Tuesday, December 18, 2018

አምዶም ገብረስላሴ ታሰረ

ባለፈው ቅዳሜ በመቀሌ በተካሄደው ስብሳባ አቶ በረከት ስሞኦን እና የሕወሓት ባለስልጣናትን የተቸው አምዶም ገብረስላሴ ታሰረ።
     ለኢሳት በደረሰው መረጃ መሰረትየአረና የሕዝብ ግኑኝነት ሃላፊ አቶ  አምዶም ገብረስላሴ በቁጥጥር ስር የዋለው መቀሌ አክሱም ሆቴል በተባለው አካባቢ ሲሆን፣ሰው ደብድበሃል በሚል  መታሰሩንም  መረዳት ተችሏል።አምዶም  መቀሌ አዲሸንዲህ በተባለ  ቦታ እንደታሰረ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።አምዶም ገብረስላሴ ባለፈው ቅዳሜ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ በተካሄደው  ሰብሰባ የሕወሃትን ባለስልጣናት ሲተች ንግግሩ እንዲቋርጥ መደረጉም ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment