Monday, March 27, 2017

Ethiopia: Survivors of landfill disaster get eviction notice but have nowhere to go

ESAT News (March 27, 2017)
Survivors of the landfill landslide a fortnight ago that killed over 100 people say they have received eviction notice from authorities but have nowhere to go.
A survivor who lost seven of his family members told ESAT that 325 households have just been told to leave without any substitute of dwelling and compensation.
Asres Ewnetu, speaking on the phone from Addis Ababa, said although they have received emergency help from residents of

የዋልድባን ገዳም መፍረስ የተቃወሙት መነኩሴ በመንግስት ሃይሎች ታፍነው መወሰዳቸው ተነገረ


ኢሳት (መጋቢት 18 ፥ 2009)
በልማት ሰበብ የዋልድባ ገዳም አይፈርስ በሚል ሲቃወሙና ድርጊቱን በመገናኛ ብዙሃን ያጋለጡት የዋልድባው መነኩሴ አባ ገብረየሱስ በመንግስት ሃይሎች ታፍነው መወሰዳቸው ተነገረ።
የዋልድባው መነኩሴ የመንግስት ስራ በማጋለጣቸው ለረጅም አመታት ከኖሩበት ገዳም እንዲወጡ ተደርጉ ከአምስት አመታት በላይ መቆሚያና መቀመጫ አጥተው ከገዳም ገዳም ሲዞሩ ቆየተዋል
አሁን ደግሞ ባለፈው ጥር 2009 አም ሱባዔ ከያዙበት ጎንደር ከሚገኝ አንድ ገዳም በመንግስት ሃይሎች ታድነው መወሰዳቸው ታውቋል።
አባ ገብረየሱስ በመንግስት ታድነው ይወሰዱ እንጂ አሁንም ያሉበትን ቦታ ለማወቅት የተደረገው ጥረት እንዳልተሳካ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች አንድነት አስታውቋል። ለአፈና የዳረጋቸው ደግሞ የዋልድባ ገዳም ለልማት በሚል ሽፋን መፍረስ የለበትም በማለታቸው እንደሆነ ተገልጿል።

በምስራቅ አፍሪካ የተከሰተው የድርቅ አደጋ ወደ 700ሺ ህጻናትን ህይወት ሊያሳጣ እንደሚችል ተገለጸ


ኢሳት (መጋቢት 18 ፥ 2009)
ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶስት የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት እየተባባሰ ባለው የድርቅ አደጋ ወደ 700ሺ የሚጠጉ ህጻናት ህይወታቸውን ሊያጡ እንደሚችል ወርልድ ቪዥን የተሰኘ የእርዳታ ድርጅት ሰኞ አሳሰበ።
በደቡብ ሱዳንና ሶማሊያ የድርቁ አደጋ ወደ ረሃብ በመለወጡ ምክንያት ሰዎች በመሞት ላይ መሆናቸውን የገለጸው የሰብዓዊ ተቋሙ በኢትዮጵያና ኬንያ ድርቁ እየከፋ መምጣቱን በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል ድርቁ እየከፋ መምጣቱንና የእርዳታ አቅርቦት በበቂ ሁኔታ አለመኖሩን ችግሩን እንዳባባሰው ባለፈው ሳምንት መግለጹ ይታወሳል።

Thursday, March 23, 2017

Ethiopia: Political prisoner exposes horrific torture in prison


ESAT News (March 23, 2017)

A former political prisoner says TPLF investigators inflict unimaginable physical and psychological torture on prisoners including but not limited to damaging their reproductive organs and making them sterile for life.

In an interview with the VOA Amharic service, Habtamu Ayalew, former spokesperson for the opposition Andinet Party said not only he had endured physical torture, the psychological scar is still enduring even worse.

Tuesday, March 21, 2017

በኢትዮጵያ የተከሰተው የድርቅ አደጋ አለም አቀፍ ድጋፍ ባለመገኘቱ እየተባባሰ መምጣቱ ተነገረ

ኢሳት (መጋቢት 12: 2009)

በኢትዮጵያ ተከስቶ ላለው የድርቅ አደጋ የሚያስፈልገው አለም አቀፍ ድጋፍ እየተገኘ ባለመሆኑ ድርቁ እያደረሰ ያለው አደጋ እየተባባሰና ስጋት እየሆነ መምጣቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገለጸ።
ይኸው የድርቅ አደጋ በተለይ በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል በርካታ ሰዎች በከፋ የምግብ እጥረት የአካልና የጤና ችግር እንዲደርስባቸው ያደረገ ሲሆን፣ ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች የሆነ ህጻናት ወደ ማገገሚያ ማዕከል እየገቡ መሆኑን ድርጅቱ በድርቁ ዙሪያ በሚያወጣው ሳምንታዊ ሪፖርት አመልክቷል።
የኢትዮጵያ መንግስትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወደ ስድስት ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ለአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ዕርዳታ ያጋለጠውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ እንደሚያስፈልግ ከወራት በፊት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

በቴኔሲ ናሽቪል ከተማ አንድ ኢትዮጵያዊ ባለሆቴልን የገደለ ተጠርጣሪ ለመያዝ ፍለጋው ተጠናክሮ ቀጥሏል

 ኢሳት (መጋቢት 12: 2009)
የአሜሪካ ፖሊሶች በሳምንቱ መገባደጃ ዕሁድ በዚህ በአሜሪካ የቴኔሲ ግዛት ናሽቪል ከተማ ኢትዮጵያዊ ባለሆቴሉን የገደለ ተጠርጣሪን ለመያዝ ለሶስተኛ ቀን ፍለጋ አጠናክረው መቀጠላቸውን ገለጡ። የ41 አመቱ ኢትዮጵያዊ አቶ ግጠም ደምሴ  አይቤክስ የተባለውን የምግብ ቤቱን ቅዳሜ ምሽት ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ ድርጅቱን ዘግቶ በመውጣት ላይ እንዳለ ፊቱን የሸፈነ ግለሰብ በተደጋጋሚ የተኩስ ዕርምጃን በመውሰድ ግድያ መፈጸሙን የግዛቲቱ ፖሊስ አስታውቋል። የናሽቢል ፖሊስ በከተማዋ ከ10 አመት በላይ የኖረውን ኢትዮጵያዊ ጉዳይ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ለማዋል ከእማኞች የተገኘን መረጃ መሰረት በማድረግ ፍለጋውን አጠናክሮ እንደቀጠለ የግዛቲቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ (ኒውስ ቻናል 15) ዘግቧል። ተጠርጣሪው ጭንብል ያጠለቀ ግለሰብ መሆኑም ከቤቱና ከአካባቢው ካሜራዎች የተገኙ መረጃዎች አመልክተዋል። ፖሊስ ተጠርጣሪውን ለመያዝ ከእማኞችና ከካሜራ የተገኙ አካላዊ ምልክቶችን መሰረት በማድረግ ፍለጋውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል። የወንጀሉን ምክንያት መነሻ ለማወቅም የቴኔሲ ግዛት ናሽቢል ልዩ የመርማሪ አካላት ተመሳሳይ ምርመራ እያካሄዱ እንደሆነም ታውቋል።

በቆሼ በደረሰ አደጋ የሟቾች ቁጥር በመቶዎች ሊበልጥ እንደሚችል የጸጥታ አካላት ገለጹ

ኢሳት (መጋቢት 12: 2009)

በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቆሻሻ መደርመስ (መናድ) በደረሰው አደጋ የሟቾች ቁጥር መንግስት ከሚገልጸው በመቶዎች ሊበልጥ እንደሚችል ኒው ዮርክ ታይምስ ጋዜጣ የጸጥታ አካላትን ዋቢ በማድረግ ዘገበ።
ቁፋሮ እየተካሄደበት ባለው ስፍራ ለጸጥታ ስራ ተሰማርቶ የሚገኝና ማንነቱ እንዳይገለጽ የጠየቀ የጸጥታ ባልደርባ አሁንም ድረስ በርካታ ሰዎች ከቁፋሮ አለመውጣታቸውን ለጋዜጣው አስረድቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአንድ ሳምንት በላይ በዘለቀው ቁፋሮ የ113 ነዋሪዎችን አስከሬን ብቻ ሊገኝ መቻሉን ቢያሳውቅም፣ የጸጥታ አባሉ የሟቾች ቁጥር መንግስት ከገለጸው በመቶዎች ሊበልጥ እንደሚችል ለኒው ዮርክ ታይምስ ጋዜጣ አስረድቷል።

