Tuesday, December 18, 2018

አምዶም ገብረስላሴ ታሰረ

ባለፈው ቅዳሜ በመቀሌ በተካሄደው ስብሳባ አቶ በረከት ስሞኦን እና የሕወሓት ባለስልጣናትን የተቸው አምዶም ገብረስላሴ ታሰረ።
     ለኢሳት በደረሰው መረጃ መሰረትየአረና የሕዝብ ግኑኝነት ሃላፊ አቶ  አምዶም ገብረስላሴ በቁጥጥር ስር የዋለው መቀሌ አክሱም ሆቴል በተባለው አካባቢ ሲሆን፣ሰው ደብድበሃል በሚል  መታሰሩንም  መረዳት ተችሏል።አምዶም  መቀሌ አዲሸንዲህ በተባለ  ቦታ እንደታሰረ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።አምዶም ገብረስላሴ ባለፈው ቅዳሜ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ በተካሄደው  ሰብሰባ የሕወሃትን ባለስልጣናት ሲተች ንግግሩ እንዲቋርጥ መደረጉም ይታወሳል።

Friday, December 14, 2018

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ በተከሰተ ግጭት እስካሁን የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ፡፡

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ በተከሰተ ግጭት እስካሁን የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተነገረ፡፡ ከአንድ መቶ የሚበልጡ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል ተብሏል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሡ ዳምጠው ዛሬ ለሸገር እንደተናገሩት ከትናንት በስትያ አንስቶ በቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ ግጭት ተከስቷል፡፡ በግጭቱ እስከ አሁን የ13 ሰዎች ህይወት ማለፉ የተነገረ ሲሆን ከአንድ መቶ የሚበልጡ ደግሞ ቆሰለዋል ተብሏል፡፡ በንብረት ላይም ጉዳት መድረሱን አቶ አድማሱ ተናግረዋል፡፡

Thursday, December 13, 2018

ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ክፍል መዘጋቱ ተረጋገጠ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 4/2011) ማዕከላዊ በመባል የሚጠራው የወንጀል ምርመራ ክፍል መዘጋቱን አረጋግጬአለሁ ሲል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።

ኮሚቴው ማዕከላዊን ተዘዋውሮ ከጎበኘበኋላ በሰጠው መግለጫ ማዕከላዊ ተዘግቶ ክፍሎቹ ለቡራዩ ተፈናቃዮች በጊዜያዊ መኖሪያነት እያገለገሉ ነው ብሏል።
የኮሚቴው አባላት አረጋገጥን እንዳሉትም በማዕከላዊ አንድም እስረኛ የለም።

በአዲስ አበባ ከ2ሺህ በላይ ነዋሪዎች ቤተክርስቲያን መጠለላቸው ታወቀ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 4/2011) ከአዲስ አበባ በተለምዶ አጃምባ በሚባል አካባቢ ቤት ሰርተው ለዓመታት የቆዩ ከ2ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተፈናቅለው ቤተክርስቲያን መጠለላቸውን ገለጹ።

ህገወጥ ናችሁ ተብለው በሌሊትበተኙበት በአፍራሽ ግብረሃይል ቤታቸው የፈረሰባቸው ተፈናቃዮች በፋኑዔል ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተጠልለው መኖር ከጀመሩ 15ቀናትያለፋቸው መሆኑን ለኢሳት ገልጸዋል።
በወቅቱ በድንገት በተወሰደው የማፍረስ ተግባር በተፈጠረ ግርግር

Monday, December 3, 2018

ፖሊስ ሜጀር ጀኔራል ክንፈ ዳኘው የተጠረጠሩባቸውን ተጨማሪ የወንጀል ተሳትፎዎች አቀረበ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 24 ፣ 2011 (ኤፍ ቢ ሲ) መርማሪ ፖሊስ ሜጀር ጀኔራል ክንፈ ዳኘውን በተመለከተ እስካሁን በሰራው የምርመራ ስራ አገኘኋቸው ያላቸውን ተጨማሪ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤት አቅርቧል።

ፖሊስ በዛሬው እለት ግለሰቡን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ካቀረባቸው ማስረጃዎች በተጨማሪነት አዳዲስ ያላቻውን ነው ያቀረበው።

በአፋር ክልል በተቀሰቀሰ ግጭት አንድ የአፋር ወጣት ተገደለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በአፋር ክልል በመሬት ይገባኛል ጥያቄ ኤል ውሃ አካባቢ ቡርካ በሚባል ቦታ በተቀሰቀሰ ግጭት ሰላም ለማስከበር በሚል ጣልቃ በገባ የመከላከያ ሰራዊት አንድ የአፋር ወጣት መገደሉን ለኢሳት የደረሰ መረጃ አመልክቷል።

በአፋር ዛሬ የሚጀመረውንና አብዛኛውን አመራሮችን ያሰናብታል ተብሎ የሚጠበቀው የክልሉ ገዢ ፓርቲ ጉባዔውን በሚያካሂድበት ወቅት ዋዜማ የተቀሰቀሰው ግጭት ሶስተኛ ቀኑን መያዙ ታውቋል።
ጉባዔውን በሁከት በማጀብ የአቶ ስዩም አወል ቡድን የሚፈጽመው ሴራ ሳይሆን አይቀርም ተብሏል።

በቤንሻንጉልና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ጥቃት የሚፈጽመው ኦነግ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በቤንሻንጉል ጉምዝና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ጥቃት በመፈጸም ላይ ያለው የኦነግ ጦር መሆኑን የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አስታወቀ።
ለእርዳታ የተዘጋጀ ከ2ሚሊዮን ብር በላይ በታጣቂዎች መዘረፉም ታውቋል።
በሁለቱ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ውጥረት ቀጥሏል።
መከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ በግጭቱ አካባቢዎች መስፈራቸውን የቤንሻንጉል ጉምዝ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ሰይፈዲን ሀሩን  ለኢሳት ገልጸዋል።

የወልቂጤ አካባቢ ወጣቶች በልዩ ሃይል እየታፈሱ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በጉራጌ ዞን የወልቂጤ አካባቢ ወጣቶች በአካባቢው ልዩ ሃይል እየታፈሱ መሆኑ ተሰማ።
በጉራጌና በቀቤና ብሔረሰቦች መካከል ቀደም ሲል ተቀስቅሶ የነበረው ግጭትም አሳሳቢ ወደሚባል ደረጃ እየተሸጋገረ መሆኑን ኢሳት ወደ አካባቢው ደውሎ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በፌደራል ደረጃ ጉዳዩን ለመፍታት የተደረገው ሙከራ ሊሳካ አልቻለም የሚሉት የኢሳት ምንጮች ግጭቱ እንዲባባስ የሚፈልጉ አካላት ደግሞ በአካባቢው ውጥረት እየፈጠሩ ነው ብለዋል።
ሁኔታውን ለማረጋጋት የፌደራሉ መከላከያ ሃይል በአካባቢው መሰማራቱም ታውቋል።

የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ መጠናከር አለበት ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011)የኢትዮጵያ ችግር ከስረ መሰረቱ እንዲነቀል የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ መጠናከር እንዳለበት የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ገዱ አንዳርጋቸው ገለጹ።
በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራው የአማራ ክልል የልኡካን ቡድን በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ካለው የአማራ ተወላጆችና የአማራ ጉዳይ ያገባናል ካሉ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ምክክር አድርገዋል።
ከስብሰባው ተዳሚዎች ለቀረቡ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ችግር ከስረ መሰረቱ እንዲነቀል የእነዚህ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ የኦሮሞና የአማራ ህዝቦች በትንሹ መገናኘት ሲጀምሩ፥መቻቻል ሲጀምሩ በሀገሪቱ ላይ ምን ያህል ተጽዕኖ ማምጣት እንደሚችሉ አሳይተውናል።

አርበኞች ግንቦት ሰባት በመጪው ምርጫ በ547 ወረዳዎች ለመወዳደር ማቀዱን አስታወቀ

አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ በመጪው ምርጫ በ547 ወረዳዎች ዕጩዎቹን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ተናገሩ።ንቅናቄው በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በንቃት የሚያሳትፍ ድርጅት ሊመሰርት መዘጋጀቱንም አቶ አንዳርጋቸው ጨምረው ተናግረዋል።
አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ በመጪው ምርጫ በ547 ወረዳዎች ዕጩዎቹን ለማቅረብ መዘጋጀቱን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ተናገሩ። አቶ አንዳርጋቸው ይኸን ያሉት ንቅናቄው በብሪታኒያ እና አካባቢዋ ከሚገኙ አባላቱ ጋር በመከረበት ስብሰባ ላይ ነው። ንቅናቄው በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በንቃት የሚያሳትፍ ድርጅት ሊመሰርት መዘጋጀቱንም አቶ አንዳርጋቸው ጨምረው ተናግረዋል። አዲስ የሚቋቋመው ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ እና መርሐ-ግብር በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ውስጥ ዝግጁ ይሆናሉም ተብሏል። በትናንትናው ዕለት በለንደን ከተማ የተካሔደውን ውይይት የተከታተለችው ሃና ደምሴ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች። 

Friday, November 30, 2018

የሰራዊቱ አባላት ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ከወር በፊት ያለ ፈቃድ ወደ ቤተመንግስት የተንቀሳቀሱ ወታደሮችን ያስተባበሩ የሰራዊቱ አባላት ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቀረቡ። ከወታደራዊ ዲሲፒሊን በማፈንገጥና ሕግን በመጣስ የተንቀሳቀሱትን ወገኖች በሕግ ተጠያቂ ማድረግ ነገ ተመሳሳይ ነገር እንዳይፈጸም ይከላከላል ሲሉ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ገልጸዋል።

Wednesday, November 28, 2018

U.S. Assistant Secretary of State visits Ethiopia

 ESAT News (November 28, 2018)
US Assistant Secretary of State for African Affairs, Tibor Nagy is in Addis Ababa for an official working visit as part of his tour to East Africa.
Nagy and General Thomas D. Waldhauser, Commander of U.S. Africa Command (AFRICOM), met with Ethiopia’s Minister of Defense Aisha Mohammed to discuss opportunities for security cooperation between the United States and Ethiopia, according to the U.S. Embassy in Addis Ababa.
Speaking to NPR’s “All Things Considered” a week ago, Mr. Nagy called Ethiopia’s Prime Minister Abiy Ahmed “visionary.”
“It shows you what one courageous, visionary leader can do to impact not only her or his own country, but the region,” Nagy said speaking about Ahmed who is credited for reforms in his country and ending a two decae old animosity with Eritrea.
“Now the waves are kind of washing over other parts of the region. I mean, during my discussions with African leaders, I pointed to Ethiopia as – what a positive force can mean for Africa.”
It is Nagy’s first visit to Ethiopia since his confirmation in July. He served as U.S. Ambassador to Ethiopia from 1999 to 2002

Wednesday, November 21, 2018

ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ አርአያነታችንን እናስመስክር አሉ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 11/2011) በኢትዮጵያ አሁን የተገኘው ለውጥ በሁሉም ህዝብ ትግል የመጣ በመሆኑ እኛም ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ አርአያነታችንን ማስመስከር ይገባናል ሲሉ ጀነራል ሰዓረ መኮንን ገለጹ።
የኢትዮጵያ የሃገር መከላከያ ሚኒስቴር ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንን በአንድ የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ የመጣው ለውጥ የሁሉንም ሕዝብ ተሳትፎ የጠየቀ በመሆኑ ሰራዊቱም የዚህ ለውጥ ተጠቃሚ እና ደጋፊ ነው ።
በለውጡ የሰራዊቱን ኑሮ ከማሻሻል ጀምሮ ለአከባቢው ሰላም የነበረን ሚና ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ መቀመጡንም ገልጸዋል።
እናም ከለውጡ ጋር መሄድና የዘመናዊ ሰራዊት ግንባታን ማፋጠን ይገባናል ብለዋል።
ጠቅላይ ኢታማጆር ሹም ሰዓረ መኮንን እናደሉት የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግል ላገኘው ለውጥ መከላከያ ሰራዊቱ አጋርነቱን ያረጋገጣል።
እኛ ለሕዝባችን የመጨረሻ ምሽግ ነን ሲሉም ሰራዊቱ ከለውጡ እና ከሕዝቡ ጋር መቆሙንም አረጋግጠዋል።

በሜቴክ ሳቢያ የ36 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ አስከተለ

(ኢሳት ዲሲ–ህዳር 12/2011)የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን በአፋር ክልል እገነባዋለሁ በማለት የተንቀሳቀሰበት የእንፋሎት ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በሜቴክ ሳቢያ የ36 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ ማስከተሉ ተገለጸ።

በጄኔራል ክንፈ ዳኘው ይመራ የነበረው ሜቴክ ከኮንትራት ስምምነቱ ውጪ ከውጭ ያስገባቸው መሳሪያዎች አሮጌዎችና ያልተሟሉ በመሆናቸው ለፕሮጀክቱ መክሸፍና ለተከተለው ኪሳራ ምክንያት እንደሆነም መረዳት ተችሏል።
137 ሜጋ ዋት ያመነጫል የተባለው የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም መክሸፉ ተመልክቷል።

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ሆነው ሊሾሙ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 12/2011) ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በነገው ዕለት የሀገሪቱ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ሆነው እንደሚሾሙ ተገለጸ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በሚያደርገው ስብሰባ ወይዘሪት ብርቱካንን የምርጫ ቦርዱ ሀላፊ እንዲሆኑ በጠቅላይ ሚንስትር አብይ የሚቀርበውን ሀሳብ መነሻ በማድረግ ድምፅ ይሰጣል ተብሏል።
ወይዘሪት ብርቱካን ከሰባት አመታት ስደት በኋላ መንግስት ባደረገላቸው ጥሪ በቅርቡ ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸው ይታወሳል።
ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንደ አዲስ ለሚደራጀው ብሔራዊ ምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ኃላፊ እንዲሆኑ መታጨታቸው ሲነገር ቆይቷል ።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ  ስያሜውንና አጠቃላይ አደረጃጀቱን በማሻሻል ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ ሆኖ ይቋቋማል ተብሎ ይጠበቃል።

በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ግጭቶች ተቀሰቀሱ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 12/2011) በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ግጭቶች መቀስቀሳቸው ተገለጸ።

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አሶሳ ዩኒቨርስቲ በተነሳው ግጭት ሶስት ሰዎች ተገድለዋል።
34 ሰዎችም ክፉኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በቴፒ ሳምንታት የዘለቀው ግጭት አሁንም አልበረደም።
በልዩ ሃይል በርካታ ሰዎች ተደብድበው ሆስፒታል ገብተዋል። በአፋርም የህዝብ ተቃውሞ ቀጥሏል።
በቢሾፍቱ ደብረዘይት ቄሮ ነን ባሉ ወጣቶች ሱቃችንን ልቀቁ እየተባልን ነው ሲሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
በአንዳንድ ዩኒቨርስቲዎች መለስተኛ ግጭቶች መፈጠራቸውን የገለጸው ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ለማደናቀፍ የሚሰሩ ወገኖች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ዒላማ አድርገዋል ብሏል።

Monday, November 19, 2018

Ethiopia: Capital launches mixed-use, integrated residential project

by Engidu Woldie
ESAT News (November 19, 2018)
An integrated residential project was launched today at the historic La Gare (Train Station) in the capital Addis Ababa.
The mixed-use project, which lands on 360,000-sq-m area, is expected to have 4000 residences and cost 50B birr, (approximately $1.9B at current exchange rates).
A key component of the project was building residences for the 1,600 citizens to prevent eviction from their village.

ጠበቃ ለማቆም ገንዘብ የለኝም በማለት በችሎት ፊት ምለው የተናገሩት አቶ ኢሳያስ ዳኘው (የሜ/ጀነራል ክንፈ ወንድም) ሚሊዬነር መሆናቸው ተረጋገጠ!

BBC Amharic

ከዚህ ቀደም በራሳቸው ጠበቃ ማቆም እንደማይችሉ ለተናገሩት አቶ ኢሳያስ ዳኘው ፖሊስ አለኝ ያለውን ማስረጃም አቅርቦ ለፍርድ ቤቱ አሰምቷል። በራሳቸው ስም በፀረ ሙስና ኮሚሽን የሐብት መዝገብ ቅፅ ላይ ራሳቸው ያስመዘገቡት ዝርዝር
➤ 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ባለ 1 ፎቅ ቤት በራሳቸው ስም የተመዘገበ፣

Thursday, November 15, 2018

ኮለኔል ገብረእግዚአብሔር አለምሰገድ በቁጥጥር ስር ዋሉ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 6/2011) በሶማሊያ የኢትዮጵያ ጦር አዛዥና በኢጋድ የዋና ጸሃፊው የፖለቲካ አማካሪ ኮለኔል ገብረእግዚአብሔር አለምሰገድ በተለምዶ ገብሬ ዲላ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ።

በኮንትሮባንድ ንግድና በሶማሌ ክልል በተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እጃቸው እንዳለበት የሚጠረጠሩት ኮለኔል ገብረእግዚያብሄር ባለፈው ሳምንት በጂጂጋ ከተፈጠረው ግጭት ጋር በመሪነት እንደተሳተፉ ይነገራል።
ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ በወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ለ10 ተከታታይ አመታት የቆዩት ኮለኔል ገብረእግዚያብሄር በሃገር ሃብት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ካደረሱ የህውሃት የጦር መሪዎች ዋናው እንደነበሩ መረጃዎች ያመለክታሉ።

የ205 ግለሰቦች የባንክ ሒሳብ ታገደ

(ኢሳት ዲሲ–ህዳር 6/2011) የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የ205 ግለሰቦች የባንክ ሒሳብ እንዲታገድ አደረገ።

ፌደራል ፖሊስ በቀድሞ የደህንነትና የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮችና ቤተሰቦቻቸው ስም የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦች መረጃ እንዲሰጠው በጠየቀው ደብዳቤ በተጠርጣሪዎቹ ግለሰቦች ሚስትና ልጆቻቸው ስም የተከፈቱትን በዝርዝር ገልጿል።
በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ የሜቴክ ሃላፊዎች ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘውን ጨምሮ የ147 ሰዎች የባንክ ሂሳብ በሙስና ተጠርጠረው የባንክ ሂሳባቸው ሲታገድ የአቶ ጌታቸው አሰፋና የ57 ሰዎች የባንክ ሂሳብ ደግሞ ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘ አካውንታቸው እንዲታገድ ተደርጓል።

ለፍርድ የማቅረቡ ዘመቻ ይደገፋል ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ህዳር 6/2011) በዜጎች ላይ የሰብአዊ መብት ሲፈጽሙ በነበሩ ባለስልጣናት ላይ መንግስት የጀመረውን ለፍርድ የማቅረብ ዘመቻ እንደሚደግፈው ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ገለጸ።

የጥቃቱ ሰለባዎችን በተመለከተ የሰበሰባቸውን መረጃዎች ለሕግ አስከባሪ አካላት እንደሚሰጥም አስታውቋል።
የፍርድ ሔደቱ ከበቀል የጸዳ እንዲሆንም ጥሪ አቅርቧል።
ከተመሰረተ ሩብ ክፍለ ዘመን ያስቀጠረውና በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በመመዝገብና በማጋለጥ የሚታወቀው የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ የወቅቱን የመንግስት መግለጫ በተመለከተ  መግለጫ ያወጣው ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ነው።
“የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ፈጻሚዎች ላይ መንግስት በመውሰድ ላይ ያለው ርምጃ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል በሚል ርዕስ ሰመጉ ባወጣው መግለጫ በሕግ ጥላ ስር በሚገኙ ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ የማሰቃየት ድርጎቶችን በተመለከተ አቃቤ ሕግ ይፋ ያደረገውን ሪፖርት ሰመጉ የሚያውቀውና ሲያጋልጠው የቆየ መሆኑንም አስታውሷል።

Monday, November 12, 2018

Ethiopia: Warrants issued for Abay Tsehaye, Maj. Gen. Kinfe Dagnew as arrest on army and intelligence officials continues

Most of the officials wanted for a range of crimes hail from Tigray region. The regional government has not been willing to handover the suspects, according to the sources, who also said there has been a recent increase in the number of Tigrayan federal officials and army generals that sought refuge in the region.
Ethiopia’s attorney general today said the alleged crimes by the officials include illicit financial flights, illegal purchases by government enterprises mainly by METEC former managers.
The attorney general, Berhanu Tsegaye aslo said members of the intelligence and security who have committed human rights violations would also be brought to justice.

Friday, November 9, 2018

በሰራዊቱ ውስጥ የተጀመረውን የለውጥ ርምጃ ለማጠናከር በርካታ ጄነራሎችን ጨምሮ ከ160 በላይ ከፍተኛ የጦር አዛዦች ከሰራዊቱ መሰናበታችውን የቅርብ ምንጮች ለኢሳት ገለጹ።

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 30/2011) ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድም ጎንደር ከተማ ላይ ትናንት በሰጡት መግለጫ ባለፉት 7 ወራት ከተሰሩ ስራዎች ትርጉም ያለውና መሰረት የረገጠ ስራ የተሰራው በሰራዊቱ ውስጥ እንደሆነ ገልጸዋል። ፋይል የሰራዊቱን አመራር ለማሰባጠር በተወሰደው ርምጃ የተነሱት ወታደራዊ ሃላፊዎች በፈቃደኝነት እንደለቀቁም ገልጸዋል። ባለፉት 7 ወራት ትርጉም ያለው የማሻሻያ ርምጃ የተወሰደው በሃገር መከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገልጸዋል። በተቋሙ ውስጥ የቀየርነው ሚኒስትሩን ብቻ ሳይሆን ተልዕኮውንም

በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች ወሰን ላይ የጅምላ መቃብር መገኘቱ ተገለጸ።

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 30/2011) ፖሊስ እንዳስታወቀው የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ዒሌ ታማኝ በሆነው የልዩ ሃይል ተፈጸሟል በተባለ ግድያ የ200 ሰዎች አስክሬን በአንድ ጉድጓድ የተቀበረበት የጅምላ መቃብር ተገኝቷል። ፋይል ግድያው የተፈጸመው በሁለቱ ክልሎች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ወቅት እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ ተጨማሪ የጅምላ መቃብር ለማግኘት ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል። አቶ አብዲ ዒሌ በስልጣን ዘመናቸው ፈጽሟቸዋል ለተባሉት ወንጀሎች በህግ ተይዘው በእስር ላይ የሚገኙ መሆኑ ታውቋል። የጅምላ መቃብሩ መገኘቱ የተመለከተው መረጃ የወጣው ትላንት በነበረው

Several mass graves found in Somali region of Eastern Ethiopia

ESAT News (November 9, 2018)
A day after police told a court in Addis Ababa that they have found a mass grave in an area between the Oromo and Somali regions in Eastern Ethiopia containing the bodies of about 200 people, president of the Somali region told ESAT that investigations were underway on “several” mass graves found in the region.
In a brief comment to ESAT on the news of the founding of a mass grave containing the about 200 bodies that was disclosed in court yesterday, Mustafa Omer, president of the Somali region, said the regional government, together with elders, are conducting forensic investigations on “several” mass graves found in the region.

የቡና ቱሪዝም ቀንን ለማክበር የወጡት መግለጫዎች አይወክሉኝም ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 30/2011) የዘንድሮው የቡና ቱሪዝም ቀንን ለማክበር የወጡት መግለጫዎች አይወክሉኝም ሲል የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር ዓለም ዓቀፍ የቡና ፕሮግራም በቡና መገኛ ምድር በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን በዓል አስመልክቶ በሳምንቱ መጀመሪያ በተሰራጨው መግለጪያ የቡና መገኛ ጂማ ነው የሚለው አገላለጽ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቷል።

Wednesday, November 7, 2018

በሊቢያ ኢትዮጵያውያን በስቃይ ላይ ናቸው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በሊቢያ ኢትዮጵያውያን በስቃይ ላይ መሆናቸው ተገለጸ።

በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን ለቀናት ምግብና ውሃ አጥተው በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል።
አብዛኞቹ ከጎንደር የተሰደዱ መሆናቸውን የሚገልጹት ኢትዮጵያውያኑ ባለፈው ቅዳሜ ገጀራና የጦር መሳሪያ የያዙ የሊቢያ ታጣቂዎች ድብደባ ፈጽመውባቸው ለከፍተኛ ጉዳት መዳረጋቸውን ተናግረዋል።

በአፋር ተቃውሞ ሲደረግ ዋለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በአፋር የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲደረግ ዋለ።

አሳይታ፣ አዳአር፣ በራሂሌ፣ ገላኢሉ፣ ዳሎል፣ ገዋኔና ኮነባ በተሰኙ የአፋር ከተሞች በተደረገው ተቃውሞ የክልሉን መንግስት የሚመራው ገዢ ፓርቲ ለህዝብ ስልጣኑን እንዲያስረክብ ተጠይቋል።
ሁለተኛ ወሩን እያጠናቀቀ ያለው የአፋር ተቃውሞ ፌደራል መንግስቱ በአስቸኳይ ጣልቃ ገብቶ የክልሉ ህዝብ ከተደቀነበት አደጋ እንዲታደገው ጥሪ ቀርቧል።
የአፋር ህዝብ ፓርቲ ለኢሳት እንደገለጸው የፌደራሉ መንግስት በቶሎ ምላሽ ካልሰጠ በአፋር ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ የሚያስከትል ተቃውሞ ይቀሰቀሳል።

ዓለም አቀፉ የቡና ቱሪዝም ፕሮግራም ተቃውሞ አስነሳ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) የቡና መገኛ ጂማ ነው በሚል በቡናና ሻይ ልማት ባለስልጣን የሚከበረው የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የቡና ቱሪዝም ፕሮግራም ተቃውሞ አስነሳ።

ዛሬ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ህዝቡ አደባባይ በመውጣት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ አውግዟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቡናና ሻይ ባለስልጣን ጋር በመተባባር የዘንድሮውን የቡና ቱሪዝም ለማክበር በከፋ የተያዘው ፕሮግራም ተሰርዞ በጂማ እንዲሆን መደረጉ ብሔርን ከብሔር የሚያጋጭና ታሪክን የሚቀማ ተግባር ነው ሲል የከፋ ዞን አስተዳደር ቅሬታውን ገልጿል።

በሕገወጥ መንገድ የገቡ የጦር መሳሪያዎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011)ወደ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ በሶስት ወራት ውስጥ የገቡ የጦር መሳሪያዎች ብዛት ከ1 ሺ 500 በላይ መብለጡን ፖሊስ ገለጸ።

የጦር መሳሪያዎቹም በአብዛኛው ቱርክ ሰራሾች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን በብዛት የሚገባውም በሱዳን በኩል እንደሆነ ተመልክቷል።
በፌደራል ፖሊስ የተደራጁ ልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክተር ኮማንደር ከተማ ደባልቄ ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት እስከ መስከረም መጨረሻ ባሉት ሶስት ወራት 1 ሺ 560 ሕገ ወጥ ሽጉጦች ወደ ሃገር ቤት ገብተው በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የኤርትራው ፕሬዝዳንት ወደ ጎንደር ከተማ ሊሄዱ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቄ የፊታችን አርብ ጎንደር ከተማ ይገባሉ ተባለ።

ፕሬዝዳንቱ በአማራ ክልል በሚያደርጉት ጉብኝት የክልሉን ርዕሰ ከተማ ባህርዳርን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎችም ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተመልክቷል።
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የፊታችን አርብ ጎንደር ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የአማራ ክልል ባለስልጣናት አቀባበል እንደሚያደርጉላቸው ተመልክቷል።

Thursday, November 1, 2018

ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ታጣቂዎችን ለማቋቋም የጀርመን መንግስት ቃል ገባ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 22/2011)በትጥቅ ትግል ላይ ቆይተው በመንግስት ጥሪ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወስነው ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ታጣቂዎችን ለማቋቋም የጀርመን መንግስት የልማትና የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ ተገለጸ።

በአጠቃላይ ትጥቅ ፈተው ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ታጣቂዎች ቁጥር 35ሺ ያህል መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ገልጸዋል።

Ethiopia appoints first female supreme court president

ESAT News (November 1, 2018)
Ethiopia’s parliament appointed the first female supreme court president today in what is seen as the latest move by a reformist Prime Minister in increasing women’s role in his government.
Prime Minister Abiy Ahmed nominated Meaza Ashenafi to lead the highest court of the land which was unanimously approved by the Parliament.
A women’s right activist and a former judge for the high court, Ashenafi’s work was the subject of a Hollywood movie with Angelina Jolie as its executive producer.

ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ድብደባ ሊፈጽሙ ነበር ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 22/2011)የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ፕሬዝዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ድብደባ ለመፈጸም ሙከራ በማድረጋቸው በህግ ሊጠየቁ ነው ተባለ።

ዶክተር አሸብር የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሁለት አባላትን በስብሰባ ላይ ለመደብደብ መሞከራቸው ተገልጿል።
በዶክተር አሸብር የድብደባ ሙከራ ከተደረገባቸው አንዷ ኮለኔል ደራርቱ ቱሉ መሆኗም ታውቋል።
ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ሊያመራ መሆኑን የገለጹት ምንጮች በዶክተር አሸብር በኩል የሽምግልና ጥያቄ መቅረቡን ጠቅሰዋል።

በጋምቤላ የቦምብ ጥቃት ደረሰ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 22/2011)በጋምቤላ የቦምብ ጥቃት ደረሰ።
በአንድ የክልሉ ባለስልጣን ጠባቂ ፖሊስ ትላንት የተፈጸመው የቦምብ ጥቃት የሁለት ሰዎችን ህይወት ማጥፋቱ ተገልጿል።
አዲሱ የጋምቤላ አመራር ወደ ስልጣን መምጣቱን ተከትሎ ያኮረፉ ሃይሎች የሽብር ተግባር ሊፈጽሙ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳለም ታውቋል።
ቦምቡን ያፈነዳው ግለሰብ የህወሃት አባል እንደሆነም የኢሳት ምንጮች ያደረሱን መረጃ አመልክቷል።

Monday, October 22, 2018

የአቶ ጌታቸው አሰፋ ሃብት እንዲታገድና የዝውውር መብታቸው እንዲገደብ ተጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 12/2011) የቀድሞ የደህንነት መስሪያ ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ ሃብታቸው እንዲታገድና የዝውውር መብታቸው እንዲገደብ አንድ የአሜሪካ ኮንግረስ ማን ጠየቁ።

የኮሎራዶው ኮንግረስ ማን ማይክ ኮፍ ማን የኤች አር 128 የውሳኔ ሀሳብን ጠቅሰው በአቶ ጌታቸው አሰፋ ላይ ርምጃ እንዲወሰድ ለሁለት የአሜሪካ ሚኒስትሮች የጻፉትን ደብዳቤ ዛሬ አስገብተዋል።
ኮንግረስ ማን ኮፍ ማን አቶ ጌታቸው አሰፋ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡና በውጭ ያላቸው ሃብት እንዲታገድ መጠየቃቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

Thursday, October 18, 2018

ሁለት የሰብዓዊ መብትና የህግ ባለሙያዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ

ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 8/2011)የአዲስ አበባ ወጣቶችን በማደራጀት ክስ የተመሰረተባቸው ሁለት የሰብዓዊ መብትና የህግ ባለሙያዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉና ሚካዔል መላከ አዲስ አበባ ከሌላ አካባቢ በመጣ ሰው አትተዳደርም የሚል ቅስቀሳ በማድረግና የአዲስ አበባ ወጣቶችን ሲያደራጁ ነበር የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።
የፖሊስ ክስ ላይ ለዚህ እንቅስቃሴ የሚረዳ ግንኙነት ከፍልስጤም ኤምባሲ ጋር መደረጉን የሚያመለክት ነው።
የአዲስ አበባ ወጣቶችን ለማደራጀት ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ ሌሎች ሰዎችም በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።
ባለፈው ቅዳሜ በአዲስ አበባ ሀሮምሳ በሚል የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ የአዲስ አበባ ወጣቶችን የማደራጀት እንቅስቃሴ በይፋ መጀመሩ የሚታወስ ነው።
የህግ ባለሙያና ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ሚካዔል መላከ የተያዙት ትላንት ነበር።
ጠበቃ ሄኖክ ትላንት ቢሮ ውስጥ እንዳለ በፖሊስ መያዙን የሚገልጹት የኢሳት ምንጮች በቢሮው የሚጠቀምባቸው ኮምፒውተሮችና ሌሎች እቃዎች ተበርብረው መወሰዳቸው ታውቋል።
ዛሬ የአራዳ የመጀመሪያው ፍርድ ቤት ጠበቃ ሄኖክና ሚካዔል ላይ የተከፈተውን ክስ ማዳመጡን ነው ለማወቅ የተቻለው።
በፖሊስ የቀረበው ክስ የአዲስ አበባን ወጣቶች ለማደራጀት ተንቀሳቅሳችኋል የሚል ነው።
ፖሊስ በክስ መዝገቡ ጠበቃ ሄኖክና ሚካዔል መላከ፡ አዲስ አበባን ከሌላ ክልል የመጣ ከንቲባ ሊመራት አይገባም የሚል አቋም ይዘው ሲቀሰቅሱ ነበር ሲል አመልክቷል።
በተጨማሪም የፍልስጤም ወዳጅነት ማህበር ማቋቋም የሚል የፖሊስ ክስ እንደሚገኝበትም ጉዳዩን የተከታተሉ ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል።
ከፍልስጤም ኤምባሲ ጋር በመገናኘት የወዳጅነት ማህበር ለመመስረት ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋል ነው የሚለው ፖሊስ።
ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ በተለይ በህወሃት አገዛዝ ዘመን በግፍ ለሚታሰሩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና ጋዜጠኞች በነጻ ጥብቅና በመቆም የሚታወቅ ነው።
በቅርቡም ከአዲስ አበባ ግጭት ጋር በተያያዘ ለታሰሩት የአርበኞች ግንቦት ሰባት አቀባበል ኮሚቴ አባላት ጠበቃ በመሆን ቆሞላቸዋል።
ለአሁኑ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ለሆኑትና በህወሀት አገዛዝ በተደጋጋሚ ለእስር ተዳርገው ለነበሩት ለአቶ ታዬ ደንደአም ጠበቃ በመሆን ተሟግቶላቸዋል።
በተመሳሳይ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ሚካዔል መላከም በግፍ ለሚታሰሩ ሰዎች ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማድረግ የሚታወቅ ነው።

የስደተኞች ቁጥር ወደ አንድ ሚሊየን ተጠጋ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 8/2011) በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞች ቁጥር ወደ አንድ ሚሊየን መጠጋቱን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን አስታወቀ።
ከጥር እስከ ነሐሴ ብቻ ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ስደተኞች ቁጥር ከ36 ሺ በላይ መሆኑን የገለጸው ይህው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አካል የኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር መከፈቱን ተከትሎም የስደተኞቹ ቁጥር መጨመሩን አመልክቷል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር እስከ ነሐሴ 31/2018 በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞች ቁጥር 905ሺ 831 መድረሱን የገለጸው የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ከዚህ ውስጥ ከፍተኛውን ቁጥር የያዙት የደቡብ ሱዳን ተወላጆች መሆናቸውን አመልክቷል።
በኢትዮጵያ የሚገኙ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች 422ሺ 240 ሲሆኑ በብዛት በሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት በቁጥር 257ሺ 283 የሚሆኑት ሶማሊያውያን ናቸው።

ለውጡን ለማደናቀፍ የታጠቁ ወታደሮች ወደ ቤተመንግስት ተልከዋል ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 8/2011) የታጠቁ ወታደሮችን ወደ ቤተመንግስት የላኩት አካላት ለውጡን ለማደናቀፍ እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ።
በወቅቱ ለድርጊቱ የጥንቃቄ ምላሽ ባይሰጥ ኖሮ ሃገሪቱን ወደ ቀውስ የሚከታት ነበር ሲሉም ገልጸዋል።
ሆኖም ሁሉም ወደ ቤተመንግስት የተንቀሳቀሱት ወታደሮች ይህንን ግንዛቤ ጨብጠው ነበር ለማለት እንደሚያስቸግርም አመልክተዋል።
መስከረም 30 ቀን 2011 ዓመተ ምህረት ቁጥራቸው 250 የሚሆን የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነትጥቃቸው ወደ ቤተመንግስት ያደረጉት ጉዞ አብይ መነጋገሪያ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩም በወቅቱ ከሰራዊቱ አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት የሰራዊቱ የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ አግባብ እንደነበር በመግለጽ ጥያቄውን ያቀረቡበት መንገድ ግን ሕገ ወጥ ነው ሲሉ መግለጻቸው ይታወሳል።
የሰራዊቱ አባላት ከጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ሰአረ መኮንንና ከሌሎች የሰራዊቱ አመራሮች ጋር ከተወያዩ በኋላ ድርጊቱን ከበስተጀርባ የመሩና ያቀነባበሩ የሰራዊቱ አዛዦች መታሰራቸውን ጄኔራል ሰአረ መኮንን በሳምንቱ መጨረሻ አስታውቀዋል።
ከታሰሩት የሰራዊቱ አዛዦች ጀርባ ግለሰብም ይሁን ቡድን ካለ ምርመራ መቀጠሉንም አመልክተዋል።

የአዲስ አበባ ወጣቶች ከጦላይ ወታደራዊ ካምፕ ተለቀቁ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 8/2011) ባለፈው ወር መጀመሪያ በጅምላ ታፍሰው ወደ ጦላይ ወታደራዊ ካምፕ ተወስደው የነበሩ ከ1ሺህ በላይ የአዲስ አበባ ወጣቶች ዛሬ መለቀቃቸው ተገለጸ።
ለወጣቶቹ ስልጠና ተሰጥቶ መለቀቃቸውን የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ወደ ቤተሰቦቻቸው የማጓጓዝ ስራ መጀመሩን አስታውቋል
ከፍተኛ ተቃውሞ ያስነሳውና ህገመንግስታዊ መብቶችን የጣሰ ነው የተባለው የአዲስ አበባ ወጣቶች እስርን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ያለአግባብ የታሰሩ ከነበሩም ለለውጡ የከፈሉት መስዋዕትነት አድርገው እንዲመለከቱት ጠይቀዋል።
ወጣቶቹ ዛሬ ሲለቀቁ ሰላም ለሁላችንም ስለሆነች እንጠብቃት የሚል ጽሁፍ የታተመበት ቲሸርት እንዲለብሱ መደረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ከአንድ ወር በላይ በአደገኛ ሁኔታ በጦላይ የወታደራዊ ካምፕ ታፍሰው የተወሰዱት የአዲስ አበባ ወጣቶች ዛሬ መፈታታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
በኮሚሽኑ መግለጫ ወጣቶቹ ህገመንግስታዊና የህግ ጉዳዮች ላይ ስልጠና ከተሰጣቸው በኋላ መለቀቃቸው ገልጿል።

Wednesday, October 17, 2018

በህገወጥ መንገድ የገባና 20 ሚሊየን ብር የሚያወጣ እቃ ተያዘ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 12/2011) የደህንነት ካሜራዎችን ጨምሮ ለዲፕሎማቲክ አገልግሎት በሚል ሰበብ በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገባ 20 ሚሊየን ብር የሚያወጣ እቃ መያዙ ተነገረ።

የገቢዎች ሚኒስቴር  እንዳስታወቀው በሁለት ስማቸው ባልተጠቀሰ ኤምባሲዎች እና በአንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ስም በህገወጥ መንገድ ለዲፕሎማቲክ አገልግሎት በሚል የገቡ እቃዎች ተይዘዋል።

Ethiopia: OLF disarming residents in East and West Wollega

ESAT News (October 17, 2017)
Reports reaching ESAT say combatants of the Oromo Liberation Front (OLF), a separatist ethnic front, has been disarming non-Oromo residents in East and West Wollega.
Resident who spoke to ESAT said the OLF soldiers had confiscated their weapons that they said have owned legally. The residents said the administration in West Wollega has been taken over by the OLF soldiers and the Qeerroo, a vigilante youth network in the Oromo region.
Some residents flee their villages fearing attack by the OLF, according to information obtained by ESAT.
ESAT attempted to reach OLF representative in North America for comment, but to no avail.
Dawud Ibsaa, the leader of the separatist group admits in an interview with the VOA last week that he has armed soldiers in the south and west of the Oromo region although he did not say how many.

ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ የአርጎባ ብሄር ተወላጆች ከተጠለሉበት ትምህርት ቤት ተባረሩ። ለዜጎች መፈናቀል የወረዳ መስተዳሮች እጅ አለበት ተባለ።

( ኢሳት ዜና ጥቅምት 07 ቀን 2011 ዓ/ም ) ከኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ቦሌ እና በምስራቅ ሸዋ ዞን አዋሳኝ አካባቢዎች በማንነት ላይ ባነጣጠሩ ጥቃቶች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ቁጥራቸው ከ146 በላይ የሚሆኑ የአርጎባ ብሔር ተወላጆች አስታዋሽ አጥተን ለችግር ተዳርገናል አሉ። እስካሁንም በመንግስት በኩል በቂ ዕርዳታ እንዳልተደረገላቸው ጉዳተኞቹ ይናገራሉ። ተፈናቃዮቹ በጊዜያዊ መጠለያነት ተጠግተው ይኖሩበት ከነበረው የመልካ ጅሎ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ እንዲወጡም ተደርገው ቀይ መስቀል በሰጣቸው ጊዜያዊ መጠለያ ድንኳን ውስጥ ተጠልለዋል። ቀይ መስቀል ብርድ ልብስ፣ ውሃ መጠጫ እና አንድ ከረጭት ዱቄት ብቻ የረዳቸው ሲሆን የወረዳው መስተዳድር ለአንድ ቤተሰብ በነፍስ ወከፍ አንድ ሽህ ብር ብቻ ከመርዳት ውጪ ወደ ቀድሞ ይዞታቸው እንዲመለሱም ሆነ መልሶ ለማቋቋም ያደረገላቸው እገዛ የለም። ቤተሰቦቻቸው ከሚያደርጉላቸው እገዛ በተጨማሪ የአርጎባ ህዝቦች ድርጅት የ100 ሺህ ብር እርዳታ የለገሰ ሲሆን፤ የምንጃር ወረዳ ወጣቶች በበኩላቸው ከጎናቸው በመቆም አስፈላጊውን እገዛ አድርገውላቸዋል። መንግስት መጠለያ ቦታ እንደሚሰጣቸው ቃል ቢገባላቸውም ማረፊያ መጠለያን ጨምሮ ከመኖሪያቸው ባዶ እጃቸውን በመውጣታቸው የአልባሳት፣ የቁሳቁስ እና ምግም አላገኙም። በተለይም ሕጻናት ልጆች ያሏቸው ወላጆች ለተጨማሪ ጉዳቶች ተጋላጭ ሆነዋል። የሚመለከተው የመንግስት አካል ለችግራቸው በአፋጣኝ እልባት እንዲሰጣቸው ተማጽኖ አሰምተዋል። በአርሲ ቦሌ ለጠፈጠረው ችግሮች በአገር ሽማግሌዎች በኩል የማስታረቅ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን በምስራቅ ሸዋ በኩል ግን እስካሁን አልተደረገም። ተፈናቃዮቹን ወደ ነበሩበት ቦታ እንዲመለሱ ለማድረግ ጥረት ቢደረግም ሥጋት

በአፋር ክልል የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የወጡ ዜጎች በልዩ ሃይል አባላት ጥቃት ደረሰባቸው

( ኢሳት ዜና ጥቅምት 07 ቀን 2011 ዓ/ም ) የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችን አንግበው በሰመራ ከተማ ወደ አደባባይ በወጡ ዜጎች ላይ የልዩ ሃይል አባላት በወሰዱት እርምጃ ቢያንስ 8 ሰዎች በጥይት ቆስለው ዱብቲ ሆስፒታል መግባታቸውን ነዋሪዎች በስልክ ለኢሳት ገልጸዋል። የመከላከያ ሰራዊት ገብቶ ግጭቱን ማስቆሙም ታውቋል። የአፋር ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት የክልሉ መንግስት ሊለወጥ ባለመቻሉ በህዝቡ ላይ የሚደርሰው ችግር እየጨመረ እንጅ እየቀነሰ አልሄደም። የአፋር ዱከሂና ወጣቶች ክንፍ አባል የሆነው ሙሳ ሂኮ የተንዳሆ እና የቀሰም ቀበና የስኳር ፋብሪካዎች ሲተከሉ ቃል የተገባላቸውን አገልግሎት አለማግኘታቸውን ገልጿል። ወጣት ሙሳ ጥያቄዎቻችን ባለመመለሱ ኢትዮጵያዊነታችንን እየተጠራጠርን ነው ይላሉ። መንግስት የወጣቱን ድምጽ መስማትና ለጥያቄው አፋጣኝ መልስ መስጠት እንዳለበት በጅጅጋ የፖለቲካል ሳይንስና አለማቀፍ ግንኙነት መምህር የሆነው ሙሳ አደም ገልጿል፡፡ ወጣቶች ባቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ዙሪያ የአፋር ክልላዊ መንግስት ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በሚቀጥለው ዘገባችን ይዘን እንቀርባለን።

Tuesday, October 16, 2018

የአዲስ አበባ ወጣቶች እንዲፈቱ የተከፈተውን ዘመቻ ተከትሎ ሊፈቱ መሆኑ ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 6/2011)በጦላይ ወታደራዊ ካምፕ በስቃይ ላይ የሚገኙ የአዲስ አበባ ወጣቶች እንዲፈቱ የተከፈተውን ዘመቻ ተከትሎ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ላይ እንደሚፈቱ ተገለጸ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርጋዴር ጄኔራል ደግፌ በዲ ለቢቢሲ አማርኛው እንደገለጹት ከ1ሺህ በላይ የሚሆኑት ወጣቶች በዚህ ሳምንት መጨረሻ ይለቀቃሉ።
ኮሚሽነሩ ወጣቶቹ የታሰሩት በጎዳና ላይ ንብረት ሲያወድሙና ሁከት ሲፈጥሩ ነው ብለዋል።
ከአንድ ወር በላይ ሆናቸው። ክስ አልተመሰረተባቸውም። ፍርድ ቤትም አልቀረቡም። በጅምላ ታፈሰው፡ በየክፍለከተማው ፖሊስ ጣቢያ ለቀናት ቆይተው፡ በሰንዳፋ እንዲሰባሰቡ ከተደረጉ በኋላ ወዶ ጦላይ ተወሰዱ።

የካቢኔ አባላት ሹመት ጸደቀ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 6/2011)የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 16 የካቢኔ አባላትን ሹመት አጸደቀ።
በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ አቅራቢነት ሹመታቸው የጸደቀው ሚኒስትሮች ከኢሕአዴግና አጋር ድርጅቶች የተውጣጡ ሲሆን ከተለመደው አሰራር ብዙም የተለወጠ ነገር እንዳልታየበትም አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።
አራት ነባር ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከነሚኒስትርነታቸው በቀጠሉበት በአዲሱ ካቢኔ አዲስ የሰላም ሚኒስቴር በሚል ለተቋቋመው ተቋምም ሚኒስትር ተመድቦለታል።
28 የነበሩ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶችን ወደ 20 በሰበሰበው አዲሱ አወቃቀር የሰላም ሚኒስቴር በሚል ለተሰየመው ተቋም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በሚኒስትርነት ተሹመዋል።

በምዕራብ ወለጋ በሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች የኦነግ ታጣቂዎች ከቄሮና አባገዳዎች ጋር በመሆን በማስተዳደር ላይ መሆናቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ

 ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 06 ቀን 2011 ዓ/ም ) ኦነግ በሰየ ወረዳ ወየ ቡቡካ በሚባለው ቀበሌ ከጥቅምት 1 ቀን 2011 ዓም ጀምሮ የመንግስት ታጣቂዎችን እንዲሁም በአካባቢው ከ32 ዓመታት ላላነሰ ጊዜ የሰፈሩትን የአማራ ተወላጆች መንግስት ፈቅዶላቸው የያዙትን የነፍስ ወከፍ የጦር መሳሪያ፣ የወያኔ ታጣቀዊዎች ናችሁ በማለት ትጥቅ እያስፈታ መውሰዱን ነዋሪዎች ተናግረዋል። የኦነግን ጥቃት በመፍራት ጫካ የገቡ ሰዎች መኖራቸውንም ነዋሪዎች ገልጸዋል። አካባቢውን የኦነግ ታጣቂዎች፣ ቄሮዎችና አባ ገዳዎች በጋራ ተመራርጠው እያስተዳደሩት ሲሆን፣ የመንግስት አካላት በአካባቢው አለመኖራቸውን ተናግረዋል። መንግስት እርምጃ እንዲወስድ ለኦሮምያ ክልል ባለስልጣናት ቢያመለክቱም ጠብቁ የሚል መልስ ከማግኘት የዘለለ ምላሽ እንዳላገኙ ነዋሪዎች ገልጸዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን መልስ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

Monday, October 15, 2018

በአቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ፖሊስ የሚያደርገውን ምርመራ እንዲያጠናቅቅ ተጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 5/2011)የሰኔ 16ቱን የቦምብ ጥቃት አስተባብረዋል በሚል ወንጀል የተጠረጠሩት የብሔራዊ የመረጃና ደህንነት ባልደረባ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ፖሊስ የሚያደርገውን ምርመራ እንዲያጠናቅቅ ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ ቀጠሮ ሰጠ ፡፡
ፖሊስ ችሎቱ በፈቀደለት 10 ቀናት የሰው ምስክር መቀበሉን ብሎም ከመስሪያ ቤታቸው የተገኘው ቦምብ ለምርመራ መወሰዱንና ሌሎች ተግባራትን ማከናወኑን ጠቅሷል፡፡
ፖሊስ የቀድሞው የደህንነት ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ኡርጌን በተመለከተ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎትን  ለተጨማሪ የምርመራ ስራ 10 ቀናት እንዲፈቀደለት ጠይቋል፡፡
የሰኔ 16ቱን የቦምብ ጥቃት አስተባብረዋል በሚል ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በቡኩላቸው በቁጥጥር ስር ከዋሉ 4 ወራት መቆጠሩንና ፖሊስ የሚጠይቃቸው የግዜ ቀጠሮዎች ተገቢነት የላቸውም በማለት ቅሬታችውን አቅርበዋል፡፡

ብርጋዴር ጄኔራል ሃይሉ ጎንፋ ተሾሙ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 5/2011) ብርጋዴር ጄኔራል ሃይሉ ጎንፋ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ።
በሳምንቱ መጨረሻ ብርጋዴር ጄኔራል ከማል ገልቹና ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ የኦሮሚያና የአማራ ክልሎች የጸጥታ ከፍተኛ ሃላፊዎች ሆነው መሾማቸው ይታወሳል።
በምርጫ 1997 በኢትዮጵያውያን ላይ የተካሄደውን ጭፍጨፋ በመቃወምና፣የምርጫውን መጭበርበር በማውገዝ ሰራዊት ይዘው ወደ ኤርትራ የገቡት ብርጋዴር ጄኔራል ከማል ገልቹ የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደርና ጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ ሆነው በሳምንቱ መጨረሻ መሾማቸው ተሰምቷል።
ከእሳቸው ጋር በተመሳሳይ ሰራዊቱን አስከትለው ኤርትራ የገቡት ሌተናል ኮሎኔል አበበ ገረሱ የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሆነው መሾማቸው ተመልክቷል።
በነሐሴ ወር 1998 ሰራዊት አስከትለው ኤርትራ የገቡትን ሁለት ከፍተኛ መኮንኖች በመከተል በተመሳሳይ የመንግስትን የአፈናና የግድያ ድርጊት በማውገዝ በመስከረም 1999 ኤርትራ የገቡት ብርጋዴር ጄኔራል ሃይሉ ጎንፋ የኦሮሚያ ክልል የፖሊስ ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።

ሰራዊቱ ያሉበትን ችግሮች ለመቅረፍ የማሻሻያ ርምጃዎች በመውሰድ ላይ ናቸው

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 5/2011)የኢትዮጵያ ሰራዊት ያሉበትን ችግሮች ለመቅረፍ በየደረጃው የማሻሻያ ርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆናቸውን ጄኔራል ሰአረ መኮንን ገለጹ።
ወደ ቤተመንግስት የተጓዙትን የሰራዊቱን አባላት ድርጊት ጋጠወትና ጸረ ሕገ መንግስት በማለት የጠቀሱት ጄኔራል ሰአረ መኮንን ከድርጊቱ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ አመራሮቹ መታሰራቸውን ገልጸዋል።
አስተማሪ የሆነ ርምጃ እንደሚወስድም ቃል ገብተዋል።
ባለፈው ሳምንት ረቡዕ መስከረም 30/2011 ወደ ቤተመንግስት የተንቀሳቀሱት የአጋዚ ክፍለ ጦር አባላት መሆናቸውን የገለጹት ጄኔራል ሰአረ መኮንን ይህው ሃይል በሶማሌ ክልል የተፈጠረውን ችግር ለማረጋጋት እዚያው መቆየቱን አስታውሰዋል።
አዲስ አበባና አካባቢዋ ከተፈጠረው አለመረጋጋት ጋርም በተያያዘ ይህው ሰራዊት ግዳጅ ውስጥ መቆየቱን የገለጹት ጠቅላይ ኢታማጆር ሹም ጄኔራል ሰአረ መኮንን ያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ወደ ስድስት መቶ የሚሆኑ ሶማሊያውያን የተገደሉበት አንደኛ ዓመት ሢታሰብ ተከሳሹ በአደባባይ እንዲወገድ ተደረገ። በአዲስ አበባና በሶማሊያ ከአርባ ዓመት በኋላ በረራ የተጀመረ ሲሆን፣ በዕለቱ አልሸባብ ጥቃት ፈጽሟል።

( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) በሶማሊያ ታሪክ አሰቃቂውን የቦምብ ፍንዳታ በመፈጸም ስድስት መቶ ለሚጠጉ ሰላማውያን ዜጎች ሞት ምክንያት የሆነው ሀሰን አዳን ይስሀቅ ትናንት የሟቾቹ አንደኛ ዓመት ሲከበር በአደባባይ እንዲወገድ ተደርጓል። ሀሰን አዳን ልክ የዛሬ ዓመት ነበር ከፍተኛ ተቀጣጣይ ቦምብ የተጠመደበት የኪራይ የጭነት መኪና እያሽከረከረ ሰው ወደሚበዛበት የሞቃዲሾ ጎዳና በመግባት ፍንዳታውን የፈጸመው። ጥቃቱን አስመልክቶ እስካሁን ኃላፊነቱን የወሰደ ቡድን ባይኖርም፣ ሀሰን አዳን ቀደም ሲል የአልሸባብ ሚሊሻዎች መሪ ከመሆኑ አኳያ ከጥቃቱ ጀርባ ቡድኑ ሳይኖር እንደማይቀር ይታመናል። በፍንዳታው ውዶቻቸውን ካጡት ሶማሊያውያን መካከል የስድስት ህጻናት ልጆች እናት የሆነችው ፎዊሳ ሳላህ ኡስማን አንዷ ነች። የፎይሳ ባለቤት ወይም የስድስቱ ህጻናት አባት አስከሬን እንደሌሎቹ ሰለባዎች ሁሉ አልተገኘም።በከፍተኛው ፍንዳታ ወደ ፍርስራሽነት ተቀይሯል። ፎይሳ ውዷን ካጣች ዓመት ቢቆጠርም፣ መጽናናትን እምቢ አንዳለች ነው። ትናንት በመኖሪያ ቤቷ ተገኝተው ላነጋገሯት የቢቢሲ ጋዜጠኞች፦“አሁንም በጥልቅ ሀዘን ላይ ነኝ።ልቤ እንደተሰበረ ነው።ምንም ነገር መሥራት አልችልም” ስትል እያለቀሰች ተናግራለች። የተከሳሽ ሀሰን አዳን ይስሀቅን ጉዳይ ሲከታተል የነበረው ፍርድ ቤት ባሳለፈው ውሳኔ መሰረትም፣ ተከሳሹ በትናንትናው ዕለት -የገደላቸው ሰላማውያን የሙት ዓመታቸው

የዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች ተገቢውን ትምህርት ማግኘት ባለመቻላቸው ትምህርታቸውን አቋረጡ።

( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) በዓዲግራት ዩንቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች በተቋሙ አስተዳደር ለሚደርስባቸው አስተዳደራዊ በደሎች መፍትሄ እንዲሰጣቸው በተደጋጋሚ ጊዜያት ቢጠይቁም ምላሽ ማግኘት አልቻሉም። ይህን ተከትሎ ትምህርታቸውን በተገቢው ሁኔታ መከታተል ባለመቻላቸው ለማቋረጥ መገደዳቸውንና አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጠን ሲሉ ለጤና ጥበቃ ሚንስቴር በደብዳቤ አሳውቀዋል። የመማር ማስተማሩ አስመልክቶ በጻፉት ደብዳቤ ላይ እንዳሉት የ6ኛ ዓመት ተማሪዎች ባለፉት 9 ወራት ብቻ ለ5 ወራት ከመማር ማስተማር ውጪ ነበሩ። የ5ኛ እና የ4ኛ ዓመት ተማሪዎች /በበኩላቸው በተመሳሳይ ተገቢውን የመማር እድል በማጣታቸው ከተመሳሳይ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ወደኋላ ቀርተዋል። ዩንቨርሲቲው በበኩሉ የአስተማሪ ስፔሻል ሃኪሞች እጥረት፣ ያሉትም ጥቂት ስፔሻሊስት ሃኪሞች የሥራ መደራረብና የደመወዝና የጥቅማጥቅም መብት አለመከበር፣ ከሌሎች ዩንቨርሲቲዎች የሚያመጣቸው የተጋባዥ መምህራን ጋር በተመሳሳይ የደመወዝና በጥቅማጥቅም ጉዳይ አለመስማማት ያስከተለው የተጋባዥ መምህራን እጥረት፣ ዩንቨርሲቲው የራሱ የሆነ የማስተማሪያ ሆስፒታል የሌለው ሲሆን የዓዲግራት ጠቅላላ ሆስፒታልም ከተማሪዎቹ ቁጥር ጋር የሚመጣጠን አለመሆኑ፣ በሆስፒታሉ በቁጥርም ይሁን በዓይነት በቂ የሆነ ታካሚዎች አለመገኘትን፣ በሆስፒታሉ በቂ የሆነ የህክምና መገልገያ እና የማስተማሪያ ቁሳቁስ አለመኖር፣ የተመደበለትን በጀት በራሱ ማንቀሳቀስ አለመቻሉን በምክንያትነት አቅርቧል። የዩንቨርሲቲው አስተዳደር ተማሪዎቹ የሚያቀርቡትን ጥያቄዎች ያለመቀበል፤ ወይም ከተቀበሉ በኋላ መፍትሔ ያለመስጠት፣ ለህክምና ትምህርት የሚሰጡት በጀት ማሳነስና ለችግሮቹ ትኩረት ያለመስጠትና በመጠናቸው ልክ አለመረዳትና በቸልተኝነት በማለፍ ችግሮቹ እንዲባባሱ አድርገዋል። የሕክምና ትምህርት ከፍተኛትኩረት የሚሻ የትምህርት መስክ በመሆኑ መንግስት ትኩረት በመስጠት ለጥያቄያቸው መፍትሔ እንዲሰጠን ሲሉ ለጤና ጥበቃ ሚንስቴር እና በግልባጭ ለዓዲግራት ዩንቨርስቲ ቦርድ፣ ለዓዲግራት ዩንቨርስቲ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት፣ ለዓዲግራት ዩንቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እናለ ዓዲግራት ዩንቨርስቲ ሕክምና ትምህርት ቤት በደብዳቤ አሳውቀዋል።

የቀደሞው የመረጃና ደህንነት ሰራተኛ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠባቸው።

( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ለጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ በተዘጋጀው የድጋፍና የምስጋና ሰልፍ ወቅት የተፈጸመውን የሽብር ድርጊት አቀነባብረዋል ተብለው ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር በዋሉት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ተሰጠ። ባለፈው ቀጠሮ አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ቤት ውስጥ የተገኘውን ቦምብ እና በመስቀል ዓደባባይ ከፈነዳው ቦምብ ቅሪት አካል በማመሳከር አጠናቆ ለማቅረብ የአስር ቀናት ቀጠሮ መውሰዱ ይታወሳል። ነገርግን መርማሪ ፖሊስ በተሰጠው ቀናት ውስጥ የቴክኒክ ምርመራውን ማጠናቀቅ አለመቻሉን ለችሎቱ በመግለጽ ተጨማሪ የአስር ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ለችሎቱ አመልክቷል። ተጠርጣሪው አቶ ተስፋዬ ኡርጌ በበኩላቸው ፍርድ ቤቱ ለመርማሪ ፖሊስ ተደጋጋሚ የምርመራ ጊዜ ተሰጥቶታል። የዛሬውም የመጨረሻ ቀጠሮ ተብሎ ነበር። መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መጠየቅ አይገባውም። በተጨማሪም አቶ ተስፋዬ ኡርጌ የፍርድ ቤቱን ሂደት በአካል ቀርበው ሳይከታተሉ የስም ማጥፋት ወንጀል የፈጸሙብኝ የመገናኛ ብዙሃን ላይ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድልኝ ሲሉ ለችሎቱ አቤቱታቸውን አሰምተዋል። ፍርድ ቤቱ በበኩሉ የከሰሳሽ መርማሪ ፖሊስን እና የተከሳሽን ቃል ካዳመጠ በኋላ የተዛባ መረጃ ለህዝብ ማቅረብ በህግ እንደሚያስጠይቅ በመግለጽ፤ ይህን በሚፈጽሙት ላይ ሕጋዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል ብሏል። ለመርማሪ ፖሊስ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ፖሊስ የጠየቀውን የአስር ቀናት ቀነ ቀጠሮ ውድቅ በማድረግ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ በመፍቀድ ለጥቅምት 12 ቀን 2011 ዓ.ም ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በአማሮ ወረዳ 3 የ መከላከያ ሰራዊት አባላት በታጣቂዎች ተገደሉ

( ኢሳት ዜና ጥቅምት 05 ቀን 2011 ዓ/ም ) የአካባቢው ነዋሪዎች በሰራዊቱ አባላት ላይ ጥቃት የፈጸሙት የኦነግ ታጣቂዎች ናቸው ቢሉም፣ በመንግስት በኩል እስካሁን የተሰጠ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የለም። የግድያው መንስዔ ላለፉት 16 ወራት የዘለቀው በአማሮ ወረዳ የሚካሄደው በጉጂና በኮሬ ማህበረሰቦች መካከል ያለው ግጭት እንደገና በማገርሸቱ ነው። ባለፈው አርብ በስራ ላይ በነበሩ የኮሬ ተወላጆች ላይ በተፈጸመ ጥቃት አንድ የ10 አመት ታዳጊ ወጣት ሲገደል 2 ሌሎች አርሶአደሮች ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ ቆስለዋል። ግጭቱ በዳኖ ቀበሌም ቀጥሎ በኮሬ በኩል አቶ ጌዲዮን ሊባ እና ኢለሙሳ አየለ የተባሉት ግለሰቦች የቆሰሉ ሲሆን፣ ግጭቱን ለማብረድ ጣልቃ በገቡት የመከላከያ አባላት ላይ በደረሰ ጥቃት 2 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወዲያውኑ ሲገደሉ፣ አንደኛው ደግሞ ቆስሎ በህክምና ላይ እያለ ህይወተሩ አልፏል። ሌላ አንድ ወታደርም በከባድ ሁኔታ ቆስሎ ሆስፒታል ተኝቷል። የመከላከያ ሰራዊት በወሰዱት የአጸፋ እርምጃ ሁለት የታጠቁ ሃይሎች መገደላቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል። የመከላከያ አባላቱ የቀብር ስነስርዓት ዛሬ ተፈጽሟል። በቡርጂና ጉጂ ብሄረሰቦች መሃል በተደረገው የተኩስ ልውውጥም እንዲሁ በቡርጂ በኩል አንድ አርሶ አደር በከፍተኛ ሁኔታ ቆስሏል። ከአማሮ ዲላ፣ ከቡርጂ ሃገረማርያም የሚወስዱ መንገዶች ለአመት ከአራት ወር ያክል በመዘጋታቸዉ የሁለቱም ወረዳ ህዝቦች በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰቃዩ ነው። የመከላከያ ኢታማዦር ሹሙ ጄ/ል ሳዕረ መኮንን ሰራዊታቸው በአካባቢው ተሰማርቶ ጸጥታ እያስከበረ እንደሚገኝና ይህ ሰራዊት ወደ ቡራዩ፣ አዲስ አበባና በሶሚሊ እና ኦሮምያ ድንበሮች አካባቢ ተልዕኮ ግዳጁን ሲወጣ እንደነበር ገልጸዋል።

Friday, October 12, 2018

በራያ ህዝብ ላይ የሚደርሱት የመብት ጥሰቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። አሁንም 23 ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ናቸው።

 ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም )ካለ ሕዝብ ፈቃድ ከወሎ ክፍለሃገር ተወስዶ ወደ ትግራይ እንዲካለሉ የተደረጉት ራያዎች በተደጋጋሚ ጊዜያት የሚያነሱትን የማንነት ጥያቄዎች ለማዳፈን በትግራይ ክልል የሚደርስባቸው መጠነ ሰፊ የመብት ጥሰቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። በአዲሱ ዓመት የትምህርት ዘመን ህገ መንግስቱ የሰጠን መብት ይከበርልን፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋችን እንድንማር ይፈቀድልን ያሉ 23 ትምህርት ቤቶች በህዝባዊ ተቃውሞ ምክንያት እንደተዘጉ ናቸው። የእነሱን ፈለግ በመከተል ሌሎች ትምህርት ቤቶችም ይዘጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የራያን ህዝብ የማንነት ጥያቄዎች ለማዳፈን በማኅበረሰቡ ውስጥ ታዋቂ የሆኑ፤ በትግራይ ክልል ውስጥ በተለያዩ የስራ ዘርፎች የተሰማሩ የራያ ተወላጅ የሆኑ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን በመጠቀም ማንነት ጥያቄውን በትግራይ ክልል ውስጥ በማድረግ የወረዳ ጥያቄዎችንም ጭምር እንመልሳለን። የሚሉ መረጃዎችን በማሰራጨት የኅብረተሰቡን የማንነት ጥያቄ በልዩ ዞን ለማስመሰልና ጥያቄውን ለማፈን ሙከራ እየተደረገ ነው። የኅብረተሰቡ ጥያቄ በትግራይ ክልል ውስጥ የልዩ ዞንና የወረዳ ጥያቄ ሳይሆን፤ የማንነት ጥያቄው በታሪክም፣ በትውልድም፣ በስነልቦናም፣ ከምንተሳሰረው ህዝብ ጋር የመኖር ጥያቄ ነው። የልዩ ዞን በትግራይ ክልል ተመለሰ አልተመለሰ ኅብረተሰቡ በዛ አይስማማም። በምንም ዓይነት በየትኛውም አስተዳደር ቢሆን በምንም መስፈርት በየትኛውም ዓይነት የአስተዳደር እርከን ከዛ ክልል ጋር የመኖር ጥያቄ ሳይሆን ከማንነቱ ጋር ከሚተሳሰረው የወሎ ህዝብ ጋር የመቀላቀል ጥያቄ መሆኑን የራያ ሕዝብ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አገዘው ሕዳሩ አስታውቀዋል።

አርበኞች ግንቦት7 በሃረር ከተማ ስብሰባ እንዳያካሂድ ተከለከለ

 ( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም )ክልሉ ለድርጅቱ መስከረም 18 ቀን 2011 ዓም በጻፈው ደብዳቤ “ በጸጥታ ምክር ቤት ጉዳዩ ታይቶ በክልሉ ባለው ሃገራዊ ሁኔታ አንጻር ተገምግሞ የተጠየቀው ፍቃድ አለመፈቀዱን እንገልጻለን” ብሎአል። ክልከላውን በማስመልከት ልክልሉ ም/ል ፕሬዚዳንት አቶ ጋቢሳ ተስፋዬና ለጸጥታ ክፍል ሃላፊው አቶ አበበ መብራቱ ስልክ በተደጋጋሚ ብንደውልም ሊመልሱልን አልቻሉም። የአርበኞች ግንቦት7 የአመራር አባል የሆኑት አቶ አበበ ቦጋለ በሰጡን አስተያየት፣ ክልሉ የጣለው እገዳ የተጀመረውን ለውጥ የሚያጨልም ተደርጎ መታየት የለበትም ያሉ ሲሆን፣ አገሪቱ ሽግግር ላይ ስላለች አንዳንድ ቦታ ላይ ለውጡን ለመቀልበስ የሚፈልጉ ሃይሎች ሴራ መሆኑን በመረዳት ከክልሉ አስተዳደርና ከፌደራል መንግስቱ ጋር እየተነጋገርን አገር የማረጋጋት ስራ እንሰራለን ብለዋል። ክልከላው በአርበኞች ግንቦት7 ላይ ብቻ ለምን ሆነ? ሌሎች ድርጅቶችስ ለምን አልተከለከሉም በማለት ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ “ድርጅቱ የሚከተለው የፖለቲካ አስተሳሰብ ባለፉት 27 አመታት ሲራመድ ከነበረው አስተሳሰብ ጋር የተለዬ በመሆኑ የተፈጠረ ድንጋጤ” ሊሆን ይችላል ብለዋል። አርበኞች ግንቦት 7 ቅዳሜ ጥር 3 በአዳማ የድጋፍና የውይይት ፕሮግራም እንደሚያካሂድ ታውቋል።

በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አረፉ

( ኢሳት ዜና ጥቅምት 02 ቀን 2011 ዓ/ም ) ነዋሪነታቸው በደቡብ አፍሪካ ጆበርግ ከተማ ውስጥ የበረው አንጋፋው አገር ወዳድ ሼህ ወርቁ ኑሩ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት ተሳታፊ የነበሩት ሼህ ወርቁ ኑሩ በደቡብ አፍሪካ ስደተኞች ተወዳጅና አሰባሳቢ አባት ነበሩ። በኢትዮጵያ የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የሰብዓዊ መብት መጣስን፣ የህወሃት/ኢህአዴግ አፈና በዜጎች ላይ ሲያደርስ የነበረውን ሰቆቃ በማውገዝ የዜጎች መብት እንዲከበር ሳይሰለቹ ድምጻቸው ከሚያሰሙት የሃይማኖት አባቶች መሃከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። የኢሳት ዝግጅት ክፍል ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እንገልጻለን።

Thursday, October 11, 2018

መንግስት ኦነግን ትጥቅ ያስፈታል ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 30/2011) መንግስት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲል ኦነግን ትጥቅ ለማስፈታት እንደሚገደድ የኢትዮጵያ መንግስት አስታወቀ።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ዛሬ በሰጡት መግለጫ መንግስት የታጠቁ ሃይሎች በሃገር ውስጥ እንዲንቀሳቀስ በማድረግ ሁለት መንግስት እንዲኖር አይፈቅድም ብለዋል።
ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ለማድረግ የወሰነ ሃይል በመሳሪያ ጭምር እንደማይንቀሳቀስ የገለጹት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ ኦነግ ትጥቅ ለመፍታት አልተስማማንም የሚለውን አቋሙን እንዲመረምር የአፍ ወለምታም ከሆነ ይህንኑ እንዲያርም ጥሪ አቅርበዋል።
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ወደ ሃገር ቤት ሲገባ በቦሌም ሆነ በዛላ አምበሳ የገቡት አባላትና አመራሮቹ ያለትጥቅ መግባታቸውን ያስታወሱት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ካሳሁን ጎፌ የትኛውም የፖለቲካ ሃይል መሳሪያ ይዞ እንዲንቀሳቀስ እንደማይፈቀድም አስታውቀዋል።
የተመለሱት የኦነግ ወታደሮች በመንግስት እጅ ሆነው በስልጣን ላይ መሆናቸውንም አመልክተዋል።

በሃዋሳ አሮጌው ገበያ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በእሳት ወደመ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 30/2011) በአዋሳ ከተማ የሚገኘው አሮጌው ገበያ ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ወደመ።
በገበያው የተነሳውን እሳት ለማጥፋት የከተማው ማዘጋጃ ቤት የእሳት አደጋ ሰራተኞች በስፍራው የደረሱት እሳቱ ከተነሳ ከ1 ሰአት ተኩል በኋላ መሆኑም ታውቋል።
ከአዋሳ ከተማ መቆርቆር ጋር አብሮ እንደተመሰረት የሚነግርለት ገበያ በከተማው አዲስ የገበያ ስፍራ በመመስረቱ አሮጌው ገበያ በመባል ይጠራል።
በዚህ ስፍራ ለረጅም ዘመናት በንግድ ስራ የተሰማሩ የከተማው ነዋሪዎች ሀብት ንብረት አፍርተው ኖረዋል።
እድሜ ልክ  ያፈሩትን ንብረት ግን በአንድ ሌሊት ማጣታቸው ትልቅ ሀዘን ሆኖባቸዋል።
እሳቱ ከምሽቱ አንድ ሰኣት አካባቢ  ከፍራሽ ተራ እንደተናሳ የተገለጸ ሲሆን ፣ ልብስና ጫማ መሸጫ መደብሮች በተለምዶ ታይዋን ተራ፣ጥራጥሬ መሸጭ፣የባህል አልባሳት መሸጫ፣ አትክልት ተራ መደበሮች ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ታውቋል።
የወደመው ንብረት ግምቱ ምንያህል እንደሆን ነዋሪዎች በዚህ ሰዓት ማወቅ እንዳልቻሉ ተናግረዋል።
የከተማው ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት የከተማው ማዘጋጃ ቤት እሳቱን ለማጥፋት ያደረገው ሙከራ እጅግ ደካማ እንደነበር ገለጸዋል።
ጨምረውም  የእሳት አደጋ ባለሙያዎቹ አደጋው ከደረሰ በኋላ የተገኙት ከተለያዩ መጠጥ ቤቶች ሲሆን በወቅቱም ሰክረው እንደነበር ጠቅሰዋል።

የአዲስ አበባ ወጣቶች ከጦላይ ማሰልጠኛ ሊወጡ ነው።

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 30/2011)ከአዲስ አበባ ከተማ የታፈሱትና ወደ ጦላይና ሌሎች ማሰልጠኛዎች የተወሰዱት ወጣቶች ስልጠናቸውን ጨርሰው በቅርቡ እንደሚወጡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ወጣቶቹ የተያዙት ፖሊስ ላይ ድንጋይ ሲወረውሩና ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ ናቸው ብለዋል።
አንድም የታሰረ ወጣት የለም ያሉት ኮሚሽነሩ ወጣቶቹ የተያዙት እንዲታሰሩ ሳይሆን ከህገወጥ ተግባር እንዲወጡና ስለህግ የበላይነት ስልጠና እዲያገኙ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የአዲስ አበባ ወጣቶች የተያዙት ፖሊስ ላይ ድንጋይ በመወርወ፣ መሳሪያ ለመንጠቅና በተለያዩ ወንጀሎች ላይ በመሞከራቸው ነው።

Wednesday, October 10, 2018

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጥሪ አቀረበ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 28/2011) በኢትዮጵያ በተለያዩ ቦታዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች  ድጋፍ ለማድረግ እንዲቻል የህብረተሰቡ እገዛ ያስፈልገኛል ሲል  የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጥሪ አቀረበ ።ከ90ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖች ከ523 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልግም ተመልክቷል።
በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ትናንት በነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ማህበሩ ባለፋት ጊዜያት በርካታ  ድጋፎች ቢያደርግም የገንዘብ እጥረት ገጥሞኛል ብሏል።
እናም ሕብረተሱ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል ፡፡
በእለቱም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር  ለአንድ አምቡላንስ መግዣ የሚውል  የ1.2 ሚሊየን ብር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡

የትሕዴን ወታደሮች ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ላይ ናቸው

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 28/2011)ከ2ሺህ በላይ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ትሕዴን/ ወታደሮች ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ላይ መሆናቸው ተገለጸ።
ወታደሮቹን ጭነው ከሚጓዙ ከባድ ተሽከርካሪዎች አንዱ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ ሶስት ወታደሮች መሞታቸው ታውቋል በኢትዮጵያ መንግስትና በትህዴን መካከል በቅርቡ አስመራ ላይ ውይይት መደረጉን ተከትሎ በዛሬው እለት በዛላምበሳ ለገቡት ወታደሮች አቀባበል እንደሚደረግ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በ1993 ዓመተምህረት የተመሰረተው የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ትህዴን በትጥቅ ትግል 19ዓመታትን ቆይቷል።
የመጀመሪያ መሪውን በግድያ ሁለተኛውን በኩብለላ ያጣው የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ትህዴን የህወሀትን አገዛዝ በመሳሪያ ትግል ለማስወገድ የተቋቋመ እንደሆነ ይገልጻል።
ህወሀት ለህዝብ የገባውን ቃል በማጠፍ ጭቋኝ ስርዓት ሆኗል በሚል ጫካ የገቡት የትህዴን ታጋዮች በኢትዮጵያ እኩልነት እንዲሰፍንና የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ የሚያስችል ትግል እያካሄደ እንደነበረ ንቅናቄው ካሰራጫቸው ጽሁፎች መረዳት ይቻላል።
ሁለተኛው መሪው ሞላ አስገዶም ከህወሀት ደህንነቶች ጋር በመሆን የተወሰኑ ወታደሮችን ይዘው ወደ ኢትዮጵያ መኮብለላቸው የሚታወስ ነው።

የምርጫ ሕግ ማሻሻያ ረቂቅ ሕግ ለውይይት ቀረበ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 29/2011) የኢትዮጵያን የምርጫ ሕግ ለማሻሻል የተዝዘጋጀው ረቂቅ ሕግ ለውይይት ቀረበ።
የምርጫ ቦርድ አባላት ከተቃዋሚዎችና ከገዢው ፓርቲ በእኩል መጠን ይሳተፉበታል የተባለው ረቂቅ ሕግ ቅሬታዎችን የሚያስተናግድ የምርጫ ፍ/ቤት እንደሚቋቋም ያስረዳል።የፍርድ ቤቱ ተግባር ከምርጫ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን የሚመረምርና ምላሽ የሚሰጥ እንደሆነም ተመልክቷል።
አዲስ የተረቀቀውና ለውይይት የቀረበው የምርጫ ሕግ ማሻሻያ ሰነድ የሃገሪቱን የምርጫ ስነ-ስርዓት መቀየርን ጭምር ታሳቢ ያደረገ እንደሆነ ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ የተገኘው መረጃ ያመለከታል።
የሃገሪቱን የምርጫ ስርዓት ለመለወጥ ሕገ-መንግስቱን ማሻሻል ጭምር እንደሚያስፈልግ የታወቀ ቢሆንም የቀረበው ረቂቅ ሕግ እስከ ሕገ-መንግስት ማሻሻያ የዘለቀ እንደሆነም ተመልክቷል።

Ethiopia: Scaffolding on Lalibela rock-hewn churches damages structure

ESAT News (October 9, 2018)
Scaffolding erected ten years ago at the site of UNESCO heritage rock-hewn churches of Lalibela is causing structural damages to the historic site, priests and residents of the tourist town said.
The priests and residents of Lalibela who took to the streets on Sunday to vent their concern said the scaffolding that was put together for the purpose of protecting the historic site from natural disasters was actually causing more damages to the rock-hewn churches.
The residents say they have communicated their concerns to authorities but nothing has been done to reverse the damages being done on the churches.

በጅግጅጋ ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ንብረታቸው የወደመባቸው ባለሃብቶች የካሳ ጥያቄያቸው እስካሁን መልስ አለማግኘታቸውን ገለጹ

( ኢሳት ዜና መስከረም 29 ቀን 2011 ዓ/ም ) ከ300 በላይ የሚሆኑትና በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ አሌ እንደመሩት በሚታመነው ግጭት ንብረታቸው የወደመባቸው የከተማዋ ነጋዴዎች፣ በአጠቃላይ ከ700 ሚሊዮን ብር ያላነሰ ካሳ ከመንግስት ይጠብቃሉ። መንግስት ካሳ ለመስጠት ፈቃደኛ ቢሆንም፣ እስካሁን ድረስ መልስ ባለማግኘታቸው ለከፍተኛ ችግር መደረጋቸውን ነጋዴዎች ገልጸዋል። በጉዳዩ ዙሪያ አዲስ የተቋቋመውን የክልሉን አስተዳደር ባለስልጣናት ለማናገር ብንሞክርም አልተሳካልንም።

በቄለም ወለጋ ወረዳ የተለያዩ የገጠር ቀበሌዎች ኦነግ እንደሆኑ የሚገልጹ ወታደሮች ነዋሪዎችን የግል የጦር መሳሪያዎችን እንዲያስረክቡና ገንዘብም እንዲሰጡ እያስገደዱ ነው

( ኢሳት ዜና መስከረም 29 ቀን 2011 ዓ/ም ) ኢሳት ያነጋገራቸው በቄለም ወለጋ ደምቢዶሎ አካባቢ ፣ በሰዮ ወረዳ፣ ወልጋይ፣ ቢቢካና ቀስሪ መንደሮች የሚኖሩ በ1977 ድርቅ ወቅት ከወሎ የተለያዩ አካባቢዎች ሄደው የሰፈሩና በአካባቢው ለአመታት የኖሩ ዜጎች ፣ በአካባቢው የሚንቀቀሳቀሱ ወታደሮች፣ “ከአሁን በሁዋላ አካባቢውን የሚያስተዳድረው ኢህአዴግ ሳይሆን እኛ ነን፣ ኢህአዴግን አናውቀውም፤ የግል የጦር መሳሪያ ያላችሁ፣ መሳሪያችሁን አስረክቡ፣ ገንዘብም ክፈሉ” እያሉ እንደሚያስገድዱዋቸው ገለጸዋል። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት የቀበሌ አስተዳደሩን የኦነግ ታጣቂዎች ተረክበው እየሰሩ ሲሆን፣ የኦዴፓ መሪዎች በአካባቢው ባለመኖራቸው የደህንነት ስጋት ገጥሟቸዋል። መንግስት እውቅና ሰጥቶን ለረጅም ጊዜ የታጠቅነውን የነፍስ ወከፍ መሳሪያ አስርከቡ መባላቸውን የተቃወሙት ነዋሪዎቹ፣ መንግስት ፈቅዶ የታጠቅነውን መሳሪያችሁን አስረክቡ ቢለን ለማስረከብ ፈቃደኞች ነን ብለዋል። የኦነግ ወታደሮች ህዝቡን እየሰበሰቡ ኢህአዴግ እንደማያውቁትና ማንኛውንም ነገር ለኦነግ ወታደሮች እየነገሩ መፍትሄ እንደሚያገኙ እየተናገሩ መሆኑንም ያነጋገርናቸው በርካታ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በአካባቢው የመከላከያ ሰራዊትም ሆነ የመንግስት ሹም አለመኖሩን፣ ትናንት ምሽት የቀበሌውን አስተዳደሪ ይዘው በመምጣት መሳሪያ አላችሁ ወይ እያሉ ሲጠይቁ ማምሸታቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የኦዴፓ የገጠር ዘረፍ ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ኦነግ ትጥቁን ካልፈታ መንግስት ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ በፌስቡክ ገጻቸው ላይ መጻፋቸው ይታወቃል። ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ትናንት ፓርላማውን ሲከፍቱ ባሰሙት ንግግርም፣ መንግስት ህግን ለማስከበር ጠንካራ እርምጃ መውሰድ እንደሚጀመር ገልጸዋል። የኢህአዴግ ጉባኤ ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድን በድጋሜ መሪ አድርጎ በመረጠበት ወቅት ጠ/ሚኒስትሩ ባሰሙት ንግግር መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር የተጠናከረ እርምጃ

Monday, October 8, 2018

Ethiopia to issue visa on arrival to Africans

ESAT News (October 8, 2018)
Ethiopia says it will meet the deadline set by the African Union for African travelers to get visa on arrival instead of applying prior to their trip.
The African Union has set a goal for a visa free travel within the continent by 2020.
Seychelles is so far the only country that requires no visas to all Africans.
Speaking at the opening of a bicameral parliament, President Mulatu Teshome says the country would strive to meet the deadline for a visa free Africa which he said help create continental unity.
The President said a visa free travel will also help boost the country’s tourism by increasing the volume of travelers to the country

በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የቤት መስሪያ ብድር ሊሰጥ ነው

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 28/2011)የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የቤት መስሪያ ብድር ለመስጠት መወሰኑን ገለጹ።
የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ ባጫ ጊኒ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደምበኞቹን ለማገልገልና እራሱንም ለማሳደግ በስፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመላ ሃገሪቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቅርንጫፍ ባንኮች ያሉት ግዙፍ የገንዘብ ተቋም ነው።
የባንኩ አጠቃላይ ካፒታል ከ3 መቶ ቢሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ነው የሚነገረው። በሃገሪቱ ካለው አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ 67 በመቶው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገኛል።
በመላ ኢትዮጵያ ከተሰጡ ብድሮች ደግሞ ንግድ ባንኩ 53 በመቶውን ይሸፍናል።
እናም በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ የመጣው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ የጀመሩትን የኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት በማድረግ ለዲያስፖራው የቤት መስሪያ ብድር አመቻቻለሁ ብሏል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ባጫ ጊና ሰሞኑን ከዲያስፖራው አባላት ጋር ባካሄዱት ውይይት ባንኩ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለቤት መስሪያ የሚሆን ብድር ይመቻችላቸዋል ብለዋል።

በቡራዩ ተፈጸመውን ወንጀል ያቀነባበሩ ግለሰቦች በአሸባሪነት ተከሰሱ

(ኢሳት ዲሲ–መስከረም 28/2011) በቡራዩ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ ያቀነባበሩና የፈጸሙ ግለሰቦች በአሸባሪነት መከሰሳቸው ታወቀ።
ግለሰቦቹ በአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ከቡራዩ በመጡ ወጣቶች መካከል ግጭት እንዲከሰት በተለይ ፓስተር በተባለው የአዲስ አበባ አካባቢ መንቀሳቀሳቸውን አቃቤ ሕግ ገልጿል።ከቡራዩ የመጡትን ወጣቶች በማደራጀትና ሽጉጥ በመተኮስ ግጭት እንዲከሰት ማድረጋቸውን በፍርድ ቤት የቀረበው ክስ ያስረዳል።
በተጠርጣሪዎቹ ቤት 74 ገጀራና ቢላዋ መገኘቱም ተመልክቷል።
ሳምሶን ጥላሁን፣አለሙ ዋቅቶላ፣ቡልቻ ታደሰ፣ሃሺም አሚር፣ሽፈራው እና አሊ ዳንኤል የተባሉት 6ቱ ተከሳሾች በሳምንቱ መጨረሻ በፌደራሉ የመጀምሪያ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት መቅረባቸውን የገለጸው ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ተከሳሾቹ ግጭቱን በማነሳሳት፣በማስተባበርና ጥቃት ፈጻሚዎችን በመንግስት ተሽከርካሪ በማሸሽ አብይ ተዋናዮች መሆናቸውን አመልክቷል።