማእረግ እድገት እንዲሰጡ መደረጉን ምንጮቹ አስረድተዋል። ጄ/ል አበባውና ጄ/ል ሰዓረ በሙስና ከተዘፈቁ የጦር አዛዦች እንደሚጠቀሱ አክለው ገልፀዋል። ..ይህ በእንዲህ እንዳለ በመከላከያ ከፍተኛ ግመገማ ከሰሞኑ እየተካሄደ ሲሆን ስር የሰደዱ ቀውሶች እየፈነዱ መሆኑ ታውቋል።


የደህንነት ሃይሎች ዜጎችን እያፈኑ መውሰዱን ቀጥለውበታል!

ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ተጠናክሮ የቀጠለው የገዢው ፓርቲ አፈና መንግስት ራሱ ያስታጠቃቸውን ታጣቂዎች ትጥቅ እስከማስፈታት መድረሱን ምንጮች ገለጹ

በትግራይና በአማራ ክልሎች ባለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው አፈና ቀጥሎ ጥቅምት 26 ቀን 2007 ኣም የሰላም ታጋይ እየጠባለ የሚታወቅ ወጣት ሽሻይ አዘናው በመቀሌ ከተማ በትግራይ ክልል የፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ገ/ህይወት ካህሳይ እና በደህንነት ሃይሎች ከሚሰራበት የኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ታስሮ እና ቤቱ ተበርብሮ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዷል። ሽሻይ አዘናዉ የዓረና ትግራይ መስራችና ማእከላዊ ኮሚቴ አባል የነበረ በቅርቡ ደግሞ ከዓረና ወደ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ የተቀላቀለ ወጣት ነው።

በተመሳሳይ ዜና ደግሞ ቋራ በደላ ቀበሌ አካባቢ መሳሪያ የታጠቁ አርሶአደሮች መሳሪያቸውን እየተነጠቁ ነው። ትክል ድንጋይ አካባቢም እንዲሁ በርካታ ታጣቂዎች መሳሪያቸውን እንዲያስረክቡ መደረጋቸውን የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል። ባለፉት ሶስት ቀናት በትግራይ ክልል በምዕራባዊያን ዞን ቃፍታ ሁመራ ወረዳ ዳንሻ ከተማ የአረና ፓርቲ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ዘነበ ሲሳይ ጥቅምት 25፣ 2007 ዓም ከቤታቸው ተወስደው ሲታሰሩ፣ እንዲሁም በተመሳሳይ ቀን በሁመራ አረና የቁጥጥር ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ አማረ ተወልደ ታስረዋል። ከወራት

በፊት የታሰሩትን አብራሃ ደስታንና አያሌው በየነን ጨምሮ 7 የፓርቲው አመራሮች በእስር ላይ ናቸው። በተመሳሳይ ቀን በአማራ ክልል ምዕ/ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ወረዳ የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን አበበ እና ሶስት የድርጅቱ አባላት ተይዘው ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። ባለፉት ሶስት ቀናት ብቻ ከ10ያላነሱ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል። የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት አንዱአለም አራጌ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ ናትናኤል መኮንንና ሃብታሙ አያሌው አሁንም በእስር ላይ ናቸው።

የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል እና የሰሜን ጎንደር የዞን ሰብሰቢ አቶ አግባው ሰጠኝም እንዲሁ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። ሶስት የሰማያዊ ፓርቲ የአርባምንጭ አመራሮች አሁንም ድረስ በእስር ላይ ናቸው።

በምእራብ ጎጃም በፍኖተሰላም ከተማ የመኢአድ የወረዳው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ) ሰብሳቢ የሆነው ዘሪሁን ብሬ ረቡዕ ጥቅምት 26፣ 2007 ዓም ተይዞ ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስዷል።


አቶ በረከት ስምዖን ያስገቡትን የስልጣን ጥያቄ ሕወሓቶች እንዳልተቀበሉት ተነገረ; “እለቃለሁ የሚል ከሆነ ሃብቱ መመርመር አለበት” ተብሏል

ምንሊክ ሳልሳዊ

-በውሳኔው የማይስማማ ከሆነ በሱና በቤተሰቡ በወዳጆቹ ስም የተመዘገበው ሃብት እንዲጣራ ተብሏል::
-ሳያገግሙ ስብሰባ እንዲመራ እና ሚዲያ ላይ እንዲቀርብ ታዟል::

የብአዲን/ኢሕአዲግ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ በረከት ስምኦን ያቀረቡት የስልጣን መልቀቂያ ለጊዜው በሚል ውድቅ መደረጉን ሆኖም በቅርቡ መልስ ይሰጥበታል ሲሉ የሕወሓት ባለስልጣናት መመለሳቸውን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::

አብዛኛውን ጊዜ ራሳቸውን ከቤት በማስቀመጥ እና በማዝናናት ያሳልፋሉ የተባሉት አቶ በረከት ስምኦን በልባቸው ላይ በተገጠመላቸው አርቴፊሻል መሳሪያ በጤንነታቸው ላይ ከባድ እክል እንደፈጠረባቸው እና ከወራት በፊት ሳኡድ አረቢያ ታክመው ቢመጡም ሊሻላቸው እንዳልቻለ እንዲሁም ባለፈው ሳምንት በድጋሚ ቢሄዱም ሆስፒታሉ ተስፋ እንዳስቆረጣቸው ሲታወቅ ከሕክምና መልስ ወደ ቢሯቸው የገቡት በጣት የሚቆጠር ቀናት እንደሆነ ታውቋል::

ይህን ሰሞን ስብሰባ መምራት አለብህ በሚዲያ መታየት አለብህ የሚል ግዳጅ ከሕወሓት ባለስልጣናት ወርዶላቸው የተደናበሩት አቶ በረከት ማገገም እንኳን ሳይችሉ በስራ መደራረብ እንዲሞቱ እየተደረገ ነው ሲሉ ከቤተሰባቸው አንዱ የሆኑት ሲናገሩ ተሰምቷል::አቶ በረከት በከፍተኛ ህመም ውስጥ እንዳሉ ሲታወቅ የሕወሓት ባለስልጣኖች የአዜብን ቡድን እንደመቱት ወዲያው በረከትንም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ አሽቀንጥረው ካሳንቺስ አዲስ ቢሮ እንደሰጡት ሲታወቅ መገፋቱ እያንገበገበው በሽታውን እንዳባባሰበት ታውቋል::


ኢሕአዴግ ለምርጫ አልተዘጋጀም!

ይድነቃቸው ከበደ

ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

እንደ መግቢያ፡- በመዝገበ ቃላት አተረጓጎም መሠረት “ዲሞክራሲ ማላት በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት ማለት ሲሆን የመጨረሻውም ሥልጣን በሕዝብ ቁጥጥር ስር ያለ፣በቀጥታ በራሳቸው ወይም እነርሱ በወከሉት ወገን ብቻ በሥራ የሚተረጐምና በነፃ ምርጫ ስርዓት የተመረኮዘ ነው” ይላል፡፡ በአብርሃም ሊንከን አባባል “ዲሞክራሲ ከሕዝብ የወጣ ፣በሕዝብ የተመረጠና ለሕዝብ የሚያገልግል መንግስት ነው፡፡”በማለት የሰጠው ትርጓሜ በአብዛኛው ተቀባይነት ያገኝ ሃሳብ ነው፡ሦስቱ መሠረታዊ የመንግስት ምሶሶዎች ተብለው የሚታወቁት ማለትም ሕግ አውጪ፣ሕግ አስፈጻሚ እና ሕግ ተርጓሚ በሁለት መንገድ ሥራቸውን ያከናውናሉ፡፡እነኚኽም አካሄዶች ቀጥተኛ እና የተወካይ ዲሞክራሲ ተብለው ተለይተው ይታወቃሉ ፡

የፈርዖኖች ድንኳን እየፈረሰ ነው

“ዓረብ ስፕሪንግ” እየተባለ ስለሚነገረው ህዝባዊ አብዮት ብዙ ተብሏል። ያ ህዝባዊ አመፅ ለውጥ አምጥቷል።ማን ይነካኛል ብሎ ዜጎቹን መከራ ሲያበላ የነበረው የቱኒዚያው ቤኒ ዓሊ ዛሬ የተረሳ ግለሰብ ሁኗል። እኔ ከሌለው ይህች አገር ትጠፋለች ሲል የነበረው ጋዳፊ ከተደበቀበት የአይጥ ጉድጓድ ውስጥ ተጎትቶ ወጥቶ እንደ ውሻ ተቀጥቅጦ ሙቷል። ሆስኒ ሙባረክም እንዲሁ ተርስቶ ቀርቷል። የየመንም አምባገነን አገር ጥሎ ሂዷል።በሶሪያም አምባገነኖች ከእንግዲህ ተረጋግተው ህዝባቸው ላይ የሚያላግጡበት ዘመን አብቅቷል።በቱኒዚያዊው ሙሃመድ ቦዛዚ መስዋዕትነት የተጀመረው ህዝባዊ ዓመፅ ብዙ የዓረብ አገራትን አዳርሷል። ይህ ህዝባዊ አመፅ ከዓረቡ ዓለም ባሻገር ወደ ጥቁር ህዝቦች ተሽጋግሯል። ቡርኪና ፋሶዎች ለ27 ዓመት ስልጣኑን ሙጥኝ ብሎ የኖረውን ብሌስ ኮምፓዖሬን ከተቆናጠጠው የስልጣን ወንበር ላይ አባረውታል።ብሌስ ኮምፓዖሬ የገዛ ወገኑን ሠላም እያሳጣ በጎሬቤት አገሮች ዋና አስታራቂ፤ የሠላም ሰው መስሎ ለመታየት ይኳትን ነበር። አሜርካኖች ቁልፍ ወዳጃችን ይሉትም ነበር። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በጎረቤት አገሮች መረጋጋት ዋና ተዋኒያኒ እያለ ያሞጋግሰው ነበር። ብሌስ

Saturday, November 8, 2014

የሰላም ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ ታሰረ

ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማስተባበርና በማቀራረብ እርቅ ለማስፈን እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት የመግባባት፣ አንድነትና ሰላም (ሰላም) ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አቶ ፋንታሁን የታሰረው ‹‹የሰላም ጥሪ›› በሚል ነጭ ሰንደቅ አላማ በማውረብለብና የማህበሩን አላማ የሚገልጹ፣ እንዲሁም ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ ችግር የሚላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር የያዘ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በመበተን ማህበሩን በማስተዋወቅ ላይ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡

በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

መልዕክት ከቃሊቲና ከቂሊንጦ

ነገረ ኢትዮጵያ
የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ የዝግጅት ክፍል አባላት ወደ ቂሊንጦና ቃሊቲ እስር ቤቶች በማቅናት እስረኞችን ጠይቀዋል፡፡ እስረኞቹ ያስተላለፉትን መልዕክት ነገረ ኢትዮጵያ እንደሚከተለው ጠቅለል አድርጋ አቅርባዋለች፡፡‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ አይቀርም›› እስክንድር ነጋበማህበራዊ ድረ-ገጽም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች መልካም ልደት ለተመኛችሁልኝ ሁሉ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ የቡርኪናፋሶው አምባገነን መውደቁን በመስማቴ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ይህ ለእኔ ውድ የልደት ቀን ስጦታየ አድርጌ እቆጥረዋለሁ፡፡ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥም ለውጥ የሚቀር አይደለም፡፡ የእኛ ችግር ከማንም የባሰ ነው፡፡ ቱኒዚያ ላይ የተጀመረው አብዮት ሰሜን አፍሪካ አንቀጥቅጧል፡፡ ኢትዮጵያ ከሰሜን አፍሪካ አገራት ይልቅ ለእነ ቦትስዋና ትቀርባለች፡፡ የቦትስዋና ጉዳይ ሌሎቹንም ማነቃነቁ የማይቀር ነው፡፡ ይህ ለውጡ ቅርብ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ

Friday, November 7, 2014

No journalism in Ethiopia

by Palesa Tshandu

Journalism in Ethiopia is becoming obsolete following the government’s lock-down on press freedom, according to Ethiopian journalists attending the Power Reporting journalism conference. Wits Vuvuzela spoke to some of the Ethiopian delegates who all asked not to be identified for fear of repercussions when they return to their home.

“There is no such thing as journalism in Ethiopia,” said the Ethiopian delegate, drawing on the frustrations experienced by many practising journalists in the country. Ethiopia is one of the most repressive nations in Africa for journalists and is the second worst jailer of journalists, according to the Committee to Protect Journalists (CPJ), after neighbouring Eritrea.

በወያኔ ባለስልጣናት እና በቅርብ ሰዎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤ እየታየ ነው። – ከምንሊክ ሳልሳዊ

- የመከላከያ እና ፖሊስ ሰራዊቱ ላይ አለመተማመኑ እየጨመረ መጥቷል።
- የደህንነት አባላቱ መረጃን በግል ጥቅም በመለወጥ እየሰሩ ነው የሚል ግምገማ ቀርቦባቸው ተንጠዋል።
- የሃገሪቱን ጉዳይ በተመለከተ ለበታች “ተከታይ ” ባለስልጣናት መረጃ መስጠት ቆሟል።
- የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ አይደሉም ።
በኢትዮጵያ ውስጥ መጭው ጊዜ በህዝቡ ዝምታ ተከትሎ በስርአቱ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ይከተላል የሚል መረጃ መሰማት ከጀመረ ጀምሮ በወያኔ ባለስልጣናት እና በቅርብ ሰዎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ መኖሩን ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል።የአስመራ ተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ ሪሞት ኮንትሮል ወያኔ እጅ ነው ስለዚህ የትጥቅ ትግል ወያኔን አያስፈራውም ያሉት ምንጮች የሃገር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ወያኔ ልሙጥ የሚላቸው የተቃዋሚ ፓርቲዎቹ አጋር ዲያስፖራዎች በለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ህዝቡን በማንቃት ረገድ እያደረጉት ያለው ርብርብ ትልቅ ስጋት እንደፈጠረባቸው እንዳስደነገጣቸው ሲታወቅ በድንጋጤ የመጣ ለኢሕአዴግ አንዳንድ ወቅታዊ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ያሉ ባለስልጣናት ከሃገር እንዳይወጡ እና ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ፓስፖርታቸውን ከመነጠቅ ጀምሮ በአይነቁራኛ እንደሚጠበቁ ታውቋል። የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑ

እሥሩ ተጧጡፏል፣ አንድነት ምርጫ እንዳይወዳደር አገዛዙ ይፈልጋል (ግርማ ካሳ)

ዜጎች መታሰራቸው እየቀጠለ ነው። በተለይም የአንድነት ፓርቲ አባላት (በጎንደር፣ በትግራይ፣ በመቱ፣ በአዲስ አበባ ፣ በወላይታ ….) ። ብዙዎች ከፍተኛ ደብደባ እየደረሰባቸው ነው። ሕወሃት ፣ በሕዝብ እንደተጠላ ስላወቀ የአንድነት ፓርቲ እንዲዳከም ወይም ከምርጫው ዉጭ እንዲወጣ እየሰራ ነው። አንድነት ሊያሸንፈው እንደሚችል ስላወቀ።

የድርጅቶች መተባበር አስፈላጊ በመሆኑ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር ተስማምቶ የቅድመ ዉህደት ስምምነት ፈርሞ ነበር። ሁሉም ነገር አልቆ ነበር። ሆኖም ምርጫ ቦርድ ወይንም አገዝዙ፣ ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ዉህደቱን አስቁሞታል። ይኸው እስከአሁን ድረስ በአቶ አበባው ለሚመራው መኢአድ እውቅና አልሰጠም ብሎ መኢአዶችን ምርጫ ቦርድ እያጉላላቸው ነው።

Wednesday, November 5, 2014

አማራ! አማራ! አማራ! ብቸኛዉ የወያኔ ዘፈን

“ሞኝና ወረቀት የያዙትን አይለቁም” የሚለዉ ቆየት ያለ ያለ የአገራችን ተረት ትርጉም ያልገባዉ ሰዉ ካለ የቅኔ አዋቂ መፈለግ ወይም መጽሐፍ ማገላበጥ የለበትም። ማድረግ ያለበት ቀላል ነገር ቢኖር ወያኔንና የወያኔን ስራ ትኩር ብሎ መመልከት ብቻ ነዉ። በመሠረቱ ወረቀት የያዘዉን አለመልቀቁ ወያኔን ጨምሮ ሁላችንም የምንፈልገዉ ነገር ነዉና ወረቀት ሊመሰገን ይገባል። ሞኝ የያዘዉን አለመልቀቁና ከግዑዙ ወረቀት ጋር መነጻጸሩ ግን ሞኝ አማራጭ የሚባል ነገር የማያዉቅና ግዜና ሁኔታ ሲለዋወጡ ያቺኑ በልጅነቱ የያዛትን አቋም ሙጭጭ አድርጎ እንደያዘ እድሜ ልኩን የሚኖር የሀሳብ ደሃ መሆኑን ያመለክታል። ሞኝን ሞኝ እያለን የምንጠራዉም በዚህ ደካማና ግትር አቋሙ የተነሳ ነዉ። ወያኔ ጫካ ዉስጥ እያለ ለአስራ ሰባት አመት፤ ከጫካዉ ወጥቶ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ደግሞ ለሃያ ሦስት አመታት የያዛቸዉን አቋሞችና የወሰዳቸዉን እርምጃዎች ረጋ ብሎ የተመለከተ ሰዉ ወያኔ፤ ወረቀትና ሞኝ ያላቸዉን የቅርብ ግኑኝነት በቀላሉ መመልከት ይችላል። ሦስቱም አንድ ነገር ከያዙ ሌላ የመያዝ ፍላጎትም ችሎታም የላቸዉም። አዎ! በእርግጥም ሞኝ በሞኝነቱ፤ ወረቀት የተፈጥሮ ጠባዩ በመሆኑ ወያኔ ደግሞ የወረቀትም የሞኝም ጠባይ ስላለዉ ሦስቱም የያዙትን አይለቁም።

Tuesday, November 4, 2014

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የመጀመሪያ ዙር ህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ

• የ24 ሰዓት (የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቷል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡

‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ›› እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡

‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል›› ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-

1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡

ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡

በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡


በሰሜን ጎንደር ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘጉ

ኢሳት ዜና :-የቅማንት ተወላጆች ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ በተጠራ የስራ ማቆም አድማ በዞኑ የሚገኙ ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ካለፈው አርብ ጀምሮ የተዘጉ ሲሆን፣ መንግስት እስከ መስከረም 30 መልስ የማይሰጥ ከሆነ፣ ተቃውሞው ግብር ባለመክፈል እንደሚቀጥል አስተባባሪዎቹ ለኢሳት ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም በርካታ አስተባባሪዎች ተይዘው የታሰሩ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው እስከ መስከረም መጨረሻ መልስ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

እስካሁን ከ130 ሺ ያላናሱ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው የቀሩ ሲሆን፣ ሌሎች ትምህርት ቤቶችና የመንግስት መስሪያ ቤቶችም  በአድማው ይቀጥላሉተብሎ ይጠበቃል። በተዘጉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚውለበለቡ ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ ተደርጓል። ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ የተደረገበት ምክንያት የህዝቦችን መብቶች የሚወክሉ አይደሉም በሚል ነው።


የወያኔ ግፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

ዘረኛዉ ወያኔና ባለሟሎቹ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላና በሸኮ መዠንገር አካባቢ የሚያካሄዱትን የማንአለብኝነት የመሬት ዝርፍያና ዜጎችን እርስ በርስ በማጋጨት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያደርጉት አራዊታዊ ሩጫ የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝብ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችል እልቂት እየተፈጸመበት ነዉ። የመዠንገር ህዝብ የሞትና የህይወትን ያክል የማይወጣዉ ምርጫ ስለቀረበለት ተወልዶ ያደገበትን የአባቶቹንና የአያቶቹን አካባቢ ለቅቆ በመዉጣት እራሱን ለመከላከል ባደረገዉ እንቅስቃሴ የብዙ ንጹሃን ዜጎችና ቁጥራቸዉ ቀላል የማይባል ምስኪን ወታደሮችም ህይወት ማለፉ በይፋ እየተሰማ ነዉ። ይህንን ተከትሎ ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች በአካባቢዉ ብዙ ዘመን በቆዩ ብሄሰቦች መካክል ሆን ብለዉ ግጭት እንዲነሳ እያደረጉ በህዝብ መካክል ግጭትትና ዕልቂት የተነሳ በማስመሰል በአካባቢዉ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።

የአንድነት ፓርቲ አዲስ አመራር መግለ ጫሰጠ

‹‹‹‹ኢንጂነር ግዛቸው በአንድነት ቤት እንደጀግና መታየት አለባቸው››
‹‹ከመኢአድ እና ሰማያዊ ፓርቲዎች ጋር ተዋህደን መስራት አለብን››
አቶ በላይ ፍቃዱ /የአንድነት ሊቀመንበር/
—————-‹የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁ አሸባሪ ነው››
‹‹ዘንድሮም አዋጁ ይሰረዝ ብለን መጠየቃችንን እንቀጥላለን››
አቶ ግርማ ሰይፉ /የፓርላማ ተወካይ የአንድነት ም/ፕሬዚዳንት/
——————————–
ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጥቅምት 20 ቀን 2007 ዓ.ም፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ‹‹በፖለቲካ እስረኞች ላይ እየተፈጸመ ያለው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል!›› በሚል ርዕስ በጽ/ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር፡፡ መግለጫውንም የሰጡት የወቅቱ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ በላይ ፍቃዱ፣ ም/ ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ሰይፉ እና የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ የማነ ብርሃን ናቸው፡፡

ጦማርያንና ጋዜጠኞቹ ለሳምንት ቀጠሮ ተሰጠባቸው



ዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለ10ኛ ጊዜ ችሎት የቀረቡት የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ሶስቱ ጋዜጠኞች ለሳምንት (ህዳር 3/2007 ዓ.ም) ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡

ፍርድ ቤቱ ዛሬ በጦማርያንና በጋዜጠኞቹ ቀደም ሲል የቀረበውን የክስ ማሻሻያ አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ምርመራው አላለቀም በሚል ምክንያት አጭር ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በዛሬው ችሎት ላይ ከተሰየሙት ዳኞች መካከል ሁለቱ አዲሶች በመሆናቸው ምክንያት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ጠበቃ አምሃ መኮንን ገልጸዋል፡፡ ዳኞች ብቻ ሳይሆን ችሎት ክፍሉም በመቀየሩ ክፍሉ ጠባብ ነው በሚል፣ የተከሳሽ ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች ችሎት መግባት አለመቻላቸውም ታውቋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በነገው ዕለት ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተከሳሾች ዋስትና ጉዳይ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን አቶ አምሃ ጨምረው አስረድተዋል፡፡

በተከሳሾች በኩል ደግሞ፣ ሁለቱ ሴት ተከሳሾች (ኤዶም ካሳዬ እና ማህሌት ፋንታሁን) በቃሊቲ ማረሚያ ላይ ያነሱትን የመብት ጥሰት አቤቱታ በተመለከተ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር በቀጣይ ቀጠሮ ድጋሚ ቀርቦ እንዲያስረዳ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ሁለቱ ተከሳሾች በቀን ለ10 ደቂቃ ብቻ ስማቸው ቀድሞ በተመዘገቡ ሰዎች ብቻ እየተጎበኙ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡


Monday, November 3, 2014

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር “የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ እራስህን ከወያኔ አሽከርነት(መጠቀሚያነት) ልታርቅ ይገባል” አለ

በህዝብ ላይ የሚደርሰው ጭቆናና እርዛት እስከመቼ?

ከኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ የተሠጠ መግለጫ

የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት ዘወትር ስልጣናቸውን ለማራዘም ካላቸው ነቢራዊ ፍላጎት የተነሳ በህዝብ ላይ ግድያ እና እስር ከመፈፀም አልፈው ሐገራችን ኢትዮጵያን ከማትወጣበት ማጥ ውስጥ ለመክተት ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡ በቅርቡ እንኳን በአሶሳ ከተማ ንፁሀን የትግራይ ወጣቶች ማንነታቸው እስካሁን ባልታወቁ ታጣቂዎች ተገድለዋል ይኸውም መንግስትእየተከተለው ብልሹ የዘውግ አስተዳደር ዋጋ እያስከፈለ መሆኑ እየታየ ነው በሌላ በኩል ይህ ግድያ መንግስት እራሱ የትግራይ ህዝብን ከጎኑ ለማሠለፍ በማሠብ እንደገደላቸው ግምታቸውን አስቀምጠዋል እንደምክንያት የጠቀሱት ምርጫ 97ን ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ መንግስት ተቃውሞውን ለማባባስ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ከቀድሞዋ የትምህርት ሚኒስቴር ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ግቢ ወደውጭ ቦንብ በመወርወር 6 ፖሊሶችን በመግደል ፖሊሶችን ለማነሳሳት እና ህዝቡን ለማሳሳት ቢሞክርም በመጨረሻ ጉዳዩን የአሜሪካ ኤምባሲ ይፋ ሲያወጣው የመንግስት ሴራ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአሶሳው፣ የአምቦው፣ የጎንደሩ እና የወለጋው ግድያም ከዚህ የተለየ አይሆንም፡፡የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴም ለመንግስት እና ለህዝቡ የሚከተለውን መልዕክት ማስተላለፍ ይወዳል፡፡የመምህራኑ መልዕክት ለመንግስት

ማንኛውም መንግስት ህዝቡን ማዳመጥ ይኖርበታል መንግሥት ሕዝብን የሚያዳምጠው በሕገ መንግሥቱ ስለሚገደድ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ የሕዝብ ወገን ነኝ የሚል ሥልጣን የያዘ ፓርቲና መንግሥት፣ ሕዝብን ምረጠኝ የሚል ፓርቲና መንግሥት፣ የሕዝብ ከበሬታና አመኔታ ሊያገኝና ዓላማውን በተግባር ላይ ሊያውል የሚችለው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ሥልጣን ላይ የሚቆየው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ሕዝብን ማዳመጥ ለራስ ተብሎም መደረግ ያለበት ነው፡፡ የማያዳምጥ መንግሥት የማይደመጥ መንግሥት ይሆናልና፡፡

የመምህራኑ መልዕክት ለኢትዮጵያ ህዝብ

የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሐይማኖትህ፣ ለሐገርህ እና ለቀጣይ ትውልድ አስበህ እራስህን ከወያኔ አሽከርነት(መጠቀሚያነት) ልታርቅ ይገባል፡፡ መንግስት ህዝቡ ፊቱን ካዞረበት እና ካልተገዛለት ማንንም ሊገዛ እንደማይችል የቅርባችን የጋዳፊ አገዛዝ ምስክር ነው፡፡ ስለሆነም ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ከኢህአዴግ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት መመስረት የለብንም ከዚያም አልፎ ከወያኔ ጋር ተለጥፈው ህዝባቸውን የሚያስወጉ ጎረቤቶቻችንን ጭምር ከማንኛውም ማህበራዊ ህይወት በማግለል ትምህርት ልንሠጣቸው ይገባል፡፡ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!!!!!!!!!!
የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

የመኢአድ አባላት እየታደኑ በመታሰር ላይ ናቸው!!

ኢሳት ዜና :-መጪውን ምርጫ ተንተርሶ በሚመስል መልኩ በምስራቅና ምእራብ ጎጃም አመራሮችና አባላት መታሰራቸውን ድርጅቱ አስታወቀ

በተመሳሳይ ዜና ደግሞ የወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ እና የዞኑ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወኖ በዳሳ ጥቅምት 22 ቀን 2007 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ እያሉ በከተማው የፖሊስ አዛዥ መመሪያ በመንግስት ሀይሎች “እኛ ሀገር እየመራን እናንተ ትቃወሙናላችሁ እናንተን እናጠፋቹሃለን” በማለት ከባድ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ለፍኖተ ነፃነት አስታውቀዋል፡፡ አመራሮቹ በድብደባው ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ታውቋል፡፡

አቶ ወኖ በዳሳ ራሳቸውን ስተው በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ቢወሰዱም እስካሁን እንዳላገገሙ እና የዞኑ የአንድነት ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ ህክምና አግኝተው ከወጡ በኋላም በከተማው ደህንነቶች ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝም ታውቋል፡፡


ህወሃትና የጦር አበጋዞቹ እሴቶች

ህወሃት የትግሬ ተወካይ ብቻ ሳልሆን ለትግራይ ህዝብ የሚያመልከውን አምላክም ጭምር የምመርጥለት እኔ ነኝ በሚል እብሪት ውስጥ ይገኛል። በዚህ እብሪቱም እየተመራ የምታመልኩትን ልመርጥላችሁ ብሎ አጠቃላይ ሙስሊሙንም ክርስትያኑንም እያመሰው እንደሆነ እያየን ነው። እኔን የማይቀበል እጣ ፈንታው ከመታመስ በላይ የሆነ ወዮታ ነው የሚል ያልተፃፈ አዋጅም አለው። ህወሃት በትግራይ ትከሻ ላይ ተፈናጦ፤ ትግራይን ምርጫ አሳጥቶ እኔን እምኑ መንገዳችሁም ህይወታችሁም እኔ ብቻ ነኝ ብሎ ራሱን የትግራይ ጣዖት አድርጎ ሹሟል። ይሄን ጣዖት አንቀበልም፤ እኛ የራሳችን ሂሊና ያለን እንደ ሰው ማሰብ የምንችል ነን ያሉ ብዙ የኢትዮጵያ ልጆች ባልታወጀው አዋጅ መሠረት አብዮታዊ ፀሎት እየተፀለየላቸው አፈር ለብሰው ቀርተዋል።የህወሃት የእብሪቱ መጀመሪያ “እኔ ያልኩት ካልሆነ ሁሉም ገደል ይግባ” ማለቱ ነው። የትግራይ ተወካይ እኔ ብቻ ነኝ ሌላው ሁሉ የትግራይ ህዝብ ጠላት ነው የሚል እምነቱ የድርጅቱን ሥር የሰደደ መሠሪነትና እብሪት የሚያሳይ ነው።

በተለያዩ ክልሎች ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቁ በሚል ከትምህርታቸው እየተፈናቀሉ ነው



አቡ ዳውድ ኡስማን

በቤኒሻንጉል ጉምዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአሶሳ ከተማ በሚገኙ የ1ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው መማር እንዳይችሉ እየተደረጉ መሆናቸውን ምንጮች አስታወቁ፡፡

በአሶሳ ከተማ በሚገኙ ት/ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው በትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት እንደማይችሉ የት/ቤቱ አስተዳደሮች እየከለከሏቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

በቤኒሻንጉል ጉምዝ በአሶሳ ከተማ በሚገኝ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት 35 የሚሆኑ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን ካላወለቃችሁ መማር አትችሉም በመባላቸው ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀላቸውን ምንጮች አስታውቀዋል፡:

የትምህርት ቤቱን ርዕሰ መምህርን በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር በአሶሳ ከተማ በስፋት በህዝብ ዘንድ የሚታወቀው ሰለፊያ ተብሎ የሚጠራው መስጂድ ኮሚቴዎች ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ርዕሰ መምህሩ “እናንተ አሸባሪዎች እስካሁን አላቹ እንዴ” በማለት የተሳለቀባቸው ሲሆን ሴት ተማሪዎቹ ሂጃባቸውን እስካላወለቁ ድረስ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንደማይቀጥሉ ምላሽ እንደሰጣቸው ታውቋል፡፡

በተመሳሳይም በትግራይ ክልል በሽሬ እንደስላላሴ ከተማ በሚገኙ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው መማር እየተከለከሉ መሆናቸውን ምንጮች ዘግበዋል፡፡

በበሽሬ እንደስላሴ ከተማ የሚኖሩ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቃችሁ ተማሩ በመባላቸው ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው በቤት ውስጥ ተቀምጠው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

የትምህርት ቤት አስተዳደሮች የተማሪዎችን ወላጆች በመሰብሰብ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገሩ ሲሆን ወላጆችን እና ተማሪዎችን ሲያስፈራሩ እንደነበር ተዘግቧል፡፡

በመላው ሃገሪቱ የሙስሊሞች ዋነኛ የእምነታቸው መገለጫ የሆነውን ሂጃብ እንዲያወልቁ ለማድረግ በመንግስት በኩል ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የፌደራል ጉዳዬች ሚኒስተር ዶ/ር ሽፈራው በኢስላም ላይ ባላቸው የግል ጥላቻ በመነሳት ከመሰሎቻቸው ጋር በመቀናጀት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ለማፈናቀል በክፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ የሚታወቅ ሲሆን በመላው ሃገሪቱም በሴኩላሪዝም ሽፋን ሙስሊሞች ትምህርታቸውን አልያም ሃይማኖታቸውን እንዲመርጡ በማስገደድ ሙስሊሙን ከትምህርት ገበታ ለማራቅ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
ሂጃብ የሙስሊም ሴት ህልውናዋ እንጂ ለድርድር የሚቀርብ የፖለቲካ አጀንዳ አይደለም።

Sunday, November 2, 2014

በአፋር ክልል ዱብቲ ከተማ አንድ ወጣት ባልታወቁ ኃይሎች ተገድሎ ተገኘ

በአፋር ክልል በዱብቲ ከተማ አንድ ወጣት ተገድሎ ተገኘ። ከሁለት ሳምንታት በፊት በዱብቲ ከተማ ሲዒድ አባተ የተባለ ወጣት ባልታወቁ ኃይሎች በከፉኛ ተደብድቦና ተገድሎ መገኘቱን ከቦታው ዘግይቶ ዛሬ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ግድያውን የፈፀሙትን አካላት እሰካሁን አልተያዙም።

ሲዒድ አባተ አፋር ባይሆንም በዱብቲ ከተማ ተወልዶ ያደገና በዱብቲ ወጣቶች ዘንድ የሚወደድ ልጅ እንደነበረ አንዳንድ የዱብቲ ነዋሪዎች የሆኑ አብሮ አደጎቹ ያስረዳሉ። የዱብቲ ከተማ ፖሊስም የዚህ ወጣት ህይወት ማትረፍ እንዳልቻሉና ወንጀለኞችን ፈልጎ ለህግ ለማቅረብ በመጠነኛ መልኩም የጣሩ ቢሆንም እሰካሁን አልተሳካም። አሁንም በከተማዋ የሚኖሩ ነዋሪዎች ለህይወታቸው እንደሚሰጉ ይናገራሉ።

በዚህ ጉዳይ ላይ የዱብቲ ከተማ የፖሊስ ኮሚሽን ጽ/ቤት አስተያየት ለማካተት ያደረኩት ሙከራ አልተሳካም ።

ሲዒድ ላይ በተፈፀመው ግዲያ በጣም ማዘናችንን እየገለፅን ለወዳጅ ቤተሰቦቹ መፅናናትን እንመኛለን ።


የወላይታ ዞን የአንድነት አመራሮች በመንግስት ሀይሎች ከባድ ድብደባ ተፈፀመባቸው

(ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ) የወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ እና የዞኑ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወኖ በዳሳ ትላንት ጥቅምት 22 ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ በ 8 ሰዓት ከስብሰባ ወጥተው በወላይታ ሶዶ ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ እያሉ በከተማው የፖሊስ አዛዥ መመሪያ በመንግስት ሀይሎች “እኛ ሀገር እመራን እናንተ ትቃወሙናላችሁ እናንተን እናጠፋቹሀለን” በማለት ከባድ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ለፍኖተ ነፃነት አስታወቀ፡፡ አመራሮቹ በድብደባው ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ታውቋል፡፡

በድብደባው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው አቶ ወኖ በዳሳ ራሳቸውን ስተው በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ቢወሰዱም እስካሁን እንዳላገገሙ እና የዞኑ የአንድነት ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ ህክምና አግኝተው ከወጡ በኋላም በከተማው ደህንነቶች ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝም ታውቋል፡፡
የወላይታ ዞን የአንድነት አመራሮች ላይ ድብደባ እንዲደርስ መመሪያ የሰጡት የከተማው የፖሊስ አዛዥ በአቶ ወኖ ላይ በደረሰው ከባድ ጉዳት ተደናግጠው በአምቡላንስ እንዲወሰዱ ካደረጉ በኋላ የዞኑ የአንድነት ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ “በአንድም ሚዲያ ስለሁኔታው እንዳይናገሩ” በሚል ክትትል እያስደረጉባቸው ያገኛል፡፡

Britain has suspended aid programme to support Ethiopia’s police force amid mounting allegations of torture, rape and murder by the regime

Britain has given £1 billion in aid, including around £70 million for “governance and security” projects, to the country over three years Photo: SAUL LOEB/AFP

Britain has suspended most of a £27 million aid programme to support Ethiopia’s police force, The Telegraph has learnt, amid mounting allegations of torture, rape and murder by the regime.

Ministers pulled the plug on a scheme intended to improve criminal investigations, help Ethiopian police “interact with communities on local safety” and help women access the justice system.

The cancellation coincides with an Amnesty International report that documents how the Ethiopian security forces have conducted a campaign of torture, mutilation, rape and murder in order to suppress political opposition.

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወደ ዝዋይ እስር ቤት በለሊት ተወሰደ

(ኢ.ኤም.ኤፍ) እውቁ ጋዘጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በጻፋቸው ጽሁፎች ምክንያት በፍርድ ቤት 3 አመት ተፈርዶበት በቅሊንጦ እስር ቤት እንዲቆይ ተደርጎ ነበር። ዛሬ የደረሰን ዘገባ እንደሚያመለክተው ደግሞ፤ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከቅሊንጦ ወደ ዝዋይ መወሰዱን ለማወቅ ተችሏል። ይህም በህገ መንግስቱ ላይ “አንድ እስረኛ ለቤተሰቡ ጥየቃ አመቺ እንዲሆን፤ የቅርብ ቤተሰብ ባለበት ስፍራ መታሰር አለበት” የሚለውን የእስረኛ ሰብአዊ መብት አያያዝ የጣሰ ነው። ለማንኛውን ዛሬ ከተመስገን ወንድም የደረሰውን ዘገባ ከዚህ በታች አቀናብረን አቅርበነዋል።

እንደለመድነው ዛሬም እኔና ሰውዓለም ታዬ የተመስገንን ስንቅ ይዘን በጠዋት ነው ቂሊንጦ እስር ቤት የደረስነው።  በመታበይ ሰማይ የደረሱት የእስር ቤቱ አስተዳደሮች በንቀት “ማን ጋር ናቹህ?” አሉን።

“ተመሰገን ደሳለኝ ጋር”

“ማን ትባላለቹም?” ነገርናቸው።

“ዞኑ ስንት ነው?”

“ዞን አንድ” አልናቸው። መታወቂያ ጠይቁንና፤ መታወቂያ ሰጠናቸው። አገለብጠው መዘገብ ላይ ከፃፉ በኋላ ወረወሩል። መታወቂያችንን አንስተን እነሱን አልፈን ገባን፡፡

ብዙዎቹ ወፌ ላላ የሚሏት ግርፋት በዚህ መንግስት መገረፋቸውን ሲነግሩንና ሲፅፉልን አንብበናል። ቂሊንጦ ደግሞ የታሰሪ ቤተሰብን በሚሸማቀቅ ሁኔታ ወፌ ላላ እሚባል ፍተሸ አላቸው። ወፌ ላላን ተፈትሽን አለፍን። ተመሰገንን ልናስጠራ ስንል እስረኝ አንደሚጠራልን ተነገረን። ስንዞር የሙስሊም መፍትሄ አፈላለጊ ኮሜቴዎች አንዱ የሆነው አቡበከር ነው። ሲያየን በፊቱ ላይ ሃዘን አየንበት። ሌላ ግዜ በፈገግታ ስላምታ የሚያስቀድመው አቡበከር በመከፋት “ተሜን ዛሬ ለሌት ዝዋይ ወሰዱት።” አለን። ትላንት ተመስገን ስንጠይቀው ስለዚህ ጉዳይ ምንም እሚያውቀው ነገር የለም፤ አልነገሩትም። ለሱ እንኳን ባይነግሩት እኛ ቤተሰብ አንደሆን እያወቁ ሊነግሩን አልፈለጉም። የያዝኩትን ስንቅ ሳየው የእናቴ ንግግር ትዝ አለኝ። “በሉ ቶሎ ሂዱ ምግቡ ሳይቀዘቅዝ አድርሱለት” ነበር ያለችው። …. እናቴ ምግቡም ይቀዘቅዛል፤ ልጅሽም የለም …. አቡበከርን አመስግነን ወጣን፡፡

አሳሬዎቹ ተሜን በተለያየ ጊዜ ሀገሩን ለቆ እንዲሰደድ ያላደረጉት ነገር የለም ከሀገር ሀገር ማዘዋወሩ ቢያቅጣቸው ካንደኛው የግዞት እስር ቤታቸው ወደሌላኛው የግዞት እስር ቤታቸው ማዘዋወሩ ላይ ግን ታስክቶላቸዋል!! ተሜን ሲወሰዱት አላየሁም፤ ግን ተሜን አውቀዋለሁ ለሀገሩ ሲል ጉዞው ቀራኒዬ ድረስ አንደሆነ፡፡ ወደ መኪናው ሲወሰዱት እስረኞቹን እያበረታታ ሲሰናበታቸው ….ፖሊሶቹን አንድ ቀን ከህዝብ ጎን እንደሚሆኑ እያሰበ… ሊነጋ ሲል እምትወጣውን ፀሐይ በተስፋ እያየ በፈገግታ ወደ ዝዋይ እንደሄደ ሳሰበው ደሰ አለኝ፡፡ በአይምሯዬ  ወደ ዝዋይ አቅጣጫ እየተመለከትኩ እንዲህ አልኩ።

ተመሰገን ደሳለኝ….

ከሀገር ወጣ ቢሉት፣ አልወጣም እዳለ

ከኛ ጎንን ሁን ሲሉት፣ ከህዝቡ እንደሆነ

ባላማው እንደፀና

እነደኮራ ሄደ፣ አንደተጀነነ!


Saturday, November 1, 2014

በልብ በሽታ የሚሰቃዩት አቶ በረከት ስሞኦን ለዳግም ህክምና ሳውዲ አረቢያ ሾልከው ገቡ

ኢትዮጵያን ሃገሬ ጅድ በዋዲ ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው

በልብ በሽታ የሚሰቃዩት አቶ በረከት ስሞን ህመሙ ጠንቶባቸው ከሁለት ወር በፊት በሼክ አላሙዲን የግል አውሮፕልና ተጭነው በድበቅ ለህክመና ሳውዲ አረቢያ መግባታቸው ይታወሳል። በወቅቱ ሳውዲ አረቢያ ጅዳ የሚገኝ አንድ «ቡግሻን» hospital እየተባለ የሚጠራ ሪፈራል ሆስፒታል የልብ ቧንቧ ማስፋት ህክምና ቢደረግላቸውም የባለስልጣኑ የጤነነት ሁኔታ የሚጠበቀውን ያህል ለወጥ ባለማሳየቱ ለዳገም ህክምና ቀጠሮ ተሰቷቸው ከሳምታት ቆይታ በሃላ ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን መዘገባችን ይታወሳል ።

ይህ በዚህ እንዳለ ዛሬም የአቶ በረከት ጤንነት መልካም ሁኔታ ላይ እንዳልሆነ ምንጮች የሆስፒታሉን የምርመራ ውጤት አብነት ጠቅሰው ይናገራሉ ። አቶ በረከት በጤነታቸው መታወክ ፍጹም መረጋጋት እንደማይታይባቸው የሚገልጹት እንዚህ ውስጥ አዋቂዎች ቀደም ሲል ባለስልጣኑ ህክምና ላይ በነበሩበት ወቅት ወደ ሳውዲ አረቢያ በሚስጠር ለህክምና መግባታቸውን ተከትሎ በተለያዩ ድህረገጾች ዜናው በስፍት መናፈሱ በውስጣቸው በተፈጠረው አለመረጋጋት በልባቸው ምት አለመስተካከል በወቅቱ በቂ ህክማና መውሰድ እናዳልቻሉ ታውቋል። የአቶ በረከት የጤነንት ሁኒታ ዛሬም አስተማማኝ እንዳልሆነ የሚያውሱ እንዚህ የአይን እማኞች ከእለት ተዕለት የባለስልጣኑ የአካል መጠን በማይጠበቅ ሁኔታ መቀነስ እና የፊታቸው ገጽታ መለዋወጥ በውስጣቸው መልካም ነገር እንደማይታይ ያሳብቃል ብለዋል።

የአቶ በረከት ስሞኦን ህይወት ለመታደግ የአቅማቸውን ያህል ጠረት እያደረጉ የሚገኙ «ቡግሻን» hospital የሳውዲ አረቢያ ሆስፒታል ዶክተሮች ሰለበሽታው አደገኝነት ግንዘቤ በማስጨበጥ አቶ በረከት ከተለያዩ መጠጦች እና አይምሮ አደዛዥ እጾች መራቅ እንዳለባቸው እና የጤነንታቸው ሁኔታ አስተማማኝ ሁኔታ ከሲደርስ እረፍት መስውሰድ እንደሚገባቸው ሙያዊ ምክሮቻቸውን ለገሰዋቸዋል። ይህ በዚህ እንዳለ አቶ በረከት ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲያቀኑ የህክምና ውጪያቸውን እየሸፈኑ ከሚገኙት ሼክ አላሙዲን ባሻገር ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ባለስልጣናት ሚስጠር መሆኑ አያሌ ወገኖችን በስፋት እያነጋገር ነው ። ከሁለት ወር በፊት አቶ በረከት እኩለ ለሊት ከቦሌ አይሮፕላን ማረፊያ ወደ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕልና በድብቅ ለህክማን መግባታቸው ለኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወሬው የደረሰው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዘ-ሃበሻ እና ጎልጉል ድህረገጾች በተለቅቁ መረጃዎች መሆኑን የሚናገሩ ምንጩች ለሁለተኛ ግዜ ዳግም ህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲመለሱ በሼክ አልሙዲን በኩል በክበር «በፕሮቶኮል» ሊገቡ እንደሚቸል በወቅቱ ከጅዳ ቆንሳል ጽ/ቤት የወጡ መርጃዎች ቢያረጋግጡም የአቶ በረከት ስሞኦን እንደ ተለመደ በድብቅ ወደ ሳውዲ አረቢያ መግባት ባለስለስልጣኑ በውስጥም በውጨም ጥሩ ወዳጅ እንደሌላቸው የሚነገረውን ሃቅ ያጠናክረዋል ብለዋል ።
አቶ በረከት ትላንት በተደረገላቸው ምርመራ የቅርብ ክትትል እንደሚያሻቸው የሚገልጹ የሆስፒታል መረጃዎች ባለስልጣኑ የተሰጣቸውን ምክር እና የተለያዩ መደሃኒቶቻቸውን ይዘው ከሆስፒታሉ ውጭ ወደ ሚገኘው ምስጢራዊ ማረፊያቸው ማቃናታቸው ተገልጾል፡ ይህ በዚህ እንዳለ አሁን ዘግይቶ በደረሰን ዜና መስረት አቶ በረከት ስሞኦን ዛሬ ማምሻውን ለአስቸኳይ ጉዳይ ህክምናቸውን አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ምስጢራዊ መረጃዎቻችን አክለው አረጋግጠዋል ።


ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሕዝብ እንደማይመርጠው አውቋል – ግርማ ካሳ

ኦሮሞ ነን የሚሉ ኦነግ እየተባሉ በአሥር ሺሆች ታሰሩ። አማርኛ ተናጋሪውን፣ ጉራጌዉን፣ ጋሞዉን ፣ ወላያታውን ….ግንቦት ሰባት ናችሁ እያሉ ማጎር ቀጠሉ። የቀራቸው ትግሬው ነበር። በትግራይ የተነሳዉን ጠንካራ የዲሞክራሲና የለዉጥ ጥያቄ እየጨመረባቸው ሲመጣ፣ “ደሚት ናችሁ” በማለት፣ ይኸው የግፍ ዱላቸውን የትግራይ ተወላጆች ላይ ማሳረፍ ጀመረዋል።

ዛሬ አራት ወጣት ፖለቲከኞች፣ ሃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ ፣ ዳንኤል ሺበሺና አብርሃ ደስታ ሽብርተኞች ተብለው በኦፊሴል ክስ ተመስርቶባቸዋል። አምስት በመቶ ሊፈቱ ይችላሉ የሚል ግምት ነበረኝ። እንኳን ሊፈቱ ጭራሽ ሌሎች ስድስት ኢትዮጵያዉያን ተጨምረዋል። የአ/አ ዩኒቨርስቲ ማስትሬት ተማሪ የሆነው ወጣት ዘላለም ወርቅአገኘሁ፣ ዮናታን ወልዴ ፣ አብርሃም ሰለሞን ፣ ሰለሞን ግርማ ፣ ባህሩ ደጉና ተስፋዬ ተፈሪ ይባላሉ።