Friday, November 30, 2018

የሰራዊቱ አባላት ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ከወር በፊት ያለ ፈቃድ ወደ ቤተመንግስት የተንቀሳቀሱ ወታደሮችን ያስተባበሩ የሰራዊቱ አባላት ወታደራዊ ፍርድ ቤት ቀረቡ። ከወታደራዊ ዲሲፒሊን በማፈንገጥና ሕግን በመጣስ የተንቀሳቀሱትን ወገኖች በሕግ ተጠያቂ ማድረግ ነገ ተመሳሳይ ነገር እንዳይፈጸም ይከላከላል ሲሉ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ገልጸዋል።

Wednesday, November 28, 2018

U.S. Assistant Secretary of State visits Ethiopia

 ESAT News (November 28, 2018)
US Assistant Secretary of State for African Affairs, Tibor Nagy is in Addis Ababa for an official working visit as part of his tour to East Africa.
Nagy and General Thomas D. Waldhauser, Commander of U.S. Africa Command (AFRICOM), met with Ethiopia’s Minister of Defense Aisha Mohammed to discuss opportunities for security cooperation between the United States and Ethiopia, according to the U.S. Embassy in Addis Ababa.
Speaking to NPR’s “All Things Considered” a week ago, Mr. Nagy called Ethiopia’s Prime Minister Abiy Ahmed “visionary.”
“It shows you what one courageous, visionary leader can do to impact not only her or his own country, but the region,” Nagy said speaking about Ahmed who is credited for reforms in his country and ending a two decae old animosity with Eritrea.
“Now the waves are kind of washing over other parts of the region. I mean, during my discussions with African leaders, I pointed to Ethiopia as – what a positive force can mean for Africa.”
It is Nagy’s first visit to Ethiopia since his confirmation in July. He served as U.S. Ambassador to Ethiopia from 1999 to 2002

Wednesday, November 21, 2018

ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ አርአያነታችንን እናስመስክር አሉ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 11/2011) በኢትዮጵያ አሁን የተገኘው ለውጥ በሁሉም ህዝብ ትግል የመጣ በመሆኑ እኛም ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ አርአያነታችንን ማስመስከር ይገባናል ሲሉ ጀነራል ሰዓረ መኮንን ገለጹ።
የኢትዮጵያ የሃገር መከላከያ ሚኒስቴር ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንን በአንድ የውይይት መድረክ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ የመጣው ለውጥ የሁሉንም ሕዝብ ተሳትፎ የጠየቀ በመሆኑ ሰራዊቱም የዚህ ለውጥ ተጠቃሚ እና ደጋፊ ነው ።
በለውጡ የሰራዊቱን ኑሮ ከማሻሻል ጀምሮ ለአከባቢው ሰላም የነበረን ሚና ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅጣጫ መቀመጡንም ገልጸዋል።
እናም ከለውጡ ጋር መሄድና የዘመናዊ ሰራዊት ግንባታን ማፋጠን ይገባናል ብለዋል።
ጠቅላይ ኢታማጆር ሹም ሰዓረ መኮንን እናደሉት የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግል ላገኘው ለውጥ መከላከያ ሰራዊቱ አጋርነቱን ያረጋገጣል።
እኛ ለሕዝባችን የመጨረሻ ምሽግ ነን ሲሉም ሰራዊቱ ከለውጡ እና ከሕዝቡ ጋር መቆሙንም አረጋግጠዋል።

በሜቴክ ሳቢያ የ36 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ አስከተለ

(ኢሳት ዲሲ–ህዳር 12/2011)የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን በአፋር ክልል እገነባዋለሁ በማለት የተንቀሳቀሰበት የእንፋሎት ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በሜቴክ ሳቢያ የ36 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ ማስከተሉ ተገለጸ።

በጄኔራል ክንፈ ዳኘው ይመራ የነበረው ሜቴክ ከኮንትራት ስምምነቱ ውጪ ከውጭ ያስገባቸው መሳሪያዎች አሮጌዎችና ያልተሟሉ በመሆናቸው ለፕሮጀክቱ መክሸፍና ለተከተለው ኪሳራ ምክንያት እንደሆነም መረዳት ተችሏል።
137 ሜጋ ዋት ያመነጫል የተባለው የሃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም መክሸፉ ተመልክቷል።

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ሆነው ሊሾሙ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 12/2011) ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በነገው ዕለት የሀገሪቱ የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ሆነው እንደሚሾሙ ተገለጸ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በሚያደርገው ስብሰባ ወይዘሪት ብርቱካንን የምርጫ ቦርዱ ሀላፊ እንዲሆኑ በጠቅላይ ሚንስትር አብይ የሚቀርበውን ሀሳብ መነሻ በማድረግ ድምፅ ይሰጣል ተብሏል።
ወይዘሪት ብርቱካን ከሰባት አመታት ስደት በኋላ መንግስት ባደረገላቸው ጥሪ በቅርቡ ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸው ይታወሳል።
ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንደ አዲስ ለሚደራጀው ብሔራዊ ምርጫ አስፈጻሚ ተቋም ኃላፊ እንዲሆኑ መታጨታቸው ሲነገር ቆይቷል ።
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ  ስያሜውንና አጠቃላይ አደረጃጀቱን በማሻሻል ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ ሆኖ ይቋቋማል ተብሎ ይጠበቃል።

በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ግጭቶች ተቀሰቀሱ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 12/2011) በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ግጭቶች መቀስቀሳቸው ተገለጸ።

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አሶሳ ዩኒቨርስቲ በተነሳው ግጭት ሶስት ሰዎች ተገድለዋል።
34 ሰዎችም ክፉኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በቴፒ ሳምንታት የዘለቀው ግጭት አሁንም አልበረደም።
በልዩ ሃይል በርካታ ሰዎች ተደብድበው ሆስፒታል ገብተዋል። በአፋርም የህዝብ ተቃውሞ ቀጥሏል።
በቢሾፍቱ ደብረዘይት ቄሮ ነን ባሉ ወጣቶች ሱቃችንን ልቀቁ እየተባልን ነው ሲሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
በአንዳንድ ዩኒቨርስቲዎች መለስተኛ ግጭቶች መፈጠራቸውን የገለጸው ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የተጀመረውን የለውጥ ሂደት ለማደናቀፍ የሚሰሩ ወገኖች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ዒላማ አድርገዋል ብሏል።

Monday, November 19, 2018

Ethiopia: Capital launches mixed-use, integrated residential project

by Engidu Woldie
ESAT News (November 19, 2018)
An integrated residential project was launched today at the historic La Gare (Train Station) in the capital Addis Ababa.
The mixed-use project, which lands on 360,000-sq-m area, is expected to have 4000 residences and cost 50B birr, (approximately $1.9B at current exchange rates).
A key component of the project was building residences for the 1,600 citizens to prevent eviction from their village.

ጠበቃ ለማቆም ገንዘብ የለኝም በማለት በችሎት ፊት ምለው የተናገሩት አቶ ኢሳያስ ዳኘው (የሜ/ጀነራል ክንፈ ወንድም) ሚሊዬነር መሆናቸው ተረጋገጠ!

BBC Amharic

ከዚህ ቀደም በራሳቸው ጠበቃ ማቆም እንደማይችሉ ለተናገሩት አቶ ኢሳያስ ዳኘው ፖሊስ አለኝ ያለውን ማስረጃም አቅርቦ ለፍርድ ቤቱ አሰምቷል። በራሳቸው ስም በፀረ ሙስና ኮሚሽን የሐብት መዝገብ ቅፅ ላይ ራሳቸው ያስመዘገቡት ዝርዝር
➤ 2 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ባለ 1 ፎቅ ቤት በራሳቸው ስም የተመዘገበ፣

Thursday, November 15, 2018

ኮለኔል ገብረእግዚአብሔር አለምሰገድ በቁጥጥር ስር ዋሉ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 6/2011) በሶማሊያ የኢትዮጵያ ጦር አዛዥና በኢጋድ የዋና ጸሃፊው የፖለቲካ አማካሪ ኮለኔል ገብረእግዚአብሔር አለምሰገድ በተለምዶ ገብሬ ዲላ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ።

በኮንትሮባንድ ንግድና በሶማሌ ክልል በተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እጃቸው እንዳለበት የሚጠረጠሩት ኮለኔል ገብረእግዚያብሄር ባለፈው ሳምንት በጂጂጋ ከተፈጠረው ግጭት ጋር በመሪነት እንደተሳተፉ ይነገራል።
ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ በወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ለ10 ተከታታይ አመታት የቆዩት ኮለኔል ገብረእግዚያብሄር በሃገር ሃብት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ካደረሱ የህውሃት የጦር መሪዎች ዋናው እንደነበሩ መረጃዎች ያመለክታሉ።

የ205 ግለሰቦች የባንክ ሒሳብ ታገደ

(ኢሳት ዲሲ–ህዳር 6/2011) የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የ205 ግለሰቦች የባንክ ሒሳብ እንዲታገድ አደረገ።

ፌደራል ፖሊስ በቀድሞ የደህንነትና የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮችና ቤተሰቦቻቸው ስም የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦች መረጃ እንዲሰጠው በጠየቀው ደብዳቤ በተጠርጣሪዎቹ ግለሰቦች ሚስትና ልጆቻቸው ስም የተከፈቱትን በዝርዝር ገልጿል።
በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ የሜቴክ ሃላፊዎች ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘውን ጨምሮ የ147 ሰዎች የባንክ ሂሳብ በሙስና ተጠርጠረው የባንክ ሂሳባቸው ሲታገድ የአቶ ጌታቸው አሰፋና የ57 ሰዎች የባንክ ሂሳብ ደግሞ ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ጋር በተያያዘ አካውንታቸው እንዲታገድ ተደርጓል።

ለፍርድ የማቅረቡ ዘመቻ ይደገፋል ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ህዳር 6/2011) በዜጎች ላይ የሰብአዊ መብት ሲፈጽሙ በነበሩ ባለስልጣናት ላይ መንግስት የጀመረውን ለፍርድ የማቅረብ ዘመቻ እንደሚደግፈው ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ገለጸ።

የጥቃቱ ሰለባዎችን በተመለከተ የሰበሰባቸውን መረጃዎች ለሕግ አስከባሪ አካላት እንደሚሰጥም አስታውቋል።
የፍርድ ሔደቱ ከበቀል የጸዳ እንዲሆንም ጥሪ አቅርቧል።
ከተመሰረተ ሩብ ክፍለ ዘመን ያስቀጠረውና በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በመመዝገብና በማጋለጥ የሚታወቀው የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ የወቅቱን የመንግስት መግለጫ በተመለከተ  መግለጫ ያወጣው ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ነው።
“የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ፈጻሚዎች ላይ መንግስት በመውሰድ ላይ ያለው ርምጃ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል በሚል ርዕስ ሰመጉ ባወጣው መግለጫ በሕግ ጥላ ስር በሚገኙ ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ የማሰቃየት ድርጎቶችን በተመለከተ አቃቤ ሕግ ይፋ ያደረገውን ሪፖርት ሰመጉ የሚያውቀውና ሲያጋልጠው የቆየ መሆኑንም አስታውሷል።

Monday, November 12, 2018

Ethiopia: Warrants issued for Abay Tsehaye, Maj. Gen. Kinfe Dagnew as arrest on army and intelligence officials continues

Most of the officials wanted for a range of crimes hail from Tigray region. The regional government has not been willing to handover the suspects, according to the sources, who also said there has been a recent increase in the number of Tigrayan federal officials and army generals that sought refuge in the region.
Ethiopia’s attorney general today said the alleged crimes by the officials include illicit financial flights, illegal purchases by government enterprises mainly by METEC former managers.
The attorney general, Berhanu Tsegaye aslo said members of the intelligence and security who have committed human rights violations would also be brought to justice.

Friday, November 9, 2018

በሰራዊቱ ውስጥ የተጀመረውን የለውጥ ርምጃ ለማጠናከር በርካታ ጄነራሎችን ጨምሮ ከ160 በላይ ከፍተኛ የጦር አዛዦች ከሰራዊቱ መሰናበታችውን የቅርብ ምንጮች ለኢሳት ገለጹ።

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 30/2011) ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድም ጎንደር ከተማ ላይ ትናንት በሰጡት መግለጫ ባለፉት 7 ወራት ከተሰሩ ስራዎች ትርጉም ያለውና መሰረት የረገጠ ስራ የተሰራው በሰራዊቱ ውስጥ እንደሆነ ገልጸዋል። ፋይል የሰራዊቱን አመራር ለማሰባጠር በተወሰደው ርምጃ የተነሱት ወታደራዊ ሃላፊዎች በፈቃደኝነት እንደለቀቁም ገልጸዋል። ባለፉት 7 ወራት ትርጉም ያለው የማሻሻያ ርምጃ የተወሰደው በሃገር መከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገልጸዋል። በተቋሙ ውስጥ የቀየርነው ሚኒስትሩን ብቻ ሳይሆን ተልዕኮውንም

በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች ወሰን ላይ የጅምላ መቃብር መገኘቱ ተገለጸ።

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 30/2011) ፖሊስ እንዳስታወቀው የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ዒሌ ታማኝ በሆነው የልዩ ሃይል ተፈጸሟል በተባለ ግድያ የ200 ሰዎች አስክሬን በአንድ ጉድጓድ የተቀበረበት የጅምላ መቃብር ተገኝቷል። ፋይል ግድያው የተፈጸመው በሁለቱ ክልሎች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ወቅት እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ ተጨማሪ የጅምላ መቃብር ለማግኘት ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል። አቶ አብዲ ዒሌ በስልጣን ዘመናቸው ፈጽሟቸዋል ለተባሉት ወንጀሎች በህግ ተይዘው በእስር ላይ የሚገኙ መሆኑ ታውቋል። የጅምላ መቃብሩ መገኘቱ የተመለከተው መረጃ የወጣው ትላንት በነበረው

Several mass graves found in Somali region of Eastern Ethiopia

ESAT News (November 9, 2018)
A day after police told a court in Addis Ababa that they have found a mass grave in an area between the Oromo and Somali regions in Eastern Ethiopia containing the bodies of about 200 people, president of the Somali region told ESAT that investigations were underway on “several” mass graves found in the region.
In a brief comment to ESAT on the news of the founding of a mass grave containing the about 200 bodies that was disclosed in court yesterday, Mustafa Omer, president of the Somali region, said the regional government, together with elders, are conducting forensic investigations on “several” mass graves found in the region.

የቡና ቱሪዝም ቀንን ለማክበር የወጡት መግለጫዎች አይወክሉኝም ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 30/2011) የዘንድሮው የቡና ቱሪዝም ቀንን ለማክበር የወጡት መግለጫዎች አይወክሉኝም ሲል የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር ዓለም ዓቀፍ የቡና ፕሮግራም በቡና መገኛ ምድር በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን በዓል አስመልክቶ በሳምንቱ መጀመሪያ በተሰራጨው መግለጪያ የቡና መገኛ ጂማ ነው የሚለው አገላለጽ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቷል።

Wednesday, November 7, 2018

በሊቢያ ኢትዮጵያውያን በስቃይ ላይ ናቸው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በሊቢያ ኢትዮጵያውያን በስቃይ ላይ መሆናቸው ተገለጸ።

በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ከ20 በላይ ኢትዮጵያውያን ለቀናት ምግብና ውሃ አጥተው በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል።
አብዛኞቹ ከጎንደር የተሰደዱ መሆናቸውን የሚገልጹት ኢትዮጵያውያኑ ባለፈው ቅዳሜ ገጀራና የጦር መሳሪያ የያዙ የሊቢያ ታጣቂዎች ድብደባ ፈጽመውባቸው ለከፍተኛ ጉዳት መዳረጋቸውን ተናግረዋል።

በአፋር ተቃውሞ ሲደረግ ዋለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) በአፋር የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲደረግ ዋለ።

አሳይታ፣ አዳአር፣ በራሂሌ፣ ገላኢሉ፣ ዳሎል፣ ገዋኔና ኮነባ በተሰኙ የአፋር ከተሞች በተደረገው ተቃውሞ የክልሉን መንግስት የሚመራው ገዢ ፓርቲ ለህዝብ ስልጣኑን እንዲያስረክብ ተጠይቋል።
ሁለተኛ ወሩን እያጠናቀቀ ያለው የአፋር ተቃውሞ ፌደራል መንግስቱ በአስቸኳይ ጣልቃ ገብቶ የክልሉ ህዝብ ከተደቀነበት አደጋ እንዲታደገው ጥሪ ቀርቧል።
የአፋር ህዝብ ፓርቲ ለኢሳት እንደገለጸው የፌደራሉ መንግስት በቶሎ ምላሽ ካልሰጠ በአፋር ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ የሚያስከትል ተቃውሞ ይቀሰቀሳል።

ዓለም አቀፉ የቡና ቱሪዝም ፕሮግራም ተቃውሞ አስነሳ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) የቡና መገኛ ጂማ ነው በሚል በቡናና ሻይ ልማት ባለስልጣን የሚከበረው የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የቡና ቱሪዝም ፕሮግራም ተቃውሞ አስነሳ።

ዛሬ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ህዝቡ አደባባይ በመውጣት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ አውግዟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቡናና ሻይ ባለስልጣን ጋር በመተባባር የዘንድሮውን የቡና ቱሪዝም ለማክበር በከፋ የተያዘው ፕሮግራም ተሰርዞ በጂማ እንዲሆን መደረጉ ብሔርን ከብሔር የሚያጋጭና ታሪክን የሚቀማ ተግባር ነው ሲል የከፋ ዞን አስተዳደር ቅሬታውን ገልጿል።

በሕገወጥ መንገድ የገቡ የጦር መሳሪያዎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011)ወደ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ በሶስት ወራት ውስጥ የገቡ የጦር መሳሪያዎች ብዛት ከ1 ሺ 500 በላይ መብለጡን ፖሊስ ገለጸ።

የጦር መሳሪያዎቹም በአብዛኛው ቱርክ ሰራሾች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን በብዛት የሚገባውም በሱዳን በኩል እንደሆነ ተመልክቷል።
በፌደራል ፖሊስ የተደራጁ ልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክተር ኮማንደር ከተማ ደባልቄ ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት እስከ መስከረም መጨረሻ ባሉት ሶስት ወራት 1 ሺ 560 ሕገ ወጥ ሽጉጦች ወደ ሃገር ቤት ገብተው በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የኤርትራው ፕሬዝዳንት ወደ ጎንደር ከተማ ሊሄዱ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 28/2011) የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቄ የፊታችን አርብ ጎንደር ከተማ ይገባሉ ተባለ።

ፕሬዝዳንቱ በአማራ ክልል በሚያደርጉት ጉብኝት የክልሉን ርዕሰ ከተማ ባህርዳርን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎችም ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተመልክቷል።
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የፊታችን አርብ ጎንደር ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የአማራ ክልል ባለስልጣናት አቀባበል እንደሚያደርጉላቸው ተመልክቷል።

Thursday, November 1, 2018

ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ታጣቂዎችን ለማቋቋም የጀርመን መንግስት ቃል ገባ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 22/2011)በትጥቅ ትግል ላይ ቆይተው በመንግስት ጥሪ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወስነው ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ታጣቂዎችን ለማቋቋም የጀርመን መንግስት የልማትና የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባቱ ተገለጸ።

በአጠቃላይ ትጥቅ ፈተው ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ታጣቂዎች ቁጥር 35ሺ ያህል መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ገልጸዋል።

Ethiopia appoints first female supreme court president

ESAT News (November 1, 2018)
Ethiopia’s parliament appointed the first female supreme court president today in what is seen as the latest move by a reformist Prime Minister in increasing women’s role in his government.
Prime Minister Abiy Ahmed nominated Meaza Ashenafi to lead the highest court of the land which was unanimously approved by the Parliament.
A women’s right activist and a former judge for the high court, Ashenafi’s work was the subject of a Hollywood movie with Angelina Jolie as its executive producer.

ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ድብደባ ሊፈጽሙ ነበር ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 22/2011)የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ፕሬዝዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ድብደባ ለመፈጸም ሙከራ በማድረጋቸው በህግ ሊጠየቁ ነው ተባለ።

ዶክተር አሸብር የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሁለት አባላትን በስብሰባ ላይ ለመደብደብ መሞከራቸው ተገልጿል።
በዶክተር አሸብር የድብደባ ሙከራ ከተደረገባቸው አንዷ ኮለኔል ደራርቱ ቱሉ መሆኗም ታውቋል።
ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ሊያመራ መሆኑን የገለጹት ምንጮች በዶክተር አሸብር በኩል የሽምግልና ጥያቄ መቅረቡን ጠቅሰዋል።

በጋምቤላ የቦምብ ጥቃት ደረሰ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 22/2011)በጋምቤላ የቦምብ ጥቃት ደረሰ።
በአንድ የክልሉ ባለስልጣን ጠባቂ ፖሊስ ትላንት የተፈጸመው የቦምብ ጥቃት የሁለት ሰዎችን ህይወት ማጥፋቱ ተገልጿል።
አዲሱ የጋምቤላ አመራር ወደ ስልጣን መምጣቱን ተከትሎ ያኮረፉ ሃይሎች የሽብር ተግባር ሊፈጽሙ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳለም ታውቋል።
ቦምቡን ያፈነዳው ግለሰብ የህወሃት አባል እንደሆነም የኢሳት ምንጮች ያደረሱን መረጃ አመልክቷል።