Wednesday, January 31, 2018

ህክምና የተከለከሉት አቶ በቀለ ገርባ ጤና አሳሳቢ ነው ተብሏል

~ "የግራ አይናቸው እስከወዲያኛው ላያይ ይችላል" ምኒልክ ሆስፒታል
ምኒልክ ሆስፒታል እስር ላይ የሚገኙትና ህክምና የተከለከሉት አቶ በቀለ ገርባ ተገቢ ህክምና ካላገኙ አይናቸው እስከወዲያኛው ላያይ ይችላል ማለቱን ልጃቸው ቦንቱ በቀለ ለቪኦኤ ገልፃለች። የደም ግፊት በሽታ ያለባቸው አቶ በቀለ ገርባ በቂሊንጦ እስር ቤት ህክና ተከልክለው ቆይተዋል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት አቶ በቀለ ገርባ ህክምና እንዲያገኙ በተደጋጋሚ ለእስር ቤቱ ትዕዛዝ ቢያስተላልፍም እስር ቤቱ ሳያሳክማቸው ቆይቷል።
በዚህም ምክንያት የአቶ በቀለ ገርባ የግራ አይን የተጎዳ ሲሆን ህመሙ ከባሰባቸው በኋላ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ልጃቸው ለቪኦኤ ገልፃለች። የምኒልክ ሆስፒታልም አቶ በቀለ ገርባን ማከም እንደማይችል በመግለፅ ወደ ሌላ የግል የህክምና ተቋም "ሪፈር" ፅፎላቸዋል። ምኒልክ ሆስፒታል አቶ በቀለ በአግባቡ ህክምና ካላገኙ አይናቸው እስከወዲያኛው ላያይ ይችላል ሲል ሁኔታው አሳሳቢ መሆኑን ገልፆአል ተብሏል። አቶ በቀለ ገርባ ተገቢ ህክምና ካላገኙ አይናቸው እስከወዲያኛው ላያይ ይችላል የሚል አስደንጋጭ የባለሙያ ማስጠንቀቂያ በተሰጠበት ሁኔታ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት አቶ በቀለን በግል የህክምና ተቋም አላሳክምም ማለቱን ልጃቸው ለቪኦኤ ገልፃለች።

የወይዘሮ አዜብ መስፍን የውስጥ ሪፖርት ከአመታት በኋላ ተጋለጠ

የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ሕወሃት/ንብረት የሆኑ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን እንዲሁም ሌሎች ኩባንያዎችን በተመለከተ ወይዘሮ አዜብ መስፍን ለሕወሃት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያቀረቡት የውስጥ ሪፖርት ከአመታት በኋላ ተጋለጠ።
በሃገሪቱ ህግ መሰረት የፖለቲካ ፓርቲ የመገናኛ ብዙሃን እንዳይኖረው ይከለክላል።
ይህ ባለ 92 ገጽ ሪፖርት የሕወሃት ኩባንያዎችን ዝርዝር አፈጻጸምና ገቢያቸውን የተመለከተ እንደሆነም መረዳት ተችሏል።
ወይዘሮ አዜብ መስፍን ለሕወሃት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያቀረቡት ሪፖርት እስከተጻፈበት 2007 ድረስ የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ሕወሃት/ ንብረት የሆኑት የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና የዜና አገልግሎት ተቋማት መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉት ሬዲዮ ፋና የአሁኑ ፋና ቴሌቪዥን እንዲሁም ዋልታ ዜና አገልግሎትና ዋልታ ቴሌቪዥን መሆናቸውም በሪፖርቱ ተመልክቷል።

በሰሜን ወሎ እየተካሄደ ያለውን የስራ ማቆም አድማ ተከትሎ ከ200 በላይ ሰዎች ታሰሩ

በወልድያ፣ መርሳ፣ ስሪንቃና ቆቦ ከተሞች በመካሄድ ላይ ያለውን የስራ ማቆም አድማ ተከትሎ ከትናንት ጀምሮ ከ200 በላይ ዜጎች ታስረዋል። ከታሰሩት መካከል የመንግስት ሰራተኞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ነጋዴዎችና ወጣቶች ይገኙበታል። በርካታ ወጣቶች ከተያዙ በሁዋላ ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። ከፍተኛ የእስር ዘመቻ እየተካሄድ ያለው ወልድያ ላይ ነው። ቀደም ሲል የክልሉ ፕሬዚዳንት ገዱ አንዳርጋቸው የሚታሰር ሰው እንደማይኖር ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም፣ ቃላቸው ሳይጠበቅ በስብሰባ ላይ የተሳተፉ ምክሮችን የለገሱ ሰዎች ሳይቀሩ እየታሰሩ ነው። 
ምንም እንኳ አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት በአካባቢው ተሰማርቶ የሚገኝ ቢሆንም፣ ህዝቡ ግን ዛሬም የስራ ማቆም አድማውን ቀጥሎ ውሎአል። ሆቴሎች፣ ሱቆችና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ መስሪያ ቤቶችና ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። ከወልደያ እስከ ቆቦ ያለው መንገድ እንደተዘጋ ሲሆን፣ ወታደሮች መንገዶችን ለማስከፈት ሙከራ አላደረጉም። 

የፓርላማ አባላት ኮንትሮባንዲስት እየተባሉ የሚጠሩት ሰዎች ስም እንዲገለጽ ጠየቁ

 ጥር 22 ቀን 2010 ዓም የግማሽ አመት ሪፖርታቸውን ለፓርላማ ያቀረቡት የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሞገስ ባልቻ፣ የኮንትሮባንድ ነጋዴዎችን መቆጣጠር ካልቻለ፣ ትልቅ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ቀውስ እንደሚፈጠር አስጠንቅቀዋል። የፓርላማ አባላቱም እነዚህ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ስማቸው እንዲገለጽላቸው ለባለስልጣኑ ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ ባለስልጣኑ ግን መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።
ሪፖርተር እንደዘገበው አንድ የፓርላማ አባል ስሙ የማይጠራው ኮንትሮባንዲስት ማነው?” ሲሉ ሌላው የፓርላማ አባል ደግሞ ገቢዎችና ጉሙሩክ በእነዚህ ሃይሎች ጡንቻ መታሰሩን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት አንድ ብሔር ነጥሎ የማጥቃት ግጭት እንዲፈጠር ምክንያት ናቸው የተባሉት ኮንትሮባንድ ነጋዴዎች መሆናቸውን በመጥቀስ የተናገሩት የፓርላማ አባሉ፣ የውጭ ንግድ በሚካሄድባቸው መስመሮች ድንገት መብራት ከጠፋ፣ ኮንትሮባንድ የጫኑ መኪኖች እያለፉ መሆኑ በገሃድ ይታወቃል ብለዋል።
የበላስልጣኑ የህግ ማስከበር ዘርፍ ሃላፊ አቶ ዘመድ ተፈራ የኮንትሮባንድ ነጋዴዎችን ስም ከመግለጽ የሚወሰደውን እርምጃ መጠበቅ የተሻለ ነው ብለዋል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ለተቋቋመው ግብረ ኃይል የኮንትሮባንዲስቶችን ስም ዝርዝር ማቅረባቸውንም ጠቅሰዋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኮንትሮባንዲስቶቹ የራሳቸው መጋዘን ያላቸው፣ በኔትወርክ የተደራጁና ተግባራቸውም በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ነው ብለዋል።

በምስራቅ አፍሪካ በቂ ምግብ ካላገኙት 5 ሚሊዮን ህጻናትና እርጉዝ ሴቶች መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን ናቸው

በምስራቅ አፍሪካ በቂ ምግብ ካላገኙት 5 ሚሊዮን ህጻናትና እርጉዝ ሴቶች መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን ናቸው
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ክፍል አስተባባሪ ግብረሃይል ባወጣው ሪፖርት ባለፈው አመት በአፍሪካ ቀንድ በቂ ምግብ ካላገኙት 5 ሚሊዮን 200 ሺ ህጻናትና እርጉዝ ሴቶች መካከል 3 ሚሊዮን 600 የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን ናቸው። 
በአፍሪካ ቀንድ 5 ሚሊዮን 5 መቶ ሺ ዜጎቭ በተለያዩ ምክንያቶች ሲፈናቀሉ፣ 1 ሚሊዮን 400 የሚሆኑት ደግሞ ስደት ጠያቂዎች ናቸው። 
14 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች የምግብ እጥረት ያጋጠማቸው ሲሆን፣ በዚህ አመትም የምግብ እጥረቱ ተባብሶ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

በሰሜን ወሎ ያለው ውጥረት መቀጠሉ ታወቀ። በብአዴን አመራሮች የሚጠሩ ሰብሰባዎችም እየተበተኑ መሆኑ ተሰምቷል።

ከቆቦ ጀምሮ እስከ መርሳ ዛሬ መንገዶች ዝግ ናቸው። ከቆቦ ወደ ትግራይ የሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች በወታደሮች ታጅበው መሆኑን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በወልዲያ የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ወታደሮች በህዝቡ ላይ ግፍ እየፈጸሙ መሆናቸውን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ከመርሳና ወልዲያ በትንሹ 500 ወጣቶች በአፋር ጭፍራ በረሃ ተወስደው በስቃይ ላይ ናቸው ተብሏል። ሰሜን ወሎ ከ10 ቀናት በፊት የጀመረው ህዝባዊ ተቃውሞ ውጥረቱ አልበረደም። በርካታ መንገዶች እንደተዘጉ ናቸው። የንግድ እንቅስቃሴው እንደቆመ ነው። በመርሳ፣ በሲሪንቃ፣ በወልዲያና በቆቦ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መደበኛ እንቅስቃሴያቸውን መጀመር አልቻሉም። ትምህርት ቤቶችም ዝግ ናቸው። የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ባሰማራቸው የብአዴን አመራሮች የተጠሩት ስብሰባዎች ዓላማቸው በየከተሞቹ ያለውን የሰላም መደፍረስ ለመቅረፍ እንደሆነ ቢገለጽም በአብዛኞቹ ከተሞች በህዝብ ተቃውሞ ስብሰባዎቹ መጨናገፋቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በቆቦ አቶ አለምነው መኮንን ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸው ስብሰባው ሲበተን፣ በመርሳ የሀገር ሽማግሌዎች ከብአዴን አመራሮች ጋር ያለስምምነት

በወልቃይ የወርቅ ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ የወልቃይት ተወላጆች ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ተገልጸ።

  ልዩ ስሙ ኢድሪስ በሚባል የወርቅ ክምችት በሚገኝበት ስፍራ በወርቅ ቁፋሮ ስራ በተሰማሩ የወልቃይት ተወላጆች ላይ ድብደባውን የፈጸሙት በትግራይ ፖሊሶች የታገዙ በአካባቢው በሰፈሩ ሰዎች መሆናቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በሌላ በኩል በወልቃይት የማይጸብሪ ከተማ ነዋሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው ተሰምቷል። ተቃውሞው በማንነታችን በእኩል እየታየን አይደለም በሚል እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ። የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሃት አዲስ አበባን ከመቆጣጠሩ በፊት ጀምሮ የትግራይ ተወላጆች እንዲሰፍሩ ከተደረጉባቸው አካባቢዎች አንዱ ኢድሪስ ይባላል። ይህ አካባቢ በወርቅ ምርት የበለጸገ እንደሆነ ይነገርለታል። የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሃት በ1983 ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ በብዛት የትግራይ ተወላጆች በኢድሪስ በመስፈር ወርቅ እያመረቱ መጠቀም ጀምረዋል። ነባሮቹ የአካባቢው ነዋሪዎች የሆኑት የወልቃይት ተወላጆች መገፋት የጀመሩትም እነዚህ የትግራይ ሰፋሪዎች አካባቢውን ከተቆጣጠሩት በኋላ ነው። ኢሳት ያነጋገራቸውና ለጊዜው ድምጻቸው እንዳይሰማ የጠየቁት የወልቃይት ተወላጆች እንደሚሉት በትግራይ ሚሊሻና በትግራይ ፖሊስ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሰፋሪዎች ነባሩን እያስለቀቁ የወርቅ ምርቱን ተቆጣጥረውታል። በወርቅ ቁፋሮ የተሰማሩ

በኢትዮጵያ ሁሉን ያቀፈ ሀገራዊ ጉባዔ እንዲጠራ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ማህበር ጥሪ አቀረበ።

 ማህበሩ ወቅታዊውን የኢትዮጵያ ሁኔታ የተመለከተ ባለ 34 ገጽ ሪፖርቱን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ጠመንጃ ያነሱ የነጻነት ሃይሎች፣ በሀገር ቤት የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሚመለከታቸው ሁሉም የኢትዮጵያ ድርጅቶች ተሳታፊ የሆኑበት ጉባዔ በመጥራት ኢትዮጵያን ከተደቀነባት ሀገራዊ ቀውስ መታደግ ይገባል ሲል ማህበሩ አስታውቋል። ሪፖርቱ በኢትዮጵያ የሚፈጸሙ አፈናዎች፣ ግድያዎችንና መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በዝርዝር ያጋለጠ እንደሆነ ተገልጿል። የማህበሩ ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ሃይለማርያም ለኢሳት እንደገለጹት በኢትዮጵያ የሚፈጸሙት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፉ መጥተዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎች የፈለጉትን ሀሳብ የማራመድም ሆነ የሚደግፉትን የፖለቲካ ድርጅት በተመለከተ ስሜታቸውን በአደባባይ ለመግለጽ የሚችሉበት እድል ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል የሚሉት አቶ ያሬድ ሁኔታዎች ከምንጊዜውም በላይ እየከፉ መተዋል ይላሉ። በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለሰብዓዊ መብት ታጋዮች፣ለጋዜጠኞችና ለሲቪክ ማህበራት ፈጽሞ የሚመች አይደለም ሲሉም ይገልጻሉ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ማህበር ባወጣው ባለ 34 ገጽ ሪፖርት አሁን ያለውን የኢትዮጵያ ቀውስ በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎችን ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ የሚያቀርብ ነው። በኢትዮጵያ አሁን ያለው ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በሪፖርቱ ያመለከተው የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ማህበር ከቁጥጥር ውጭ ወጥቶ ከፍተኛ ጥፋት ከማስከተሉ በፊት ሀገራዊ ጉባዔ እንዲጠራ ማህበሩ ጠይቋል። ሁሉም የሚመለከታቸው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች የሚሳተፉበት ጉባዔ በአስቸኳይ እንዲጠራ በመጠየቅ ለተለያዩ ዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች፣ ሃያላን ሀገራትና ለህወሃት አገዛዝ መልዕክት ማስተላለፉን አቶ ያሬድ ለኢሳት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ማህበር በቀድሞ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ውስጥ ይሰሩ በነበሩና በምርጫ 1997 በተፈጠረው ቀውስ ከሀገር በስደት በወጡ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመ ማህበር መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

የሼህ መሀመድ አላሙዲን ቤተሰቦች ሳውዳረቢያ ውስጥ ታሰሩ።

የቢሊየነሩ ተውልደ ኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች የታሰሩት ሼህ መሀመድ አላሙዲን በድርድር ገንዘብ ከፍለው ከእስር እንዲወጡ የቀረበላቸውን አማራጭ ባለመቀበላቸው እንደሆነም ተመልክቷል። የሳውዳረቢያ መንግስት በቁጥጥር ስር ካዋላቸው ባለሃብቶች አንዱ የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሼህ መሀመድ አላሙዲን በህዳር ወር ሳውዳረቢያ ሪያድ ውስጥ መታሰራቸው ይታወሳል። በእሳቸው የተጀመረው እስር ደግሞ በቤተሰቦቻቸውም ላይ መቀጠሉን ነው ሚድል ኢስት ሞኒተር ትላንት ባወጣው ዘገባው ያሰፈረው። በቤተሰቦቻቸው ላይ እስሩ የተከተለው ሌሎቹ ባለሃብቶችና ልኡላን በድርድር ገንዘብ ከልፈው ሲለቀቁ ሼህ መሀመድ አላሙዲን ገንዘብ ለመክፈልም ሆነ ንብረታቸውን አሳልፈው ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው እንደሆነም ተመልክቷል። በሳውዲው አልጋ ወራሽ መሀመድ ቢን ሰልማን በተመራው የጸረ ሙስና ዘመቻ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ልኡላንና ባለሃብቶች ወደ አንድ መቶ ቢሊየን ዶላር ለማስመለስ የተንቀሳቀሰው የሳውዳረቢያ መንግስት ከዕቅዱ በላይ ገንዘብ ማስመለሱም ታውቋል። ለምርመራ ከተጠሩ 381 ሰዎች በአሁኑ ወቅት ሼህ መሀመድ አላሙዲንን ጨምሮ 56ቱ በሪትዝ ካርልተን

Tuesday, January 30, 2018

በወልድያ በርካታ የአገር ሽማግሌዎች ታሰሩ

የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት ገዱ አንዳርጋቸው ወልድያ ላይ የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱ ሌሎችም ሰዎች እንደማይታሰሩ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም፣ ከትናንት ምሸት ጀምሮ በርካታ የሃገር ሽማግሌዎች ቤታቸው እየተሰበረ ታስረዋል። አብዛኞቹ በሌሊት መታሰራቸውን ምንጮች ገልጸዋል። በአድማው ተሳትፈዋል የተባሉት ወጣቶችም እንዲሁ ታስረዋል። ነዋሪዎች ከትናንት ምሽት ጀምሮ 100 የሚሆኑ ወጣቶችና የሃገር ሽማግሌዎች በሌሊት እየታደኑ ተይዘዋል።
የአጋዚ ወታደሮች ከከተማው ለቀው እንደሚወጡ ፕሬዚዳንቱ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም፣ ዛሬም ተራራ ላይ ሰፍረው ጥብቅ ክትትል እያደረጉ ናቸው። አቶ ገዱ ቃል የገቡት ነገር አለመፈጸሙን የገለጹት ነዋሪዎች፣ ይባስ ብሎ በእለቱ በስብሰባው ላይ አስተያየት የሰጡ ወጣቶች እንዲያዙ ምክንያት ሆነዋል በማለት ወቀሳ እያሰሙ ነው።

18 የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች እና የጦር አዛዦች በተለያዩ አካባቢዎች የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ስለሚከላከሉበት ሁኔታ መተማ ላይ መከሩ

የኢሳት አስታማማኝ ምንጮች እንደገለጹት በመተማ ዮሃንስ በቅርቡ የደረሰውን የቦንብ ጥቃት ተከትሎ 10 የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች ለ5 ተከታታይ ቀናት ስብሰባ አካሂደዋል። 
በሰብሰባው ላይ የተሳተፉት የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች፣ ከኮሎኔልነት በላይ ማዕረግ ያላቸው በሱዳን ድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሰው ጦር አዛዦእ እንዲሁም በጭልጋ፣ አዘዞ፣ ደባርቅና አካባቢዋ የሚንቀሳቀሰው ጦር አዛዦች ናቸው። የስብሰባው ዋና አጀንዳ በተለያዩ አካባቢዎች የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን እንዴት መመከት አለብን የሚል እንደነበር የሚገልጹት ምንጮች፣ ስብሰባው በከፍተኛ ሚስጢር እና በወታደራዊ ጥበቃ የተካሄደ ነው። 

በሰሜን ወሎ መቄት ከተማ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። ከወልዲያ ወደ ደቡብ ጎንደር የሚወስደው መንገድም ተዘግቷል።

በጎንደር ዩኒቨርስቲ ተቃውሞ መነሳቱም ታውቋል። በሰሜን ወሎ በተለያዩ አካባቢዎች ውጥረት መቀጠሉ ታውቋል። መቄት ከወልዲያ ወደ ደቡብ ጎንደር በሚወስደው መንገድ ላይ ከሚገኙ ከተሞች አንዷ ናት። በተለያዩ ጊዜያት በተነሱ ተቃውሞዎች መቄት ስሟ ሳይጠቀስ አያልፍም። ሰሞኑንም ሰሜን ወሎን ካዳረሰው ተቃውሞ ጋር ተነስታለች። የመቄት ነዋሪዎች የወልዲያውን ጭፍጨፋ ፣ በመርሳና ቆቦ የተፈጸሙትን የአጋዚ ሰራዊት የግድያ ርምጃዎች በመኮነን ዛሬ ለተቃውሞ አደባባይ መውጣታቸውን ለኢሳት የደረሰው መረጃ አመልክቷል። የህወሀት አገዛዝን እንዲያበቃ በመጠየቅ በተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከአገዛዙ ታጣቂዎች ጋር ግጭት ተፈጥሮ በርካታ ሰዎች መጎዳታቸው ታውቋል። በዚህም መንገድ ተዘግቷል። ከሰሜን ወሎ ወደ ደቡብ ጎንደር የሚያመሩ ተሽከርካሪዎች ለሰዓታት ቆመው እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል። በወልዲያ ዛሬ ውጥረት ነግሶ የዋለ ሲሆን ዛሬም ከተማዋ ሙሉ በሙሉ ከእንቅስቃሴ ውጭ ሆና መዋሏን

በኢትዮጵያ ያለው የውጭ ምንዛሪ እጥረት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ በመቀጠሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኤምባሲዎችና ለቆንስላ ጽህፈት ቤቶች የሚመድበው ገንዘብ መቸገሩ ታወቀ።

 ኤምባሲዎቹ እየገጠማቸው ያለውን የውጭ ምንዛሪ እጥረት ለመቅረፍ በየሀገሩ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በኢንቨስትመንት ማበረታቻና በቤት መስሪያ ቦታ እያግባቡ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ቤት እንዲልኩ ታዘዋል። ወደ ሀገር ቤት የሚልኩት የውጭ ምንዛሪ እየታየ ለኤምባሲዎቹ የበጀት ጉድለቱ እንደሚሸፈንላቸውም ተመልክቷል። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያላት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለሳምንታት ብቻ የሚበቃ እንደሆነ እየተገለጸ ባለበት በአሁኑ ወቅት መንግስት የውጭ ምንዛሪ እጥረቱን በብድርና የውጭ ቦንድ በመግዛት ለመሸፈን የሚያደርገው ጥረት አልተሳካም። የሚሰጠው ብድርም ይሁን እርዳታ በሀገሪቱ ያለውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ዕጥረት የማይቀርፍ እጅግ አነስተኛ ሆኖ በመገኘቱ ከመድሃኒትና ነዳጅ ወጪዎች ባሻገር ሌሎች የወጭ ንግድ እቃዎችን ወደ ሀገር ቤት ለማስገባት ከፍተኛ ችግር መፈጠሩም ታውቋል። ይህም በውጭ ሀገር ለሚገኙ ኤምባሲዎችና ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች በውጭ ምንዛሪ የሚመደበው በጀትም ላይ ተጽእኖ በማድረጉ ነው ኤምባሲዎቹ የውጭ ምንዛሪ እንዲያሰባስቡ ጥሪ የተደረገላቸው። ቤት በማህበርም ይሁን በግል መመራት የሚፈልጉ፣ በግልም ይሁን በማህበር ሕንጻ መገንባት ለሚፈልጉ በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች በቂ ቦታዎች አሉ በሚል በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን

ኤች አር 128 በመባል የሚታወቀውና በአሜሪካ ምክር ቤት የወጣው ረቂቅ ሕገ ውሳኔ በምክር ቤቱ ለድምጽ አሰጣጥ እንደሚቀርብ ታወቀ።

 ሕገ ውሳኔው ለድምጽ አሰጣጥ የሚቀርበው በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት መርማሪዎች በሀገሪቱ እየተፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት እንዲያጣሩ እስከሚቀጥለው ወር ድረስ የማይፈቅድ ከሆነ ነው። የኢትዮጵያ አሜሪካውያን ሲቪክ ካውንስል ከሌሎች የማህበረሰቡ ተወካዮችና ድርጅቶች ጋር በመሆን ትላንት ከአሜሪካ ምክር ቤት አባላትና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ተወካይ ጋ ኤች አር 128 ሕገ ውሳኔ ስለሚጸድቅበት መንገድ ተወያይተዋል። ውይይቱ በአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት የአብላጫ ወንበር ያለው የሪፐብሊካን ፓርቲ መሪ ኬቨን ማካርቲ ከኢትዮጵያውያኑ ተወካዮች ጋር ተገናኝተው ለመነጋገር በጠየቁት መሰረት የተካሄደ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። በቀጣዩ ወር ማለትም እስከ የካቲት 8 ድረስ በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ የተባበሩት መንግስታት አጣሪ ቡድን በሃገሪቱ ገብቶ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን እንዲያጣራ ፍቃድ እንዲሰጥ ቀነ ገደብ ለማስቀመጥ ስምምነት ላይ መደረሱን የውይይቱ ተሳታፊዎች ከጋዜጠኞች ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል። አገዛዙ ለዚህ የማይተባበር ከሆነ ግን ኤች አር 128 በመባል የሚታወቀውና በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት እንዲከበርና የመብት ጥሰት የፈጸሙትን በሕግ ተጠያቂ የሚያደርገው ሕግ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ መለስተኛ የበረራ ሰራተኞቹን ወደ አሜሪካና ካናዳ እንዳይበሩ እገዳ መጣሉ ተነገረ።

 አየር መንገዱ የበረራ ሰራተኞቹ ወደ አሜሪካና ካናዳ እንዳይበሩ የከለከለው ወደ ሁለቱ ሀገራት የሚመጡ ባልደረቦቹ በመጡበት ጥገኝነት እየጠየቁ በመቅረታቸው ነው። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፈው ወር ብቻ 21 የበረራ ሰራተኞች ለስራ በወጡበት በካናዳና አሜሪካ ቀርተዋል። እናም የአየር መንገዱ መለስተኛ የበረራ ሰራተኞች በተለይ በአሜሪካና በካናዳ ለስራ እንደወጡ በዛው ሳይመለሱ መቅረታቸውን ተከትሎ ከእንግዲህ ወደዛ በሚደረጉ በረራዎች ላይ መለስተኛ የበረራ ሰራተኞች እንዳይሰማሩ ድርጅቱ እገዳ እንደጣለባቸው ፎርቹን ዘግቧል። አየር መንገዱ ይህን እገዳ ሲጥል ስራው በማንና እንዴት እንደሚተካ የገለጸው ነገር ግን የለም። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ብዙዎቹ ለበረራ ወደ ውጭ ሲወጡ የኮንትሮባንድ እቃ በማመላለስ በሕገወጥ ንግድ ስራ ተሰማርተው መገኘታቸውን ተከትሎ እቃ እንዳያመላልሱ መከልከላቸው ይታወሳል። አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚሰሩ መለስተኛ የበረራ ሰራተኞች አሜሪካና ካናዳ መጓዝ እንደማይችሉ መመሪያ ወጥቷል። በአየር መንገዱ ለበረራ ወደ ውጭ የሚመደቡ ሰራተኞች የ5 መቶ ሺ ብር ዋስትና እንዲያመጡ ይገደዳሉ። እናም ከአየር መንገዱ ጋር በሰራተኝነት በረው የሚጠፉ ሰራተኞች የስያዙትን የዋስትና ገንዘብ እንደሚያጡ ነው የሚነገረው። በኢትዮጵያ አየር መንገድ በዘር መድልኦ ምክንያት በርካታ ሰራተኞች ስራ ለመልቀቅ እንደሚገደዱ ነው የሚነገረው። በአየር መንገዱ የትግራይ ተወላጆች ከጽዳት እስከ ዋና ስራ አስፈጻሚ ድረስ በብዛት እንደሚገኙ ብዙዎቹ ይመሰክራሉ። እናም በአድልኦና በቢሮክራሲያዊ ትጽእኖዎች ሳቢያ አየር መንገዱን እየለቀቁ የሚሄዱ ሰራተኞች መበራከታቸው ይነገራል።

Monday, January 29, 2018

መረጃ
በወልድያ ተቃውሞው ቀጥሎአል። የአጋዚ ወታደሮች አስላቃሽ ጭስ በመበተን ሰልፈኛውን ለመበተን ሞክረዋል። ይሁን እንጅ ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው። የቀበሌው ጽፈት ቤት ተቃጥሎአል። መንገዶች በመላ ተዘጋግተዋል።
በጎብዬ ህዝብን ለመሰብሰብ የሞከረው የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ያለው አባተ፣ በሽማግሌዎች እርዳታ ተርፎ ከከተማ እንዲወጣ ተደርጓል። 
በመርሳ ወታደሮች ተሰብስበው በነበረበት ወቅት በተወረወረ ፈንጅ 18 ወታደሮች ጉዳት ደርሶባቸዋል። 16 ወታደሮች ህክምና አግኝተው ከሆስፒታል ሲወጡ፣ ሁለት ወታደሮች ግን በጽኑ ቆስለው ወልድያ ልዩ ክትትል በሚደረግበት ክፍል ውስጥ ተኝተዋል። 
የአርበኞች ግንቦት7 የሰሜን እዝ ከወልድያ ጀምሮ ባሉት ከተሞች፣ “ተነሱ” የሚሉ የጥሪ ወረቀቶችን መበተኑን ወረቀቶችን ያነበቡ የአይን እማኞች ገልጸዋል።

በቅርቡ ከወህኒ የወጡት ዶክተር መረራ ጉዲና በአምቦና በጊንጪ ከተሞች ከፍተኛ አቀባበል ተደረገላቸው።

 በተለይ በአምቦ ስታዲየም በተካሄደው የአቀባበል ስለስርአት በመቶ ሺ የሚቆጠር ሕዝብ እንደታደመም ለማወቅ ተችሏል። ወደ አምቦ ባደረጉት ጉዞ በሌሎች የምዕራብ ሸዋ ከተሞች በተለይም በጊንጪ ከፍተኛ አቀባበል የጠበቃቸውና በአምቦ ስታዲየም የጀግና አቀባበል የተደረገላቸው ዶክተር መረራ ጉዲና ለሕዝቡ በተለይም ለወጣቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ትግሉ እንደሚቀጥል ቃል የገቡት ዶክተር መረራ ጉዲና እስከ ፍጻሜው አብረን እንሁን ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር የሆኑት ዶክተር መረራ ጉዲና ባለፉት 27 አመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል። በተለይም የኦሮሞ ብሔራዊ ኮንግረስን ከመሰረቱበት ከ1988 ጀምሮ ላለፉት 22 አመታት በፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱ የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች አንዱ መሆናቸውም ይታወቃል። ዶክተር መረራ ጉዲና የንጉሱን ስርአት በኋላም የደርግን ስርአት በመቃወም በመላው ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ መኢሶን ውስጥ ሲንቀሳቀሱ

በአዲስ አበባ አምስት ነባር መንደሮች ሊፈርሱ ነው።

ፋይል ነባሮቹን መንደሮች ለማፍረስ ደግሞ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውይይት እንደሚደረግ ታውቋል። ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት እንዲህ አይነቱ ስትራቴጂ የሕወሃት አገዛዝ አብሮ የኖረውን ሕዝብ በመበታተን ራሱ የሚፈልጋቸውን ሰዎች ለማስፈር በየጊዜው የሚነድፈው እኩይ እቅድ ነው ሲሉ እቅዱን አውግዘዋል። ሕብረተሰቡም እንዲህ አይነቱን እኩይ ተግባር በጋራ በመሆን ማስቆም ይገባዋል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። በቅርቡ ከነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዶባቸው ይፈርሳሉ የተባሉት ቤቶች 78 ሔክታር መሬት ላይ ያረፉ ናቸው ተብሏል። የከተማዋ የመሬት ልማትና ማደስ ኤጀንሲ እንደሚለው ከሆነ እነዚህ ቤቶች ሲፈርሱ የተነሺዎችን መብት ባስከበረ መልኩ ነው። ይህን የማፍረስ ስነስርአት ለማካሄድም ኤጀንሲው ሙሉ በሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል ሲል ሪፖርተር በዘገባው አስፍሯል።–ቀጣዩ ስራ ከነዋሪዎች ጋር መወያየት መሆኑን በመጠቆምም ጭምር በ2010 ሁለተኛው ግማሽ አመት ላይ ለመፍረስ እቅድ የተያዘላቸው አካባቢዎችም በአራዳ ክፍለ ከተማ አሜሪካ ግቢ ቁጥር ሁለትና ገዳም ሠፈር፣ በየካ ክፍለ ከተማ ከሾላ እስከ መገናኛ ድረስ፣ በልደታ ክፍለ ከተማ ጌጃ

በሕወሃት አገዛዝ በቅርቡ በአሜሪካ የኢሕአዴግ አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አቶ ካሳ ተክለብርሃን በቴሌ ኮንፈረስ ሲያካሂዱት የነበረው ውይይት በሕዝብ ተቃውሞ ተቋረጠ።

በአሜሪካ ከ11 ከተሞች የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን ተመርጠው ከአምባሳደር ካሳ ተክለብርሃን ጋር በስልክ ኮንፈረንስ ለመወያየት ታቅዶ ራሳቸውን ካስተዋወቁ በኋላ በጥያቄና መልስ ጊዜው ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። አቶ ካሳ ስለህዳሴና ልማት እንዲሁም ኢትዮጵያን ለውጠናል ሲሉ የስልክ ውይይት ተሳታፊዎቹ ግን መጀመሪያ ሕዝብን መግደል አቁሙ ሲሉ አምባሳደሩን አውግዘዋል። በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በሕወሃት የተሾሙት አምባሳደር ካሳ ተክለብርሃን ስራ ከጀመሩ አንድ ወር ተኩል ሳይሆናቸው ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። ገና ከመሾማቸው በተቃውሞ ላይ ያለውን ዲያስፖራ የመለወጥ አቅሙ አለኝ በማለት ሲኩራሩ እንደነበር ይነገራል። በሚኒሶታ የተመረጡ የሶማሌ ኢትዮጵያ ተወላጆችን በማነጋገር ከዲያስፖራው ጋር በአደባባይ መታየት የጀመሩት አቶ ካሳ ተክለብርሃን ትላንት በቴሌ ኮንፈረንስ ከተመረጡ ሰዎች ጋር ለመወያየት ሲሞክሩ ግን ከፍተኛ ውግዘትና ተቃውሞ ደርሶባቸዋል። አቶ ጣፋ በተባሉና የሕወሃት አገዛዝ ደጋፊ በሆኑ ግለሰብ
መረጃ
ዛሬ በደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በጩኸት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል። በከተማው የማርያም በአል ሲከበር መዋሉንና ይህንን ተከትሎ ተቃውሞ እንደነበር ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በአሁን ሰአት ደብረ ታቦር ዩንቨርስቲ ብሎክ 67 በፌደራል ፖሊሶች ተከቧል። የመካኒካል ተማሪዎች በጩኸት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል።

የወልዲያው ተቃውሞ ዳግም ተቀሰቀሰ።

Image may contain: outdoorመሀል ወልዲያ ዛሬ ጠዋት ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞ ሲደረግና የመንግስት ተቋማት ላይ ጥቃት ሲሰነዘር እንደነበርም ለማወቅ ተችሏል። ከቀትር በኋላ በቤት ውስጥ የመቀመጥ የስራ ማቆም አድማ የተመታ ሲሆን ወልዲያ ሁሉ ነገር ከእንቅስቃሴ ውጭ ሆኖ እንደዋለም ታዉቋል። ህዝባዊ አመጹ በተለያዩ ከተሞች እየተካሄደ ነው። የመርሳ ከተማ አስተዳዳሪ መገደላቸውም ታውቋል። በሲሪንቃ በርካታ ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል። መንገዶች ተዘግተዋል። የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል። የመርሳው ተቃውሞ ለሶስተኛ ቀን መቀጠሉም ይነገራል። የሰሜን ወሎ ዋና ዋና መንገዶች በሙሉ ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ህዝቡ በጥምቀት በዓል የተገደሉትን ለመዘከር የሻማ ማብራት ስነስርዓት ላይ ነበር በወልዲያ አዳጎ አካባቢ። ድንገት የመከላከያና የአጋዚ ሃይል አካባቢውን ወረረና ነገሮች ተቀያየሩ። በተኩስ እሩምታ፣ በድብደባና ሩጫ አዳጎ ሰላማዊ አየሯ በቅጽበት ደፈረሰ። ጠዋት ይህ በሆነ ከሰዓታት በኋላ መሃል ወልዲያ ፒያሳ የህዝብ አመጽ ፈነዳ። የተገኘ የመንግስት ተቋም ላይ ርምጃ ተወሰደ። ከስርዓቱ ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦች ንብረት ላይም ጥቃት ተሰነዘረ። አሁንም
መረጃ ሀዲያ ዞን
በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ አቅራቢ በምትገኘው ታችኛው አቢቾ አከባቢ የህዝብ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። በህወሀት አገዛዝ ላይ ተቃውሞ በማቅረብ የጀመረው እንቅስቃሴ ወደ ሃይል እርምጃ ተለውጦ ከአገዛዙ ጋር ግንኙነት ባላቸው ግለሶቦች ንብረቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በእስከአሁን የ10 የአገዛዙ ሰዎች ንብረቶች ላይ በእሳት የማቃጠል እርምጃ እንደተወሰደ ታውቋል።

በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ በተከሰተው ግጭት የተፈናቀሉት ሰዎች ቁጥር 1 ሚሊየን ያህል መድረሱን አለም አቀፍ ሪፖርቶች አመለከቱ።

ፋይል ስደተኞቹ በ4 መቶ ጣቢያዎች መስፈራቸውን ሪፖርቱን ያቀረቡት ተቋማት ገልጸዋል። ተፈናቃዮቹ በቂ እርዳታ እየተደረገላቸው አለመሆኑንም በሪፖርቱ ተመልክቷል። በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉት ኢትዮጵያውያን በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች በተበራከተው ግጭት ምክንያት ተዘንግተዋል። በቀደሙ ሪፖርቶች 7 መቶ ሺ ሕዝብ መፈናቀሉ ሲነገር ነው የቆየው። ኦቻ የተባለው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተቋም ከብሔራዊ አደጋና መከላከል ኮሚሽን ጋር ባካሄደው ጥናት ግን በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉት ሰዎች ቁጥር 1 ሚሊየን ያህል ተጠግቷል። እንደ ሪፖርቱ ገለጻ 857 ሺ የሚሆኑ ዜጎች መፈናቀላቸው ሲረጋገጥ ቁጥሩ ከዚህም ሊልቅ የሚችልበት ሁኔታ አለ። በሁለቱም አጎራባች ክልሎች ያለው ግጭት አሁንም እንዳልበረደ ሪፖርቱ አመልክቷል። ተፈናቃዮቹ በ4 መቶ መጠለያ ጣቢያዎች ሰፍረው እንደሚገኙም ነው ሪፖርቱ የገለጸው። ከሶማሊያ የተፈናቀሉት የኦሮሞ

Wednesday, January 24, 2018

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች በሰሜን ኢትዮጵያ (አማራ ክልል) ተደጋጋሚ ጥቃቶችን እየፈጸሙ ነው



የአግ7 አርበኞች በህወሓት ሎጆስቲክ አቅርቦት ላይ ጥቃት ፈፀሙ ፡፡
ጥር 15 ቀን 2010 ዓ/ም ከቀኑ 11:40 ሲሆን በሰሜን ወሎ ዞን ሀራ ከተማ በኩል ለህወሓት መከላከያ 12ተኛ ክፍለ ጦር አገልግሎት የሚውል አንድ ቤንዝን ነዳጅ የጫነ ቦቴ ከነ ተሳቢው እና አንድ አሱዚ መከና ደረቅ ረሽን የጫነ ተሽከርካሪ በደፈጣ ይጠብቁት በነበሩ አርበኞች በተፈፀመበት ጥቃት ሙሉ በሙሉ ነዷል ፡፡ በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ውጥረት የነገሰ ሲሆን ወደ ትግራይ የሚወስደው መንገድ ዝግ ነው ፡፡ ህወሓት ለጊዜው በአፋር በኩል መጠቀምን ቢመርጥም የአፋር ሕዝብ ቁጣ በማሳየቱ በተለይም በወልዲያ ንፁሀንን ዜጎች እየገደሉ በዚህ ማለፍ ክልክል ነው በማለት መንገድ እየዘጋ ይገኛል ፡፡ በተያያዘ ዜና ያለ ክልሉ እውቅና ከትግራይ ተንቀሳቅሶ ወደ ወልዲያ በመግባት ጅምላ ጭፍጨፋ የፈፀመው የህወሐት መከላከያ ጉዳይ ዛሬም አወዛጋቢ ሁኖ ቀጥላል ፡፡
ድል የህዝብ ነው! !
የአግ7 የሰሜን ኢትዮጵያ ዕዝ! !

Tuesday, January 23, 2018

በወልድያ እና አካባቢው ያለው ውጥረት እንዳለ ነው

ዛሬ ጥር 15 ቀን 2010 ዓም ሳምንታዊው የማክሰኞ ገባያ በወጣቶች ትዕዛዝ እንዲበተን ተደርጓል። ወጣቶቹ “ የወገኖቻችን ደም ሳይደርቅ ግብይት ማድረግ አይቻልም” የሚል አቋም በመያዝ እና ወደ ገበያው በማምራት ግብይቱ እንዳይካሄድ በማድረግ ተቃውሞአቸውን ገልጸዋል።
ከወልድያ በ 20 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጎብዬ ከተማ ላይ የከተማዋ ወጣቶች ማንኛውም እቃ የጫነ ተሽከርካሪ ወደ ሰሜን የአገሪቱ ክፍል እንዳይጓዙ ከልክለው ውለዋል። ሁለት አውቶቡሶች እና አንድ ታታ የጭነት መኪና ተሰብረዋል። የተቃውሞው መነሻ የተወሰኑ የጎብዬ ወጣቶች ቆቦ ከተማ ተወስደው በወታደሮች በኤሌክትሪክ ተገርፈው መለቀቃቸውን ተከትሎ ሕዝቡ ድርጊቱን ተቃውሞ እርምጃ በመውሰዱ ነው። 
ሃራ ከተማ ላይ ደግሞ ትናንት ምሽት 2 ሞተር ሳይክሎችና አንድ ተሽከርካሪ የተቃጠለ ሲሆን፣ በከተማዋ የተቃጠሉ ተሽከርካሪዎችን ቁጥር 6 አድርሶታል። ከ3 ቀናት በፊት የመሶቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ንብረት የሆኑ ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸው ይታወቃል።

በምስራቅ ሸዋ ዞን በአለም ጤና ከተማ በመካሄድ ላይ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞ ቢያንስ 3 ሰዎች ተገደሉ

ዛሬ ጥር 15 ቀን 2010 ዓም በተለያዩ የኦሮምያ ክልል ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች የተካሄዱ ሲሆን፣ የአጋዚ ወታደሮችም ለተቃውሞ በወጡት ዜጎች ላይ በቀጥታ በመተኮስ የሰው ህወይት አጥፍተዋል። በምስራቅ ሸዋ ዞን በአለም ጤና ከተማ ቢያንስ 3 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን፣ በርካታ ሰዎችም ቆስለዋል። ከተመቱት መካከል አንዱ ህይወቱ ወዲያውኑ ሲያልፍ የሌሎች እጣ ፋንታ አልታወቀም። በአጋዚ ድርጊት የተበሳጩ የከተማዋ ነዋሪዎች በተሽከርካሪዎች ላይ ድንጋይ በመወርወር ጉዳት አድርሰዋል። አካባቢው ለተሽከርካሪ ዝግ ሆኗል። በወለጋ መንዲ ከተማም እንዲሁ የተቃውሞ ሰልፍ ሲደረግ ውሎአል። 

የፓለቲካና የሕሊና እስረኞች ካለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱና ጥፋተኞቹም በህግ እንዲጠየቁ ሲል ለኮንሶ ሕዝብ መብት የሚታገሉ ሃይሎች ገለጹ

ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ የኮንሶ ሕዝብ የሰብዓዊ መብት ታጋዮች ኅብረት በህወሃት ኢህአዴግ አገዛዝ ካለጥፋታቸው ተወንጅለው በእስር የሚማቅቁ የፓለቲካና የሕሊና እስረኞች ካለምንም ቅድመ ሁኔታዎች እንዲለቀቁ ጠይቋል።
ከህግ አግባብ ውጪ በዜጎች ላይ እስራትና ግድያ ጨምሮ የተለያዩ የመብት ጥሰቶችን የፈጸሙ የስርዓቱ ባለስልጣናትና ትእዛዙን ተቀብለው ወንጀሉን የፈጸሙ ግለሰቦችና ተቋማት ተለይተው በህግ ሊጠየቁ ይገባል። ወንጀለኞቹ ተለይተው ጉዳያቸው በገለልተኛ አጣሪ አካል ተመርምሮ ሕጋዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው ሲል ታጋዮቹ አሳስቧል። 

ዓለም አቀፍ የክርስቲያን ኢትዮጵያውያን እህቶች ሕብረት በወልድያ በደረሰው እልቂት ሃዘኑን ገለጸ

 ህብረቱ ለኢሳት በላከው መግለጫ “ በመላው አለም የምንገኝ የወንጌላውያን አማኞች ቤተ/ክ ምእመናን እህቶች በወልድያ በደረሰው ዘግናኝ እልቂት የደረሰብን ሀዘን ከፍተኛ ነው።” ብለዋል፤፡
“ እግዚአብሔር በአምሳሉ የፈጠረውን ሰው፣ በየጊዜው እንደ ቅጠል ሲረግፍ ማየትና መስማት፣ የሁላችንንም ልብ የሰበረ ነው የሚለው ህብረቱ፣ በዚህ አሳዛኝ ጭፍጨፋ ምክንያት: ከማንም በላይ የሚጎዱት: ትውልድን አምጠው የወለዱ እናቶች፣ ጧሪ ያጡ ወላጆች፣ ወላጅ አልባ የሚሆኑ ሕፃናትና እነርሱ የሚደጉሟቸው ወገኖች በመሆናቸው: ይህ መከራቸው እኛን በሴትነታችን እጅግ እንዲሰማንና ሐዘናቸውን እንድንጋራ ግድ ብሎናል” ሲሉ ገልጸዋል።
እንደህ አይነት ዘግናኝ ግፍ የተሞላበትን ድርጊት የሚፈጽሙት ሁሉ ከዚህ ድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ የጠየቀው ህብረቱ፣ መንግስትም ይህን ድርጊት የፈጸሙትንም ሆነ ያስፈጸሙትን ለፍርድ እንዲያቀርብ እንጠይቃለን ብለዋል። 
“በተለይም የወንጌላውያን አማኞች ቤተ/ክ ዝምታን መምረጣቸው ተገቢ ነው ብለን ስለማናምን፣ በኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ ውጭ ያሉት ይህን አሳዛኝ ድርጊት እንዲኮንኑት እንጠይቃለን” በማለት ህብረቱ መግለጫውን ደምድሟል።

Wednesday, January 17, 2018

ታዋቂው ፖለቲከኛ ዶ/ር መረራ ጉዲና ጨምሮ ከመቶ በላይ እስረኞች ተፈቱ

የኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ዶ/ር መረራ ጉዲናን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞች የይቅርታ ስነስርዓቱ በሚፈቅደው መሰረት በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ይፈታሉ በማለት ፣ የፌደራል ዋና አቃቢ ህግ ከተናገሩትየሚጣረስ መግለጫ ቢሰጡም፣ ዶ/ር መረራና የተወሰኑ እስረኞች ተፈተዋል። የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማእከል ዶ/ር መረራ በሁለት ቀናት ውስጥ ይፈታሉ ተብሎ የተዘገበው ስህተት ነው በማለት ነገሪ ሌንጮን ጠቅሶ ዘግቦ ነበር። የኦፌኮ መሪ ዶ/ር መረራ ጉዲና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመጣስ በአውሮፓ ህብረት ተገኝተው የመንግስትን መልካም ስም አጥፍተዋል፣ ከአርበኞች ግንቦት7 መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ጋር ተገናኝተዋል እንዲሁም በኦሮምያ ባለው ህዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴ እጃው አለበት የሚል ውንጀላ ሲቀርብባቸው ነበር።

የሙስሊሞች የመቃብር ቦታ ይከበርልን ጥያቄው መልስ ባለመሰጡ የከሚሴ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገለጹ

የሙስሊሞች የመቃብር ቦታ ይከበርልን ጥያቄው መልስ ባለመሰጡ የከሚሴ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገለጹ
በከሚሴ ከተማ የሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች የመቃብር ስፍራቸው የቆሻሻ መጣያ በመሆኑ እንዲከበርላቸው ጥያቄ አቅርበዋል።
ከአሁን በፊት በተደረጉ ህዝባዊ ስብሰባዎች ችግሩ መኖሩን በተደጋጋሚ ገልጸው የከተማው አስተዳደር መፍትሄ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም ምንም አይነት ምላሽ ሳያገኙ መቆየታቸውን ቅሬታ አቅራቢዎች ተናግረዋል፡፡
በእስልምና እምነት በመቃብር ላይ መጸዳዳትና ቆሻሻ መጣል የተከለከለ 'ሃራም' (ሀጢያት) መሆኑን የሚያነሱት ቅሬታ አቅራቢ ፤የከተማ አስተዳድሩ ለእስልምና ተከታዩ ማህበረሰብ መስጠት ያለበትን ክብር አልሰጠም ይላሉ፡፡

በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት የብረታ ብረት አምራች ፋብሪካዎች ሊዘጉ ነው የአገሪቱ ባንኮች ምንዛሬ የማቅረብ አቅማቸው ተሟጧል

 በውጭ ምንዛሬ ተገዝተው ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ጥሬ እቃዎችን ለመግዛት የሚያስችል የውጭ ምንዛሬ በአገሪቱ በመጥፋቱ ፋብሪካዎች ካለ ምርት ፆማቸውን ውለው ለማደር ተገደዋል። በተለይ በብረታ ብረት ምርት ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች የውጭ ምንዛሬ ማግኘት የሰማይ ያህል እንደራቃቸውና የውጭ ምንዛሬ ዶላር ለማግኘት ባንኮችን ደጅ ለመጥናት መገደዳቸውን የኮተቤ ብረታ ብረት ድርጅት ባለክሲዮን አቶ አሰግድ ማሞ አስታውቀዋል።
አብዛሃኞቹ በመስኩ የተሰማሩ ባለሃብቶች ጥሪታቸውን አፍስሰው የገነቧቸው ፋብሪካዎችን ታቅፈው በጥሬ ዕቃ አቅርቦት እጥረት ምክንያት እጃቸውን አጣምረው ለመቀመጥ መገደዳቸውን ባለሃብቶቹ ገልጸዋል። ሕጋዊ ባለሃብቶች ምንዛሬ አጥተው ባሉበት ሁኔታ ግን አንዳንድ ባለሃብቶች በሕገወጥ መንገድ ምንዛሬ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል። ከውጭ በማስገባት ጤናማ ፉክክር እንዳይኖር ተደርጓል። ነገርግን አንዳንድ ባለሃብቶች ያሉዋቸውን አስመልክቶ ድርጅቶቹ እነማን እንደሆኑ በዝርዝር ከመግለጽ ግን ተቆጥበዋል።

በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ 31ኛ ተከሳሽ አቶ ጌታቸር እሸቴ የስርአቱ ሰዎች እየገደሉና እየረሸኑ ድሆች የእነሱን ሐጥያት እንዲሸከሙ እየተደረጉ ነው ሲሉ በጻፉት ድብዳቤ አስታወቁ።

በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ 31ኛ ተከሳሽ አቶ ጌታቸር እሸቴ የስርአቱ ሰዎች እየገደሉና እየረሸኑ ድሆች የእነሱን ሐጥያት እንዲሸከሙ እየተደረጉ ነው ሲሉ በጻፉት ድብዳቤ አስታወቁ። አቶ ጌታቸር እሸቴ በ30 ደቂቃ ውስጥም 9 ሰዎችን ግድለሀል ተብዬ በሀሰት ውንጀላ መከሰሴን ዓለም ይወቅልኝ በማለት ተናግረዋል። ነሐሴ 28/2008 የቂሊንጦ እስር ቤት በእሳት በጋየበት ወቅት በተደረገ ተኩስ 23 እስረኞች መገደላቸውን የህወሃት መንግስት በወቅቱ ያመነ ሲሆን የዓይን ምስክሮችና አንዳንድ ታሳሪዎች ቁጥሩ በሁለት እጥፍ እንደሚሆን ይናገራሉ ። ከዚህ ጋርም በተያያዘ 38 ሰዎች በሽብር ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው የፍርድ ሂደታቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ። ከተከሳሾቹ መካከል 31ኛው ተከሳሽ የሆኑት አቶ ጌታቸር እሸቴ ይህንን አሰቃቂ ወንጀል የስርዓቱ ሰዎች መፈጸማቸውን ዓለም ይወቅልን ሲሉ ሁኔታውን በዝርዝር ጽፈዋል። ዜጎችን እየገደሉና እየረሸኑ ዜጎችን ያለ ስራቸው የእነሱን ወንጀል የሚያሸክሙትና የፖለቲካ መልስ የሚያደርጉትን ባለስልጣናት አንድ ቀን የሰማይና ምድር ገዥ የሆነው አምላክ እንደሚያጋልጣቸው ተስፋ አለኝ ሲሉም በምሬት ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብ

የትግራይ ህዝብ ከማንም በላይ ውድ ዋጋ የከፈለ በመሆኑ መካስ አለበት ሲሉ የህወሃት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና ቃል አቀባይ ገለጹ።

የትግራይ ህዝብ ከማንም በላይ ውድ ዋጋ የከፈለ በመሆኑ መካስ አለበት ሲሉ የህወሃት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና ቃል አቀባይ ገለጹ። ቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ረዳ የህወሀትን 7ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት የትግራይን ህዝብ ለመካስ አዲሱ አመራር ቆርጦ ተነስቷል። በኢትዮጵያ በክልሎች መካከል ሰፊ የልማትና የእድገት ልዩነት ፖለቲካዊ ቀውስ በፈጠረበት በዚህን ወቅት የአቶ ጌታቸው ረዳ መግለጫ ቀውሱን ይበልጥ ሊያባብሰው እንደሚችል ታዛቢዎች ይገልጻሉ። የ2016 የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን መረጃ እንደሚያመለክተው ከህዝብ ብዛትና ከቆዳ ስፋት አንጻር በትግራይ ክልል የተሰራው የአስፋልት መንገድ ከሌሎች ክልሎች በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ነው። በሆስፒታል ተጠቃሚነት የትግራይ ክልል በቀዳሚ ስፍራ ላይ ይገኛል። በትግራይ አንድ ሆስፒታል ለ285ሺህ ሰው

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በብዛት የተበላሸ ብድር ያላቸው ድርጅቶች ሰፋፊ የእርሻ ፕሮጀክቶችና የቱርክ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የሆነው አይካ አዲስ መሆኑን አስታወቀ።

 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በብዛት የተበላሸ ብድር ያላቸው ድርጅቶች ሰፋፊ የእርሻ ፕሮጀክቶችና የቱርክ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የሆነው አይካ አዲስ መሆኑን አስታወቀ። በባንኩ ከፍተኛ የተበላሸ ብድር እንዳለበት የሚታወቀውና የህወሃት ንብረት የሆነው ኤፈርት ግን በዚህ ዝርዝር ውስጥ አልተካተተም። የህወሃት ንብረት የሆነው ሬዲዮ ፋና የባንኩን ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ክፍሌ ሃይለየሱስን ጠቅሶ እንደዘገበው የልማት ባንክ በተለያዩ ዘርፎች ብድር ሰጥቶ አደጋ ውስጥ ያለውን ብድር ለማስመለስ ግብረ ሃይል አቋቁሟል። ልማት ባንኩ ከሰጠው በድር ውስጥ 8 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር የተበላሸ እንደሆነም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። የተበላሸ ብድር ያለበት ደረጃ ችግር ውስጥ በመሆኑ የማስመለሱ ነገር ላባንኩ ህልውና ውሳኝ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ሪፖርተር ያናገራቸው የልማት ባንኩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ

Thursday, January 11, 2018

የሕወሃት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረጺዮን ገብረ ሚካኤልን የወሲብ ቅሌት የሚያሳይ ማስረጃ ይፋ ሆነ

Image may contain: 2 people, people smilingየሕወሃት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረጺዮን ገብረ ሚካኤልን የወሲብ ቅሌት የሚያሳይ ማስረጃ ይፋ ሆነ። ዶክተር ደብረጺዮን በወሲብ ጉዳይ ላይ የኢሜልና የኢንተርኔት ግንኙነትን የሚያጋልጥ መረጃ ተሰብሮ ወጥቷል። በወጣው መረጃ ላይ ዶክተር ደብረጺዮን ዘወትር የሚጎበኟቸውን የወሲብ ድረገጾች፣ከዝሙት አዳሪዎች ጋር ያደረጓቸውን ግንኙነቶችና ሌሎች ቅሌቶች ይፋ ሆነዋል። የትግራይ ክልልን እንዲመሩ ትላንት የተሰየሙት ዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የኤሌክትሮኒክስ መልዕክት ሳጥናቸው ተሰብሮ ይፋ የሆነው መረጃ የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን ጥያቄ ውስጥ አስገብቶታል። ከፍተኛ የስነ ምግባር ጉድለት ያለባቸው መሆኑንም አጋልጧል። የተበተኑትን መረጃዎች ትክክለኛነት በባለሙያዎች አስጠንቶ በማረጋገጥና ተጨማሪ መረጃዎችን በማካተት ሪፖርቱን በ15 ገጽ ያጠናቀረው ጋዜጠኛ አበበ ገላው ዶክተር ደብረጺዮን ከ10 በሚበልጡ የአላማችን ከተሞች የነበራቸውን ቆይታ ፈትሿል። ገብረሚካኤል መለስ በተባሉ የትግራይ ክልል የኮሚኒኬስን ጉዳዮች ሃላፊ ማህበራዊ ገጽ ላይ በይፋ ከወጣ በኋላ በሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ደጋፊዎች ዘንድ ከፍተኛ ጫጫታ የፈጠረው መረጃ ወዲያውኑ እንዲሰረዝ ተደርጓል። ሆኖም መረጃው አስቀድሞ በመበተኑ በተለያዩ ወገኖች እጅ መግባት ችሏል። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር

Ethiopia: Courts continue handing down prison terms to political prisoners

ESAT News (January 11, 2018)
Ethiopian courts, seen by many as instruments of the oppressive regime, have continued handing down prison terms to dissidents who insist terrorism charges brought against them were politically motivated.
A court in Addis Ababa today sentenced thirty-three defendants to prison terms ranging from 15 to 18 years for allegedly being members and supporters of an opposition group, Patriotic Ginbot 7.
The same court yesterday sentenced Girum Asnake to 4 years in prison for allegedly being a member of the same opposition group.

አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አመራር አባላት የሆኑ ተከሳሾች ፍርድ ቤትን ደፍራችኋል በሚል የ6 ወራት ተጨማሪ የእስራት ቅጣት ተወሰነባቸው።

 አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አመራር አባላት የሆኑ ተከሳሾች ፍርድ ቤትን ደፍራችኋል በሚል የ6 ወራት ተጨማሪ የእስራት ቅጣት ተወሰነባቸው። ውሳኔው የተለለፈው የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት የራሱን ውሳኔ በመሻር ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ለምስክርነት አይቀርቡም ሲል ውሳኔ ማሳለፉን በመቃወማቸው ነው። የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድቤት ከዚህ ቀደም በሰጠው ውሳኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ 4 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የተከሳሾች መከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወስኖ ነበር። በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ ታዘው የነበሩት ሌሎች ባለስልጣናትም አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ፣የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት ለማ መገርሳ፣የኦሕዴድ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር አብይ አህመድና ጫልቱ ናኒ በኦሮሚያ ክልል የለገዳዴ ከተማ ከንቲባ ናቸው። በኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር አባላት አቶ በቀለ ገርባና ሌሎች ተከሳሾች በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ የተሰጠባቸው እነዚሁ ከፍተኛ ባለስልጣናት ለ3 ጊዜ ያህል ፍርድቤት እንዲቀርቡ ቢታዘዙም አንዳቸውም አልተገኙም። ከዚሁ ጋር ተያይዞም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ፍርድቤት ተጠርተው ያልተገኙት ስራ ስለሚበዛባቸው ነው በሚል ደብዳቤ መጻፉ ይታወሳል። የኦሮሚያው ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳና የኦሕዴድ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር አብይ አሕመድ ግን በወቅታዊ የሀገር ጉዳይ ላይ ስብሰባ ላይ መሆናቸውን ገልጸው የቀጠሮ ቀኑ እንዲቀየርላቸው ጠይቀው

በኢትዮጵያ 33 የፖለቲካ እስረኞች ከ15 እስከ 18 አመታት የእስር ጊዜ ተፈረደባቸው።

በኢትዮጵያ 33 የፖለቲካ እስረኞች ከ15 እስከ 18 አመታት የእስር ጊዜ ተፈረደባቸው። የፊደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በእነ ሚፍታህ ሼህ ስሩር የክስ መዝገብ በግንቦት 7 የተከሰሱ 33 ግለሰቦች ላይ የፍርድ ውሳኔ ሰጥቷል። ግለሰቦቹ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው በሽብርተኝነት ስም የተከሰሱ መሆናቸው ነው የተነገረው። በክስ መዝገቡ ከተካተቱት ተከሳሾች ቀሪዎቹ ክደው በመከራከራቸው የመከላከያ ምስክር ለማቅረብ ቀጠሮ እንደተሰጣቸው ከሀገር ውስጥ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ሲባል እስረኞችን እለቃለሁ እያለ በሌላ በኩል ከፍተኛ የእስር ቅጣት እንዲወሰን ማድረጉ ብዙዎችን ግራ ያጋባ ነገር ሆኗል። በሕወሃት የሚመራው አገዛዝ የፖለቲካ እስረኞችን እለቃለሁ በሚል ለሕዝብ ቃል ከገባ በኋላ አንድም እስረኛ ለቆ አያውቅም።

በአምቦ ዩኒቨርስቲ በተነሳ ተቃውሞ ተማሪዎች መጎዳታቸው ታወቀ

በአምቦ ዩኒቨርስቲ በተነሳ ተቃውሞ ተማሪዎች መጎዳታቸው ታወቀ። ባለፈው እሁድ የገና በአል ላይ በምግብ አዳራሽ ውስጥ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ተከትሎ ግጭት መፈጠሩ የታወቀ ሲሆን እስከትላንት ድረስም መቀጠሉ ታውቋል። በዩኒቨርስቲው የሰፈረው የአጋዚ ሰራዊት ተማሪዎች ላይ ክፈኛ ድብደባ መፈጸሙን ተከትሎ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ለትምህርት ሚኒስቴር የቅሬታ ደብዳቤ መላካቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የተወሰኑ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው ወተዋል። የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ትምህርት ሚኒስቴር ጥቃት የፈጸሙትን የጸጥታ ሃይሎች ጉዳይ እንዲያጣራ ጠይቀዋል። በሌላ በኩል በአዳማ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታጅበው ወደ መማሪያ ክፍላቸው እንደሚሄዱ ታውቋል። ተቃውሞ ተለይቶት የማያውቀው የአምቦ ዩኒቨርስቲ ሰሞኑን ቀውስ ገጥሞት ሰንብቷል። ያለፈው እሁድ የገና በዓል የአውዳመት ዝግጅት ላይ በተፈጠረው ተቃውሞ በግቢው ሰፍሮ የሚገኘው የአጋዚ ጦር በተማሪዎች መኝታ ክፍል ሰብሮ በመግባት ድብደባ መፈጸሙን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ካለፈው እሁድ ጀምሮ በዩኒቨርስቲው ተቃውሞ እየተደረገ መሆኑን የሚገልጹት የኢሳት ምንጮች የተጎዱ ተማሪዎች ቁጥር ለመግለጽ እንደማይቻል ጠቅሰዋል። ሰኞ ምሽት ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበርም ተናግረዋል። በአሁኑ

በኢትዮጵያ የተከሰተውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ በተጠራ አድማና ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ሰላም ባስና ዳሽን ቢራ አስታወቁ

 በኢትዮጵያ የተከሰተውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ በተጠራ አድማና ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ሰላም ባስና ዳሽን ቢራ አስታወቁ። የቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት ያነጋገራቸው የሁለቱ ድርጅቶች ሃላፊዎች እንዳሉት በአድማውና በጥቃቱ ምክንያት ከኪሳራ ባሻገር ህዝቡ በአገልግሎታችን እንዳይጠቀም ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጥሯል። ሰላም ባስ በአራት መስመሮች አገልግሎት ማቋረጡን ሲያሳውቅ ዳሽን ቢራ በተለይ በባህርዳር ከፍተኛ የተቀባይነት ቀውስ እንደገጠመው ገልጿል። ለቢቢሲ አማርኛ ቃለ መጠይቅ የሰጡት የሰላም ባስ አገልግሎት ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ሀጎስ አባይ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተፈጠረው ችግር ምክንያት ህዝቡ በሰላም ባስ ለመጠቀም ፍራቻ አድሮበታል። በዚህም ምክንያት የገቢ መቀነስ ታይቷል ሲሉ ገልጸዋል። በቅርቡ ወደቁልቢ ገብርዔል በመጓዝ ላይ በነበሩ አራት የሰላም ባስ አውቶብሶች ላይ ጥቃት ተሰንዝሮ መስታወቶቻቸው መሰባበሩን አቶ ሀጎስ አስታውሰዋል። ሁለት የሰላም ባሶች በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች መቃጠላቸውንም ስራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል። ሰላም ባስ በመላ ሀገሪቱ በ17 መስመሮች አገልግሎት እንደሚሰጥ የተናገሩት አቶ ሀጎስ በተፈጠረው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ምክንያት የአራቱ መስመሮች አገልግሎት መቋረጡን ገልጸዋል። በዚህም መሰረት በሀረር፣ ድሬዳዋ፣

ኢትዮጵያ ሕጻናትን በጉዲፈቻ ወደ ውጭ ለመውሰድ የሚፈቅደውን ሕግ በፓርላማ በኩል አገደች

ኢትዮጵያ ሕጻናትን በጉዲፈቻ ወደ ውጭ ለመውሰድ የሚፈቅደውን ሕግ በፓርላማ በኩል አገደች። ሕጉ የታገደው በጉዲፈቻ ስም በውጭ ዜጎች ከኢትዮጵያ የሚወሰዱ ሕጻናት ለበርካታ ጊዜያት በአሳዳጊዎቻቸው ከፍተኛ በደል እንደሚደርስባቸው በመታወቁ ነው ተብሏል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በጉዲፈቻ መልክ ከኢትዮጵያ የሚወሰዱ ሕጻናት ብዙዎቹ ደብዛቸው ሲጠፋ አንዳንዶቹ ደግሞ እስከመገደል ደርሰዋል። ሕጻናትን በጉዲፈቻ ለማሳደግ በሚል ከኢትዮጵያ በርካታ ልጆች ከሀገር እንዲወጡ ተደርጓል። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ1999 ወዲህ ብቻ 15 ሺ ሕጻናት በጉዲፈቻ መልክ ወደ አሜሪካ መወሰዳቸው ነው የሚታወቀው። ሕጻናቱ በዚህ መልክ ከሀገር ከወጡ በኋላ ግን ደህንነታቸው በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ እንደማይታወቅ ነው የሚነገረው። ብዙዎቹ በአሳዳጊዎቻቸው ከፍተኛ በደልና እንግልት

Tuesday, January 9, 2018

የኦሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ በቄሮዎች ላይ ምርመራ ማካሄድ ህገወጥ ነው አለ።

 የኦሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ በቄሮዎች ላይ ምርመራ ማካሄድ ህገወጥ ነው አለ። ቢሮው ይህን ያስታወቀው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ባለፈው ሳምንት በቄሮዎች ላይ ምርመራ እያደረኩ ነው ማለቱን ተከትሎ ነው። የቢሮው የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ እንደተናገሩት የፌደራል ፖሊስ እያደረኩ ነው ስላለው ምርመራ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የሚያውቀው ነገር የለም። የሃላፊው መግለጫ ምርመራው ትኩረት ለማስቀየር የታለመ ነው የሚሉ የፖለቲካ ምሁራንን አስተያየት የሚያጠናክር ነው ተብሏል። ምርመራው ስለመጀመሩ ብዙዎች ጥርጣሬ አላቸው። የህወሀት አገዛዝ ከገባበት ቀውስ ለመውጣት የህዝብን የትኩረት አቅጣጫ ያስቀይሳሉ ያላቸውን የተለያዩ የማደናገሪያ ፕሮፖጋንዳዎች ላይ መጠመዱን የፖለቲካ ምሁራን ይገልጻሉ። ባለፈው ሳምንት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርት በቀረበ ጊዜ በቄሮች ላይ ምርመራ ተጀምሯል ያሉት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አሰፋ አብዩ በምስራቅ ሀረርጌ በቄሮዎች እንቅስቃሴ የመንግስት መዋቅር ፈረሷል፣ እስረኞች እንዲለቀቁ ተደርገዋል፣ የመከላከያ ሰራዊት ተልዕኮ ተስተጓጉሏል ብለዋል። ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ቃለመጠይቅ የሰጡት የኦሮሚያ ክልል የፍትህ ቢሮ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ አቶ ታዬ ደንደአ የክልሉ መንግስት ስለጉዳዩ ምንም

የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ሕወሃት/ንብረት የሆነው ኤፈርት በ745 ሚሊየን ብር ያስገነባው የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካ ስራ ጀመረ።

የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት በሳምንት 1 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኘው ይህ ፋብሪካ በቀን እስከ 5 ኪሎ ግራም ወርቅ ያመርታል። ኤፈርት ከዚህም በተጨማሪ በመላዋ ትግራይ የማዕድን ማልማት ስራዎችን ለማከናወን ከ8 የአሜሪካና የካናዳ ኩባንያዎች ጋር ስምምነት ላይ ደርሷል። በዚህ ስምምነት መሰረትም በትንሹ በአመት ከአንድ ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ለማስገኘት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የኤፈርት ዋና ሃላፊ ወይዘሮ አዜብ መስፍን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እንደዘገበው ትላንት በሽሬ እንደስላሴ የተገነባው ይህ የወርቅ ፋብሪካ ኢሕአዴግ ወደ ስልጣን ከመጣ ወዲህ የተገነባ የመጀመሪያው ፋብሪካ ነው። በኢትዮጵያ ከ33 አመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገነባ እንደሆነም ተመልክቷል። ሌላው የሕወሃት ንብረት የሆነው መስፍን ኢንጂነሪንግ እንደገነባው የተገለጸው ይህ የወርቅ ፋብሪካ 745 ሚሊየን ብር እንደወጣበትም ታውቋል። ሜሌ የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ የወርቅ ፋብሪካ በቀን ከ4 እስከ 5

በኦሮምያ ወጣቶች እየታሰሩ ነው

ወጣቶቹ “የስርዓት ለውጥ እንፈልጋለን፣ አቶ ለማ ለውጡን ማምጣት ከቻለ ጥሩ ካልቻለ ግን እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን” ይላሉ
በክልሉ ከሚካሄደው ያልተቋረጠ የለውጥ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ፣ የተለያዩ ወጣቶች እየተያዙ መሆኑን ኢሳት ያነጋገራቸው ወጣቶች ገልጸዋል። በኦሮምኛ ቄሮ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ለለውጥ በመታገል ላይ የሚገኙት ወጣቶች፣ የለማ መገርሳ አስተዳደር የክልሉን ወጣቶችን ከእስር እንዲታደግ ጠይቀዋል።
ወጣቶቹ እንደገለጹት በጉድሩ ወረዳ ባለፉት 6 ቀናት ከ 16 በላይ ተማሪዎች ተይዘው ታስረዋል። የታሰሩት ወጣቶች ቁጥር በርካታ መሆኑን የሚገልጹት ወጣቶች፣ የለማ አስተዳደር በአንድ በኩል የታሰሩትን እየፈታ በሌላ በኩል ደግሞ ወጣቶች እየታሰሩ መሆኑ ግራ እንዳጋባቸው ተናግረዋል። 

ሁሉንም ተቃዋሚዎች ያካተተ አገራዊ ውይይት እንዲደረግ ጥሪ አቀረበ

በጂንካ የተጠራው የወላጆች ስብሰባ ሳይካሄድ ቀረ
“በመላው ኢትዮጵያ የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተከትሎ ገዥው ፓርቲ የሰጠው መግለጫ እውነተኛ የሆነ አገራዊ መግባባት እንዲፈጠር ሁሉንም የአገሪቱን ዜጋ ሊያሳትፍ ይገባል” ሲሉ የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት /ኦህዲኅ/ ም/ሊቀመንበር አቶ ዓለማየሁ መኮንን ገለጹ።
የገዥው ህወሃት/ኢህአዴግ ባለስልጣናት ባለፈው ሳምንት በጋራ የሰጡትን መግለጫ አስመልክቶ የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ኅብረት /ኦህዲኅ/ ም/ሊቀመንበር አራት ነጥቦችን አስቀምጠዋል።
’’የጥፋቱ ወይንም የወንጀሉ ጥፋተኛ መሆናቸውንና ወንጀለኛ መሆናቸውን ማመናቸውን እንቀበላለን። ለፍትህ፣ ለሰላምና ለዴሞክራሲ የጮሁትን የጻፉትን አፍነው በማሰራቸውና ወንጀሉ የአፈናው ውጤት መሆኑን ማመናቸውን እንስማማለን። ስርዓት እንዲወገድ የኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄ ማንሳቱንና ብሄራዊ መግባባት መፈጠር እንዳለበት ማመናቸው መልካም ነው። ነገር ግን ብሄራዊ ጥሪ አድርገው አገር ቤት

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ሃኪሞችን እና የሆስፒታል አመራሮችን ለማግኘት ለፍርድ ቤት ጽፈውት የነበረው ደብዳቤ ይፋ ሆነ

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ወርዶፋ ፣ ጥቅምት 22 ቀን 2010 ዓም ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የልደታ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት በጻፉት ደብዳቤ ሃኪሞችን እና የሆስፒታል አመራሮችን ለማግኘት ትእዛዝ እንዲጻፍላቸው ጠይቀው የነበረ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ግን ትዕዛዝ ሳይሰጥ ቀርቷል። 
ዶ/ር ፍቅሩ በደብዳቤያቸው “ ቀደም ሲል በሲውዲን ሃገር ሰርቼ ያገኘሁትን ገንዘብ እና 40 ዓመታት በልዩ የልብ ሕክምና ያዳበርኩትን እውቀት ይዤ ወደ ሃገሬ በመመለስ በሃገራችን ሁለት የልብ እና የልብ ነክ ሕክምና ሆሰፒታሎችን በማቋቋም ቀደም ሲል በህክምና እጦት ወደ ውጪ ሄደው መታከም ባለመቻላቸው ህይወታቸውን ያጡ የነበሩ የበርካታ ዜጎችን ህይወት መታደግ እንዲችሉ እና ባለፉት 11 ዓመታት ከ50 ሺ (ሃምሳ ሺ) ለሚበልጡ ዜጎች በአነስተኛ ዋጋ ህክምና እንዲያገኙ “ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

Thursday, January 4, 2018

በኢትዮጵያ ወህኒ ቤት የሚገኙ ፖለቲከኞችና ሌሎች እስረኞች ለሀገራዊ መግባባት ሲባል እንዲፈቱ ተወስኗል በሚል በመንግስት የተሰጠው መግለጫ በመንግስት ሲሰረዝና ሲደለዝ መዋሉ ታወቀ

 በኢትዮጵያ ወህኒ ቤት የሚገኙ ፖለቲከኞችና ሌሎች እስረኞች ለሀገራዊ መግባባት ሲባል እንዲፈቱ ተወስኗል በሚል በመንግስት የተሰጠው መግለጫ በመንግስት ሲሰረዝና ሲደለዝ መዋሉ ታወቀ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ማህበራዊ ገጽ ላይ ሰባት ጊዜ እየተሰረዘና እየታረመ መጻፉ ታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለም የመንግስት መግለጫን ተከትሎ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶችና ሌሎች ወገኖች በጉዳዩ ላይ አስተያየት ሰጥተዋል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል የሰቆቃው ዘመን ፍጻሜ እንደሚሆን ተስፋውን ሲገልጽ ሂውማን ራይትስ ዎች ውሳኔው መቼና እንዴት ተግባራዊ ይሆናል ሲል ጠይቋል። አቃቢ ሕግ ጉዳያቸው በሕግ ተይዞ በእስር ላይ የሚገኙ የተለያዩ ፖለቲከኞች የተሻለ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠርና የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ክሳቸው ተቋርጦ እንዲለቀቁ ተወስኗል በሚል በቅድሚያ ይፋ የሆነው መግለጫ በሶስት ሰአታት ጊዜ ውስጥ ስድስት ጊዜ ተሰርዞና ተደልዞ ለሰባተኛ ጊዜ የቀረበው መግለጫ በወንጀል የተፈረደባቸውና በወንጀል የተጠረጠሩ የሚለውን ጨምሮ ቁጥሩንም አንዳንድ በሚል ገድቦታል። ሕገመንግስቱ በሚፈቅደው የሚል በመጨመርና ማጣራት በማድረግ የሚለውን በማከል በሕገመንግስቱ መሰረት የሚለውን በመጨመር በሶስት ሰአታት ውስጥ ሲሰረዝና

የሕወሃት ንብረት የሆነው ኢፈርት ከሁለት ኩባንያዎች ጋር በፈጠረው የሶስትዮሽ ግንኙነት አዲስ የጣራ ክዳን ፋብሪካ 2 ቢሊየን በሚጠጋ ብር ሊገነባ ነው።

የሕወሃት ንብረት የሆነው ኢፈርት ከሁለት ኩባንያዎች ጋር በፈጠረው የሶስትዮሽ ግንኙነት አዲስ የጣራ ክዳን ፋብሪካ 2 ቢሊየን በሚጠጋ ብር ሊገነባ ነው። የኢፈርት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ አዜብ መስፍን ስምምነቱን ከሲንጋፖሩ ኩባንያ ኩስቶና ፈርፋክስ አፍሪካ ፈንድ ከተባሉ ኩባንያዎች ጋር ተፈራርመዋል። ፋብሪካውን በመቀሌ ወይም አቤዲ በተባሉ የትግራይ አካባቢዎች ለመገንባት የቦታ መረጣ እየተካሄደ ይገኛል። በስምምነቱ መሰረት መሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ከሁለቱ ኩባንያዎች ጋር ተጣምሮ የ60 በመቶ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል። ቀሪዎቹ 2 ኩባንያዎች ደግሞ የ40 በመቶ ድርሻ ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ኢኮኖሚውን የተቆጣጠረው የሕዉሃቱ ኤፈርት በትግራይ የሚቋቋመው የጣራ ክዳን ፋብሪካ ምርቱን ለመኖሪያ ሕንጻዎችና ለጋራ መኖሪያ ቤቶች መገንቢያነት እንደሚያውል አስታውቋል። ፋብሪካው የጂብሰም ሰሌዳዎችና ቀለማትን ለማምረት እቅድ እንዳለውም ወ/ሮ አዜብ መስፍን ገልጸዋል። በክልሎች መካከል የልማት ልዩነቶች መፈጠራቸውን ያመነው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ግምገማ ችግሩን ለማስተካከል እንደሚሰራ መግለፁ ይታወሳል። ከሕወሃት ስራ አስፈፃሚነት የታገዱት ወ/ሮ አዜብ መስፍን አሁንም ግዙፉን የኤፈርት ኩባንያ በመምራት መሶቦ በትግራይ ለሚያስፋፋው ፋብሪካ ተጨማሪ እድል ፈጥረዋል። የኤፈርት አጠቃላይ ካፒታል 8 ቢሊየን ብር ሲሆን በስሩም ከ50 ሺህ የሚበልጡ ሰራተኞችን ያስተዳድራል። ከኢትዮጵያ ልማት ባንክና ንግድ ባንኮች ያለምንም የመያዣ ዋስትና በቢሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ሳይመለስ ባክኖ መቅረቱም ሲዘገብ መቆየቱ ይታወሳል።

ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ፣መምህርና የፖለቲካ ጉዳዮች ጸሐፊ ኢብራሂም ሻፊ በስደት በሚኖርባት ኬኒያ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

Image may contain: 1 person, smiling, closeupታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ፣መምህርና የፖለቲካ ጉዳዮች ጸሐፊ ኢብራሂም ሻፊ በስደት በሚኖርባት ኬኒያ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። በሌላ በኩል አንጋፋው የህክምና ባለሙያ ፕሮፌሰር ዕደማርያም ጸጋ ተሻለ በ83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ኢብሮ በአጭሩ የሚጠራበት ስሙ ነው። መምህር ሆኖ አገልግሏል። የስፖርት ጋዜጠኝነቱ በሰፊው ይነሳለታል። የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በሚሰጣቸው ትንተናዎችም ይታወቃል። በሰብዓዊ መብቶች መከበር ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግም አስተዋጽኦው የጎላ ነው።–ጋዜጠኛና መምህር ኢብራሂም ሻፊ። ያስተማራቸው ተማሪዎቹ፣ የስፖርት ቤተሰቡ፣ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በቅርበት የሚከታተለው ሁሉ ዛሬ ጥሩ ዜና አልሰማም። በህወሀት አገዛዝ አፈና ለስደት የተዳረገው ኢብራሂም ሻፊ ትላንት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። ጋዜጠኛ ኢብራሂም በ1997 እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ከተካሄደው ምርጫ በኋላ በጅምላ ታፍሰው በተለያዩ እስር ቤቶች ከተጋዙት መካከል አንዱ ነበር። በሸዋሮቢት በእስር ላይ በነበረ ጊዜ በአገዛዙ ታጣቂዎች በደረሰበት ድብደባና ማሰቃየት የተነሳ ለህልፈት ለተዳረገበት በሽታ መንስዔ እንደሆነው የቅርብ ጓደኞቹ ይናገራሉ። በስፖርት ጋዜጠኝነቱ ትልቅ ተቀባይነትን ያተረፈው ኢብራሂም በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የአገዛዙን ተግባራት

በሰሜን ሸዋ አጣዬ የሰላም ባስ አውቶብስ በህዝብ ተቃውሞ እንዳይንቀሳቀስ ተደረገ።

በሰሜን ሸዋ አጣዬ የሰላም ባስ አውቶብስ በህዝብ ተቃውሞ እንዳይንቀሳቀስ ተደረገ። ከትላንት በስቲያ የሆነው ዛሬም ድረስ አልበረደም። የአጣዬን ከተማ መሃል ለመሃል የሚከፍለው ድልድይ ላይ የተጀመረው ተቃውሞ ሰፍቶ በፌደራል ፖሊስና በታጠቁ ሃይሎች መካከል ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንደተካሄደ የደረሰን መረጃ አመልክቷል። መነሻው ድልድዩን ሊያቋርጥ የተቃረበን የሰላም ባስ አውቶብስን ነዋሪው በማስቆሙ ነው። ምክንያቱ ደግሞ የህዝብ ሀብት ተዘርፎ የተመሰረተው የትግራይ መልሶ ማቋቋሚያ ድርጅት ኢፈርት ንብረት የሆነው የሰላም ባስ አውቶብስ ላይ ተቃውሞ ለማሳየት እንደሆነ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ህዝቡ የሰላም ባስ አውቶብስ የአጣዬን ድልድይ እንደተቃረብ እንዳይሻገር ማገቱ የተገለጸ ሲሆን ፌደራል ፖሊስ ተኩስ በመክፈት ለመበተን ላደረገው ጥረት የአጸፋ ምላሽ እንደተሰጠው ለማወቅ ተችሏል። ህዝቡ በድንጋይና የታጠቀው በመሳሪያ ከፌደራል ፖሊስ ጋር መግጠሙንም በመረጃው ተመልክቷል። ስለደረሰው ጉዳት የታወቀ ነገር ባይኖርም እስከዛሬ ድረስ ውጥረት እንዳለ ታውቋል። የሰላም ባስ አውቶቡስ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች በተነሱት ህዝባዊ ተቃውሞዎች የጥቃት ዒላማ ሆኗል። በቅርቡ በወሎ፣ ውጫሌና ኦርጌሳ የሰላም ባስ አውቶቡሶች ላይ ጥቃት የተፈጸመ ሲሆን ባለፈው

Wednesday, January 3, 2018

በቂሊንጦ ወህኒ ቤት የሚገኙት የመቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ እሳቸውንና አቶ በቀለ ገርባን ለማስገደል ትዕዛዝ ተላልፎ እንደነበር አስታወቁ።

 በቂሊንጦ ወህኒ ቤት የሚገኙት የመቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ እሳቸውንና አቶ በቀለ ገርባን ለማስገደል ትዕዛዝ ተላልፎ እንደነበር አስታወቁ። የቂሊንጦ እስርቤት የደህንነትና ጥበቃ ሃላፊ በነበሩት ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም ወልዳይ ተላልፎ የነበረው ትዕዛዝ በእስር ቤቱ ፖሊሶች እምቢተኝነት ሳይሳካ መቅረቱንም አስታውቀዋል። ይሄ መረጃ የወጣው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በእነ መቶ አለቃ ማስረሽ ሰጤ የክስ መዝገብ የተከሰሱት ሰዎች ላይ የሚሰጠው ምስክርነት በተሰማበት ወቅት ነበር። ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የነበረውን የትናንት ታህሳስ 24 /2017 ውሎ በመረጃ መረቡ ላይ አስፍሮታል። በዋናነት በችሎቱ ይታይ የነበረው በእነ የመቶ አለቃ ማስረሽ ሰጤ የክስ መዝገብ የተከሰሱት ሰዎች ላይ የሚሰጠው ምስክርነት ነበር። በችሎቱ ቀረበው የምስክርነት ቃላቸውን ይሰጡ የነበሩት ደግሞ የቂሊንጦ እስርቤት የደህንነትና ጥበቃ ሃላፊ የነበሩት ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም ወልዳይ ናቸው። የመቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ ጠያቂ ዋና ኦፊሰር ገብረማርያም ደግሞ ተጠያቂ በሆኑበት በዚህ መድረክ ላይ ፍርድ ቤቱም ጣልቃ እየገባ አስታራቂ የሚመስሉ ሀሳቦችን ለመሰንዘር ሲሞክር ተስተውሏል። ተከሳሹ የመቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ በዋናነት

የፖለቲካ እስረኞች ይፈታሉ መባሉን ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች እየቀረቡ ነው

ህወሃት/ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ዛሬ በጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ አማካኝነት በሰጠው መግለጫ በእስር ላይ የሚገኙ የፖለቲከኛ እስረኞች እንደሚፈቱ አስታውቋል። 
"በፈፀሙት ወንጀል ምክንያት በፍርድ ቤት የተፈረደባቸው ወይም ደግሞ በአቃቤ ህግ ጉዳያቸው ተይዞ በእስር የሚገኙ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትን ጨምሮ ሌሎች ግለሰቦችም የተሻለ ሃገራዊ መግባባት ለመፍጠርና የዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት በማሰብ ክሳቸው ተቋርጦ ወይም በይቅርታ እንዲለቀቁ ተወስነኗል::" ማለታቸውን የገዢው ፓርቲ ልሳናት ዘግበዋል።
በመግለጫው ላይ “አንዳንድ የፖለቲካ አባላትን ጨምሮ” የሚለው አገላለጽ ላይፈቱ የሚችሉ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ የሚያመለክት መሆኑን አስተያየቶች እየተሰጡ ነው።
ክሳቸው የሚቋረጠው ወይም በይቅርታ የሚፈቱትም በምህረት ህግና ህገመንግሥቱ በሚፈቅደው መልኩ ተገቢው ማጣራት ተደርጎ እንደሆነም መግለጫው አመልክቷል። 

ፖለቲካ እስረኞች መፈታት ለሰብአዊ መብት መከበር ጥሩ ጅምር ቢሆንም ወንጀል ፈጻሚዎች ሳይጠየቁ የሚያመልጡበት እንዳይሆን አምነስቲ ጠየቀ

ፖለቲካ እስረኞች መፈታት ለሰብአዊ መብት መከበር ጥሩ ጅምር ቢሆንም ወንጀል ፈጻሚዎች ሳይጠየቁ የሚያመልጡበት እንዳይሆን አምነስቲ ጠየቀ
ታዋቂው የሰብአዊ መብት ድርጅት፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ የፖለቲካ እስረኞች ይፈታሉ መባሉ በኢትዮጵያ ለሰብአዊ መብት መከበር አዲስ ምዕራፍ መከፈት ሊሆን ይችላል ብሎአል።
እስረኞቹ ቀድሞውንም መታሰር አልነበረባቸው የሚለው ድርጅቱ፣ ወሳኔው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ላይ ተግባራዊ እንዲሆን ጠይቋል። የጸረ ሽብር ህጉን ጨምሮ ሌሎች አፋኝ ህጎችም እንዲሰረዙ አምነስቲ ጠይቋል።
ለአመታት ስቃይ መፈጸሚያ ካምፕ ሆኖ ሲያገለግል የቆየው ማእከላዊ እስር ቤት እንደሚዘጋ መነገሩ መልካም ቢሆንም፣ በግቢው ውስጥ ሲፈጸም የነበረውን ወንጀል ለማንጻት መሆን እንደሌለበትም ድርጅቱ አስታውሷል። በአገሪቱ ሲፈጸሙ የቆዩት ወንጀሎች በሙሉ ምርመራ ተደርጎባቸው ወንጀለኞች በጥፋታቸው የሚቀጡበት አሰራር ሲፈጠር ብቻ የሰብአዊ መብት መከበር እድል ይኖራል ያለው አምነስቲ፣ ከ1983 ዓም ጀምሮ አድራሻቸው የጠፉ ዜጎች ላይ ምርመራ ማድረግና መግለጽ እንደሚገባም ድርጅቱ አስታውቋል።

የእድሜ ልክ እስር የተፈረደበት እሸቱ አለሙ ይግባኝ ጠየቀ

የሆላንድና የኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት ያለው የ63 አመቱ አቶ እሸቱ አለሙ ዘ ሄግ በሚገኘው የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት እድሜ ልክ እስር ከተፈረደበት በሁዋላ ይግባኝ መጠየቁ ተዘግቧል። እሸቱ በእስር ላይ የነበሩ 75 ሰዎችን መግደሉን ፣ ዜጎችን ያለፍድር ቤት ትእዛዝ እያወጣ ሲገድልና ሲያሰቃይ እንደነበር በፍርድ ውሳኔው ላይ ተመልክቷል።
እሸቱ በ75 ሰዎች ላይ አብዮታዊ እርምጃ እንዲወስድባቸው ያዘዘበት ወረቀት መገኘሁት ለውሳኔው መነሻ ቢሆንም፣ ጠበቃው ሳንደር አርትስ ግን የሰነዱ ትክክልኛነት አልተረጋገጠም በማለት ይግባኝ ጠይቀዋል። 
የ እሸቱ ጠበቃ የሆኑት ሳንደር አርትስ እሸቱ አብዮታዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ያዘዘበት ወረቀት ትክክለኛነት አልተረጋገጠም፣ እንዲሁም አንዳንድ ምስክሮች ሊጠየቁ አይገባም ነበር በማለት

Tuesday, January 2, 2018

ህወሃትን ለመቆጣጠር የሚደረገው ትንቅንቅን እንደቀጠለ ነው

ህወሃት ከወር በላይ ለፈጀ ጊዜ ግምገማ በማድረግ የአመራር ለውጥ እንዳደረገ ቢናገርም፣ በድርጅቱ ውስጥ ያለው ሽኩቻ አሁንም እንደቀጠለ ነው። የህወሃት ማዕከል ሆኖ ለመውጣት ሶስት ሃይሎች በዋናነት እየተፋለሙ መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ። የደህነንቱ ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ በአቶ ስብሃት ነጋ ታግዞ የወ/ሮ አዜብንና የአቶ አባይ ወልዱን ጥምረት ለመስበር ቢችልም፣ በጄ/ል ሳሞራ የኑስ በኩል የተፈጠረውን ሰንሰለት መስበር አልቻለም። አቶ ጌታቸው አሰፋ በቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት እና በአቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ሴራ ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር በመጋጨቱ ስልጣኑን ለማጣት ጫፍ ደርሶ በነበረበት ወቅት፣ አቦይ ስብሃት መለስን አሳምነው ለተወሰነ ጊዜ በስልጣን ላይ እንዲቆይ አድርገውት የነበረ ሲሆን፣ የአቶ መለስ ድንገተኛ ህልፈት ለወ/ሮ አዜብ፣ ለአባይ ወልዱና በእነሱ ዙሪያ ተሰልፈው ለነበሩ ሃይሎች ሁሉ መርዶ ይዘ ሲመጣ ለአቶ ጌታቸው ግን የደስታ ብስራት እንደነበረ ምንጮች ይገልጻሉ። አባይ ወልዱ ወደ ስልጣን ከመጣበት ቀን ጀምሮ ብቸኛ ደጋፊው አቶ መለስ ዜናዊ

በአርበኞች ግንቦት7 ስም በተከሰሱት ላይ እስከ 16 ዓመት የሚደርስ እስራት ተፈረደ

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በእነ ጌታሁን በየነ ክስ መዝገብ በተከሰሱት 9 ግለሰቦች ላይ እስከ 16 ዓመት የሚደርስ ፍርድ አስተላልፏልል። 1ኛ ተከሳሽ ጌታሁን በየነ 9ኛ አመት ፣ 2ኛ ተከሳሽ ዶ/ር አስናቀ አባይነህ እና 5ኛ ተከሳሽ አለማየሁ ንጉሴ 16 አመት ከ6ወር፣ 4ኛ ተከሳሽ ብራዚል እንግዳ 15 አመት ተፈርዶባቸዋል። 
7ኛ ተከሳሽ ያምላክነህ ገዛኸኝ፣ 8ኛ ተከሳሽ አብዱ ሙሳ እና 14ኛ ተከሳሽ ደመላሽ ቦጋለ ደግሞ እያንዳንዳቸው በ5 አመት፣ 12ኛ ተከሳሽ መቶ አለቃ ፍቅሬ እሸቱ 4 አመት ከአራት ወር እንዲሁም 13ኛ ተከሳሽ ባንተወሰን አበበ 3አመት ከ10 ወር ተፈርዶባቸዋል።
ተከሳሾቹ የተላለፈባቸውን ውሳኔ እንደሰሙ "የታገልነው የህይወት መስዋዕትነት ለመክፈል ነው፣ እናንተ ዳኞች ከእነ ሳሞራና አባይ ፀኃዬ በላይ ትጠየቃላችሁ፣ ወያኔ አንድ አመት አይቆይም፣ የጫካ ውላችሁ አይሳካም፣ እኛ የታገልነው ለመቶ ሚሊዮን ህዝብ ነው፣ ህወሓት ይቀበራል፣ነፃ እንወጣለን፣ ከግንቦት7 ጋር ወደፊት ግንቦት7 ያሸንፋል " ሲሉ ተናግረዋል። 

በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች ህዝባዊ ተቃውሞ ሲካሄድ ዋለ። በኢንጪኒ አደአበርጋ ህዝብ አደባባይ በመውጣት የህወሀትን ስርዓት አውግዟል።

 በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች ህዝባዊ ተቃውሞ ሲካሄድ ዋለ። በኢንጪኒ አደአበርጋ ህዝብ አደባባይ በመውጣት የህወሀትን ስርዓት አውግዟል። በአዳማ ዩኒቨርስቲ 18 ተማሪዎች ተባረዋል። የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል። በምስራቅ ወለጋ በገሊላ የአጋዚ ወታደሮችና ህዝቡ ፍጥጫ ውስጥ እንዳሉም የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በሌላ በኩል ትላንት በወልዲያ ተቀስቅሶ የነበረውን የህዝብ ተቃውሞ ተከትሎ በአካባቢው ተጨማሪ ሃይል መግባቱን ለማወቅ ተችሏል። ዛሬ ጠዋት ምስራቅ ወለጋ ዞን ገሊላ በተሰኘች አነስተኛ ከተማ ሶስት ኦራል ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ገብተዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የጫኑት ተሽከርካሪዎቹ ለምን ዓላማ ወደ ከተማዋ እንደገቡ አልታወቀም። ህዝቡ ተቃውሞ አንስቷል። ወደከተማዋ እንዳይዘልቁ በመደረጋቸው በአቅራቢያ ሰፍረው እንደሚገኙ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በህዝቡና በሰራዊቱ መካከል ከፍተኛ ፍጥጫ የተፈጠረ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል። በኢንጪኒ አደአበርጋ ዛሬ ህዝብ አደባባይ በመውጣት ተቃውሞውን አሰምቷል። አደአበርጋ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ተከታታይ ተቃውሞ እየተደረገባት ሲሆን ተቃውሞ እንዲቆም ያደርጋል ብሎ አገዛዙ እምነት የጣለበት የኢህአዴግ መግለጫ ከወጣም በኋላ እምቢተኝነቱ መቀጠሉን የሚያመላክት ነው ተብሏል። በኢንጪኒም በዛሬው ትዕይንተ ህዝብ ነዋሪው ግልብጥ ብሎ በመውጣት የህወሀት መንግስት ከስልጣን እንዲወርድ ጠይቋል። በሌላ በኩል የፋሲል ከነማ የእግር ኳስ ቡድን አዳማ ሲገባ በተደረገው አቀባበል ከፍተኛ ሚና የተጫወቱት የአዳማ ዩኒቨርስቲ የአማራና የኦሮሞ ተማሪዎች የሚደርስባቸው ወከባ ቀጥሎ በዛሬው ዕለት 18

በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል በመንግስት ላይ የተጀመረው ተቃውሞ አሁንም መቀጠሉ ተገለጸ

በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል በመንግስት ላይ የተጀመረው ተቃውሞ አሁንም መቀጠሉ ተገለጸ። ዛሬ ባሻምቡ ወለጋ በኦሮምኛና በአማርኛ የተጻፉ መፈክሮችን ይዘው አደባባይ የወጡት ሰልፈኞች የኦሮሞና የአማራ ሕዝብ አንድ ነው ሲሉ ተደምጠዋል። የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የኦሮሚያ ክልል መሪዎች ወደ ባህርዳር ያደረጉት ጉዞና የሁለቱን ክልሎች ትብብር መርህ አልባ ሲል ማውገዙ ይታወሳል። የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መግለጫ ትብብሩን ባጣጣለ ማግስት ግን በአማርኛ የተጻፈ መፈክር ጭምር ይዘው በአማርኛም የተቃውሞ ድምጻቸውን ያሰሙት የሻምቡ ወለጋ ነዋሪዎች ናቸው። ለመግለጫው የሰጡት አጸፋ ስለመሆኑም የተለያዩ አስተያየቶች በመቅረብ ላይ ናቸው። “አንድ ነን መቼም አንለያይም” የሚል መፈክር በማለት የተቅውሞ ድምጽእቸውን ሲያሰሙ በምስልና በድምጽ የሚያዩትና የሚደመጡት የሻምቡ

በአማራ ሳይንት ከሚገኘው ተድባበ ማርያም ገዳም ጽላት መሰረቁን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ።

በአማራ ሳይንት ከሚገኘው ተድባበ ማርያም ገዳም ጽላት መሰረቁን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። በዚህም የአካባቢው ምዕመናን የተቃውሞ ድምጻቸውን በማሰማት ላይ መሆናቸው ታውቋል። በሌላም በኩል በምዕመናን ተቃውሞ ሲቀርብባቸው የቆየው የአዲስ አበባው ሳህሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ተደብደበው ሆስፒታል መግባታቸው ታውቋል። በደቡብ ወሎ አማራ ሳይንት ወረዳ የሚገኘው የጥንታዊው የተድባበ ማርያም ገዳም በስሩ ከሚገኙት 12 አብያተክርስቲያናት የአንደኛው የመድሃኒአለም ቤተክርስቲያን ጽላት መሰረቁ የታወቀው በቅርቡ ነው። ሕዝቡም ጽላቱ እንዲመለስና የዘረፋትም ለፍርድ እንዲቀርቡ በመጠየቅ ላይ ናቸው። የገዳሙ አስተዳዳሪ ሆነው የተሾሙት ሃላፊ የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ ወደ ለንደን ከተጓዙም 5 ወራት ማስቆጠራቸው ታውቋል። አስተዳዳሪው ማህተሙ ላይ ቆልፈው ወይንም ይዘው በመሄዳቸው ስራዎች ተስተጓጉለዋል የሚል ተቃውሞም በመቅረብ ላይ ይገኛል። በጽላቱ መሰረቅ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጡ ምዕመናኑ

በግንቦት 7 ስም በሽብር ወንጀል ተከሰው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጉዳያቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተከሳሾች ከሳሞራና አባይ ጸሃዬ በላይ ተጠያቂ ናችሁ ሲሉ ዳኞቹን በችሎት ላይ መናገራቸው ታወቀ

 በግንቦት 7 ስም በሽብር ወንጀል ተከሰው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጉዳያቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተከሳሾች ከሳሞራና አባይ ጸሃዬ በላይ ተጠያቂ ናችሁ ሲሉ ዳኞቹን በችሎት ላይ መናገራቸው ታወቀ። ፍርድ ቤቱም በተከሳሾቹ ላይ እስከ 16 አመታት የሚዘልቅ እስራት የወሰነ ሲሆን ተከሳሾቹም ለሀገራችን ስንል የምንከፍለው ዋጋ ነው ሲሉ በድርጊታቸው እንደሚኮሩ ገልጸዋል። በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ችሎት የቀረቡትና በእነ ጌታሁን በየነ የክስ መዝገብ የተዘረዘሩት 9 ተከሳሾች በፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል። የቅጣት ውሳኔውም የተከተለው በዚህ ፍርድ ቤት ውሳኔ ስለማናገኝ አንከላከልም ማለታቸውን ተከትሎ ነው። ፍርድ ቤቱም ከ3 አመት እስከ 16 አመት የሚዘልቅ የእስራት ውሳኔን አሳልፎባቸዋል። ተከሳሾቹም መንግስታቸው አንድ አመት ስለማይቆይ አያሳስበንም ሲሉ ለፍርድ ቤቱ መመለሳቸው ተመልክቷል። በእነ ጌታሁን የክስ መዝገብ የተከሰሱትና በግንቦት 7 አባልነት በሽብር ድርጊት ተሳትፋችኋል የሚል ክስ ከቀረበባቸው 14 ተከሳሾች ባለፈው ሕዳር

Monday, January 1, 2018

የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ ያወጣው መግለጫ ሕዝብን ለማታለል ያለመና ከዚህ ቀደም ካወጣቸው መግለጫዎች የተለየ አለመሆኑን አስተያየታቸውን ለኢሳት የሰጡ ምሁራንና ፖለቲከኞች ገለጹ።

የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ ያወጣው መግለጫ ሕዝብን ለማታለል ያለመና ከዚህ ቀደም ካወጣቸው መግለጫዎች የተለየ አለመሆኑን አስተያየታቸውን ለኢሳት የሰጡ ምሁራንና ፖለቲከኞች ገለጹ። በኢትዮጵያ ለተፈጠረው ፖለቲካዊ ቀውስ የኢሕአዴግ አመራር ሙሉ ሃላፊነትን እወስዳለሁ ሲል በመግለጫው ማስፈሩ ከቃላት ጋጋታ ያልዘለለ ነው ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። እናም ሕዝቡ የጀመረውን ትግል አጠናክሮ በመቀጠል ለነጻነት የተጀመረውን ጉዞ ማፋጠን ያስፈልጋል ብለዋል። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ/ኦፌኮ/ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ጥሩነህ ገምታ ለኢሳት እንደገለጹት “የኢሕአዴግ መግለጫ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ቀውስ የሚፈታ ሳይሆን የሚያባብስ ነው።” መግለጫውም ገዢው ፓርቲ ከሕዝብ የተነጠለ መሆኑን ከማብራራት ያለፈ ስለመፍትሄው ያለውም ነገር የለም ብለዋል። እንዲያውም ሕዝቡ ለመብቱ የሚያካሂደውን ትግል በሃይል

የኦሮሚያ ክልል ፖሊስን የደንብ ልብስ በመዝረፍ በአምቦ ከተማ ዘረፋና ድብደባ ሲፈጽሙ የነበሩ ግለሰቦች መያዛቸውን የአምቦ ከተማ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽሕፈት ቤት አስታወቀ

የኦሮሚያ ክልል ፖሊስን የደንብ ልብስ በመዝረፍ በአምቦ ከተማ ዘረፋና ድብደባ ሲፈጽሙ የነበሩ ግለሰቦች መያዛቸውን የአምቦ ከተማ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። የመንግስትና የፓርቲ መገናኛ ብዙሃንም የግለሰቦቹን መያዝ በዘገባቸው ላይ አስፍረዋል። በሌላ በኩል የወጡ መረጃዎች እንዳመለከቱት ሶስቱም ዘራፊዎች የትግራይ ክልል ተወላጆች ሲሆኑ ስማቸውም ይፋ ሆኗል። አንዳንድ የፓለቲካ ተንታኞች እንደሚገምቱት ድርጊቱ ከተራ ዘረፋነቱ ይልቅ በሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት የተቀነባበረ ሊሆን ይችላል። የአምቦ ከተማ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤትን ጠቅሶ የሕወሃት ንብረት የሆነው ሬዲዮ ፋና እንደዘገበው የኦሮሚያ ክልል አድማ በታኝ ፖሊሶችን ልብስ በመልበስ ዘረፋ ሲፈጽሙ የተያዙት ሶስት ግለሰቦች ናቸው። በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች የዘረፋ ወንጀል ሲፈጽሙና በነዋሪው ላይ አካላዊ ጉዳት ሲያደርሱ

በዩኒቨርስቲዎች በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ ወደቤታቸው የሄዱ ተማሪዎች ጥሪ ቢደረግላቸውም መመለስ እንዳልቻሉ የመንግስት ሪፖርት አመለከተ።

በዩኒቨርስቲዎች በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ ወደቤታቸው የሄዱ ተማሪዎች ጥሪ ቢደረግላቸውም መመለስ እንዳልቻሉ የመንግስት ሪፖርት አመለከተ። ሪፖርቱ እንዳመለከተው በዩኒቨርቲዎች ውስጥ ያለው ፖለቲካዊ ቀውስ ከባድ ደረጃ ላይ ይገኛል። እናም ችግሩ መፍትሄ ካላገኘ የባሰ ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል ሪፖርቱ ይገልጻል። በኢትዮጵያ የተቀሰቀሰውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ግጭት ተቀስቅሶ በነበረባቸው 19 ዩኒቨርስቲዎች በመዟዟር ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው የመንግስት ግብረሃይል ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል። የገብረ ሃይሉ አካል የሆኑ አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ሪፖርቱን መነሻ አድርገው እንደገለጹት የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላትና ተማሪዎች በሀገሪቱ ባለው የፖለቲካ ቀውስ አሁንም በመታመስ ላይ ናቸው። ተማሪዎቹ በብሔር በመደራጀት እርስበርሳቸው በፍራቻ አይን እየተያዩ እንደሆነም ሪፖርቱ ያመለክታል። ይህን ስሜት መቀየር ካልተቻለም አሁን ካለው የባሰ ቀውስ በዩኒቨርቲዎች ውስጥ ሊከሰት እንደሚችል በሪፖርቱ ተጠቁሟል። በግጭቱ ምክንያት ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱት ተማሪዎች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ወደ የተቋማቱ ለመመለስ ፍላጎት አላሳዩም ተብሏል። እንደ ሪፖርቱ ገለጻ የተማሪዎች ስጋት አሁንም ግጭት አይቀርም ከሚል ስጋት ነው። አብዛኞቹ ዩኒቨርስቲዎች ትምህርት ጀምረው ለተማሪዎች ጥሪ ቢያደርጉም ብዙዎቹ ተማሪዎች ለመመለስ ፍቃደኛ አይደሉም ነው የተባለው። የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌቴ እንደሚሉት በዩኒቨርስቲዎች ለተነሳው ግጭት ዋነኛ ምክንያት ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ጉዳዮች ናቸው። በዚህ ምክንያት በተከሰቱ ግጭቶችም የ4 ተማሪዎች ሕይወት እንዳለፈ አረጋግጠዋል። እሳቸው ይህን ይበሉ እንጂ በግጭቱ የሞቱ ተማሪዎች ቁጥር ግን ከዚህ በላይ ነው። የዩኒቨርስቲ ተማሪዎቹ በአብዛኛው ያነሷቸው ጉዳዮች በግጭት የተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ ይደረግላቸው፣በሕዝብ ላይ የሚካሄደው ግድያ ይቁም የሚሉና ለብሔር መለያየትና ግጭት ምክንያት የሆነው የአገዛዙ ፖሊሲዎች ናቸው የሚል ነው።

በሊቢያ ከ400 በላይ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ችግር ውስጥ መሆናቸው ተገለጸ።

 በሊቢያ ከ400 በላይ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ችግር ውስጥ መሆናቸው ተገለጸ። አማጽያኑ በሚቆጣጠሩት ግዛት በስደት የገቡ ኢትዮጵያውያን በአንድ መጋዘን ውስጥ ታጭቀው በስቃይ ውስጥ እንደሚገኙም ታውቋል። በቅርቡ ብቻ 5 ኢትዮጵያውያን በድብደባና በበሽታ መሞታቸውንም የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ፋይል የኢትዮጵያ መንግስት እንዲደርስልን በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ በችግር ላይ ያሉት ኢትዮጵያውያን ለኢሳት ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያኑ ወገን ይድረስልን ሲሉም ጥሪ አድርገዋል። አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ሊቢያ የገቡት ሀገር ቤት የህዝብ ንቅናቄ በተከሰተ ሰሞን ነው። በተለይም ከኦሮሚያ፣ ከአማራና ከአዲስ አበባ አካባቢዎች በርካታ ኢትዮጵያውያን ሀገር ጥለው ወጥተዋል። በሱዳን አቋርጠው መዳረሻቸው አውሮፓ እንዲሆን አልመው፡ ሊቢያ ሲደርሱ የገጠማቸው ግን የሸሹትና ከሀገር ያስወጣቸው ስቃይና መከራ ሆኗል። ከሊቢያ መውጣት አልቻሉም። ወደኋላ መመለስም የሚሞከር አልሆነም። በመጋዘን ውስጥ ታጭቀው ከአንድ ዓመት በላይ የሆናቸው ከ2500 በላይ ኢትዮጵያውያን ኤርትራውያንና የሌሎች ሀገራት ዜጎች አሁን ያሉበት ሁኔታ አደገኛ መሆኑን ያነጋገርናቸው ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል።

በኦሮሚያ ክልል ቡኖ በደሌ ዞን ገቺና ዲዴሳ ወረዳዎች በህወሀት መንግስት የተቀነባበረ የማፈናቀል ዘመቻ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ።

Image may contain: one or more people, crowd and outdoorበኦሮሚያ ክልል ቡኖ በደሌ ዞን ገቺና ዲዴሳ ወረዳዎች በህወሀት መንግስት የተቀነባበረ የማፈናቀል ዘመቻ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ። ከደርግ መንግስት የስልጣን ዘመን ጀምሮ በአካባቢው የሰፈሩና በአብዛኛው ከአማራ የመጡ ኢትዮጵያውያን ሆን ተብሎ ለዘመናት ከሚኖሩበት ቦታ እንዲለቁ ጫና እየተደረገባቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በሌላ በኩል ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ በምዕራብ ሀረርጌ ዳሮ ለቡ ወረዳ የሶማሌ ልዩ ሃይልና የአጋዚ ሰራዊት በጋራ ህዝቡን እያሸበሩት መሆኑን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ኦፌኮ አንድ አባል ተገደሎብኛል ሲልም አስታውቋል። ፋይል ቡኖ በደሌ አሁንም ተነስቷል። ባለፈው የአማራ ተወላጆች የሆኑ ነባር የአካባቢው ነዋሪዎች ላይ በህወሀት መንግስት የተቀነባበረ የማፈናቀል ርምጃ ተወስዶ ነበር። በህዝብ ተቃውሞ ምክንያት ርምጃው ቆሞ የተፈናቀሉትም ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ መደረጉ ይታወሳል። የፖለቲካ ምሁራን እንደሚሉት በኢትዮጵያውያን መሃል ግጭት በመፍጠር የስልጣን እድሜውን ለማራዘም የሚንቀሳቀሰው የህወሃት