Monday, October 31, 2016

በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ ለተጨማሪ 6 ወራት ስጋት ሆኖ እንደሚቀጥል ተገለጸ


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ እኤአ እስከ 2017 አጋማሽ ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ድርጅት (UNOCHA) ዛሬ ሰኞ ባወጣው ሪፖርት አስታወቀ።
ድርቁ አርብቶ አደር በሆኑ በደቡብና በምስራቅ የአገሪቷ አካባቢዎች ማለትም በባሌ፣ ጉጂና፣ ቦረና ዞኖች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል። ግጦሽ እና የውሃ አቅርቦት እየቀነሰ በመምጣቱ የቀንድ ከብቶች አካላቸው በተጎሳቆለ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ይኸው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ድርጅት (UNOCHA) ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

አዲስ የተመሰረተው የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ እድገትና ብልጽግናን የሚያመጣ የፌዴራል ስርዓት መገንባት ዋነኛ አላማው መሆኑን አስታወቀ


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
በአራት የፖለቲካ ድርጅቶች የተመሰረተው የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ እድገትና ብልጽግናን የሚያመጣ የፌዴራል ስርዓት መገንባት ዋነኛ አላማው መሆኑን አስታወቀ።
በሃገራዊ ንቅናቄው የምስረታው ስነስርዓት ላይ ያወጣው የጋራ መግለጫ እንደሚያመለክተው ብሄር ብሄረሰቦች መብታቸው የተከበረባትና ሉዓላዊነቷ የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን መመስረት የህብረቱ ዋነኛ ዓላም መሆኑ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ በኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ በአርበኞች ግንቦት ሰባት፣ በአፋር ህዝብ ፓርቲ፣ እና በሲዳማ ህዝቦች ዴሞክራሲያው ንቅናቄ የተፈጠረ ህብረት መሆኑን በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ተገልጿል።

ሲራጅ ፈርጌሳ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ተከትሎ የታሰሩትን ሰዎች ቁጥር ለመግለጽ ፈቃደኛ አይደሉም


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ የተደነገገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ የታሰሩ ሰዎችን ቁጥር ለመግለጽ የመከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈርጌሳ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተዘገበ።
የኮማንድ ፖስቱ ዋና ጸሃፊ ተደርገው የተሰየሙት የመከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈርጌሳ ዕሁድ በሰጡት መግለጫ፣ 2ሺህ ሰዎች ምክር ተሰጥቷቸው ተለቀዋል ቢሉም የታሰሩትን ቁጥር ለመገለጽ ግን ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተመልክቷል።

በኢትዮጵያ በሶስት ሳምንት ጊዜ ውስጥ አንድ ሺህ ያህል ሰው መገደሉን የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ አስታወቀ


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
ለአንድ አመት ያህል በዘለቀውና በኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል በቀጠለው ግድያ በሶስት ሳምንት ጊዜ ውስጥ አንድ ሺህ ያህል ሰው መገደሉን የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ አስታወቀ።
ድርጅቱ ዕሁድ ጥቅምት 20 ቀን 2009 እንዳስታወቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ የተገደሉት ሰዎች ቁጥር 1ሺ ሲደርስ 40ሺ ሰዎች ደግሞ ታስረዋል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በኦሮሚያ ክልል ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ አባብሶታል በማለት ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ጥሪ ያቀረበው የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ፣ በሶስት ሳምንት ውስጥ የተገደሉት ሰዎች 1ሺ ሰዎች ስለመድረሳቸው ያገኘውን መረጃ ለማረጋገጥ መቸገሩን የገለጸ ሲሆን፣ ይህም የግንኙነት መስመሮች በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሙሉ በሙሉ በመቋረጣቸው የተከተለ መሆኑን አስረድቷል። የግንኙነት መስመሮቹ መቋረጥ በኦሮሚያን በአማራ ክልሎች እየተካሄደ ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ ለመደበቅ እንደሆነም አመልክቷል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል ከተካሄደውና 1ሺህ ሰዎች ከተገደሉበት ዕርምጃ የ248 ሟቾች አድራሻን በመግለጫው ያመለከተው የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ፣ ከ40 ሺህ ያህል እስረኞች የ3ሺህ 708ቱን አድራሻ አመልክቷል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆችን ተከትሎ በተካሄደው የመንግስት ሃይሎች ዕርምጃ፣ በሻላና አጄ ብቻ 85 እንዲሁም በአርሲ ነገርሌ 70 ሰዎች መገደላቸውን አስፍሯል።
የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ ይህንን የሰብዓዊ መብት ሪፖርት ለተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ም/ቤት፣ ለመንግስታቱ ማህበር የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና ለአፍሪካ ህብረት አስታውቋል።

ሶማሊያ የሚገኙ በርካታ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ትእዛዝ አንቀበልም በማለት ገሚሶቹ ሲጠፉ ሌሎች ወደ ኢትዮጵያ አንመለስም አሉ

ጥቅምት ፳፩ (ሃያ አንድ ቀን ፳፻ / ኢሳት ዜና :- የኢሳት የወታደራዊ የደህንነት ምንጮች እንደገለጹት በሶማሊያ በአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ስም ያልታቀፉትና ላለፉት 4 አመታት ከአልሸባብ ጋር ሲዋጉ ከነበሩት ወታደሮች መካከል በመቶዎች የሚቆጠሩት ትእዛዝ አንቀበልም በማለት አምጸው ከቀዩ በሁዋላ ከ70 ያላናሱት የጦር መሳሪያዎቻቸውን ሸጠው ባህር ተሻግረው ወደ አረብ አገራት ሰያቀኑ፣ ቀሪዎቹ ወደ አገሩ ከተመለሰው ጦር ጋር አብረን አንጓዝም በማለት ወደ ተለያዩ አካባቢዎች መበታተናቸውን ገልጸዋል።

አመጹ ለወራት የዘለቀ መሆኑን የገለጹት ምንጮች፣ ወታደሮች ከሚያነሱዋቸው ጥያቄዎች መካከል ዘረኝነትና የክፍያ መቋረጥ ዋነኞቹ ናቸው። በአመጹ ውስጥ የተሳተፉት ወደ ኢትዮጵያ እንደመለሱ ለማግባባት ሙከራ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም ወደ አገራቸው ሲመለሱ ከፍተኛ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በመግለጽ ማግባባቱን ሳይቀበሉት ቀርተዋል።

Ethiopia: unrest causing tourism crisis

ESAT News (October 31, 2016)
Ethiopian tourism minister contradicted the official narrative on the non effect of the state of emergency by admitting that the industry has been seriously derailed following the marshall law.
The minister, Ayisha Mohammed, said addressing a meeting that deliberated on the struggling industry that not only the number of tourists has decreased drastically following the state of emergency but those tourists who are in the country already have faced problems at check points, banks and Internet access which has been blocked by the regime.

U.S. Embassy complains of Ethiopia Internet shutdown

ESAT News (October 31, 2016)
The United States Embassy in Addis Ababa said the shutdown of Internet by the Ethiopian regime has severely affected its activities.
Responding to complaints by Ethiopians, who are having difficulty in communicating with the Embassy due to the blockage of the Internet and social media, the Embassy said it shared the frustrations of the public. “We share your frustration, as the restrictions severely affect our activities as well.”

Tuesday, October 25, 2016

አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት ህትመት ማቋረጡን አስታወቀ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሃገሪቱ በሚታተሙ የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ በማሳደሩ ምክንያት ህትመት ለማቆም መገደዱን አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት ይፋ አደረገ።
ከአስር አመት በፊት በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተመዝግቦ በወር አንድ ጊዜ ለህትመት ይበቃ የነበረው መጽሄቱ በመንግስት የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስራውን እንዳይቀጥል ማድረጉን የመጽሄቱ መስራችና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጸዳለ ለማ ለዜና ክፍላችን አስታውቃለች።
በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሲታተም የቆየው አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት በተለይ በኦሮሚያ ክልል ሲካሄድ የቆየውን ህዝባዊ ተቃውሞ ስፊ ዘገባን በመስጠት ሲዘግብ መቆየቱ ይታወሳል።
ይሁንና መጽሄቱን ተግባራዊ ተደርጎ በሚገኘው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ስራውን መቀጠል እንዳልቻለና የማይቻል አስቸጋሪ ደረጃ ውስጥ መግባቱን አዘጋጇ አስረድታለች።
የመንግስት ማተሚያ ቤቶች የህትመት ውጤታቸውን ለማሳተም ወደ ድርጅቱ ሲሄዱ ከኮማንድ ፖስቱ ፈቃድ እንዲያመጡ ይጠይቁ እንደነበር ህትመቱን ለማቆም የተገደደው የአዲስ ስታንዳርድ መጽሄቱ አዘጋጆች ገልጻለች።
መንግስት በማተሚያ ቤት በኩል እየፈጸመ ካለው ወከባ በተጨማሪ የህትመት ውጤቶችን የሚሸጡ ግለሰቦችንና የንግድ ድርጅቶች ጋዜጦችንና መጽሄቶችን ለመረከብ ፍራቻ አድሮባቸው እንደሚገኝም ታውቋል።
መጽሄቱ በአዋጁ ምክንያት ከህትመት ሲወጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን የተለያዩ አበይት ጉዳዮችን ግን በኦንላይን ህትመቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
የዚሁ አዋጅ መውጣት ተከትሎ በሃገሪቱ የሚታተሙ የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች ጋዜጦችን ማሳተም አስቸጋሪ እየሆነባቸው መምጣቱን ሲገልፁ መቆየታቸው ይታወሳል። ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው አዋጅ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በማንኛውም አካል ላይ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ስልጣንን ሰጥቷል።
ያለ-ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የቤት ለቤት ፍተሻ እንዲካሄድ የደነገገው አዋጁ፣ በመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች ላይ ቁጥጥር እንዲካሄድ ውሳኔን አስተላልፏል።
የአዋጁ መውጣትን ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ የተደረገ ሲሆን ሰዎች ለሚሰጧቸው አስተያየቶች ተጠያቂ እንደሚሆኑም ተደንግጓል። የጋዜጠኛ መብት ተማጋች ድርጅቶች አዋጁ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን አፍኖ እንደሚገኝ በመግለጽ ላይ ናቸው።
መቀመጫውን በዚህ በአሜሪካ ያደረገው ኮሚቴ ቱ ፕሮቴክት ጆርናሊስት (CPJ) ኢትዮጵያ በአለማችን በመገናኛ ብዙሃን ላይ አፈና ከሚያካሄዱ 10 ዋነኛ ሃገራት መካከል አንዷ መሆኗን ይገልጻል።
በሃገሪቱ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሁሉንም የመረጃ መለዋወጫ መንገዶች በመዝጋት ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንን አደጋ ውስጥ ከቶ እንደሚገኝ ሰኞ ባወጣው መግለጫ አስተውቋል።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአሜሪካ ህግ አውጪ አካል በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የውሳኔ ሃሳብ እንዲያጸድቅ አለም-አቀፍ ዘመቻ በማካሄድ ላይ መሆኑን ገለጸ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
የአሜሪካ ህግ አውጪ አካል የሃገሪቱ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የውሳኔ ሃሳብ እንድያጸድቅ እያካሄደ ያለው እንቅስቃሴ ተቀባይነት እንዲያገኝ አለም አቀፍ ዘመቻ በማካሄድ ላይ መሆኑን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ።
አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ የዘመቻው አካል የሆነና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር መድረክ ሰኞ በዚህ በአሜሪካ ኒው ዮርክ ከተማ መካሄዱ ታውቋል።
በሃገሪቱ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ በኒው ዮርክ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ በርካታ አለም አቀፍ ተቋማትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ግለሰቦች ተሳታፊ መሆናቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገልጿል።

ኢትዮጵያን የሚጎበኙ የውጭ ሃገር ቱሪስቶች ቁጥር በመቀነስ ላይ ነው ተባለ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ ሃገሪቱን የሚጎበኙ የውጭ ሃገር ቱሪስቶች ቁጥር በመቀነስ ላይ መሆኑ ተገልጸ።
መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉት ዲፕሎማቶች ከመዲናይቱ 40 ኪሎሜርት ርቀው እንዳይሄዱ የተቀመጠው እገዳ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጭ ሃገር ዜጎች ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩ ታውቋል።
መንግስት ዲፕሎማቶቹ ከመዲናይቱ 40 ኪሎሜርት ርቀው ሲሄዱ ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ ያለባቸው ለደህንነታቸው ነው ሲል መግለጹ ይታወሳል።

በኢትዮጵያ መንግስት የተፈጸመ የኢንተርኔት የስለላ ተግባር ክስ መቀጠል ይገባዋል ሲል አንድ ድርጅት ገለጸ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
በአንድ አሜሪካዊ ዜጋ ላይ በኢትዮጵያ መንግስት የተፈጸመ የኢንተርኔት የስለላ ተግባር ክስ መቀጠል ይገባዋል ሲል ጉዳዩን በመከታተል ላይ የሚገኘው ድርጅት ይግባኝ አቀረበ።
ኤሌክትሮኒክስ ፍሮንቲየር ፋውንዴሽን የተሰኘውና የስለላ ድርጊቱ የተፈጸመባቸውን አቶ ኪዳኔን ጉዳይ በመከታተል ላይ የሚገኘው ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስት ለፈጸመው የስለላ ድርጊት ተጠያቂ መሆን ይገባዋል ሲል ይግባኙን ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ለሚገኝ የይግባኝ ፍርድ ቤት አቅርቧል።

Wednesday, October 19, 2016

UK foreign secretary refuse to address the case of Andargachew Tsige

ESAT News (October 19, 2016)

UK’s Foreign Secretary, Boris Johnson, has on Tuesday refused to answer questions in the House of Commons about the case of Andargachew ‘Andy’ Tsege, a British father of three who is held on Ethiopia’s death row, Reprieve, an organization following the case of Andy said in a release.

Tuesday, October 18, 2016

State of emergency is militarized response: rights researcher

ESAT News (October 18, 2016)
A senior researcher with Human Rights Watch says the state of emergency declared by the TPLF regime in Ethiopia meant a militarized response that will have a counterproductive effect in the long term stability of Ethiopia.
Felix Horne, senior researcher for the Horn of Africa with HRW also said that by declaring the state of emergency, the regime showed that it is not willing to take steps for change. “It is a message that they are not willing to open up the political space. They are not willing to address many of the grievance. It is a very worrying development,” Horne said in an exclusive interview with ESAT.

Saturday, October 15, 2016

የአርበኞችግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መግለጫ

የአርበኞች ግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2009 ዓ.ም. አካሂዶ በወቅቱ የአገራችን ሁኔታዎች ተነጋግሮ ውሳኔዎችን አሳልፏል፤ ሠራዊቱንም አነጋግሯል።

Monday, October 10, 2016

በኢትዮጵያ የተከሰተው አለመረጋጋት በኢንቨስትመት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ተባለ

ኢሳት (መስከረም 30 ፥ 2008)
በኢትዮጵያ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አለመረጋጋት በሃገሪቱ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩንና ለውጭ ባለሃብቶች ስጋር መፍጠሩን አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትና ባለሙያዎች ገለጹ።
ይኸው በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች እየተካሄደ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ በኢትዮጵያ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ በሚደረገው ጥረት ላይ ሁለገብ የሆኑ መሰናክሎች እንደፈጠረ ብሪታኒያ ለንደን ከተማ በሚገኘው ብሉምበርግ ኢንተሊጀንሲ አለም አቀፍ የምጣኔ ሃብት ባለሙያ ማርክ ቦህሉንድ ለብሉምበርግ አስረድተዋል።
ባለፈው ሳምንት በቢሾፍቱ ከተማ የደረሰውን ዕልቂት ተከትሎ በተለያዩ የኦሮሚያ የክልል ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞዎች ሲካሂዱ የነበረ ሲሆን፣ በዚሁ ድርጊት 11 ፋብሪካዎች መውደማቸው ይፋ ተደርጓል።

የአውሮፓ ህብረት የማሻሻያ እርምጃዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጠየቀ

ኢሳት (መስከረም 30 ፥ 2008)
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ በሃገሪቱ የማሻሻያ ዕርምጃዎችን ተግባራዊ እንዲደረጉ ሰኞ ጠየቀ።
በወቅታዊ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በተያዘው ወር ሁለተኛ መግለጫውን ያወጣው ህብረቱ ሁሉንም ወገኖች የሚያሳትፍ የማሻሻያ ዕርምጃ እንዲወሰድ ማሳሰቡን ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ታይምስ ጋዜጣ ህብረቱን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።
ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ ስላለው አለመረጋጋት ስጋቱን ገልጾ የነበረውን የኢትዮጵያ የልማት አጋር የሆነው የአውሮፓ ህብረት በሃገሪቱ በተለይ በኦሮሚያ ክልል ለወራት የዘለቀው ህዝባዊ ተቃውሞ አሳስቦት እንደሚገኝ አመልክቷል።

“የቢሾፍቱ እልቂት ከደረሰ በሁዋላ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በአጋዚ ወታደሮች ተገድለዋል”

መስከረም ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያውያንንና የአለምን ህዝብ ድንጋጤ ውስጥ የከተተው የቢሾፍቱ እልቂት ከተከሰተ በሁዋላ የተነሱ ህዝባዊ ንቅናቄዎችን ለማፈን የአጋዚ ወታደሮች በወሰዱት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መገደላቸውን ከተለያዩ አካባቢዎች የኢሳት ወኪሎች ያሰባሱበዋቸው መረጃዎች አመልክተዋል።
ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ በተካሄደባቸው በምስራቅ ሸዋና በምዕራብ አርሲ እልቂቱ ከፍተኛ እንደነበር ወኪሎቻችን ገልጸዋል።

ዢው ፓርቲ ከወጣቶች ጋር እርቅ ለመፍጠር ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ተደረገ

መስከረም ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአማራ ክልል በባህርዳር ዙሪያ ወረዳ አንዳሳ በሚባለው አካባቢ ከጎበዝ አለቆች ጋር እርቅ መፍጠር እንፈልጋለን በሚል ገዢው ፓርቲ ያቀረበውን ጥያቄ ወጣቶች ውድቅ አደረጉት። ወጣቶቹ፣ ማንኛውም ሰው፣ ፖሊስም ሆነ ወታደር ረብሻ ቢፈጥር እርምጃ እንወስዳለን በማለት የተማማሉ ሲሆን፣ አካባቢያችንን ከእንግዲህ እኛ የመረጥናቸው እንጅ እናንተ የምትመርጡት አያስተዳድረውም በማለት በፖሊሶች እና በአመራሮች ላይ ድንጋይ በትኖ አባሯቸዋል።
ሰባት አሚት በሚባለው አካባቢ ደግሞ የቀበሌ አመራሮችን ለመምረጥ የተደረገው ሙከራ ከሽፏል። የአካባቢ ካድሬዎች ምርጫ እናስደርጋለን ብለው ቢሄዱም ህዝቡ ፈቃደኛ ሳይሆን የቀረ ሲሆን፣ የቀበሌውን ቁልፍ በመቀየር ቀበሌውን በእጁ አስገብቷል።

አቶ አንዳርጋቸውን ጽጌን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ ሪፕሪቭ የተሰኘው ተቋም ገለጸ

ኢሳት (መስከረም 30 ፥ 2008)
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ በእስር ላይ የሚገኙ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞችን ደህንነት አድጋ ውስጥ እንደከተተ አንድ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ሰኞ አስታወቀ።
መቀመጫውን በብሪታኒያ ያደረገው ሪፕሪቭ ተቋም የሃገሪቱ መንግስት በኢትዮጵያ ያለውን ወቅታዊ ጉዳይ ግምት ውስጥ በመክተት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲያመቻችና ይፋዊ ጥያቄን እንዲያቀርብ አስቧል።

Wednesday, October 5, 2016

U.S. Embassy confirms the death of American in Ethiopia

ESAT News (October 5, 2016)
The Embassy of the United States of America in Addis Ababa confirmed on Wednesday that an American was killed in Holeta, 26 miles west of the capital when a van she was travelling was struck by a stone thrown by unknown assailants.
The Embassy said the cause of death was head injury by a rock thrown by unknown assailants. ESAT broke the story Tuesday quoting credible hospital sources.

Tuesday, October 4, 2016

በአዲስ አበባ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተገለጸ

ኢሳት (መስከረም 24 ፥ 2009)
የእሬቻ ዕልቂትን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በመዛመት ላይ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ ማክሰኞ በመዲናይቱ አዲስ አበባ መቀስቀሱን እማኞች ለኢሳት ገለጹ።
በከተማዋ አንዳንድ አካባቢዎች ረፋድ ላይ የተጀመረው ተቃውሞ በአየር ጤና ብስራተ-ገብርዔል አካባቢ ተዛምቶ ማምሸቱ ታውቋል። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ በስም ያልገለጧቸው ሃይሎች ሁከት ለመፍጠር ጥረት አድርገዋል ሲል ማክሰኞ ምሽት ድርጊቱን አረጋግጧል።
በመዲናይቱ አዲስ አበባ የተስተዋለውን ይህንኑ ተቃውሞ ተከትሎ የአለም አቀፍ ድርጅት ሰራተኞች ከስራ መውጫ ሰዓታቸው አስቀድመው ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ መደረጉም ታውቋል።
ማክሰኞች ምሽት በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች በርካታ የጸጥታ ሃይሎች መሰማራታቸውንና ነዋሪዎች በጊዜ ወደ ቤት ለመግባት ጥረት ሲያደርጉ መታየቱንም እማኞች አክለው ገልጸዋል።

Monday, October 3, 2016

ከእሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ የተገደሉ ሰዎችን ድርጊት በማውገዝ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ተቃውሞዎች ተካሄዱ

ኢሳት (መስከረም 23: 2009)
በቢሾፍቱ ከተማ ዕሁድ ከእሬቻ በዓል አከባበር ጋር በተገናኘ የተገደሉ ሰዎችን ድርጊት በማውገዝ በተለያዩ የኦሮሚያ የክልል ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። 
በሃዘን ድባብ ውስጥ በምትገኘው የደብረዘይት ከተማ እንዲሁም ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው የአምቦ ከተሞችና በምስራቅ አርሲ ዞን ከእሁድ ጀምሮ ህዝቡ ተቃውሞን እያሰማን እንደሚገኝ ነዋሪዎችን ለኢሳት አስታውቀዋል። 
በምስራቅ አርሲ ዞን ስር በሚገኙ የገጠር ከተሞች እንዲሁም በሻሸመኔና አጎራባች ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞው በመካሄድ ላይ ሲሆን የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ተቃውሞውን ለመቆጣጠር የሃይል ዕርምጃን እየወሰዱ እንደሆነ ታውቋል። 

በቢሾፍቱ ከተማ በእሬቻ በዓል ላይ የሞቱ ተጨማሪ አስከሬኖች መገኘታቸው ተገለጸ

ኢሳት (መስከረም 23: 2009)
በቢሾፍቱ ከተማ ዕሁድ ከእሬቻ በዓል አከባበር ጋር በተገናኘ የሞቱ ሰዎች ተጨማሪ አስከሬን ሰኞ ጠዋት መገኘቱን እማኞች ለኢሳት ገለጹ። 
የቤተሰብ አባሎቻቸውን ያጡ በርካታ ሰዎች በሆራ ሃይቅ ዙሪያ በመሰባሰብ በሞት የተለዩ ሰዎችን በመፈለግ ላይ ሲሆኑ በትንሹ የ10 ሰዎች አስከሬን ከ24 ሰዓት በኋላ መገኘቱን የከተማዋ ነዋሪዎች አስታውቀዋል። 
የቢሾፍቱ ከተማ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ባይሳ በበኩላቸው፣ አደጋው በደረሰ ማግስት ሰኞ ጠዋት ብቻ ሆስፒታሉ የአንድ ሰው አስከሬን መረከቡን ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል። 
ይሁንና የከተማዋ ነዋሪዎችና እማኞች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የገቡበት ያልታወቁ ሰዎችን ለማፈላለግ አሁንም ድረስ በበዓሉ አከባበር ስፍራ በለቅሶ እና በሃዘን ውስጥ መሆናቸውን አስረድተዋል። 

በቢሾፍቱ ሰኞ ረፋድ ድረስ 23 አስከሬኖች መገኘታቸው እማኞች ገለጹ

ኢሳት (መስከረም 23: 2009)
ሰኞ ረፋድ ድረስ ተጨማሪ 23 አስከሬን በእሬቻ በዓል አከባበር ስፍራ በነበረ ጉድጓድ ውስጥ መውታጣቸውን እማኞች ለዜና ክፍላችን አስታውቀዋል። 
ለደህንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የበዓሉ ታዳሚዎች ዕሁድ ምሽት ጀምሮ የሞቹ ሰዎችን ለማፈላለግ እየተካሄደ ባለው ዘመቻ በአጠቃላይ ተጨማሪ የ26 ሰዎች አስከሬን መገኘቱን ገልጸዋል። 
መንግስት ድርጊቱን ለመሰፋፈን ጥረት በማድረግ ላይ በመሆኑ እማኝነታችንን መስጠት እንፈልጋለን ያሉት ግለሰቦች በስፍራው የነበረው ጉድጓድ በአግባቡ አለመታጠሩና አለመጠናቀቁ ጥያቄ እንደፈጠረባቸው አክለው ገልጸዋል። 

Entire Oromo region flares up in violent protest following the Ireecha massacre

ESAT News (October 3, 2016)
From Borena in the south to Sendafa, and Aweday in the east to Wolega, the entire Oromo region of Ethiopia erupted in protest on Monday with people venting their anger in burning government plated vehicles and offices. People in all major towns in the region took to the streets on Monday in protest for the killing of hundreds of festival goers in Bishoftu, who were celebrating the annual Ireecha, a religious festival to welcome spring.

Sunday, October 2, 2016

የቢሾፍቱው እልቂት የህወሓት መቀበሪያ ጉድጓድ ቁፋሮ ነው!!!

መስከረም 22 ቀን 2009 ዓ.ም.
ከአርበኞች ግንቦት 7
ዛሬ መስከረም 22 ቀን 2009 ዓም ዓመታዊ ባህላዊ የእሬቻ በዓል ለማክበር በሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ከተማ የሚገኝ ሀይቅ ዳር ተሰባስቦ ነበር። በበዓሉ ትውፊት መሠረት ለፈጣሪ ምሥጋና ለማቅረብ ብዙዎች ቄጠማ፣ ለምለም ሳርና አበባዎችን ይዘው ነበር። ሕዝቡ አጋጣሚውን በመጠቀም የህወሓት አገዛዝ በክልሉና በመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚያደሰውን በደል ለመቃወም የተቃውሞ ድምጾችን አሰማ፤ የተቃውሞ ምልክቶችን አሳየ።
ሕዝባዊ ተቃውሞ ባጋጠመው ጊዜ ሁሉ የሚሸበረው የህወሓት አገዛዝ ለሰላማዊ ተቃውሞ የሰጠው ምላሽ እንደተለመደው ጥይት ነበር። ሕዝብ በማንኛውም ቦታ ተቃውሞ የማቅረብ መብት አለው። በየትኛውም ዓለም ሕዝባዊ በዓላት ዓይነተኛ የተቃውሞ ማቅረቢያ ቦታዎች ናቸው። ተቃውሞው የቀረበበት ድባድ በጣም ሰላማዊየነበረ በመሆኑ የተለየ ጥበቃ ሊሰጠው ሲገባ የአገዛዙ ምላሽ ግን ከተለመደው የባሰ ሆነ። በታንኮች ላይ ከተጠመዱ መትረሶች ተኩሰው በርካታ ሰው መፍጀታቸው አልበቃ ሲላቸው በሄሊኮፕሮች ላይ በተጠመዱ መትረሶች ሕዝቡን ፈጁ። የሞተውና የቆሰው ሕዝብ ብዛት ምን ያህል እንደሆነ መናገር ለጊዜው አይቻልም፤ ያም ሆኖ ግን ሟቶች በመቶዎች ቁስለኞች ደግሞ በሺዎች ነው የሚቆጠሩት።

በህዝባችን የነጻነት ተጋድሎ እየኮራን ለመጨረሻው ድል ታጥቀን እንነሳ!



በኦሮምያ እና በአማራ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄደው የነጻነት ትግል በእጅጉ አስደማሚ ነው። ባለፉት ሳምንታት በጎንደርና በባህርዳር ለስድስት ቀናት እንዲሁም በተለያዩ የሰሜን ጎንደርና የምዕራብ ጎጃም ከተሞች የተደረገው የስራ ማቆም አድማ በአገራችን የቅርብ ጊዜ ታሪክ ያልታየ ወደር የለሽ ተግባር ነው።
ህዝቡ የስራ ማቆም አድማ ያደረገው የሚበላውና የሚጠጣው ተርፎት እንዳልሆነ ይታወቃል። እንዲያውም በአገሪቱ የሰፈነው አስከፊ ድህነትና የኑሮ ውድነት እንኳንስ ስራ ተፈትቶ፣ 24 ሰአታት ቢሰራም የሚቋቋሙት እንዳልሆነ እናውቃለን። ነገር ግን ህዝቡ፣ ረሃቡንና ጥማቱን ለሳምንታት ችሎ የአድማውን ጥሪ ተግባራዊ አድርጓል። ይህ ምን ይነግረናል? በቅድሚያ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንዳልነው ህዝቡ በዚህ ዘረኛና አፋኝ አገዛዝ መንገሽገሹን ያሳየበት ነው፤ “ልማቱ ተስፋፍቷል፣ ህዝቡም የደስታና የምቾች ኑሮ መኖር ጀምሯል” እያሉ በድህነቱና በብሶቱ ሲሳለቁበት ለቆዩት እውነተኛ ኑሮውን አሳይቷቸዋል። ይህንኑ ፕሮፓጋንዳ አምነው በመቀበል ወሬውን ሲያራግቡ ለነበሩ የአገር ውስጥና የውጭ የአገዛዙ ጠበቃዎች ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል ። እንዲሁም አገዛዙን ለማስወገድ ህዝቡ ማንኛውንም አይነት መስዋትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ያሳየበት ነው። ረሃብና ጥማቱን ችሎ ከውስጡ የተጣበቀውን አለቅት ለማስወገድ መወሰኑን አሳይቷል። “ሩጥ ስንለው የሚሮጥ፣ ተቀመጥ ስንለው የሚቀመጥ ህዝብ ፈጥረናል” በማለት ሲሳለቁበት በነበረቡት ገዢዎች ላይ እየጠራ ተሳልቆባቸዋል። ከእንግዲህም እሱ በፈለገው እንጅ እነሱ በፈለጉት መንገድ እንደማይገዛላቸው ነግሯቸዋል።

በዛሬው የኢሬቻ በዓል በተፈጠረው ግጭት በመቶዎች የሚቆጠር ህይወት መጥፋቱን ኦፌኮ አስታወቀ

1451በዛሬው ዕለት በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ኃይቅ ለመከበር በዝግጅት ላይ የነበረውና ከኦሮሞ ክብረ በዓሎች አንዱ የሆነው ኢሬቻ በዓል መንግሥትን በተቃወሙ ወጣቶችና በመንግሥት ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ተቋርጦ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አስታወቀ። የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፤ ፓርቲያቸው ባጠናቀረው መረጃ ሰዎች በተኩስ፣ በአስለቃሽ ጭስ እና በመረጋገጥ ሕይወታቸው እንዳለፈ ነው። 
በርካታ የቆሰሉ ሰዎች አሁንም በሆስፒታል እንደሚገኙ አክለው የተናገሩት ዶ/ር መረራ የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ተናግረዋል።

Hundreds dead at Ireecha celebrations


ESAT News (October 2, 2016)
Hundreds of festival goers have reportedly been killed on Sunday in the town of Bishoftu, the site of the annual Ireecha celebrations, an important religious festival by the people of Oromo in welcoming spring. Fana broadcasting, one of the organs of the ruling party reported that 52 people died in a stampede.