ትግላችን ከሌሎች ብሄሮች ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን ማዳን ነው ሲሉ የቤኒሻንጉል ህዝብ ንቅናቄ የፖለቲካ ሃላፊ ገለጹ

ኢሳት (መጋቢት 12: 2009)

የቤኒሻንጉል ህዝብ ንቅናቄ (ቤህኒን) የሚካሄደው የነጻነት ትግል ሃገራዊና ከሌሎች ብሄሮች ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን የማዳን መሆኑን የድርጅቱ የፖለቲካ ሃላፊ ገለጹ።
የቤህኒን የፖለቲካ ሃላፊ አልሃጂ አፈንዲ ጠሓ በተለይ ለኢሳት እንደገለጹት በህወሃት/ኢሀዴግ  የሚመራውን አገዛዝ ለማስወገድ የሚካሄደው የነጻነት ትግል ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ድርጁቱ በሃገር ውስጥ የሚካሄደው የትጥቅ ትግል በህወሃት/ኢህአዴግ ላይ ያነጣጠረ እንጂ በመሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት የማድረስ አላማ እንደሌለውም ገልጸዋል። በቅርቡ በህዳሴ ግድብ ላይ የተነጣጠረ ጥቃት ለማድረስ ተንቀሳቅሰዋል የተባለውንም ከቆምንለት አላማ ጋር የሚሄድ አይደለም ሲሉ አስተባብለዋል።

Monday, March 20, 2017

Ethiopia: Andargachew Tsige spends 1000th day in detention

ESAT News (March 20, 2017)
Ethiopia’s prisoner of conscience, Andargachew Tsige, has now spent 1000 days on Ethiopia’s death row, after the country’s security forces kidnapped and rendered him there in June 2014, Reprieve, an international human rights organization following his case said in a statement.
An Ethiopian born British citizen, Andargachew ‘Andy’ Tsege, a vocal critic of Ethiopia’s ruling party, was taken into custody by Ethiopian regime security while transiting through a Yemeni airport almost three years ago.

በተለምዶ “ቆሼ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተቀበሩ ሰዎችን ለማግኘት ወራትን ሊፈጅ ይችላል ተባለ

ኢሳት (መጋቢት 11 ፥ 2009)
በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ “ቆሼ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰው አደጋ በቆሻሻ ክምር የተቀበሩ ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ ለማግኘት ወራትን ሊፈጅ እንደሚችል የነብስ አድን ሰራተኞች አስታወቁ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍለጋን የማካሄዱ ዘመቻው ወደ መጠናቀቁ ተቃርቧል ቢልም፣ የአካባቢው ነዋሪዎች አሁንም ድረስ ከ80 የሚበልጡ ሰዎች አለመገኘታቸውን ገልጸዋል። የነብስ አድን ሰራተኞች በበኩላቸው በቆሻሻ ክምሩ ያልተገኙ ሰዎችን ሙሉ ለሙሉ ፈልጎ ለማግኘት የወራት ጊዜን እንደሚወስድ ለሮይተርስ የዜና ወኪል አስረድተዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ቀናት በተካሄደ የቁፋሮ ስራ የ115 ነዋሪዎች አስከሬን የተገኘ ሲሆን፣ በርካታ ከአደጋው የተረፉ ሰዎች አሁንም ድረስ የገቡበት አለመታወቁን ነዋሪዎች ይገልጻሉ።

Tuesday, March 14, 2017

Ethiopia: Death toll reaches 90 in landfill landslide

ESAT News (March 14, 2017)
Excavators and bulldozers dig deep into a mountain of rubbish for the third day in a landfill in the outskirt of the Ethiopian capital Addis Ababa trying to find bodies buried under the pile of garbage in Saturday night’s collapse of the landfill.
State media reported that the death toll reached 72 by Tuesday night but it is not clear how many still remain unaccounted for. Other sources close to ESAT put the death toll at 90.

Monday, March 13, 2017

Ethiopia: Amnesty says gov’t failures to blame for dozens of deaths at rubbish dump

Amnesty International said today that the death of more than 60 people in a landslide at a vast rubbish dump on the outskirts of the Ethiopian capital over the weekend is a clear case of dereliction of duty by the Ethiopian authorities.
Dozens are still missing since the landslide at the 36-hectare Repi municipal dumpsite in Addis Ababa on 11 March, and many families have been left homeless after their makeshift houses were buried under tonnes of waste.

Friday, March 10, 2017

Ethiopia: Court denies bail to Dr. merera Gudina

Dr. Merera Gudina
ESAT News (march 10, 2017)

The federal high court on Friday denied bail for Dr. Merera Gudina who is detained and charged with alleged violations of the state of emergency and sedition.

Ethiopia: PG7 fighters attack prison freeing political prisoners

ESAT News (March 10, 2017)

A group of armed men on Thursday attacked a prison in north Gondar freeing political prisoners. Patriotic Ginbot 7, an armed group opposing the Ethiopian regime claimed responsibility for the attack.

Wednesday, March 8, 2017

የደሞዝ ጭማሪ ተግባራዊ ባለመደረጉ መምህራንና ሰራተኞች ተቃውሞ አቀረቡ፥ በአንዳንድ አካባቢዎች የመምህራን አድማ ተጀምሯል።

ኢሳት (የካቲት 29 ፥ 2009)

መምህራንን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች በቅርቡ ተደርጓል የተባለውን የደሞዝ ጭማሪ ተግባራዊ አልተደረገልንም ሲሉ ተቃውሞ አቀረቡ። በአንዳንድ አካባቢዎች የመምህራን አድማ ተጀምሯል።
በተለይ በጎጃምና በጎንደር አንዳንድ መምህራን አድማ አስነስታችኋል በሚል እየታሰሩ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። አድማው ከደሞዝ ማስተካከያ የተያያዘ ነው ቢባልም፣ አጠቃላይ የነጻነት ጥያቄን ያዘለ መሆኑን ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል።

በሶማሌና ኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ወረዳዎች በዘለቀው ግጭት ሚና የነበራቸው ሰዎች ለህግ እንዲቀርቡ ጥሪ ቀረበ

ኢሳት (የካቲት 29 ፥ 2009)

የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት ከአራት ወር በላይ በክልሉና በሶማሌ ክልል አዋሳኝ ወረዳዎች የዘለቀው ግጭት መፍትሄ እንዲያገኝ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ።
በሁለቱ ክልሎች የድንበር አካባቢ ያለው ግጭት ለሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት መሆኑን ያወሳው ምክር ቤቱ፣ ከሁለቱም ክልሎች ችግሮቹ ተባብሰው እንዲቀጥሉ ሚና የነበራቸው የመንግስት መዋቅር አካላት ለህግ ኣንዲቀርቡም ጥሪን አቅርቧል።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራሮችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት በመንግስት ድጋፍ የሚደረግላቸው ታጣቂዎች ጥቃቱን እየፈጸሙ እንደሆነ ሲገልጹ ቆይተዋል።

ሂልተን ሆቴል በጨረታ እንዲሸጥ ተወሰነ

ኢሳት (የካቲት 29 ፥ 2009)

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው አለም አቀፍ ሆቴል የሆነውን ሂልተን አዲስ ሲያስተዳድር የቆየው መንግስት ሆቴሉ በጨረታ እንዲሸጥ ወሰነ።
በአጼ ሃይለ-ስላሴ መንግስት ዘመን ስራውን የጀመረው ሆቴል ለጨረታ እንዲቀርብ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ከሂልተን አዲስ የቦርድ ዳይሬክተሮች ጋር ሰሞኑን ምክክር ማካሄዱንና ለጨረታው ሽያጭ ዝግጅት እንዲያደርጉ ትዕዛዝ መስጠቱን አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል። እንደፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1969 አም ስራውን የጀመረውን ይህንኑ ሆቴል ለማስተዳደር መንግስት ከሂልተን ወልድዋይድ (አለም አቀፍ) ኩባንያ ጋር የ50 አመት ስምምነት የነበረው ሲሆን፣ ይኸው ስምምነት በየአስር አመቱ ሲታደስ መቆየቱ ታውቋል።
ይሁንና በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው የመጨረሻ ውል ፍጻሜው ሲቀርብ ሂልተን አዲስ በጨረታ እንዲሸጥ በመንግስት በኩል ውሳኔ መድረሱን ጋዜጣው አስነብቧል። ለበርካታ አመታት በቆየው በዚሁ ስምምነት ሂልተን ወርልድዋይድ ከሂልተን አዲስ የ20 በመቶ ከገቢ ትርፍ ጥቅም ተጋሪ ሆኖ የቆየ ሲሆን፣ ሆቴሉ ለጨረታ ሲቀርብ ሂልተን ወርልድዋይድ ሆቴሉን ለመግዛት ዋነኛ ተጫራች ሆኖ ለመቅረብ ፍላጎት አሳይቷል።

በየካቲት ወር የዋጋ ግሽበት ሰባት በመቶ መድረሱ ተገለጸ

ኢሳት (የካቲት 29 ፥ 2009)

አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ ክልሎች የተከሰተን የምግብ ዋጋ ንረት ተከትሎ የሃገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በየካቲት ወር በአንድ በመቶ በማደግ ሰባት በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ገለጸ።
በየካቲት ወር ምግብ ነክ የዋጋ ግሽበት 7.8 በመቶ ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፣ ቁጥሩ ካለፈው ወር የ2.8 በመቶ አካባቢ ጭማሪ ማሳየትን ሮይተርስ የኤጀንሲውን ሪፖርት ዋቢ በማድረግ ማክሰኞ ዘግቧል።

በደቡብ ሱዳን የዘር ማጥፋት ድርጊት ሊፈጸም ከጫፍ መደረሱን ተመድ ገለጸ

ኢሳት (የካቲት 29 ፥ 2009)

በረሃብ አደጋ አጋጥሟት ባለው ደቡብ ሱዳን የዘር ማጥፋት ድርጊት ከጫፍ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረቡዕ ይፋ ባደረገው አዲስ ሪፖርት አስታወቀ።
በሃገሪቱ ባለው የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ላይ ለሰባት ወር የፈጅት ጥናት ማካሄዱን የገለጸው ድርጅቱ፣ በደቡብ ሱዳን በተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ ያለውን ግጭት ምክንያት በማድረግ በፕሬዚደንት ሳልባኪር የሚመራው መንግስት በማንነት ላይ የሚፈጸም ጥቃት እየወሰደ እንደሚገኝ አጋልጧል።
የሃገሪቱ ብሄራዊ የደህንነት አገልግሎት፣ ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች ታጣቂዎች ይህንኑ ድርጊት በተቀናጀ መልኩ እየፈጸሙት ነው ያለው የተባበሩት መንግስታ ድርጅቱ በተወሰኑ አካባቢዎች ሰው ሰራሽ ረሃብ እንዲከሰት መደረጉንም በሪፖርቱ አስፍሯል።

Friday, March 3, 2017

በኦሮሚያና ሶማሌ ድንበር አካባቢዎች የተከሰተው ግጭት ወደ ተለያዩ አካባቢዎች እየተዛመተ መሆኑ ተገለጸ

ኢሳት (የካቲት 24 ፥ 2009)
የኦሮሚያ ክልልን ከሶማሌ ክልል ጋር በሚያዋስኑ የድንበር አካባቢዎች በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት ዕልባት አለማግኘቱንና ወደ ተለያዩ ቀበሌዎች በመዛመት ላይ መሆኑን ነዋሪዎች ገለጹ።
በምስራቅ ሃረርጌ ጨናቅሳን ተብሎ በሚጠራ ከተማ ያሉ ነዋሪዎች የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይሎች የኦሮሚያ ክልልን ጥሰው በመግባት እየፈጸሙት ባለው ጥቃት ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ ከ100 በላይ ነዋሪዎች መገደላቸውን አስታውቀዋል።
በዚሁ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ አብዱራህማን ዱባ ታጣቂዎች ከጨንቃሳን በተጨማሪ በባቢሌ፣ በጉርሱም እና በተለያዩ መንደሮች መዛመቱን ለአዲስ ስታንዳርድ መጽሄት አስረድተዋል።
ባለፈው ሳምንት የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግ የሶማሌ ክልል ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል እየፈጸሙት ባለው ጥቃት ከሁለቱም ወገኖች ከ400 በላይ ሰዎች መሞታቸውን በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው ሪፖርት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል