Thursday, January 10, 2019

ወለጋ ላይ ጦርነት አዲስ አበባ ላይ ሰላማዊ ትግል የሚለው አካሄድ ተቀባይነት የለውም ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 2/2011)ወለጋ ላይ ጦርነት አዲስ አበባ ላይ ሰላማዊ ትግል የሚለው አካሄድ ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም ሲል የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ኦዴፓ አስታወቀ።

የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ዓለሙ ስሜ ለኢሳት እንደገለጹት በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው ኦነግ በወለጋ ውጊያ እያደረገ በአዲስ አበባ ስለ ሰላማዊ ትግል መናገር አይቻልም ብለዋል።
ሸኔ ኦነግ ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ በሶስተኛ ወገን እንደራደር ማለቱን በተመለከተ የፓርቲያቸውን አቋም የገለጹት ዶክተር ዓለሙ ስሜ ከእንግዲህ ድርድር የሚባል ነገር የለም መሳሪያውን አስቀምጦ በምርጫ ቦርድ በሚደረግ የፓርቲዎች ንግግር ላይ መሳተፍ ይችላል ሲሉ ጥሪውን ውድቅ አድርገዋል።

በኦሮሚያ ክልል በወለጋና በጉጂ ሰላም መስፈኑን፣ ሁሉ ነገር ወደ ቀድሞው ሰላማዊ ህይወት መመለሱን የገለጹት ዶክተር አለሙ ዛሬ በአቶ ገላሳ ዲልቦ ከሚመራው ኦነግ ጋር የተደረገውም ውይይት ውጤታማ እንደሆነ ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment