Thursday, December 28, 2017

የአገራችንን ትንሳኤ ዕውን ለማድረግ ያለን ብቸኛ አማራጭ የኢትዮጲያ አገራዊ ንቅናቄ የነደፈውን ሁሉን አሳታፊ የሽግግር መንግስት መመስረት ብቻ ነው።

የኢትዮጲያን ፖለቲካ በቅርብም ሆነ በሩቅ ለሚከታተል አንድ ዕውነት ፍንትው ብሎ እንደሚታየው ግልጽ ነው። ለ27ዓመታት አገራችንን በጨለማ ጉዞ ይመሯት የነበሩት በትግራይ ስም የተደራጁት ጥቂት አፋኝ ቡድኖች የስልጣን ዕድሜአቸው መገባደጃው አፋፍ ላይ መድረሱን ነው። ኢትዮጲያዊ ውስጥ በአሁን ሰዓት በርግጥ መንግስትና ህግ አለ ወይ ሊያስብል በሚችል ደረጃ የሕዝባችን የፖለቲካውም ሆነ የኢኮኖሚና የማህበረሰባዊ ህይወቱ እጅግ አደገኛና በማንኛውም ጊዜ ወደ ስርዓተ አልበኝነት ሊቀየር የሚችልበት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ሕዝባዊ ዕምቢተኝነቱ፣ በየቦታው በህወሃት/ወያኔ ጠንሳሽነት የሚለኮሰው የብሄር ግጭት፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ህዝብ ከቀዬው መፈናቀል፣ ጣሪያ የነካው የኑሮ ውድነት፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያላሰለሰ ተቃውሞና የዩኒቨርሲቲዎቹ መዘጋት፣ የአንደኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንና ተማሪዎች የሚያሳዩት ሰላማዊ ሰልፍ፣ በመከላከያውና በደህንነቱ መሃል እየሰፋ የመጣው የስልጣን ሽኩቻና የመሳሰሉት እንቅስቃሴዎች በግልጽ የሚያብቁት ሕወሃት ይህንን ህዝባዊ ማዕበል እንደ ቀድሞው በማስፈራራትም ሆነ በአስመሳይ የመግለጫ ጋጋታዎች ማለፍ የማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ነው። ይህ የህዝብ ማዕበል ግራና ቀኝ ክፉኛ እያላጋውና ጥልቅ ተሃድሶ ብሎ የቆፈረውም ጉድጓድ ራሱን መልሶ እየቀበረው ነው።  ከዚህ ሁሉ ይበልጥ ግን አገዛዙ ምን ያህል እንደተሽመደመደና የሞት ቀነ ቀጠሮውን ቁጭ ብሎ እንደሚጠብቅ ግዑዝ አካል ያስመሰለው ራሱ መርጦና አስመርጦ ያስቀመጣቸው የፓርላማ አባላት ለረዥም ዘመን ይጫወቱ የነበረውን የአጨብጫቢነትና የሁሉን አጽዳቂነት ሚና አልፈው ዛሬ ጥያቄ ማቅረብና የአገዛዙን ፈላጭ ቆራጭ የህወሃት ሹመኞች ማፋጠጥ መጀመራቸው ነው።  ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ካልተመለሱ ደግሞ ፓርላማ እንደማይገቡ ሲያስታውቁና አይናችን እያየ ፓርላማው ሲፈርስ ያኔ የህወሃት/ወያኔ አንድ እግር በርግጥም ወደ መቃብሩ መግባቱን ያለጥርጥር አሳይቶናል። የኢሕአዴግ እንቅልፍ የዛፍ ላይ እንቅልፍ መሆኑ ቀርቶ አሁን ከዛፉ ላይ ተፈጥፍጦ ወድቋል። በዚህ ኢሕአዴግ በተባለው ድርጅት ሆድና ጀርባ ላይ ለአመታት ተመቻችቶ ተኝቶ የነበረው ሕወሃት አሁንም ድረስ ከዕንቅልፉ የነቃ አይመስልም። በሙት መንፈስ የሚንከላወስ አደገኛ ዞምቢ ሆኗል። በጊዜ ካልታገተ የሀገር መፍረስና የፍጹም ስርዓተ አልበኝነት መንገስ የነገው ዕጣ ፈንታችን ሊሆን ይችላል።
አምባገነን መንግስታት የህዝባቸውን ፍትሃዊ ጥያቄ መመለስ ሲያቆሙ ሊከሰት የሚችለውን መጨረሻ የሌለው ስርዓተ አልበኝነትና እንስሳዊ ኑሮ ከቅርባችን ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ የመንና ሊቢያ መማር ትልቅ አዋቂነት ነው። ከነኚህ አሳዛኝ ሀገራት ትምህርት ሊወስድ የሚያስችል አቅምም ሆነ ፍላጎት የሌለው አንድ ሀይል ቢኖር የደናቁርት ስብስብ የሆነው ሕወሃት ብቻ ነው።ኢትዮጲያ በርግጥም መስቀለኛ መንገድ ላይ ናት።ይህ ሁኔታ ላገራችን ኢትዮጲያ ትልቅ ፈተና ቢሆንም በአግባቡና በስርዓቱ ከተያዘ ግን ትልቅ ታሪካዊ ዕድል የመሆንም ተስፋ አለው።
በኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ መካከል የተፈጠረው ልዩነትም ይሁን በፓርላማ አባላቱ ላይ የሚታየው ለህወሃት ጥቅምና ስልጣን አናገለግልም የሚለው ደፋር ውሳኔ ጊዜውና ህዝቡ የሚጠይቀው አበረታች እርምጃ ቢሆንም መዳረሻው ግን አይደለም። ለውጥ ፈላጊ የሆኑ የአገዛዙ አካላት አሁንም በድፍረት ከህዝባቸው ጋር ዕምቢ ለወያኔ/፣ ዕምቢ ለዘረኝነትና ላንድ ብሄር የበላይነት በሚለው አቋማቸው እስከመጨረሻው በጽናት ይገፉበት ዘንድ አደራ እንላለን።
 እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል በሚል አህያዊ ፍልስፍና የሞት ሞታቸውን ለሚፍገመገሙ የህወሃት/ወያኔ ባለስልጣናት ይህ የህዝብ ምሬትና ዉረዱልን የሚለው ድምጽ እያየለ በመጣ ቁጥርና ስልጣነ መንበራቸው መነቃነቅ ሲጀምር ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ አንዳንድ ፍንጮችን አይተናል። የብሄር ግጭቶችን በመለኮስ የርስ በርስ ፍጅቶችን፣ የህዝብ መፈናቀሎችን፣ ህጻን ሽማግሌ፣ ወንድ ሴት ሳይል ንጹሃን ዜጎችን ባደባባይ መረሸን፣ የተለመደ እርኩሳዊ ባህሪያቸዉ እየሆነ ከመጣ ሰነባብቷል። የኛ ሃላፊነት መሆን ያለበት ደግሞ ይህንን ወያኔ ለ27 አመታት ካጠረልን ክልላዊ ቅዠትና ወሰናዊ አስተሳሰብ አልፈን እንደ አንድ ሀገር ልጆች መተያየትና ችግሮቻችንን በትዕግስት፣ በመቻቻልና በፍጹም ቅንነት የመፍታት ፍላጎትና ችሎታን ማዳበሩ ላይ ነው። የኦሮሞ ኢትዮጲያ፣ ወይም የወላይታ ኢትዮጲያ፣ የአማራ ኢትዮጲያ ወይንም የሶማሌ ኢትዮጲያ፣ የዚህ ወይንም የዚያ ኢትዮጲያ የሚባል ነገር የለም። የሁላችንም እናት፣ የሁላችንም ቤት የሆነች አንድ ኢትዮጲያ ብቻ ናት ያለችን። በአጥፍቶ መጥፋት ዕብደት የተለከፈው ሕወሃት/ወያኔ ደግሞ እኔ ከሌለሁ እናንተም ኢትዮጲያም አትኖሩም በሚል የደንቆሮ ዕብሪት ይቺን አንድ የጋራ ቤታችንን ሊያወድማት ዝግጅቱን አጠናቋል። ይህንን ዕብደቱን አስቁመን አገራችንን ማዳንና ህወሃትንም ወደሚገባው የፍትህ ሆስፒታል ወስደን ማሳከም ጊዜው የሚጠብቅብን ታሪካዊ ሃላፊነት ሆኗል። በምንም አይነት መንገድ በኢትዮጲያ ህዝብ ዕጣ ፈንታ ቁማር አንጫወትም። ለጊዜያዊ ጥቅምና ስልጣን ሲሉ ከወያኔ ጋር ቁማሩን ሊጫወቱ የሚፈልጉትን ሃይሎችንም ተው፣ አያዋጣም ልንላቸው ግድ ይላል።
የኢትዮጲያ ሕዝብ የሚችለውን ሁሉ አድርጓል፣ እያደረገም ነው። አሁን ከፖለቲካ ድርጅቶችም ሆነ ከሀገር ወዳድ ልሂቃን ብዙ ይጠብቃል። በራሳቸው ተነሳሽነት በከባድ መሳሪያ ከታገዘ ነፍሰ በላ የአጋዚ ጦር ጋር ባዶ እጃቸውን ሲፋለሙ የወደቁት የኦምቦ፣ የባህርዳርና የጨለንቆ  ህጻናት ደም ትግላችንን አደራ እያለ ከመቃብር ባሻገር ይጠራናል። ደማቸው ደመ ከልብ ሆኖ እንዳይቀር የወደቁለትን የነጻነትና የዲሞክራሲ አላማ ከግብ ማድረስ የሁላችንም ሃላፊነት ነው። በለውጥ ፈላጊ ኃይሎች መካከል ያለውን የተለያየ ያስተሳሰብ ልዩነትና ከንቱ የጎንዮሽ መጓተት ወደጎን አድርጎ ይህን አስከፊ ስርዓት ማስወገድ ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባል። ሁሉም ተቃዋሚ ሀይል በተቀናጀ መልኩ በሕወሃት/ወያኔ ላይ በህብረት ይዘምት ዘንድ ንቅናቄአችን ጥሪውን ያቀባርል። የንቅናቄአችን የመጨረሻ አላማ ምንድነው ብላችሁ ለምትጠይቁ መልሳችን አንድና አንድ ብቻ ነው። የሕወሃትን አገዛዝ ከስር መሰረቱ ገርስሶ አንድነቷ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ላይ የተገነባች አዲስ ኢትዮጲያን ማየት ብቻ ነው! ይህን ዕውን ማድረግ ደግሞ የምርጫ ወይንም የልሂቃን ቅንጦት ሳይሆን እንደሀገር የመኖርና ያለመኖር ሕልዉናችንን የሚወስን ብቸኛ አማራጭ ስለሆነ ብቻ ነው።የኢትዮጲያ አገራዊ ንቅናቄ ለዚህ አላማ መሳካት ግብዓት ይሆን ዘንድ የሽግግር መንግስት ሰነድ አዘጋጅቷል።
ይህንን የህወሃት/ ወያኔን ሁለንተናዊ ድክመትና አገር የማስተዳደር አቅም ማጣት ተከትሎም ሀገራችን ኢትዮጲያ ወደ አልተፈለገ የርስ በርስ ግጭት ከማምራቷ በፊት መፍትሄ መፈለግ አለበት እያሉ የሚጎተጉቱ ድምጾችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየሰማን ነው። በተለይም ደግሞ የአውሮፓ ህብረትና የአሜሪካ መንግስት ህወሃት/ወያኔ ከሁሉም ተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ መቀመጥና መደራደር አለበት ሲሉ ተደምጠዋል። በድህረ ደርግ ዘመን ህወሃቶችን ለስልጣን ያበቁትና በኢትዮጲያ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ የነበሩት አሜሪካዊው ዲፕሎማት ሚስተር ኸርማን ኮኸንም ከሰሞኑ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ስለወያኔ ያላቸውን ስጋት ሲገልጹ ከርመዋል። ዲፕሎማቱ ሲናገሩም በጥቂት ዘረኞች መዳፍ ውስጥ የወደቀው የኢትዮጲያ ፖለቲካና ኢኮኖሚ የፈጠረው ሁለንተናዊ ቀውስ ባስቸኳይ የፖለቲካ መፍትሄ ካልተገኝለት ያገሪቱ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ጠንከር ባሉ የማስጠንቀቂያ ቃላቶች ገልጸዋል። ባጭሩ አነጋገር ምዕራባዊያኑ በአንድ ወቅት ይተማመኑበት የነበረው የ11 % የኢኮኖሚ ዕድገትም ሆነ አሸባሪዎችን መዋጋት የሚለው የህወሃት ፕሮፓጋንዳ የተደማጭነት ዋጋውን አጥቷል። ለ27 ዓመታት ምለው የተገዘቱበት ዲሞክራሲን የማስፈንም ሆነ ድህነትን የመቅረፍ ወሬ ምዕራባዊያንን ከማጭበርበርና ከማሳሳት ያለፈ ምንም አይነት ፋይዳ እንደሌለው ጌቶቻቸው የተገነዘቡት ጉዳይ ሆኗል። ለዚህም ነው በቅርቡ እንደአማራጭ የቀረበውን የኢትዮጲያ አገራዊ ንቅናቄን የሽግግር መንግስት ፍኖተ መንገድ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት ዶክተር ዲማ ነገዎንና ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን የአውሮፓ ፓርላማ የጋበዛቸውና የሽግግር መንግስት  ራዕያቸውን እንዲያስረዱ የጋበዟቸው። ለዚህም ነው የአሜሪካን መንግስትም ይሁን ዕዉቅ ዲፕሎማቷ ሁሉን አቀፍ ስለሆነው የሽግግር መንግስትና ድርድር በየመግለጫዎቻቸው ሊያሳስቡ የተገደዱት።
ንቅናቄአችን አርበኞች ግንቦት 7 ባሁን ሰዓት በመንደርና በዘር ተሰባስበው ራሳቸውን ህወሃት በማለት አገራችንን ወደማትወጣው አዘቅት እየወሰዷት ባሉት የፋሺስት ጥርቅሞች ላይ ክንዳችንን አስተባብረን እንረባረብባቸው የሚለው። እነኚህ ወሮበሎች  ሀገር መምራት አለመቻላቸውን ብቻ ሳይሆን በነሱ ድክመት እየፈራረሱ ያሉ የተለያዩ መንግስታዊ መዋቅሮች ባሉበት በአሁን ሰዓት የተቃዋሚ ሃይሎች በሙሉ ሀገራችን ኢትዮጲያና  ህዝባችን ከተጋረጠባቸው የስርዓተ አልበኝነትና የርስ በርስ የመጠፋፋት ዕልቂት አፋፍ የማዳን ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት አለባቸው ብሎ ያምናል። ለሀገርም ሆነ ለህዝብ ደንታ ቢስ የሆነ አገዛዝ የኢትዮጲያን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ወደጨለማ በሚያመራበት ጊዜ ዝም ብለን ቆመን ማየት የታሪክ ተወቃሾች ማድረጉ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የአገዛዙ ተቃዋሚ ነኝ የሚል ሃይል የሚስማማበትን የዲሞክራሲና የፍትህ ስርዓት የመገንባት ተስፋውንም ፍጹም ስለሚያጨልመውም ጭምር ነው። ሀገርና ህዝብ ከሌለ ማናቸውን አይነት የፖለቲካ ስርዓት የመገንባት ህልም ከንቱ ቅዠት፣ ባዶ ተስፋ ብቻ ሆኖ ይቀራልና ። መንግስትና ህግ በሌለበት ሁኔታ ራሳችንን እንደመንግስት ቆጥረን፣ አስፈላጊውን ሃላፊነት በትከሻችን ላይ አስቀምጠን፣ በሀገራችንና በህዝባችን ስም መደረግ ያለበትን ሁሉ እናደርግ ዘንድ አደራ እንላለን።
ይህን አለም አቀፍ ትኩረት የሳበውንና የመጨረሻ መፍትሄ ተብሎ የተወሰደውን የሽግግር መንግስት አማራጭ መንገድ ሁሉም ተቃዋሚ ሀይሎች ትኩረት እንዲሰጡትና እንዲደግፉት ንቅናቄአችን ያሳስባል። ከዚህ መፍትሄ በመለስ ያሉት አማራጮች በሙሉ ከዚህ በፊት ባንድም ሆነ በሌላ የተሞከሩና ያልሰሩ መሆናቸውን እዚህ ላይ መተንተኑ ለቀባሪው ማርዳት ይሆንብናል። የኢትዮጲያ ህዝብ እየጠየቀ ያለው የስርዓት ለውጥ መሆኑን ከግምት አስገብቶ በከፍተኛ ጥንቃቄና አርቆ አስተዋይነት የተዘጋጀው ይህ የሽግግር መንግስት ሰነድ የለውጥ ፈላጊ የሆኑ ያገዛዙ አካላትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ የሚያተርፍበትና ሀገራችንና ህዝባችን ካንዣበበባቸው የርስ በርስ ግጭት የሚያድናቸው ሰነድ መሆኑን ስንገልጽ በሙሉ መተማመንና የህዝባችንን ሙሉ ትብብር ከግምት አስገብተን ነው።

ግልጽ ደብዳቤ፦ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)

ጉዳዩ፦ በቂሊንጦ እሳት ሰበብ ስለታሰሩት ሰዎች የተደረገውን ምርመራ በተመለከተ
እንደሚታወቀው ኢሰመኮ በቀን 20 ጥቅምት 2010፣ በደብዳቤ ቁጥር ሰመኮ/2.1/29/2010 እንደገለጸው ነሐሴ 1/2008 አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (ቂሊንጦ) ግቢ ውስጥ የተነሳውን እሳት መንስዔ ለማጣራት በተደረገው ምርመራ አሰቃቂ የመብቶች ጥሰቶች ተፈፅመዋል። በእነ መቶ ዐለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ (38 ተከሳሾችን) በተመለከተ መንግሥት ባለበት አገር ይፈፀማሉ ተብለው የማይጠበቁ የጥፍር መንቀል፣ በሚስማር ሰውነት የመብሳት፣ ግርፋት እና የመሳሰሉት አካላዊ ጉዳት የሚያደርሱ፣ ሰብኣዊ ክብርን የሚያዋርዱ የጭካኔ ተግባራት በተያዙ ሰዎች ላይ ተፈፅሞባቸዋል። ይሄ ሁሉ የሆነው ፍርድ ቤት በአደራ እንዲጠብቃቸው ያስረከበው የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ኃላፊነቱን ባለመወጣቱ ነው። ሆኖም፣ ዋነኞቹ የምርመራው (ወይም በትክክለኛ አገላለጽ የማሰቃየት ተግባሩ) በፖሊሶች የተፈፀመ መሆኑን ታራሚዎቹ ለፍርድ ቤት በተደጋጋሚ ገልጸዋል።

በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ የተከሰተው የህዝብ ፍጅት እንዲቆም ጥሪ አቀረበ።

በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ የተከሰተው የህዝብ ፍጅት እንዲቆም ጥሪ አቀረበ። መለዮ ለባሽም መሳሪያውን ከሕዝብ ላይ እንዲያነሳ የጠየቀው ቅዱስ ሲኖዶስ የሀገሪቱን ቀውስ ለመፍታት የአደራ መንግስትም እንዲቋቋም ጥሪ አቅርቧል። በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዎስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ “በሀገር ውስጥና በመላው አለም ለምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያን ለምትወዱ ወገኖቻችን” በሚል ርዕስ ጥሪውን አቅርቧል። ሲኖዶሱ ባወጣውም ጥሪ ኢትዮጵያ የፈተና ደመና እያንዣበባት ነው ሲል አጽንኦት ሰጥቷል። በኦሮሞና በኢትዮጵያ ሶማሌ ወገኖቻችን ውስጥ ጥቅመኛ ፖለቲከኞች ያቀጣጠሉት ፍጅት በኢትዮጵያውያን መካከል እንኳን ሊደረግ ሊታሰብ የማይችል እንደነበርም በማስታወስ በሁኔታው በእጅጉ ማዘኑን ሲኖዶሱ ገልጿል። የሀገሪቱ የመከላከያ ሰራዊትና የፖሊስ ሃይል እንዲሁም የደህንነቱ ተቋም የገዛ ዜጎቹን ከማሰቃየት እንዲታቀብም ቅዱስ ሲኖዶሱ በመግለጫው ጠይቋል። ሁሉም የጸጥታ ሃይሎች ከሕዝቡ ጎን እንዲቆሙም ጥሪ አቅርቧል። መለዮ ለባሹ የታጠቀውን የጦር መሳሪያ የሀገሩን ድንበር ለማስጠበቅ ያነገበው መሆኑን ተገንዝቦ አፈሙዙን ከሰላማዊ ህዝቡ ላይ ዞር እንዲያደርግ አሳስቧል። በኢትዮጵያ ውስጥ የቀጠለውን ችግር ለማስቆምና በሀገሪቱም ዘላቂ መረጋጋት ለማምጣት የአደራ መንግስት እንዲመሰረት ጥሪ ያቀረበው በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተከርስቲያን ቅዱስ

አቶ በቀለ ገርባ ለምስክርነት የጠሯቸው የኦሮሚያ ክልል ባላስልጣናት ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ጠየቁ

አቶ በቀለ ገርባ ለምስክርነት የጠሯቸው የኦሮሚያ ክልል ባላስልጣናት ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ጠየቁ። ጥያቄውን ያቀረቡት በድርጅታቸው ኦህዴድ በኩል መሆኑ ታውቋል። በሚሰጣቸው ተለዋጭ ቀጠሮም በችሎት ቀርበው ምስክርነት እንደሚሰጡም ለፍርድ ቤቱ በጻፉት ደብዳቤ አስታውቀዋል። ከኦህዴድ ጽሕፈት ቤት ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 18/2010 በተጻፈው ደብዳቤ እንደተመለከተው አቶ በቀለ ገርባ በምስክርነት የጠሯቸው የክልሉን ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳን ጨምሮ አራት ባላስልጣናት ናቸው። ከአቶ ለማ መገርሳ በተጨማሪ የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር አብይ አሕመድ፣አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ እንዲሁም ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ የተባሉ የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት ናቸው ። ከኦሕዴድ ጽሕፈት ቤት ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተጻፈው ደብዳቤ ባለስልጣናቱ በቀጠሯቸው መገኘት ያልቻሉበትንና ተለዋጭ ቀጠሮ የጠየቁበትንም ምክንያት አስፍሯል። በአስቸኳይ ሀገራዊ ስብሰባ ምክንያት ቀርበው መመስከር ስለማይችሉ

ሕጻናትን ጨምሮ 8 የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በኢትዮጵያ መጠለያ ካምፕ ጋምቤላ ውስጥ መገደላቸው ተሰማ

ሕጻናትን ጨምሮ 8 የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በኢትዮጵያ መጠለያ ካምፕ ጋምቤላ ውስጥ መገደላቸው ተሰማ። ሬዲዮ ታማዙጅ የተባለ ጣቢያ ከሱዳን እንደዘገበው ሴቶችና ሕጻናትን ጨምሮ የሙርሌ ጎሳ አባላት የሆኑ ሱዳናውያን ዲማ የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ተገድለዋል። የካምፑ የስራ ሃላፊ አንድሪው ካካ እንዳረጋገጡትም ከትላንት በስትያ ታህሳስ 17 ለሊት ላይ በስደተኞች መጠለያ ውስጥ ተኩስ ተከፍቶ 8ቱ ሰዎች ተገድለዋል። ከስምንቱ የሙርሊ ጎሳ አባላት መካከል 4ቱ ሕጻናት፣ 3ቱ ሴቶች አንዱ ደግሞ የ60 አመት አዛውንት መሆናቸውን ሬዲዮ ጣቢያው ዘግቧል። ሟቾቹ በደቡብ ሱዳን በተፈጠረ ግጭት ሳቢያ በኢትዮጵያ በስደት ተጠልለው የነበሩ መሆናቸውን የካምፑ ሃላፊ ገልጸዋል። በዚሁ ጥቃት አንድ ሌላ ስደተኛም መቁሰሉ ተነግሯል። የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ ወደ አካባቢው ቢደርሱም የሕወሃት ባለስልጣናት ግን ስለስደተኞቹ መሞት ማረጋገጫ አልሰጡም። በጋምቤላ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሙርሌ ጎሳ አባላት ላይ በተመሳሳይ ሁኔታ ከደቡብ ሱዳን የመጡ ታጣቂዎች በመቶ የሚቆጠሩ ሕጻናትን በሃይል መውሰዳቸውንና ግድያ ሲፈጽሙ እንደነበርም ይታወሳል።

Ethiopia: Patriarchate in exile called for formation of caretaker gov’t

ESAT News (December 28, 2017)
Expressing deep concern over the current political crisis in Ethiopia, the exiled Patriarchate of the Ethiopian Orthodox Church has called for the establishment of a caretaker government.
Abuna Merkorios
The patriarchate said in a press statement it sent to ESAT that a cloud of tribulations is looming large over the country and it was high time that the army, opposition political parties and the people work in tandem to amicably avert the impending catastrophe.

Wednesday, December 27, 2017

በኦሮምያና ሶማሊ ድንበር አካባቢ ባለው ግጭት ብዙ ተዋንያን አሉ ሲሉ አቶ አብዲ ሙሃመድ ተናገሩ

ከ600 ሺ በላይ ዜጎችን ያፈናቀሉትን የሶማሊ ክልል መሪ አቶ አብዲ ሙሃመድን ገጽታ ለመገንባት በሚል የመንግስትና የአገዛዙ ደጋፊ ጋዜጠኞች ወደ ጅግጅጋ ተጉዘው ቃለምልልስ ያደረጉላቸው ሲሆን፣ አቶ አብዲም ከሁለቱ ክልሎች ግጭት ጀርባ ሌሎች በርካታ ተዋናዮች አሉ ብለዋል። ተዋናዮችን ግን በስም ከመግለጽ ተቆጥበዋል። ግጭቱን ለማስቆም አለመቻሉንና አሁንም ድረስ የቀጠለ መሆኑን አቶ አብዲ ተናግረዋል። እኝሁ በከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል መጠየቅ እንዳለባቸው አስተያየቶች እየቀረቡባቸው የሚገኙት አቶ አብዲ፣ ከፍተኛ የመከላከያ ሰራዊት አዛዦችና የህወሃት ባለስልጣናት ድጋፍ እንዳላቸው ይታወቃል። በእርሳቸው ቁጥጥር ስር የሚገኘውን 13 ሺ የሶማሊ ልዩ ሃይል ጦር በአካባቢው ሰላም ለማስፈን እንደሚጠቀሙበት የዛቱት አቶ አብዲ ፣ ማንኛውንም የጸጥታ ማስከበር ስራ ከ ጄኔራል ሳሞራ የኑስና ከጄል ገብሬ ዲላ ጋር በመመካከር የሚሰሩ መሆኑን ለመርማሪዎች ተናግረው ነበር።

በአዳማ ከተማ አገዛዙን በማውገዝ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ

ታህሳስ 17 ቀን 2010 ዓም በአዳማ ከተማ ጥቁር ዓባይ እና ቦኮ ሚካኤል በመባል በሚጠሩት አካባቢዎች የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች አገዛዙን የሚያወግዙ የተለያዩ መፈክሮችን አሰምተዋል።
ከአራት ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት ድረስ በዘለቀው ትእይንተ ሕዝብ ላይ ነዋሪዎቹ ኢህአዲግ አይገዛንም፣ ንጹሃን ዜጎችን መግደልና ማፈናቀል ይቁም፣ ፍትህና ነጻነት እንፈልጋለን የሚሉ መፈክሮችን አሰምተዋል። አርሶ አደሮች፣ የቀን ሰራተኞች፣ ተማሪዎች በጋራ በአንድ ድምጽ የህወሃት ኢህአዴግን አገዛዝ ባወገዙበት ወቅት ለተወሰነ ሰዓት መንገዶች ዝግ ሆነው ነበር።

የዘይትና ስኳር እጥረቱ ተባብሶ ቀጥሎአል

በአማራ ክልል ከሚሴ ከተማ ከአረብ ሀገር ተመልሰው በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተው እንዲሰሩ የተደረጉ ዜጎች፣ የዘይትና ስኳር እጥረት ከሚፈጥረው ችግር በተጨማሪ በሚጣልባቸው የተጋነነ ግብርና የመስሪያ ዕቃ አቅርቦት ችግር ሥራቸውን መስራት እንዳልቻሉ ተናግረዋል። 
በምግብና ሻይ ቤት የንግድ ስራ የተሰማሩ ቅሬታ አቅራቢዎች እንደሚናገሩት ባለፈው ዓመት ጀምሮ የተከሰተው የስኳርና ዘይት እጥረት ችግር መፍትሄ ሳያገኝ ከስድስት ወራት በላይ በመቀጠሉ ሥራቸውን በአግባቡ መስራት ተስኗቸዋል፡፡
አንድ ኪሎ ስኳር 35 እና 40 ብር በመግዛት ይገለገሉ እነደነበር የሚገልጹት ቅሬታ አቅራቢ፤ በዚህ ዓመት በሃምሳ እና ስልሳ ብር ለአንድ ኪሎ ስኳር በመክፈል እየተገለገሉ ነው፡፡ ዘይትም ከሃያ ስድስት ብር ወደ ሰባ እና ሰማኒያ ብር መግባቱም ለስራቸው ትልቅ እንቅፋት በመፍጠር እንዲቸገሩ ማድረጉን ይናገራሉ፡፡

የወልቃይት አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ አባላት አቤቱታ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀረ

የግራ ዳኛ ዘርዓይ ወልደሰንበት ከችሎት እንዲነሱላቸው የወልቃይት አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ያቀረቡትን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አደረገው። በጸረ አማራ ሕዝብ አመለካከታቸው በገሃድ የሚታወቁት ዳኛ ዘርዓይ ወልደሰንበት ጉዳያችንን ሊዳኙት አይገባም ብለው ክስ መስርተው የነበረ ቢሆንም ተከሳሾቹ ያቀረቡትን በመረጃ የተደገፈ አቤቱታ እንደማይቀበለው አስታውቋል።
ዳኛ ዘርዓይ የቀረበባቸውን ተቃውሞ ተቀብለው ከችሎቱ እራሳቸውን ያገላሉ ተብሎ ቢገመትም እሳቸው ግን ለመነሳት ፈቃደኝነታቸውን አላሳዩም። በጽሁፌ የገለጽኩት አቋም ሀሳብ በነፃነት የመግለፅ መብቴን ተጠቅሜ ነው።ከተከሳሾቹ ጉዳይ ጋር በምንም መልኩ አይገናኝም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። ፍርድ ቤቱም ዳኛ ዘር ዓይ ያቀረቡትን ሃሳብ በመደገፍ መነሳት የለባቸውም የሚል ብይን ሰጥቷል።
ከእስረኞች ተነጥለው ጨለማ ዝግ ቤት ውስጥ የሚገኙት አቶ መብራቱ ጌታሁን ስለደረሰባቸው የጤና መታወክ አቤቱታቸውን በጽሁፍ ለፍርድ ቤቱ አስገብተዋል። በተመሳሳይ መዝገብ ተከሳሽ የሆኑት 2ኛ ተከሳሽ አቶ ጌታቸው አደመም በህመም ምክንያት ሳይቀርቡ ቀርተዋል።

በኦሮሚያና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተከሰተውን ግጭት ለማባባስና የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናትን ተጠያቂ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀመረ።

 በኦሮሚያና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተከሰተውን ግጭት ለማባባስና የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናትን ተጠያቂ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀመረ። በሕወሃቱ አመራር አቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የደህንነት መስሪያ ቤት ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ በሰፊው በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑንም መረጃዎች አመልክተዋል። ይህንን ለማስፈጸም የፓርቲና የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም የመዝናኛ ጣቢያ ጋዜጠኞችን ጭምር የጉዞና የውሎ አበል ከፍሎ ማሰማራቱን መረዳት ተችሏል። የሕወሃት ተቋማት ከሆኑት ኢ ኤን ኤን ቴሌቪዥን እንዲሁም አይጋ ፎረም ከተባለው ድረገጽና በፌስ ቡክ ላይ የተሰማሩ የህወሃት አባላትን ጨምሮ ወደ ጅጅጋ የተጓዙት ጋዜጠኞች ተፈናቃዮቹ ወደሚገኙበት በተሽከርካሪ ተጉዘው ተፈናቃዮቹን ማነጋገራቸው ታውቋል። የተመረጡ ሰዎችን ብቻ በጋራ እንዲያነጋግሩ በተመቻቸበት በዚህ መድረክ ኦሮሞዎች ጥቃትና ግፍ ፈጸሙብን የሚሉ የሶማሌ ክልል ተወላጆች አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ተደርገዋል። አሰቃቂ የሚባሉ ግፎች በተተረኩበት በዚህ መግለጫ የኦሮሚያ ክልል

የህወሃት መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚነሱ ህዝባዊ ተቃውሞዎችን ለማፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ መደረሱ ተገለጸ

የህወሃት መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚነሱ ህዝባዊ ተቃውሞዎችን ለማፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ መደረሱ ተገለጸ። በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች የተነሱትን ተቃውሞዎች ለመቆጣጠር ከድንበር ሰራዊቱን እያንቀሳቀሰ መሆኑም ተገልጿል። የአባይን ግድብ የሚጠብቀው የህዳሴ ዲቪዥን በመባል የሚጠራው የፌደራል ፖሊስ አንድ ሻለቃ ጦር በአማራ ክልል በዩኒቨርስቲዎች የተነሳውን ተቃውሞ ለማስቆም ከግድቡ መንቀሳቀሱም ታውቋል። አገዛዙ የሰራዊት እጥረት በመግጠሙም የትግራይ ሚሊሻዎችና ደህንነቶችን የፌደራል ፖሊስ ዩኒፎርም በማልበስ እያሰማራ መሆኑንም ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢሳት የመከላከያ ምንጮች እንደገለጹት የህወሃት አገዛዝ ብርቱ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል። ከመከላከያው ከ90 በመቶ በላይ ሃይሉ ከተከማቹባቸው የጦር ግንባሮች ሰራዊቱን ለማንሳት ያልፈለገው የህወሃት አገዛዝ የተነሳበትን ህዝባዊ ተቃውሞ ለማስቆም የሚችልበት አቅም እያጠረው እንደመጣ ለማወቅ ተችሏል። በመሃል ሀገር ያለው ሰራዊት አነስተኛ በመሆኑ የግድ ከድንበር ካሰፈረው ሃይል የተወሰኑትን በመቀነስ አመጽ ወደተነሳባቸው አካባቢዎች ለማሰማራት እየጣረ መሆኑም ተመልክቷል። የኢሳት ምንጮች እንደሚሉት የህወሃት አገዛዝ በኤርትራ ግንባሮች ያከማቸውን ሃይል መንካት አልፈለገም። ምክንያቱም ከኤርትራ ድንገተኛ ጥቃት ይሰነዘራል የሚል ስጋት በህወሃት ዘንድ በመኖሩ ነው። በዚህም የተነሳ ከሌሎች ዕዞች ሰራዊት በመቀነስ አመጽ ወደተቀሰቀሰባቸው አካባቢዎች በማስፈር ላይ ይገኛል። በምስራቅ የኢትዮጵያ ክፍል ያለውን ቀውስ ለማርገብ ከምዕራብ ዕዝ 12ኛ ክፍለጦር 2 ሬጅመንት ሃይል ተቀንሶ ወደ ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል እንዲሰፍር መደረጉ ታውቋል።
ለሁለት ሳምንት ያህል ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ መቋረጡ ተገለጸ። አቶ ገዱ አንዳርጋቸውም አሜሪካ መግባታቸው ታወቋዋል። በሌላ በኩል የኦህዴድና የብአዴን የፓርላማ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ካላነጋገርናቸው በፓርላማ መደበኛ ሰብሰባ ላይ እንደማይገኙ ማሳሰባቸውን ተከትሎ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሌሎች አመራሮች ጋር በመሆን የፓርላም አባላቱን ማነጋገራቸው ታውቋል። የኦህዴድና የብአዴን የፓርላማ አባላት በህዝበ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና በሐገሪቱ ውስጥ የተከሰተውን ቀውስ በተመለከተ ጠ/ሚኒስትሩን ማብራሪያ እንዲሰጧቸው ጥያቄ ካቀረቡ ሳምንታት ተቆጥረዋል። በዚህም ምላሽ ካላገኘን በሚል በፓርላማ መደበኛ ስብሰባ ላይ መገኘት ባለመቻላቸው የፓርላማው ስራ ሲስተጓጎል ቆይቷል። ሰኞ ታህሳስ 16/2010 የፓርላማ አባላቱን በጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው ሳይሆን በኢህአዴግ ሊቀመንበርነታቸው ያነጋገሩት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ አብረዋቸው የፓርላማ አባላት ያልሆኑ ሌሎች የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በአስረጅነት መግኘታቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። የህወሀት ደጋፊ የሆነው አይጋ ፎርም የተባለው ድረ ገጽ ደግሞ ከአቶ ሃይለማርያም ጋር
Image may contain: 2 people, people smiling በኢትዮጵያ በግፍ የታሰሩ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን ለማስታወስ በማህበራዊ ሚዲያዎች ዘመቻ በመካሄድ ላይ መሆኑ ታወቀ። በቲውተርና በፌስቡክ እየተካሄደ ባለው በዚሁ ዘመቻ በመላው ዓለም ኢትዮጵያውያን ተሳታፊ ሆነዋል። በየእስር ቤቱ በስቃይ ላይ የሚገኙትንና በግፍ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያን ፎቶግራፎች በመለጠፍና ስቃያቸውን በመዘርዘር ትኩረት እንዲያገኝ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል። ዘመቻውን የሚያስተባብሩት በኢትዮጵያ የሚገኙ ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ግለሰቦች እንደሆኑም ታውቋል። ዛሬ ፌስቡኩ በኢትዮጵያውያን አንድ ዘመቻ ተወሯል። መልዕክቱ ተመሳሳይ ሆኖ በዓለም ዙሪያ ባሉ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ሲስተጋባም ውሏል። የዶ/ር መረራ ጉዲና፣ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ የአቶ ኦኬሎ አኳይ፣ የወጣት ንግስት ይርጋ፣ የወጣት ሴና ሰለሞን፣ የአቶ በቀለ ገርባ፣ የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ የብ/ጄነራል ተፈራ ማሞና የሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች ፎቶግራፎች እየተለጠፉ በመታወስ ላይ ናቸው። ባለፉት 26

በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ በመከላከያ ምስክርነት የተጠቀሱት አቶ ለማ መገርሳና ዶ/ር አብይ አህመድ ፍርድ ቤት ቀርበው ሊመሰክሩ እንደሚችሉ ተገለፀ

በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ በመከላከያ ምስክርነት የተጠቀሱት አቶ ለማ መገርሳና ዶ/ር አብይ አህመድ ፍርድ ቤት ቀርበው ሊመሰክሩ እንደሚችሉ ተገለፀ። ባለስልጣናቱን በአካል አግኝቼ አነጋግሬያቸዋለሁ ያሉት የተከሳሾቹ ጠበቃ አቶ ለማ መገርሳን ጨምሮ ሌሎችም በችሎት ተገኝተው ሊመሰክሩ እንደሚችሉ ገልጸውላቸዋል። በሌላ በኩል የበቀለ ገርባ የመከላከያ ምስክር የሆኑት አቶ አንዱዓለም አራጌ በከባድ ወንጀል የተከሰሱ ናቸው በሚል ማረሚያ ቤቱ ችሎት አላቀርብም ማለቱ ተሰምቷል። በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ ከ1ኛ እስከ 4ኛ ያሉት ተከሳሾች በመከላከያ ምስክርነት እንዲገኙላቸው ጠይቀው የነበሩት አቶ ለማ መገርሳን፣ ዶ/ር አብይ አህመድን፣ ወ/ሮ ጫልቱ ሰኒንና አቶ አባዱላ ገመዳን ነበር። ለምስክርነት የተጠሩት ባለስልጣናት ግን ለሁለት ጊዜ ያህል ስብሰባ ላይ ሆነን ነው በሚል ለምስክርነት መቅረብ አለመቻላቸው ታውቋል። ታዲያ አሁን ላይ የተከሳሾቹ ጠበቃ አቶ አብዱልጀባር ሁሴን ለችሎቱ ለምስክርነት የተጠሩት ባለስልጣናት ችሎት ቀርበው ሊመሰክሩ ይችላሉ የሚል መረጃ አቅርበዋል። ፋይል ይህን ደግሞ እራሴ በአካል አግኝቼ አነጋግሬያቸዋለሁ።በቃላቸውም ይህን ምላሽ ሰጥተውኛል ብለዋል ጠበቃው አብዱልጀባር። ከዚህ በፊት ያልተገኙትም በስብሰባ ምክንያት መሆኑን አረጋግጠውልኛል ብለዋል። እንግዲህ ግለሰቦቹ እንዳሉት ከሆነና በቃላቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቀረበው የምስክርነት ቃላቸውን የሚሰጡ ከሆነ ለነገ ታህሳስ 19/2010 በችሎት ቀጠሮ ተይዞላቸዋል ይላል ኢሳት ያገኘው መረጃ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በፖሊስ ተይዘው ይቅረቡልኝ ያሉት አቶ በቀለ ገርባ ሌላኛው ምስክራቸው አቶ

በአሜሪካ የሚገኙ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ስደተኞችን በማስጠለል ላይ መሆናቸው ታወቀ

 በአሜሪካ የሚገኙ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ስደተኞችን በማስጠለል ላይ መሆናቸው ታወቀ። አብያተክርስቲያናቱ ስደተኞቹን እያስጠለሉ ያሉት የትራምፕ አስተዳደር ሕገወጥ የሚላቸውን ስደተኞች ወደ ሀገራቸው የመመለሱን ስራ በማጠናከሩ ነው። ቢያንስ 32 የሚሆኑ አብያተክርስቲያናት በራቸውን ለስደተኞች ክፍት በማድረግ ስደተኞቹን ከመባረር በመታደግ ላይ ናቸው። የአሜሪካ የስደተኞችና ጉምሩክ ሕግ አስከባሪ መስሪያ ቤት ፖሊሲ በአብያተክርስቲያናት ፣በትምህርት ቤቶች እንዲሁም በሕክምና ተቋማት ፍተሻ ማካሄድን አይፈቅድም። በመሆኑም የመኖሪያ ፍቃድ የሌላቸውና ከሀገር እንዲወጡ የተወሰነባቸው ስደተኞች ከመባረር ለመዳን በራቸውን በከፈቱ አብያተ ክርስቲያናት ገብተው ይደበቃሉ። ፖሊሲው ይህን ይበል እንጂ የስደተኞችና ጉምሩክ ህግ አስከባሪዎች በአብያተክርስቲያናትና መሰል ተቋማት እንዳይገቡ የሚከለክል ህግ የለም። አሊሪዮ ጎሜዝ የተባለና ከኤልሳልቫዶር የመጣ ስደተኛ ፍርድ ቤት ወደ ሃገሩ እንዲመለስ በመወሰኑ ከመባረር ለመዳን በአንድ ቤተክርስቲያን ተጠልሎ ይገኛል።

Tuesday, December 26, 2017

በበለደወይን አካባቢ 17 የኢትዮጵያ ወታደሮች ተገደሉ

የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በፈርጆች አቆጣጠር ከ5 ቀናት በፊት በለደወይን በሚባለው የሶማሊያ ግዛት ውስጥ 17 ወታደሮች ማንነታቸው ባልታወቁ ሃይሎች ተገድለዋል። የተወኑ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችም ተቃጥለዋል። ጥቃቱን ያደረሱት ሃይሎች የኢትዮጵያን ጦር ዩኒፎርም የለበሱ እና አማርኛ የሚናገሩ ናቸው። 
በቅርቡም ሃርትሸክ ላይ በሶማሊ ልዩ ሃይል ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ይህ ማንነቱ ያልታወቀ ቡድን ላለፉት 8 ወራት በአካባቢው እየተንቀሳቀሰ በኢትዮጵያ ጦር ላይ ጉዳት ሲያደርስ መቆየቱን ምንጮች ይገልጻሉ።
ጥቃቱ መፈጸሙን በተመለከተ በአገዛዙ በኩል ምንም መግለጫ አልተሰጠም። ነገር ግን የሶማሊ ልዩ ሃይልም ሆነ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ይህን ማንነቱ ያልታወቀ ሃይል ለማደን ተደጋጋገሚ ሙከራዎችን ቢያደርጉም እስካሁን እንዳልተሳካላቸው ምንጮች አክለው ገልጸዋል።

በአርባምንጭ ከተማ ፖሊሶች እስከ ጦር መሳሪያቸው መጥፋታቸው ታወቀ

የአካባቢው የፖሊስ ምንጮች እንደገለጹት በቅርቡ የኡራኤል በአል ሲከበር ለጥበቃ ከተላኩ ፖሊሶች መካከል የተወሰኑ ፖሊሶች ሙሉ ትጥቃቸውን ይዘው ጠፍተዋል። በበአሉ ላይ ከሰንደቃላማ ጋር በተያያዘ መጠነኛ የሆነ አለመግባባት በህዝቡ እና በፖሊሶች መካከል ተፈጥሮ ነበር። ህዝቡ “ አንመካም በጉልበታችንን” የሚል ዝማሪ እያሰማ ታቦቱን አጅቦ መጓዙን የሚገልጹት ምንጮች፣ ግጭት ይፈጠራል ተብሎ ቢፈራም ዝግጅቱ በሰላም መጠናቀቅ ችሎአል። በዝግጅቱ ላይ ከነበሩ ፖሊሶች መካከል የተወሰኑ ፖሊሶች ወደ ጽ/ቤታቸው ተመልሰው ሪፖርት አለማድረጋቸውንና ጠፍተዋል ተብሎ እምነት መያዙን ምንጮች ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በርካታ የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መታሰራቸው ታውቋል። በቅርቡ የተማሪዎችን አመራሮች ለመምረጥ በተደረገ ስብሰባ ላይ ተማሪዎች የተለያዩ ሃሳቦችን በመያዛቸው ለመስማማት ሳይችሉ መቅረታቸውን የሚገልጹት ምንጮች፣ ምሽት ላይ የግቢው የእቃ መጋዘን መጋየቱንና ከዚሁ ጋር ተያይዞ 20 የሚሆኑ ተማሪዎች እንታሰራለን በሚል ፍርሃት ከግቢው ሲጠፉ ፣ የተወሰኑ ተማሪዎች ደግሞ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ተማሪዎቹ ከቃጠሎው ጋር ግንኙነት ይኑራቸው አይኑራቸው የታወቀ ነገር የለም።
ከዚሁ ከአርባምንጭ ሳንወጣ ቦንኬ በሚባል አካባቢ አንድ ከወለጋ አካባቢ የመጣ እና በኤልክትሪክ መስመር ዝርጋታ ላይ ይሰራ የነበረን ግለሰብ መቶ አለቃ ኤርምያስ የሚባል የአካባቢው ፖሊስ ተኩሶ የገደለው ሲሆን፣ ህዝቡ ፖሊሱን በመክበብ በቁጥጥር ስር አውሎ ለፖሊስ ማስረከቡን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የፓርላማ አባላትን በጥብቅ የደህንነት ጥበቃ ስር ሆነው አነጋገሩ።

በኢህአዴግ አባላት የተያዘው ፓርላማ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ መደበኛ ስብሰባዎችን እስከማቋረጥ የደረሰ ሲሆን፣ ለዚህ ምክንያቱ በሀገሪቱ እየተቀጣጠለ ያለውና መቋጫ ሊገኝለት ያልቻለው ሕዝባዊ አመጽና ግድያ እንደሆነ ታውቋል።
በተለይ ባለፈው ሳምንት የ ኦሮሞ ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት -(ኦ ህ ዴድ ) እና የብሔረ አማራ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ብአዴን) አባላት የሆኑ የምክር ቤት እንደራሴዎች እጅግ አሣሳቢ ደረጃ ላይ በደረሰው በሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ለምናነሳቸው ጥያቄዎች አቶ ኃይለማርያም በአካል ተገኝተው ምላሽ ካልሰጡ ከእንግዲህ አንሰበሰብም በማለት በማደማቸው ስብሰባው ጠቅላላ ተቋርጧል።
ይህን ተከትሎ አቶ ኃይለማርያም በትናንትናው ዕለት የፓርላማ አባላቱን በዝግ ስብሰባ ያነጋገሩ ሲሆን፣ ለሦስት ሰዓታት የዘለቀው ይህ ስብሰባ ለታማኝ መገናኛ ብዙሀን ሳይቀር በመከልከሉ አባላቱ በምን ጉዳይ ላይ እንደተነጋገሩ ለማወቅ አልተቻለም።
በአካባቢው ከፍተኛ የደህንነት ጥበቃ የተደረገ መሆኑን፣ ሁሉም ተሰብሳቢዎች ማንኛውንም አይነት የአሌክትሮኒክስ እቃዎችን ውጭ አስቀምጠው እንዲገቡ መደረጉንና አጠቃላይ ፍተሻው ከዚህ በፊት ከነበሩት ሁሉ ከፍተኛ እንደነበር ታውቛል።

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በፖሊስ ተገደው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ተጠየቀ

በተከሳሾች በመከላከያ ምስክርነት ተቆጥረው መቅረብ ያልቻሉት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በፖሊስ ተገደው ፍርድ ቤት በመቅረብ እንዲመሰክሩላቸው የአቶ በቀለ ገርባ ጠበቃ ጠየቁ።
አቶ ኃይለማርያምን መክርላከያ ምስክር በማድረግ የቆጠሯቸው፣ የኦሮሞ ፌዴራሊስንት ኮንግረስ አመራሩን አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ ስር ከ1ኛ እስከ 4ኛ ድረስ ያሉት ተከሳሾች ናቸው።
ቀደም ሲል ፍርድ ቤቱ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ቀርበው እንዲመሰክሩ ትዕዛዝ ልኮ የነበር ቢሆንም፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በጊዜ መጣበብ ምክንያት መቅረብ እንዳልቻሉ ለፍርድ ቤቱ መልስ ሰጥቷል።
የተከሳሾች ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅህፈት ቤት የሰጠው መልስ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ቀርበው መመስከር አይችሉም ይሁን ወይም በጊዜ መጣበብ ሳቢያ አልተመቻቸው የሚል መሆኑ ግልፅ እንዳልሆነ በመጥቀስ፣ “ምላሹ መመስከር አይችሉም ከሆነ ትክክል ስላልሆነ የሚመቻቸው ጊዜ ተጣርቶ እንዲመሰክሩ ይመቻች”ሲሉ ጠይቀዋል።

Saturday, December 23, 2017

አዲስ አበባ(DR.Tadesse Biru Kersmo)

ስለአዲስ አበባ አዘውትረን የምንናገርበትና የምንጽፍበት ወቅት እየመጣ ነው !!!
አዲስ አበባ - አጠገቧ ባሉ ከተሞች ሕፃናትና አዛውንት በአጋዚ ጥይት ሲቆሉ የማትሰማ፤ ብትሰማም ምላሽ የማትሰጥ ከተማ ናት። ማዕከላዊ፣ ቃሊቲና ቂሊንጦን ይዛ ስለእነዚህ የማታውቅ ለመምሰል የምትጥር፤ የገዛ ራስዋን እየሸነገለች የምትኖር ከተማ ናት።
አዲስ አበባ - በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ነዋሪዎቿ በኑሮ ውድነት የሚጠበሱባት፤ በጥቂት ሺዎች የሚቆጠሩ ሀብታሞች ደግሞ የመቶ ብሮች ኖቶችን በጭፈራ ቤት ዘፋኞች አናት ላይ የሚነሰኑስባት የጉድ ከተማ ነች።
አዲስ አበባ - ለሁለት ሚሊዮን ነዋሪዎች በተሠራ መሠረተ ልማት ከ8-10 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ የሚገለገልባት በሕዝብ ብዛት ልትፈነዳ የደረሰች ከተማ ነች።

Friday, December 22, 2017

የኦህዴድ ተወካዮች የፓርላማ ውይይቱ እንዲቋረጥ አደረጉ

ዛሬ ታህሳስ 13/2010 ዓም ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ የሚኖራትን ልዩ ጥቅም ለመወያየት የኦህዴድ የፓርላማ አባላት ለውይይት ተጠርተው የነበረ ቢሆንም፣ የኦሮምያ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እና እርሳቸውን ደግፈው የቆሙ የፓርላማ አባላት ባስነሱት ተቃውሞ ውይይቱ እንዲቋረጥ ተደርጎ ፓርላማው ተበትኗል። በቅርቡ ከአፈ ጉባኤ ወንበራቸው ለመነሳት የስልጣን መልቀቂያ አቅርበው የነበሩት አፈ ጉባኤው አባ ዱላ ገመዳ ከአቶ አዲሱ እና ከሌሎች የፓርላማ አባላት የተለዬ አቋምይዘው ታይተዋል።

የፌደራል ጠ/አቃቢ ህግና የህወሃት ጄኔራሎች በሶማሊ ክልል በዘረጉት የጥቅም ሰንሰለት የተነሳ በሶማሊ ክልል ባለስልጣናት ላይ ምርመራ እንዳይደረግ እየተከላከሉ ነው

ጠቅላይ አቃቢ ህግ አቶ ጌታቸው አምባዬ በሶማሊ ክልል ውስጥ በርካታ የንግድ እና የመኖሪያ ቦታዎች ይዘው በወኪል የመሬት ሽያጭ ንግድ እንደሚያካሂዱ፣ ከእርሳቸው በተጨማሪ ዋና ዋና የሚባሉት የህወሃት ጄኔራሎች በመሬት ንግድ ውስጥ መሳተፋቸው የሶማሊ ክልል ባለስልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች በኦሮሞ ህዝብ ላይ በፈጸሙት ወንጀል እንዳይጠቀየቁ እየተከላከሉላቸው መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። ከክልሉ መሬት አስተዳደር ሃላፊ አቶ አብዲ ጀማል ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው አቶ ጌታቸው፣ ሁለቱ ባለስልጣናት በክልሉ መሪ እውቅና ከፍተኛ የሆነ የመሬት ሽያጭ ንግድ እያካሄዱ ይገኛሉ። በጅጅጋ የመሬት ዋጋ ከአዲስ አበባ የመሬት ዋጋ እንደማይተናነስ የተናገሩት ምንጮች፣ በዚህም የዝርፊያ ሰንሰለት አቃቢ ህጉና የሶማሊ ክልል ባለስልጣናት ከፍተኛ ሃብትና ንብረት ሰብስበዋል። (ፎቶ አለ)

በሶማሊ እና ኦሮምያ ክልል አጎራባች በሚገኙ ከተሞች የሚገኙ ታጣቂዎች እንዲነሱ ትዕዛዝ ተላለፈ

የመከላከያ አዛዦች ባስተላለፉት ትእዛዝ በሁለቱ ክልሎች የድንበር ከተሞች ላይ የሚገኙ የሶማሊ እና የኦሮምያ ክልል ታጣቂዎች ከአካባቢው እንዲርቁ እና ከተሞቹ ሙሉ በሙሉ በመከላከያ ሰራዊት ቁጥጥር ስር ይውላሉ። ትዕዛዙን የማይፈጽሙ የሁለቱ ክልሎች ታጣቂዎች ትጥቃቸውን እንዲያወርዱ ተደርጎ እርምጃ ይወሰድባቸዋል ተብሎአል። ከኦሮምያ ክልል ከምስራቅ ሃረርጌ በኩል 8 ወረዳዎችን መከላከያ ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠራቸዋል። 
የኦሮምያ ክልል ታጣቂዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከአጋዚ ወታደሮች ጋር አለመግባባት እየፈጠሩ አልፎ አልፎም እርስ በርስ እየተታኮሶ ከሁለቱም ወገን የሰው ህይወት ሲጠፋ ቆይቷል። አቶ ለማ መገርሳ የኦሮምያ ታጣቂዎች ህዝቡን ከጥቃት እንዲከላከሉ አስፈላጊውን መስዋትነት እንዲከፍሉ በመገናኛ ብዙሃን ተናግረው ነበር። የአሁኑ ትዕዛዝ ለብዙ የኦሮምያ ክልል ባለስልጣናት የሚዋጥ አልሆነም። ህዝቡ መከላከያ ከክልሉ እንዲወጣ እየጠየቀ ባለበት በዚህ ሰአት መከላከያን በብዛት እያስገቡ ክልሉን እንዲቆጣጠር የማድረጉ እንቅስቃሴ ህዝቡን እያስቆጣው ነው።

በካራሚሌ ከተማ ህዝቡ ለመከላከያ ሰራዊት አገልግሎቶችን ባለመስጠት ተቃውሞውን እየገለጸ ነው።

ወታደሮቹ ወደ ከተማው ገብተው ማረፊያ ቦታ በጠየቁበት ወቅት የወረዳው ባለስልጣናት ፣ “ እናንተ በክልሉ ትዕዛዝ ስላልመጣችሁም ማረፊያ ቦታ ልንሰጣችሁ አንችልም “ በማለት ቢሮዋቸውን ቆልፈው ሲሄዱ፣ ወታደሮቹ ቢሮዎችን እየሰበሩ ገብተው ተቀምጠውባቸዋል። በድርጊቱ የተቆጣው ህዝብ ለወታደሮች ምንም አይነት አግልገሎት ላለመስጠት ቃል የገባ ሲሆን፣ ወደ ሱቆች በመሄድ ውሃ ለመግዛት ሲጠይቁ እንኳን ከፍተኛ ዋጋ ተጠይቀዋል። በህዝቡ አድማ ምንም ለማድረግ ያልቻሉት ወታደሮች ከሶስት ቀናት በፊት አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል። 
መከላከያ ከክልሉ እንዲወጣ የሚጠይቁ በርካታ የተቃውሞ ሰልፎች ዛሬም ተደርገዋል። በአምቦ፣ ጊንጪ፣ ጉደር፣ ግንደበረት፣ እና በሌሎችም የምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች የስራ ማቆም አድማ ሲደርግ ውሎአል። መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ሆነው ውለዋል። የንግድ ድርጅቶችና ባንኮችም ተዘግተዋል። የስራ ማቆም አድማው ለሚቀጥሉት 3 ቀናት ቀጥሎ እንደሚውል ታውቛል።በካራሚሌ ከተማ ህዝቡ ለመከላከያ ሰራዊት አገልግሎቶችን ባለመስጠት ተቃውሞውን እየገለጸ ነው። 

Wednesday, December 20, 2017

በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ዛሬ ተቃውሞ መካሄዱ ተገለጸ

 በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ዛሬ ተቃውሞ መካሄዱ ተገለጸ። በዱከም የቻይና የኢንዱስትሪ ዞን መመስረትን በመቃወም ሰልፍ ተካሄዷል። መቱ ለሶስተኛ ቀን ተቃውሞ ተደርጎባታል። በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ዛሬ ግጭት መፈጠሩም ታውቋል። በድሬዳው ዩኒቨርስቲ ዛሬ ግጭት መፈጠሩን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ባለፈው ሰኞ በርካታ ተማሪዎች የተጎዱበት ግጭት ከተከሰተ በኋላ ዩኒቨርስቲው በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የነበረ ቢሆንም ዛሬም በተማሪዎች ተቃውሞ ተቀስቅሷል። በኢሉባቡር መቱ ለ3ኛ ቀን በተካሄደ የተቃውሞ ትዕይንት ልብሳቸውን ያወለቁ ወጣቶች አደባባይ ወጥተው ተቃውሟቸውን አሰምተዋል። በአዲስ አበባ አቅራቢያ ባለችው ዱከም ከተማ የቻይናን የመሬት ወረራ በመቃወም ሰልፍ ተደርጓል።

በሐገር ቤት የሚንቀሳቀሱ ሁለት ፓርቲዎችና በውጭ ሀገር የሚገኙ የተቃዋሚዎች ስብሰባ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን ገለጹ

በሐገር ቤት የሚንቀሳቀሱ ሁለት ፓርቲዎችና በውጭ ሀገር የሚገኙ የተቃዋሚዎች ስብሰባ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን ገለጹ። ሰማያዊ ፓርቲ እንዲሁም መኢአድና ሸንጎ በዋሽንግተን ዲሲ በሳምንቱ መጨረሻ ባካሄዱት ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ እንዳስታወቁት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታውቀዋል። ሁለቱ የሀገር ቤት ድርጅቶችና ሸንጎ በሚል አጭር መጠሪያ የሚታወቀው በውጭ የሚገኙ ተቃዋሚዎች ስብሰባ በጋራ ባወጡት መግለጫ እንዳስታወቁት በአደረጃጀት፣በፋይናንስ፣በአቅም ግንባታ፣አለም አቀፍ የፋይናንስ ድጋፍ በማሰባሰብ እንዲሁም በብሔራዊ እርቅና በመሳሰሉት ጉይዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል። ይህም ትብብር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ ወቅታዊና ተጨባጭ ምላሽ የሚሰጥ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የትብብሩ አካል እንዲሆኑና ድጋፍ እንዲሰጡም ሶስቱም ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል። ሰማያዊና መኢአድ በሀገር ቤት ህጋዊ ዕውቅና አግኝተው የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ሲሆኑ የሁለቱ ድርጅቶች መሪዎች ላለፉት ጥቂት ወራት በሰሜን አሜሪካ በድርጅታዊ ስራ ላይ መቆየታቸው ተመልክቷል። እነዚህ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ሕዝብ ሸንጎ ጋር ያደረጉት ስምምነት ሁሉም ድርጅቶች ነጻነታቸውን በጠበቀ መልኩ ያደረጉት ስምምነት እንደሆነም መረዳት ተችሏል።

የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ የሱዳን ጦር የሀገራችንን ድንበር በመጣስ በቅርቡ የፈጸመው ወረራ አለም አቀፍ ሕግን የሚጻረር ነው ሲል ለፕሬዝዳንት አልበሽር በጻፈው ደብዳቤ አሳሰበ።

የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ የሱዳን ጦር የሀገራችንን ድንበር በመጣስ በቅርቡ የፈጸመው ወረራ አለም አቀፍ ሕግን የሚጻረር ነው ሲል ለፕሬዝዳንት አልበሽር በጻፈው ደብዳቤ አሳሰበ። የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን ድንበር በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣም ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል። የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ ለሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር አልበሽር ይህን መሰል ደብዳቤ ሲጽፍ የመጀመሪያው አይደለም። የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን ተላልፎ ተሰቷል ከተባለበት ጊዜ አንስቶ ጉዳዩ ያሳሰበው መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል። አሁን ለፕሬዝዳንት አልበሽር የተጻፈውና ለተባበሩት መንግስታት እንዲሁም ለአፍሪካ ህብረት በግልባጭ የተገለጸው ደብዳቤ የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን ድንበር በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ይጠይቃል። እንደ ኮሚቴው ደብዳቤ ገለጻ የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን ድንበር ተላልፎ ወረራ መፈጸሙ አለም አቀፍ ህግን የሚጻረር ነው። የአንድን ሉአላዊ ሀገር ድንበርን ተሻግሮ መግባትና በሕዝብ ላይ ጉዳት ማድረስ የተባበሩት መንግስታትን ቻርተር ይጥሳልም ነው ያለው የኢትዮጵያ የድንበር ጉዳይ ኮሚቴ። እናም የፕሬዝዳንት አልበሽር መንግስት በተደጋጋሚ ጊዜ የኢትዮጵያን ድንበር በመጣስ የሚያደርገው ወረራ ሊቆም እንደሚገባ አሳስቧል። በኮሚቴው ደብዳቤ ላይ እንደተገለጸው የሕወሃት አገዛዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁንታ ያላገኘ በመሆኑ ማንኛውም ከሱዳን ጋር የተገባ

በምስራቅ ሃረርጌና በኢሉባቦር ዞኖች የተቃውሞ ሰልፎች ተካሄዱ

በምስራቅ ሃረርጌ በኮምቦልቻ ከተማ እንዲሁም በኢሉባቦር ዞን በመቱ ከተማ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂደዋል።በኮምቦልቻ የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በተሳተፉበት የተቃውሞ ሰልፍ መከላከያ ሰራዊቱ ከአካባቢያቸው እንዲወጣ ጠይቀዋል። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የሰጡትን መግለጫም ተማሪዎቹ አድሎአዊ የተሞላበት በማለት አውግዘውታል። የታሰሩ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ሃሳባቸውን በነጻነት የገለጹ ወጣቶች እንዲፈቱም ተማሪዎች ጠይቀዋል።
ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት በአካባቢው እንደሚገኙና በጨለንቆ አካባቢ ተጨማሪ 20 ቤቶችን ማቃጠላቸውን ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል ።
በመቱ ደግሞ ለ3ኛ ቀን በተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ መከላከያ ሰራዊቱ ከክልሉ እንዲወጣ እንዲሁም በኦሮሞ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት እንዲቆምና በሶማሊና በኦሮምያ ክልሎች መካከል የሚካሄደው ድራማ ይቁም በማለት ሰልፈኞቹ ጠይቀዋል።
“ የወያኔ አገዛዝ እየወደቀ በመሆኑ ህዝቡ አይኑን ስርዓቱ ላይ ማድረግ እንደሚገባውና ትግሉን ወደ ሁዋላ ከሚጎትቱ የብሄር ግጭቶች ራሱን እንዲያርቅ” ተሳታፊዎች ምክራቸውን ለግሰዋል። 

በአማሮ ወረዳ ያለው ግጭት እንደቀጠለ ነው

በአማሮ ወረዳ ያለው ግጭት እንደቀጠለ ነው
ከድንበር ማካለል ጋር በተያያዘ በአገዛዙ ካድሬዎች የተነሳውና ላለፉት 5 ወራት መፍትሄ አጥቶ የቀጠለው የኮሬና የጉጂ ኦሮሞ ብሔረሰቦች ግጭት፣ ትናንት ታህሳስ 10 ቀን 2010 ዓም ምሽት ላይ በተነሳዉ ግጭት በአማሮ ወረዳ ጎልቤ በተባለዉ ቀበሌ ሁለት የኮሬ አርሶ አደሮች ሕይወት ሲጠፋ በተመሳሳይ ሰዓትም በቡርጂ እና በጉጂ መሃል ግጭቱ ተቀስቅሶ አንድ የቡርጂ አርሶ አደር ወዲያዉ ሕይወቱ ሲያልፍ አንዱ ደግሞ ቆስሏል።
ባለፈው እሁድና ሰኞ የደኢህዴን ልሳን በሆነዉ የደቡብ ቲቪ ግጭቱ እንደቆመና የህዝብ ለህዝብ እርቅ እንደተደረገ በተነገረ ማግስት አዲስ ግጭት መቀስቀሱ ህዝቡን ይበልጥ እያነጋገረው ነው።
በአካባቢዉ የአጋዚ እና የአካባቢ ፖሊስ አባላት ቢኖሩም ግጭቱን ለማስቆም ፈቃደኝነት አላሳዩም። ከሐምሌ 16 2009 ዓም ወዲህ በኮሬ በኩል ብቻ የሞቱት ዜጎች ቁጥር 30 መድረሱና የቆሰሉት ደግሞ 64 መሆናቸዉ ታውቋል፡፡
በመንገድና በመብራት እጦት ሲሰቃይ በነበረዉ ሕብረሰብ ላይ የኔትዎርክና ኢንተርኔት አገልግሎት በመቋረጡም ከማህበራዊ ሚዲያዎች የሃገሪቷን ሁኔታ ሲከታተሉ ለነበሩት የህብረተሰብ ክፍሎች ተጨማሪ እንግልት እንደፈጠረባቸው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

እስረኞች በቀጠሮ እንዳይቀርቡ መደረጋቸውንና በሃሰት እንዲመሰክሩ እየተገደዱ መሆኑን ለፍርድ ቤት ተናገሩ

በቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ በእነ አርጋው ሞገስ ክስ መዝገብ ከተከሰሱት እስረኞች መካከል በፍርድ ቤት በተሰጣቸው ቀነ ቀጠሮ እንዳይቀርቡ የተደረጉ እስረኞች አሉ። ታህሳስ 11 ቀን 2010 ዓ.ም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት ተከሳሾች በእስር ቤት አስተዳዳሪዎች የሚደርሱባቸውን በደሎች አስመልክቶ ለችሎቱ አሰምተዋል።
ተከሳሾቹ ''በእስር ቤቱ አስተዳዳሪዎች የሚደርሱብንን የመብት ጥሰቶች በተደጋጋሚ ጊዜ ለችሎቱ ተናግረናል። የከሰሰን ማረሚያ ቤቱ ሲሆን አሁንም በከሳሻችን እጅ እንገኛለን። ማረሚያ ቤቱ ነው ወይስ ፍርድ ቤቱ ነው የበላይ?' እኛ ፍትሕ ሳናገኝ በእስር ላይ እንድንቆይ ተከሳሾቹን እያቀረበ አይደለም። ለማን አቤት እንበል? የት ሄደንስ አቤት እንበል?'' ሲሉ አቤቱታቸውን ለችሎቱ አሰምተዋል።
ተከሳሾቹ አክለውም ''ከመስከረም ወር ጀምሮ በማናውቀው ምክንያት ታፍነን ወደ ዝዋይ እስር ቤት ተወሰደን ታፍነን መጣን። አሁንም የፈለጉትን እያፈኑ ይወስዱና በቀጠሮ ቀን የሉም ይላሉ። አንድም ቀን ማረሚያ ቤቱ በችሎት ቀርቦ ለቀረበበት አቤቱታ መልስ ሰጥቶ አያውቅም። ፍርድ ቤቱ መፍትሄ እየሰጠን አይደለም።'' በማለት የእስር ቤቶቹን ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ፍርድ ቤቱ ሊታደጋቸው አለመቻሉን ተናግረዋል።

የአሜሪካ ኮንግረስ አባል ማይክ ኮፍማን የራሱን ህዝብ የሚያሸብር መንግስት የአሜሪካ አጋር መሆን አይገባውም ሲሉ ተናገሩ

Image may contain: 1 person, suitየአሜሪካ ኮንግረስ አባል ማይክ ኮፍማን የራሱን ህዝብ የሚያሸብር መንግስት የአሜሪካ አጋር መሆን አይገባውም ሲሉ ተናገሩ። ኮፍማን ይህንን ያሉት በአሜሪካ የኮሎራዶ ግዛት ዋና ከተማ በሆነችው ዴንቨር ባለፈው ቅዳሜ ኤች አር 128 በመባል የሚታወቀውን ረቂቅ ህግ አስመልክቶ በተዘጋጀው ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ነበር። ኢትዮጵያና አሜሪካ በጋራ የሚያደርጉት የጸረ ሽብር እንቅስቃሴ አደጋ ላይ ይወድቃል በሚል ማስፈራሪያ ህጉ እንዲጨናገፍ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

Ethiopia: Oromo, Amhara MPs boycott Parliament

ESAT News (December 20, 2017)
Oromo and Amhara MPs representing the Oromo People’s Democratic Organization (OPDO) and the Amhara National Democratic Movement (ANDM) have boycotted the Ethiopian Parliament saying the Prime Minister need to address the ongoing ethnic clashes and political crisis in the country.
The Parliament did not hold its regular session last Thursday and yesterday as the absence of the Oromo and Amhara MPs resulted in a below the quorum attendance. Ethiopian parliament requires 51% attendance to proceed with a regular session.

Tuesday, December 19, 2017

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሊቀመንበር የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መኖሪያ ቤቶች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሽጠው ለመንግስት ገቢ መሆናቸውን የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ አስታወቀ።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሊቀመንበር የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መኖሪያ ቤቶች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሽጠው ለመንግስት ገቢ መሆናቸውን የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ አስታወቀ።
በእነ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ ሕገ መንግስታዊ ስርአቱን በሃይል ለመናድ ሞክራችኋል በሚል በተመሰረተባቸው ክስ የሞት ፍርድ የተወሰነባቸው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ንብረታቸውም እንዲወረስ በፍርድ ቤት ተወስኗል።
ጠቅላይ አቃቢ ህግ አደረኩት ባለው የሃራጅ ሽያጭ የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በጅምር ላይ ያለ መኖሪያ ቤት በ6 ሚሊየን ሶስት መቶ ሰማንያ ሺ ብር ተሽጦ ለመንግስት ገቢ መሆኑን አስታውቋል።

በአማራ ክልል በጎጃምና ጎንደር መስመር ዋና ዋና መንገዶች ላይ በሚሊሺያ ሰራዊትና በፌደራል ፖሊስ ጥብቅ ፍተሻና ጥበቃ መጀመሩ ተገለጸ።

 የህዝብ ንቅናቄ በተፈጠሩባቸው ከተሞች የመከላከያ ሰራዊት በብዛት መግባቱ ተገልጿል። በዩኒቨርስቲዎች አሁንም ትምህርት አልተጀመረም። በአፋር፣ ጋምቤላና አሶሳ ዩኒቨርስቲዎች ለተማሪዎች የንብረት ማውጫ ፍቃድ መከልከሉም ታውቋል። በአማራ ክልል በተለያዩ ቦታዎች ውጥረት መንገሱን የሚያሳዩ መረጃዎች ለኢሳት ደርሰውታል። በጎጃምና በጎንደር መስመሮች ከፍተኛ ፍተሻና ጥበቃ በመደረግ ላይ መሆኑ ታውቋል። የሚሊሻና የፌደራል ሰራዊት በዋና ዋና መንገዶች ላይ በብዛት የሚታዩ ሲሆን በኬላዎች ጥብቅ ፍተሻ በማድረግ ላይ መሆናቸው ተገልጿል። በተለይም እህልና የተለያዩ ምርቶችን ጭነው የሚመላለሱ ከባድ ተሽከርካሪዎች በሚበዙባቸው መንገዶች ላይ ከፍተኛ ጥበቃ መደረጉ ታውቋል። ይህም በዋናነት ወደ ትግራይ የሚጓዙ ተሽከርካሪዎችን ከጥቃት ለመጠበቅ የታቀደ መሆኑን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። በሌላ በኩል ከድንበር አከባቢው ወታደሮችን በመጓጓዝ የህዝብ ተቃውሞ ይታይባቸዋል በተባሉ ከተሞች እንዲሰፍሩ በመደረግ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

በኦሮሚያ ክልል ከያቤሎ እስከ ሞያሌ መስመር በመከላከያ ሰራዊት 7 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ።

 በኦሮሚያ ክልል ከያቤሎ እስከ ሞያሌ መስመር በመከላከያ ሰራዊት 7 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ። በአከባቢው ባሉ ወረዳዎች ግጭት ተፈጥሯል። መንገዶች መዘጋታቸው ታውቋል። በመቱ፣ በነቀምት፣ በደምቢዶሎ፣ በዋደራ፣ በሻኪሶና በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች ዛሬ ተቃውሞች ተካሂደዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግጭት ተለይቶት የማያውቀው የሞያሌ መስመር በየዕለቱ ሰዎች መገደላቸው እየተለመደ መቷል። በተለይም የመከላከያ ሰራዊትና የአጋዚ ጦር በህዝቡ ላይ በሚወስዱት ርምጃ የሚገደሉ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን መረጃዎች ያሳያሉ። ትላንት በያቤሎና በሞያሌ መሀል በሚገኙ አካባቢዎች የተነሳውን ግጭት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊት በወሰደው ርምጃ 7 ሰላማዊ ዜጎች መገደላቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በሶማሌና ኦሮሞ ተወላጆች መሀል የተፈጠረው ግጭትን ለመከላከል በሚል ጣልቃ የገባው የመከላከያ ሰራዊት በተለይ በኦሮሞ ተወላጆች ላይ ጥቃት አጠናክሮ መቀጠሉ እየተነገረ ነው። በትላንቱ ርምጃም ከተገደሉት ሌላ በርካታ ዜጎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ታውቋል። ከያቤሎ እስከ ሞያሌ ባሉት መንደሮችና ቀበሌዎች ውጥረቱ የበረታ ሲሆን መንገዶች መዘጋታቸውን ለማወቅ ተችሏል። በያቤሎ ወረዳ

በኢትዮጵያ የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ በተለይም በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የመከላከያ ሰራዊት ጣልቃ እንዲገባ በሃይማኖት አባቶች ስም እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑ ታወቀ።

በኢትዮጵያ የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ በተለይም በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የመከላከያ ሰራዊት ጣልቃ እንዲገባ በሃይማኖት አባቶች ስም እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑ ታወቀ። የኢሳት ምንጮች ከአዲስ አበባ እንደገለጹት የመከላከያ ሰራዊት ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ያለ ክልሉ ፈቃድ እንዲገባ የሃይማኖት አባቶች ጥሪ እንዲያደርጉ ታዘዋል። የሃይማኖት አባቶች በቀጣዮቹ ቀናት በዚህ ዙሪያ የጋራ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል። በፌደራልና በአርብቶ አደሮች ሚኒስቴር በኩል ለቀረበው ጥያቄ የሕወሃትና ሌሎች ከሕወሃት ጋር በቅርበት የሚሰሩ ባለስልጣናት ለሃይማኖት አባቶቹ በስልክና በአካል ስለጉዳዩ ማብራሪያ እየሰጡ መሆናቸውን ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ሕወሃት መሪዎች በፓርቲያቸው ውስጥ ሹምሽር ባደረጉ ማግስት በአጋር ፓርቲዎች ውስጥም በተመሳሳይ ብወዛ በማድረግ ሁሉን ነገር ለመቆጣጠር የነበራቸው እቅድ በኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናትና በተወሰኑ የብአዴን አመራሮች ተቃውሞ መገታቱን ለማወቅ ተችሏል። እየተካሄደ ባለውና ዛሬ ሳምንቱን ባስቆጠረው የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ አብዛኞቹ የኦህዴድና አንዳንድ የብአዴን መሪዎች በያዙት ጠንካራ አቋም ሳቢያ ሕወሃት ክልሎችን በወታደራዊ

በ8 ጉዳዮች በሽብር ወንጀል በእንግሊዝ መንግስት የተከሰሱት ታዋቂው ምሁርና ፖለቲከኛ ዶክተር ታደሰ ብሩ በተከሰሱባቸው ሁሉም ጉዳዮች ነጻ ተባሉ።

በ8 ጉዳዮች በሽብር ወንጀል በእንግሊዝ መንግስት የተከሰሱት ታዋቂው ምሁርና ፖለቲከኛ ዶክተር ታደሰ ብሩ በተከሰሱባቸው ሁሉም ጉዳዮች ነጻ ተባሉ። ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው የሀገሪቱ ፍርድ ቤት በሕዝብ በተመረጠ ዳኝነት/ጁሪ/ ዶክተር ታደሰ ብሩን በሙሉ ድምጽ ነጻ ናቸው ብሏል። ዶክተር ታደሰ ብሩ ሂደቱን ሲከታተሉና ሲጨነቁ ለነበሩ ኢትዮጵያውያን ምስጋና አቅርበዋል። ዶክተር ታደሰ ብሩ የተከሰሱት የሽብር ወንጀሎች ለምርምርና ለነጻነት ትግል የተጠቀሙባቸው የኤሌክትሮኒክስ መጻሕፍትን ይዘህ ተገኝተሃል የሚልና በሽብር ማሰልጠኛ ቦታዎች ተገኝተሃል በሚል ነበር። ጉዳዮቹ በክስ መልክ በእንግሊዝ አቃቢ ሕግ ቢቀርቡም በሀገሪቱ የፍትህ ስርአት ያለ በመሆኑ ሁኔታው ተጣርቶ ነጻ እንደሚሆኑ ብዙዎች ገምተው ነበር። እንደተገመተው በሕዝብ በተመረጡ ዳኞች/ጁሪ/ሲታይ የነበረው የዶክተር ታደሰ ብሩ ክስ በ8ቱም ጉዳዮች ነጻ ተብሎ ውሳኔ አግኝቷል። ዶክተር ታደሰ ብሩ ከውሳኔው በኋላ ለኢሳት እንደገለጹት በክሱ የቀረቡ 8ቱም ጉዳዮች ትክክል እንዳልነበሩ በመጨረሻ ተረጋግጧል። ዶክተር ታደሰ ብሩ እስካሁን በነበረው የክስ ሂደት ጉዳዩ አሳስቧቸው ሲጨነቁ ለነበሩ ኢትዮጵያውያንም ምስጋና አቅርበዋል። የዶክተር ታደሰ ብሩን በሽብር ወንጀል መጠርጠር መነሻ በማድረግ በሕወሃት የሚደገፉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ጉዳዩን ሲያራግቡ እንደነበር ይታወሳል።

የሶማሌ ክልል ተወላጆች ለከፍተኛ አደጋ መጋለጣቸው ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ--ታህሳስ 10/2010) ከ5ሺህ በላይ የሶማሌ ክልል ተወላጆች በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ያለውሃና ምግብ በመቆየታቸው ለከፍተኛ አደጋ መጋለጣቸው ተገለጸ። 
ሰሞኑን ከተከሰተው ግጭት ጋር በተያያዘ የስልክም ሆነ የትራንስፖርት ግንኙነት ተቋርጧል።
አስቸኳይ ድጋፍ ካልደረሰላቸው ዕልቂት ሊከሰት እንደሚችል በማስጠንቀቅ የሶማሌ ተወላጆች የአክቲቪስቶች መረብ መግለጫ አውጥቷል። 
በአራት ቀበሌዎች ተጠልለው የሚገኙ የሶማሌ ተወላጆችን ለመደገፍ የኦሮሞ ሽማግሌዎችና ወጣቶች ጥረት እያደረጉ መሆኑም ተገልጿል።
በአካባቢው ሌላ ዙር ጥቃት ይፈጸማል የሚል ስጋት እንዳለም ለማወቅ ተችሏል።
በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በቆርኬ፣ በዳባ፣ በዋታራራና በሚሊቃዪ ቀበሌዎች ከ5ሺህ በላይ የሶማሌ ተወላጆች የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ መሆናቸው ታውቋል።
የሶማሌ ተወላጆቹ ምግብና ውሃ ካገኙ ቀናት እንዳለፋቸው እየተነገረ ነው። ህክምና አላገኙም።
ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ በሚከሰቱ በሽታዎች ህጻናት እየተሰቃዩ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
የሶማሌ አክቲቪስቶች መረብ ሰብሳቢ አቶ ጀማል ዲሪዬ እንደሚሉት ሁኔታዎች አሳሳቢ ናቸው። ስርዓቱ ምን ዓይነት ተንኮል እያሰበ እንዳለ ለማወቅ አልቻልንም።

በኦሮምያ ክልል የሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች ዛሬም ቀጥለው ውለዋል

በጨለንቆ በመከላከያ ሰራዊት አባላት የተገደሉ የኦሮሞ ተወላጆችን ለመዘከር እንዲሁም መከላከያ ከክልሉ እንዲወጣ ለመጠየቅ የሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች ዛሬም በመቱና በደምቢደሎ ተደርገዋል።
ተማሪዎችና የከተማዋ ነዋሪዎች በአንድነት በመውጣት በመከላከያ እና በሶማሊ ልዩ ሃይል እየደረሰ ያለውን ጭፍጨፋ አውግዘዋል። መከላከያም ከክልሉ እንዲወጣ ጥያቄ አድርገዋል። 
በክልሉ የሚካሄዱ የተቃውሞ ሰልፎች መቀጠላቸው በስልጣን ላይ ባለው የህወሃት ኢህአዴግ አገዛዝ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል። በክልሉ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ሰራዊት መሰማራት ህዝቡን ይበልጥ እያስቆጣው መሆኑን የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ።

እንግሊዝ ፍርድ ቤት የአርበኞች ግንቦት7 የአመራር አባል የሆኑትን ዶ/ር ታደሰ ብሩን ከቀረበባቸው የሽብር ክስ ነጻ አላቸው።

ዶ/ር ታደሰ በእንግሊዝ መንግስት 8 ያክል ክሶች ቀርበውባቸው ነበር። ለወራት ከአገር እንዳይወጡ ታግደው ጉዳያቸውን ሲከታተሉት የቆዩት ዶ/ር ታደሰ፣ እርሳቸውና ጠበቆቻቸው ባቀረቡዋቸው የመከላከያ ማስረጃዎች ከሁሉም ክሶች ነጻ ተብለዋል።
ዶ/ር ታደሰ ብሩ ውሳኔው ለአገራቸው ነጻነት ለሚታገሉት ሃይሎች ሁሉ የምስራች መሆኑን ተናግረዋል።
የዶ/ር ታደሰ የትግል አጋር እና የአርበኞች ግንቦት7 ሊቀ/መንበር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ በአጭር ጊዜ የተሰጠው ውሳኔ እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል። 
ውሳኔው የትግላቸውን ትክክለኛነትና ለምን አላማ እንደሚታገሉ ያሳዬበት መሆኑን ፕ/ር ብርሃኑ ተናግረዋል ። 
የህወሃት ኢህአዴግ አገዛዝ በጅምር ላይ ያለውን መኖሪያ ቤትዎን ወርሶ በመሸጡ ምን እንደተሰማቸው የተጠየቁት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፣ ውሳኔውን በመገኛ ብዙሃን ሲሰሙ ከመሳቅ በስተቀር ምንም እንዳልተሰማቸው ገልጸዋል።

ህወሃት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚካሄዱትን ተቃውሞዎች እንደሚቆጣጠራቸውና አባላቱ እንዲረጋጉ መከረ

 ታህሳስ 8 ቀን 2010ዓም ሃረር ከተማ ላይ በተደረገው የህወሃት ስብሰባ ላይ ጡረታ የወጡ፣ በቦርድ የተገሉና በስራ ላይ ያሉ ወታደራዊ አዛዦች ፣ ነባር አመራሮችና የድርጅቱ ነባር አባላት የተገኙ ሲሆን፣ ሰብሳቢው የህወሃት ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ክፍል ውስጥ የሚሰሩት አቶ ዘላለም ለገሰ፣ አባሎች እንዲረጋጉ መክረዋል።
አቶ ዘላለም “ እኛ በሰጠነው ጅራፍ እኛው እየተገረፍን ነው፣ እኛ ስልጣን ሰጥተን መልሰው እኛ ላይ ዞረውብናል፣ መስዋትነት መክፈል የህወሃት የተለመደ ባህሪው በመሆኑ፣ የተወሰነ መስዋት የምንከፍል ቢሆንም፣ ድል እናደርጋለን” በማለት ለአባላቱ ተናግረዋል።
“ምንም ከቁጥጥራችን ስር የሚወጣ ነገር የለም” ያሉት አቶ ዘለላም፣ ኦህዴድና ብአዴንን በእብድነት መስለዋቸዋል። “ሁለቱም ድርጅቶች ያበዱ ስለሆኑ እኛ ከአበዱት ጋር አናብድም፣ ነገር ግን አጥፊዎችን ለፍርድ ለማቅረብ እየሰራን ነው” ብለዋል። አባላቱና ደጋፊዎቻቸው እንደ ድሮው በይፋ እንዳይጋፈጡ፣ በስውር እንዲታገሉ፣ በስውር መረጃ እንዲሰጡ ትዕዛዝ ሰጥተዋል። ከዚህ በሁዋላ ፊት ለፊት መታዬት አደጋ የሚያመጣ መሆኑንም

ስኳር ኮርፖሬሽን ተበላሽቶ ቀብሬዋለሁ ያለው ሁለት መርከብ ስኳር የሃሰት መሆኑን ምንጮች አስታወቁ

በስኳር ኮርፖሬሽን በውጭ ምንዛሬ ተገዝቶ በሁለት መርከብ ተጭኖ ወደ አገር ውስጥ አስገብቸዋለሁ ያለው 3 ሺህ 777 ኩንታል በመበላሸቱ መተሃራ ውስጥ ቀብሬዋለሁ ያለው ስኳር የሃሰት መረጃ መሆኑን ምንጮቻችን አስታውቀዋል።
አገኘሁ ጌታቸው ተጨማሪ አለው
ኮርፖሬሽኑ ለስኳሩ መበላሸት የኢትዮጵያ ንግድ መርከብን በምክንያትነት ቢያቀርብም በንግድ መርከብ ተጭኖ ስኳሩ አገር ውስጥ ኮርፖሬሽኑ እስኪረከበው ድረስ ምንም ዓይነት የጥራት መጓደል እንዳልነበረው ምንጮች አክለው ገልጸዋል።
ስኳር ኮርፖሬሽኑ ባለስልጣናት ስኳሩን የቀበርነው ውጭ አገር ድረስ ልከን መበላሸቱንና ለምግብነት እንደማይውል ካረጋገጥን በኋላ ነው። ስኳሩ ሲቀበር ምስክር እንደነበራቸው ለፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ያቀረቡት መረጃ ፍጹም ታአማኒነት የሌለው ሪፖርት መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸው ስኳር ኮርፖሬሽን ስኳሩን ከተረከበ በኋላ ተበላሽቶ መቅበሩን መግለጹ በመተሃራ ስኳር ፋብሪካ አመራሮች ዘንድ ግርምትን ፈጥሯል።
ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ በሙያቸው ለረዥም ዓመታት በመተሃራ ስኳር ፋብሪካ ውስጥ ተቀጥረው ሲያገለግሉ የነበሩ ባለሙያዎችን በማግለል የህወሃት ታማኞችን በከፍተኛ አመራርነት መሾም እየተለመደ መጥቷል። ይህም በድርጅቱ ሰራተኞች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥርዋል።
የደመወዝ እድገትን ጨምሮ በዓመቱ መጨረሻ ይሰጡ የነበሩ ልዩልዩ ጥቅማጥቅሞች እንዲዘገዩ ከመደረጋቸው በተጨማሪ ለፋብሪካው የሚደረግለት እድሳት በመለዋወጫ እጥረት ምክንያት እንዲዘገይ ተደርጓል። ስኳር በአገር ውስጥ ከፍተኛ እጥረት እያለና ፋብሪካው ምርቱን ሳያቆም ለምን ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ እንዲያመርት አልተደረገም? ሲሉ ሰረተኞች ለአመራሩ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም አሳማኝ ምላሽ አላገኙም።

አቶ አባዱላ ገመዳ ቅሬታቸውን አቀረቡ

(ኢሳት ዲሲ --ታህሳስ 10/2010) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤነት በገዛ ፈቃዳቸው ለመልቀቅ ያመለከቱት አቶ አባዱላ ገመዳ በኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ ቅሬታቸውን ማቅረባቸው ተሰማ።
አቶ አባዱላ በእኔም ሆነ በድርጅቴ ኦሕዴድ ላይ የተፈጠረው ችግር በኢሕአዴግም ሆነ በመንግስት መዋቅሮች ውስጥ የሕወሃት የበላይነት በመኖሩ ነው ብለው እቅጩን ተናግረዋል።
በስብሰባው መጀመሪያ ላይ ቅሬታቸውን በይፋ ያቀረቡት አቶ አባዱላ ገመዳ ከተወሰኑ የኦሕዴድ አባላት ድጋፍ ቢያገኙም የተወሰኑት ግን እንደተቃወሟቸው ተገልጿል።
የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ በንትርክና በውዝግብ እየተካሄደ ቢሆንም በዝግ የተጠራ በመሆኑ መረጃዎችን ለማግኘት አስቸጋሪ አድርጎታል።
ነገር ግን ከተሰብሳቢዎቹ ሾልከው የሚወጡ መረጃዎች ውይይቱ በውጥረት እየተካሄደ መሆኑን ያመለክታሉ።
ለስብሰባው ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንዳረጋገጡት በኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ የቀረቡት ሰነዶች 5 ናቸው።
አንዱ በጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም የቀረበ ሲሆን 4ቱ ደግሞ በኦሕዴድ፣በብአዴን፣በሕወሃትና በደኢሕዴን ቀርበዋል።
ሁሉም ሰነዶች ደግሞ በኢትዮጵያ ያለውን አሳሳቢ፣ወቅታዊ ችግርና የሕዝቡ ተቃውሞ አለመብረዱን የተመለከቱ ናቸው።
ከ5ቱ ሰንዶች በተጨማሪ የግል ቅሬታቸውን ያቀረቡት ደግሞ አቶ አባዱላ ገመዳ መሆናቸውን ምንጮች አመልክተዋል።

Thursday, December 14, 2017

ዚምባቡዌ የቀድሞ የኢትዮጵያን ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሐይለማርያምን አሳልፋ እንደማትሰጥ አስታወቀች።

የዚምባቡዌ መንግስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ባለፈው ወር ሮበርት ሙጋቤ ከስልጣን ከተነሱ በኋላ ሀገሪቱ መንግስቱ ሃይለማርያምን ወደ ሀገራቸው እንድትሰድ በመጎትጎት ላይ ናቸው። የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሃይለማርያም አጋርና ወዳጅ የሆኑት ሮበርት ሙጋቤ አሁን በስልጣን ላይ ባይሆኑም ዚምባቡዌ ኮለኔል መንግስቱን አሳልፋ እንደማትሰጥ አንድ የሀገሪቱ ባለስልጣን ማረጋገጫ ሰጥተዋል። የዚምባቡዌ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሙጋቤ ተገደው ከስልጣን መልቀቃቸውን ካሳወቁበት ጊዜ ጀምሮ መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ኢትዮጵያ ተላልፈው እንዲሰጡ በመወትወት ላይ ናቸው። የአዲሱ የዚምባቡዌ ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ናንጋግዋ ቃል አቀባይ ጆርጅ ቻራምባ የተቃዋሚዎቹን ጥያቄ አጣጥለውታል። አያይዘውም ተቃዋሚዎቹ በማያውቁት ጉዳይ ላይ ገብተው የሚፈተፍቱ ናቸው ብለዋል። ቻራምባ ሲቀጥሉም የኮለኔል መንግስቱ ጉዳይ የሀገር

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ “በጨለንቆ የተፈጸመውን ዘግናኝ ፍጅት በዝምታ ማየቱ እውቅናውን እንደሰጠ ይቆጠራል” ሲል የኦሮምያ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ

የክልሉ የኮሚኒኬሽን ቢሮ በፌስ ቡክ ገጽ ላይ በኦሮምኛ ባወጣው ጽሁፍ የመከላከያ ሰራዊቱ በህግ የተሰጠውን መብት ጥሶ በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው ሲል ይከሳል። በአገሪቱ ህገመንግስት መሰረት የመከላከያ ሰራዊቱ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሆኖ እያለ እንደዚህ አይነት ወንጀሎች ሲፈፀሙ ከእውቅናው ውጭ ከሆነ መርምሮ የማስተካከያ እርምጃ መውሰድ ሲገባው፣ ይህንን በማድረግ ፋንታ ተመሳሳይ ወንጀሎች ሲፈጸሙ እያየ ዝምታን መምረጡ እየተፈጸመ ላለው ወንጀል እውቅና መስጠቱን ያሳያል ሲል አቶ ሃይለማርያም ተጠያቂ አድርጓል። 
የአገር መከላከያ ሰራዊት በማንኛውም ጊዜ ለህገመንግስቱ ታዛዥ በመሆን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ውግንና ሳያሳይ ነፃ ሆኖ የአገር ደህንነት የመጠበቅ ስራውን እንደሚሰራ ቢደነግግም፣ ሰራዊቱ ከተቋቋመለት አላማ ውጭ ታሪካዊ ስህተቶችን በህዝቦች ላይ እየፈጸመ ይገኛል ብሎአል።
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን በሜታ ወረዳ በጨለንቆ ከተማ በኦሮሞ ህዝብ ላይ ለተፈጸመው ዘግናኝ የጅምላ ፍጂት የመከላከያ ሰራዊቱን እና ዋናውን አዛዥ ጠ/ሚንስትር ሃይለማርያም ደሳለኝን ተጠያቂ ያደረገው ጽሁፉ፣ ከዚህ ጅምላ ፍጂት በስተጀርባ ማነው ያለው ለሚለው ጥያቄ ለህዝቡ መልስ መስጠት ግዴታ ነው ሲል ያክላል። 

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ትምህራታቸውን እያቋረጡ ወደ ቤተሰቦቻቸው እየሄዱ ነው

በአክሱም ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ተማሪዎች ላለፉት 3 ቀናት ሲያደርጉት የነበረውን ተቃውሞ ተከትሎ በከፍተኛ አለመረጋጋት ውስት በመሆናቸው ከተማውን ለቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመሄድ ሙከራ ቢያደርጉም አልተሳካላቸውም። በርካታ ተማሪዎች አስቀድመው መውጣት የቻሉ ቢሆንም፣ በጊዜ ከግቢ ያልወጡ ተማሪዎች፣ ወደ አካባቢያቸው እንዳይሄዱ ታግደዋል። ሁኔታው እጅግ አስፈሪ እንደሆነባቸውና በማንኛውም ጊዜ ጥቃት ሊፈጸምባቸው እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በግቢው የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከብሄራቸው ጋር በተያያዘ መፋጠጣቸውም ታውቋል። የአማራና የኦሮሞ ብሄር ወታደሮች በተማሪዎች ላይ ጥቃት እንዳይፈጸም አጥብቀው በመከላከላቸው ከህወሃት ወታደሮች ጋር ውዝግብ ውስጥ እንደገቡ ታውቋል። በተማሪዎች ላይ የሚፈጸመውን ማንኛውንም ጥቃት በዝምታ እንደማይመለከቱት ማስጠንቀቃቸውን ምንጮች ገልጸዋል። 

የጥበቃ ሰራተኞች እየተማረሩ ነው

በአገሪቱ የሚታየውን ውጥረት ተከትሎ በተለያዩ ተቋማት በጥበቃ ላይ የተሰማሩ የመከላከያ አባላት፣ ፖሊሶችና የጥበቃ ሰራተኞች ያለ እረፍት ጥበቃ እንዲያካሂዱ መታዘዛቸውን ተከትሎ ተቃውሞው ማሰማት ጀምረዋል።
የጥበቃ ሰራተኞች “ ደፍርሶ በጠራ” የሚል አስተያየቶች እየሰጡ ሲሆን፣ ትእዛዝ ለመቀበል አሻፈረን እያሉ ነው። በተለይ የመከላከያ አባላት ጥያቄዎችን እያነሱ መገኘታቸው ለወታደራዊ አዛዦች ራስ ምታት እየሆነ መምጣቱን ምንጮች ገልጸዋል።
በተለይ የአማራና የኦሮሞ ብሄር የመከላከያ ሰራዊት አባላት አጋዚ የተባለው ጦር በህዝብ ላይ የሚፈጽመውን ጥቃት እየተቃወሙ በመምጣታቸው በስምሪት ስም ተቃውሞ ሊያስተባብሩ ይችላሉ የተባሉት ወታደሮች እየተለ ወደተለያዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ ጥበቃ እየተደረገባቸው ነው።

በሽብር ስም የተከሰሱ ሰባት እስረኞች በነፃ ሲሰናበቱ ዘጠኙ እንዲከላከሉ ተባሉ

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 5 ቀን 2010 ዓ.ም በዋለው ችሎት በእነ ተሾመ ረጋሳ የክስ መዝገብ ስር በሽብር ስም ተከሰው የነበሩ 7 ግለሰቦችን በነፃ ተሰናበቱ። 9 ተከሳሾች ደግሞ በተከሰሱበት ክስ ከባድ ቅጣት በሚያስቀጣ አንቀፅ ስር እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል።
1ኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ተሾመ ረጋሳ ላይ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ የተቀሰቀሰውን አመፅ በአማራና በትግራይ ክልሎች በተለይም ጎንደር፣ መተማ፣ ሁመራ፣ ደሴ፣ መቀሌ፣ አክሱምና ሌሎች ከተሞች ለማስፋፋት አቅዶ እየሰራ ነበር ሲል ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቷል።
በተጨማሪም በአቶ ተሾመ ረጋሳና አብረውት በተከሰሱት ተከሳሾች ላይ የኢትዮጵያ መንግስት በኦሮሞ ህዝብ ላይ በደል ፈፅሟል፣ ኦህዴድ አይወክለንም፣ መሬት እየተሸጠ ነው።ወጣቶች የኦህዴድን ሰንደቅ አላማ አውርደው የኦፌኮን ሰንደቅ አላማ ለማስቀል ጥት አድርገዋል፣ ኦነግ ስልጣን እንዲረከብ ይፈልጋሉ የሚሉ ክሶች ቀርቦባቸዋል።
ነገርግን ዐቃቤ ሕግ በ5ኛ፣ 6ኛ፣ 7ኛ፣ 9ኛ፣11ኛ ፣13ኛ እና 15ኛ ተከሳሾች ላይ ያቀረበው ክስ አስመልክቶ ችሎቱ የሰውም ሆነ አሳማኝ የሰነድ ማስረጃ አላቀረበም ተብሏል። በመሆኑም 5ኛ ተከሳሽ ከበደ ጨመዳ፣ 6ኛ ተከሳሽ ዴቢሳ በየነ፣ 7ኛ ተከሳሽ ምህረቱ ጉልማ፣ 9ኛ ተከሳሽ መንግስቱ ጉዲሳ፣ 11ኛ ተከሳሽ ቦንሳ ኃይሉ፣ 13ኛ ተከሳሽ ጃራ ኤቢሳ እና 15ኛ ተከሳሽ አጥናፉ ቢረሳ የቀረበባቸውን ክስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ሲል ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል።

ህዝባዊው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 5/2010)
በሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ህዝባዊ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ።
በአይከል ከተማ ህዝቡ አደባባይ በመውጣት የህወሃትን አገዛዝ ማውገዙ ታውቋል።
በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው በመውጣት ላይ ናቸው። ህወሀት ከስልጣን እንዲወርድ ተማሪዎቹ ጠይቀዋል።
በጎንደር ዩኒቨርስቲ ዛሬም ትምህርት አልተጀመረም። አንድ የመንግስት ተሸከርካሪ ዩኒቨርስቲው ደጃፍ ላይ ወድሟል።
በወልዲያ ከ70በመቶ በላይ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው ወተዋል። በኡርጌሳ ወሎ ህዝቡ ከአጋዚ ሰራዊት ጋር እንደተፋጠጠ መሆኑ ታውቋል። የሰላም ባስ አውቶብስ ጥቃት እየደረሰበት ነው።

አምቦ ዉስጥ መከላከያና ፖሊስ ተጋጩ (ፃዲቅ አህመድ)

«አጋዚዎች ሞተዋል» ሲሉ የአምቦ ምንጮች ለቢቢኤን ገልጸዋል።
 
የኦሮሚያና የአማራ ክልልሉ ተቃዉሞ አዲስ አበባ ቀርቧል። ሰበታ፣አለም ገና እና ፉሪ ተቃዉሞን ተቀላቅለዋል።«ተቃዉሞው አራት ኪሎ የቀረበ ይመስላል!» ይላሉ ሁናቴውን የቃኙ የቢቢኤን ምንጮች።
በአምቦ ከተማ ዉስጥ በመከላከያ ሰራዊትና በፖሊስ መካከል ግጭት ተነስቶ ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንደነበር የአምቦ ነዋሪዎች ለቢቢኤን ገለጹ።የመከላከያ ሰራዊቶቹ በዩንቨርስቲ ተማሪዎች ላይ በሚያደርሱት ትንኮሳና ጥቃት ሳቢያ ግጭቱ መነሳቱ ታዉቋል።የመከላከያ ሰራዊት በከተማዉ ጉዳዮች ዉስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም ፖሊስ ቢያሳስብም የመከላከያ ሰራዊቱ መቀበል ባለመቻሉ ጎራ ለይተው መታኮስ እንደጀመሩ ተገልጿል።

Wednesday, December 13, 2017

የህግ የበላይነት ማስከበር ያለበት ሃይል የኦሮሞ ህዝብን መግደሉ ተቀባይነት እንደሌለውና ለህግ እንደሚቀርብ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ገለጹ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) የህግ የበላይነት ማስከበር ያለበት ሃይል የኦሮሞ ህዝብን መግደሉ ተቀባይነት እንደሌለውና ለህግ እንደሚቀርብ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ገለጹ። ጉዳቱን ያደረሰው ሃይል ማን እንደጠራውና በማን ትዕዛዝ ቦታው ላይ እንደተገኘ አላወቅንም ብለዋል። ሰሞኑን በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማ በሕወሃት የጦር አዛዦች የሚመራው ወታደራዊ ሃይል 18 ሰዎችን መግደሉንና በርካቶችን ማቁሰሉ ተዘግቧል። ይህንን ግድያ ተከትሎ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ለማ መገርሳ በሰጡት መግለጫ በሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማ 15 ሰዎች ተገድለዋል ሲሉ ተናግረዋል። ቁጥራቸው

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተነሳውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ የህወሃት አገዛዝ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን መዝጋቱ ታወቀ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተነሳውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ የህወሃት አገዛዝ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን መዝጋቱ ታወቀ። ፌስቡክና ትዊተርን የመሳሰሉት ማህበራዊ ድረ ገጾች ዝግ መሆናቸው ታውቋል። ወትሮም ደካማ የነበረው የኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት አሁን ላይ ጭራሹኑ የፌስ ቡክና ትዊተር ድረገጾች

Tuesday, December 12, 2017

የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ የቀድሞ አመራሮቹን እያሳተፈ ነው ተባለ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 3/2010)
በኢትዮጵያ የተከሰተው ቀውስ ተባብሶ በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት ስብሰባ የተቀመጠው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ የቀድሞ አመራሮቹን ማሳተፉ ታወቀ።
በቅርቡ በሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ላይ የተጀመረውና በኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ላይም የቀጠለው የቀድሞ አመራሮችን የማሳተፍ ርምጃ በመተካካት ስም ከሂደቱ የወጡትን ይበልጥ ተዋናይ እያደረጋቸው መምጣቱም ተመልክቷል።
በስብሰባው ማጠቃለያ የካቢኔ ብወዛ እንደሚኖርም ይጠበቃል።

Ethiopia: Killing of university students reignite nationwide protests

ESAT News (December 12, 2017)
The death of university students in ethnic clashes and at the hands of regime security forces have sparked nationwide protest against the TPLF regime.
Protests were held in several universities and towns across the country.

Friday, December 8, 2017

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ገለልተኛ ባለመሆኑ የመብት ጥሰቶች በሌላ ገለልተኛ አካል እንዲጣራልን ሲሉ እስረኞች ጠየቁ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ገለልተኛ ባለመሆኑ የመብት ጥሰቶች በሌላ ገለልተኛ አካል እንዲጣራልን ሲሉ እስረኞች ጠየቁ
በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ ክስ መዝገብ የተከሰሱ 38 እስረኞች በሸዋ ሮቢት እስር ቤት ውስጥ እያሉ በምርመራ ስም ኢሰብዓዊ ድርጊቶች እንደተፈጸሙባቸው አቤቱታ ማቅረባቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን እንዲያጣራ ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወሳል።
ኮሚሽኑ በበኩሉ አጣርቼዋለሁ ያለውን የምርመራ ውጤት ለፍርድ ቤትና ለተከሳሾች እንዲደርስ አድርጓል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሾቹ በሪፖርቱ ላይ አስተያየት ካላቸው እንዲያቀርቡ ከመደበኛው ቀጠሮ ውጭ ለህዳር 29 ቀን 2010 ዓ.ም እንዲቀርቡ ጠርቷቸው ነበር።
የተከሳሾቹ ጠበቆች በበኩላቸው ቀጠሮው በምርመራ ሪፖርቱ ላይ አስተያየት ለመስጠት እንደሆነ ባለመገለፁ አስተያየታቸውን በጽሁፍ ይዘው አለማቅረባቸውን አሳውቀው አስተያየታቸውን ከመደበኛ ቀጠሮ በፊት በጽሁፍ እንደሚያስገቡ ተናግረዋል።
ያለጠበቃ በግላቸው የሚሟገቱት 18ኛ ተከሳሽ አቶ አንጋው ተገኘና 3ኛ ተከሳሽ አሸናፊ አካሉ በአካል ቀርበው በቃል አስተያየታቸውን ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል።

የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሰራዊት የአርዱፍን ይዞታ ሰብሮ ለመግባት ያደረገው ሙከራ መክሸፉንና ተመቶ መመለሱን የአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር አርዱፍ አስታወቀ

የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሰራዊት የአርዱፍን ይዞታ ሰብሮ ለመግባት ያደረገው ሙከራ መክሸፉንና ተመቶ መመለሱን የአፋር አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር አርዱፍ አስታወቀ። መብታችን እስኪከበር በሕወሃትና በመልዕክተኛው የአፋር ልዩ ፖሊስ ሃይል ላይ የጀመርነው ውጊያ ይቀጥላል ሲልም አስታውቋል። የውጭ ሀገር ዜጎችና ጎብኚዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አርዱፍ አስጠንቅቋል። የብሔር ብሄረሰቦች በአል ሰላማዊ ሆኖ እንዲከበር በሚል በአርዱፍ ላይ የተከፈተው ዘመቻ ከአርዱፍ ተዋጊዎች አልፎ በሰላማዊ ዜጎች ላይም የተነጣጠረ እንደሆነ ግንባሩ አስታውቋል። በዚህም ሰላማዊ የአፋር ተወላጆች ሰቆቅና እስራት እየተፈጸመባቸው እንደሆነም በመግለጫው ተመልክቷል። ከነሀሴ ወዲህ 580 ሰዎች በሕገ ወጥ መንገድ ተይዘው በተለያዩ ስፍራዎች መታሰራቸውንም አርዱፍ አስታውቋል። የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሰራዊት ከአፋር ክልል ልዩ ሃይል ፖሊስ ጋር በመሆን፣በህዳር ወር ሶስተኛ ሳምንት በሞጎሮስ ተራራማ ስፍራ ላይ የተጀመረው ውጊያ እንደ አውሮፓውያኑ እስከ ታህሳስ 3/2017 መቀጠሉን በመግለጫው ዘርዝሯል። የሕወሃት ሰራዊት የአርዱፍን ይዞታ ሰብሮ ለመግባት ያደረገ ሙከራ ባለፈው እሁድ ሙሉ በሙሉ መክሸፉንና ተመተው መመለሳቸውን ይፋ አድርጓል። በዚህም 17 ወታደሮች ሲገደሉ በደርዘኖች የሚቆጠሩ ቆስለዋል ሲል

የህወሃት አገዛዝ ትዕግስተኛውንና በፈሪሃ እግዚአብሔር በተመሠረተ ጨዋነት ላይ የሚኖረውን ሕዝባችንን ወዳልተፈለገ ብጥብጥ እንዲያመራ እየገፋፋው ነው ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አስታወቀ።

የህወሃት አገዛዝ ትዕግስተኛውንና በፈሪሃ እግዚአብሔር በተመሠረተ ጨዋነት ላይ የሚኖረውን ሕዝባችንን ወዳልተፈለገ ብጥብጥ እንዲያመራ እየገፋፋው ነው ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አስታወቀ። “ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም ፥ ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም ”በሚል ርዕስ መግለጫ ያወጣው ቅዱስ ሲኖዶስ በሃያ አንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን እጅግ ኋላ ቀር በሆነ ፖለቲካ አገርን ለመምራት መሞክር በዘመኑ ያለመኖርን ያህል ይቆጠራል በዓለም መድረክ ፊትም ያጋልጣል ብሏል ። ቅዱስ ሲኖዶሱ እግዚእብሔርን አጋዥ በማድረግ እርስ በርሳችሁ እየተረዳዳችሁ፥ በጸሎትና በምህላ ይህን ክፉ ቀን አሳልፉ ሲል በእግዚአብሔር ስም ጥሪውን አስተላልፏል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ “ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም ፥ ኃያልም በኃይሉ ብዛት አያመልጥም”በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫው ኢትዮጵያውያን በፖለቲካ ስም የዕለት ጥቅም ለማግኘት የሚጥሩ ፖለቲከኞች እንዳያታልሏችሁ ሲል አደራውን አስቀምጧል። የሲኖዶሱ መግለጫ ሲቀጥልም የህወሃት አገዛዝ ወደ ስልጣን ሲመጣ አስፈሪውን ደርግ አባሮ ነበር። ነገር ግን አሁን ላይ እየፈጸመው ያለው ተግባር ግን ከደርግ እጅጉን ይከፋ ሆኗል ብሏል። ሲኖዶሱ እንደሚለው ዜጎቻችን በእንግልትና በስደት ላይ ሆነው ለሽያጭ ሲቀርቡ ማየት፣የመቶ አመት አሮጊት በራሳቸው ዜጎች በግፍ ተደብድበው እንዲገደሉ ሲደረግና የዕለት ተዕለት የህዝብን ሰቆቃ መስማት ልብን የሚያደማ ድርጊት ነው ብሏል ሲኖዶሱ። እግዚአብሔር

በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ውስጥ አንዱን ብሔር ማግለልና ሌላውን ማወደስ እንደሚታይ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ

በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ውስጥ አንዱን ብሔር ማግለልና ሌላውን ማወደስ እንደሚታይ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ። የቀድሞ ተማሪዎች የሚሰባሰቡት በፖለቲካና በርዕዮተ አለም አመለከታተቸው ነበር ብለዋል። በአፋር ክልል የሕወሃት አገዛዝ ኣያከበረ ያለውን “የብሔረሰቦች ቀን” በማስመልከት ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በዩኒቨርስቲዎች አካባቢ እየተየ ያለውን ተቃውሞና አመጽ በተመለከተ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። አቶ ሃይለማርያም በዩኒቨርስቲዎች አካባቢ ብሄር ተኮር በሆነ መልኩ አንዱን ብሔር የማግለልና ሌላውን ማወደስ ይታያል ሲሉ በግልጽ ተናግረዋል። ይሄ ኋላቀር የሆነ አመለካከት በመሆኑ መቀረፍ ይኖርበታል ሲሉ አሳስበዋል። የድሮ ተማሪዎች በአንድ ልብ የሚሰባሰቡት በፖለቲካ አመለካከትና ርዕዩተ አለም ነው ብለዋል። በአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት የቀድሞ የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ መምህር አቶ እንዳልካቸው ሃይለሚካኤል መንግስት በፖሊሲ ደረጃ የብሔር አደረጃጀት በዩኒቨርቲ ውስጥ እንዲተገበር ካደረገ በኋላ ተማሪዎችን ተጠያቂ ማድረጉ ስህተት ነው ብለዋል። በአርባምንጭም ሆነ በሌሎች ዩኒቨርስቲዎች የትግራይ ተወላጆችን በሕወሃት፣የኦሮሞ ተወላጆችን በኦህዴድ፣የአማራ ተወላጆችን በብአዴን የሚያደራጅ መዋቅር ተዘርግቶ የሚሰራበት ሁኔታ አለ። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ተማሪዎች በፖለቲካ አመለካከታቸውና ርዕዮተአለም የሚሰባሰቡበት እድል የለም ብለዋል ። አቶ እንዳልካቸው ሀሳባቸውን ሲያጠቃልሉ ይህ የአቶ ሃይለማርያም ንግግር ሕወሃት/ኢህአዴግ የሚመራበት የብሄር ፖለቲካ መክሸፉን አመላካች ነው ብለዋል።

Diaspora groups to hold Libya Anti Slavery March as Congressional Black Caucus met Libyan Amb. by Engidu Woldie

ESAT News (December 8, 2017)
A demonstration will be held on Tuesday in Washington, DC in protest against slave auction in Libya.
African Diaspora groups in the DMV area in collaboration with African Lives Matter-London have organized the rally which begins at 9:00 AM Tuesday at the Libyan Embassy in Washington, DC and head to the State Department.
The libyan slave auction first surfaced in a CNN International video early in November drawing condemnation against the long abandoned and inhumane practice.

በኢትዮጵያ በውጭ ምንዛሪ እጥረት ሕሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ባለማግኘታቸው ችግር ላይ እየወደቁ መሆኑን ቢቢሲ ዘገበ

በኢትዮጵያ በውጭ ምንዛሪ እጥረት ሕሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ባለማግኘታቸው ችግር ላይ እየወደቁ መሆኑን ቢቢሲ ዘገበ። መድሃኒት አስመጪዎች የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ባለመቻላቸው በተለይ የልብና የስኳር ህሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ለማግኘት ተቸግረዋል። ቢቢሲ በአዲስ አበባ ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ህሙማን የሚፈልጉትን መድሃኒት ማግኘት ባለመቻላቸው ችግር ላይ እየወደቁ መሆኑን ጠቁመዋል። በተለይም የስኳርና የልብ ህሙማን እለት እለት መድሃኒት የሚፈልጉ ቢሆንም በየመድሃኒት ቤቶቹ ዞረው ማግኘት አልቻሉም። ለቢቢሲ አስተያየቱን የሰጠው ግሩም ፈለቀ የተባለ የስኳር ህመምተኛ ካለፉት 3 ወራት ወዲህ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች የኢንሱሊን እጥረት እንዳጋጠመው ነው የገለጸው። መድሃኒቱ ቢገኝ እንኳ በውድ ዋጋ የሚሸጥበት ሁኔታ ተፈጥሯልም ሲል ምሬቱን ይገልጻል። በተለይም በግል መድሃኒት ቤቶች የስኳር ሕመም መድሃኒት ማግኘት አዳጋች እየሆነ መምጣቱን ተጠቃሚዎች ገልጸዋል። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የአንድ ግዙፍ የመድሃኒት አስመጪ ኩባንያ

Thursday, December 7, 2017

የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቶ አባይ ወልዱን ከትግራይ ክልል ፕሬዝዳንትነት ለማንሳት የሚደረገው ሙከራ ተቃውሞ እንደገጠመው ምንጮች ገለጹ

የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቶ አባይ ወልዱን ከትግራይ ክልል ፕሬዝዳንትነት ለማንሳት የሚደረገው ሙከራ ተቃውሞ እንደገጠመው ምንጮች ገለጹ። ለተቃውሞ ምክንያት የሆነውም የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከልጣናቸው ሳይወርዱ አቶ አባይ ወልዱ መነሳት የለባቸውም በሚል እንደሆነም ታውቋል። በዚህ ሳቢያ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን በቅድሚያ ለማውረድ በሕወሃት ጣልቃ ገብነት እንቅስቃሴ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ ጋር በተያያዘም ብአዴን አስቸኳይ ስብሰባ የጠራ ሲሆን ብአዴኖች የህወሃትን ጣልቃ ገብነት ለማስወገድና የአቶ ገዱን ስልጣን ለማስቀጠል የኦህዴድን ድጋፍ መጠየቃቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የጎንደር ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ከተካሄደበት ከሃምሌ 2008 ጀምሮ በሕወሃት ደጋፊዎች ዘንድ ከፍተኛ ትችት እንዲሁም ዘለፋ ጭምር እየተሰነዘረባቸው የቀጠለው አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ከልጣን ለማንሳት ከዘጠኝ ወራት በፊት የተደረገው ሙከራ ሕዝባዊ ተቃውሞን በመስጋት መታፈኑን የኢሳት ምንጮች ይገልጻሉ። በአሁኑ ወቅት አቶ አባይ ወልዱን ለማንሳት አቶ ገዱን በቅድሚያ ከስልጣን ማውረድ ጥቂት በማይባሉ የሕወሃት ደጋፊዎች ቅድመ ሁኔታ ሆኖ መቅረቡም ተሰምቷል። በአቶ ስብሃት የሚመራው ቡድንም ብአዴን ውስጥ ከሚገኙ የህወሃት ደጋፊዎች ከእነ አቶ አለምነህ መኮንን ጋር የቅንጅት ስራ መጀመሩም ተመልክቷል። የሕወሃት ደጋፊዎችን ጥያቄ ለመመለስ በሚል በአቶ ገዱ ላይ ርምጃ ለመውሰድ የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመግታት በዞንና በወረዳ የሚገኙ የብአዴን አመራሮችና አባላት እንዲሁም የኦህዴድ አመራሮች እንዲንቀሳቀሱ በብአዴን አባላት ዘንድ ጥሪ በመተላለፍ ላይ መሆኑንም መረዳት ተችሏል። በአቶ ስብሃት ነጋ የሚመራው የሕወሃት ቡድን አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን የማውረድ እንቅስቃሴ ከተሳካለት በኦሮሚያ ክልል በእነ አቶ ለማ መገርሳ ላይ ተመሳሳይ ርምጃ ከመውሰድ እንደማይመለስ ምንጮቹ ይገልጻሉ። ሁለቱ ድርጅቶች ማለትም ኦህዴድና ብአዴን፣ ደኢህዴንን ጨምሮ በየተራ ከመመታት ተባብረው የህወሃት ግፊትን መግታት እንደሚገባቸው የፖለቲካ ምሁራን አስተያየታቸውን በመስጠት ላይ ናቸው።

ሰነድ የሌላቸውን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከአውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ በፈቃደኝነትም ሆነ በማስገደድ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የአውሮፓ ሕብረትና የኢትዮጵያ አገዛዝ መስማማታቸውን አፈትልኮ የወጣ አንድ ሰነድ አመለከተ።

Image may contain: 3 people, crowdሰነድ የሌላቸውን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከአውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ በፈቃደኝነትም ሆነ በማስገደድ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የአውሮፓ ሕብረትና የኢትዮጵያ አገዛዝ መስማማታቸውን አፈትልኮ የወጣ አንድ ሰነድ አመለከተ። በስምምነቱ መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ስደተኞችን ከአውሮፓ ወደ ሀገራቸው በግዳጅ ለመመለስ ሙሉ ትብብር ያደርጋል። ስደተኞቹ ዜግነታቸውን የሚያረጋግጥ ፓስፖርት ባይዙ እንኳን የደህንነት መስሪያ ቤቱ ማንነታቸውን ካረጋገጠ በኋላ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል የጉዞ ሰነድ

የዋልድባው መነኩሴ አባ ገብረኢየሱስ ዛሬ ለሊቱን በእስር ቤት ሲደበደቡ አድረው ወደ ጭለማ ቤት መወርወራቸው ተሰማ።

Image may contain: 1 person, outdoorበሽብር ወንጀል ተከሶ ያለምንም ብይን በጭለማ ቤት ታስሮ የሚገኘው አስቻለው ደሴ አባ ገብረየሱስ ስብርብር እንዲሉ ተደርገው ከተደበደቡ በኋላ በሱ ጭለማ ክፍል መጣላቸውን መስክሯል። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣኑን አቷል ሲል ብይን መስጠቱም ተሰምቷል። በእነ አስቻለው የክስ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ አስቻለው ደሴ በሕዳር 14/2010 በዋለው ችሎት ፊት ቀርቦ ልብሱን በአደባባይ በማውለቅ በእስር ቤት እንዳኮላሹትና ከባድ ስቃይ እየደረሰበ መሆኑን የፍትህ ያለ ሲል በአደባባይ መናገሩ ይታወሳል። አሁን ላይ ህይወቴ አስጊ ሁኔታ ላይ ወድቋ ሲል የተናገረው አስቻለው የኔ አላግባብ መሰቃየ ሲገርመኝ ዛሬ ለሊት ደግሞ የዋልድባውን መነኩሴ አባ ገብረኢየሱስን ስብርብር አድርገው ደብድበው እኔ ያለሁበት ጭለማ ክፍል ወረወሯቸው ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል። መነኮሳቱ የምንኩስና ልብሳችሁን አውልቁ በሚል ድብደባው እንደጸናባቸውም ተናግሯል። መነኮሳቱ የእምነታቸው መገለጫ የሆነውን የምንኩስና ልብስ አውልቁ መባላቸው ደግሞ በርካታ የእምነቱ ተከታዮችን እያስቆጣ መሆኑ ተሰምቷል። መነኮሳቱን እየደበደቡ ያሉት የዞን 5 ሃ

የሕወሃት አገዛዝ የፕሪሚየር ሊግ ውድድሩ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቆም ሊያደርግ መሆኑን የኢሳት ምንጮች ገለጹ

ውድድሩ እንዲቆም የተፈለገው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በትግራይና በአማራ ክልል እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች መካከል የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለም በወሎ ወልዲያ ግጭት በተካሄደ ማግስት የደሴ ከተማ ነዋሪዎች የነቀምት ከነማ ክለብ ተጫዋቾችና ደጋፊዎችን በደመቀ ስነስርአት ተቀብለዋቸዋል። በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ውድድር በክለቦች መካከል ባሉ ደጋፊዎች ሁለት የስሜት ገጽታዎች እየታዩ ነው የሚገኙት። አንዱ የፍቅር መገለጫ ነው፣ሌላው ደግሞ ጥላቻ ናቸው። በስፖርት ማዘውተሪያ ስታዲየሞች በአማራና ትግራይ ክለብ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች ብሔርን መሰረት ያደርገ ግጭት እንዲቀሰቀስ ምክንያት የሆነው የባህርዳር ከነማ ከመቀሌ

Wednesday, December 6, 2017

በሰሜን ጎንደር አንድ ነዳጅ የጫነ ቦቴ ተቃጠለ። በጭልጋ ወረዳ ነጋዴ ባህር አካባቢ ኳቤር ሎምዬ ቀበሌ ነዳጅ የጫነ ቦቴ መኪና ዛሬ ጠዋት የተቃጠለ ሲሆን፣ አርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ለጥቃቱ ሃልፊነቱን ወስዷል።

በሰሜን ጎንደር አንድ ነዳጅ የጫነ ቦቴ ተቃጠለ። በጭልጋ ወረዳ ነጋዴ ባህር አካባቢ ኳቤር ሎምዬ ቀበሌ ነዳጅ የጫነ ቦቴ መኪና ዛሬ ጠዋት የተቃጠለ ሲሆን፣ አርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ለጥቃቱ ሃልፊነቱን ወስዷል። ነዳጁ ለአጋዚ ጦር የታሰበ በመሆኑ ርምጃውን መውሰዱን ንቅናቄው አስታውቋል። የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ነዳጅ የጫነ ቦቴ መቃጠሉን አረጋግጠው ቦቴው የጋየው ከዘራፊዎች ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ሊነጋ 11 ሰዓት ገደማ ነው። ነዳጅ የጫነ ተሳቢ ተሽከርካሪ ከሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጦ ኳቤር ሎምዬ ቀበሌ ደርሷል። ይህ ቀበሌ የሚገኘው በሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ነጋዴ ባህር አካባቢ ነው። አርበኞች ግንቦት ሰባት እንዳስታወቀው የንቅናቄው ታጣቂዎች ለአጋዚ ጦር ነዳጅ በማጓጓዝ ላይ በነበረው ቦቲ ተሳቢ ተሽከርካሪ ላይ ጥቃት በመሰንዘር ሙሉ በሙሉ

በፖለቲካ ምክንያት ታስረው በወህኒ ቤት የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ ማሰቃየት እየተፈጸመባቸው መሆኑ ተገለጸ።

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 26/2010) በፖለቲካ ምክንያት ታስረው በወህኒ ቤት የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ ማሰቃየት እየተፈጸመባቸው መሆኑ ተገለጸ። ከጊዜያዊ ህመም እስከ ዘላቂ የአካል ጉዳት የደረሰ ቅጣት እንደሚፈጸምባቸውም እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ እስር ቤቶች የሚፈጸሙና አሰቃቂ የሚባሉት ድርጊቶች ችሎት ፊት ሲቀርቡ ምናልባትም የህግ ባለሙያዎች መቀለጃ ወይንም የበለጠ ቅጣትን ማክበጃ ተደርገው ይወሰዳሉ። እንዲህ አይነቱ የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚፈጸመው ደግሞ ምንም አይነት ወንጀል በሌለባቸው፣ወንጀል ሰርተው እንኳን ቢሆን ህጉ እንደ ህግ ብይን ሳይሰጣቸው በእስር ቤት እንዲሰቃዩ በተደረጉ ዜጎች ላይ ነው።ለእስረኞቹ የተለያየ ስም ይሰጣቸዋል።የማሰቃያ መንገድም ይቀመጥላቸዋል። በእነ ሚፍታህ ሸህ ሱሩር የክስ መዝገብ 74ኛ ተከሳሽ የሆነው ፈረደ ክንድሻቶ ይርጋም ከነዚህ አንዱ ነው። ፈረደ ዛሬ ላይ ከደረሰበት ጉዳት ጋር በተያያዘ ሱሪ እንኳን መልበስ አይችልም።በደረሰበት የከፋ ድብደባ ምክንያትም በትክክል መራመድ አይችልም። ዳንሻ ድረስ ተወስዶ ተደብድቧል፣ወደ ትግራይ ተግዞ በገመድ ግንድ ላይ ታስሮ ትልቅ ጉድጓድ ውስጥ ተጥሏል። በጉድጓድ ውስጥ እያለ ለፈረደ ምግብና ውሃን ያቀመሰው አልነበረም። በሁመራ እጁ የኋሊት ታስሮ ጸሃይ ላይ እንዲሰጣ ተደርጓል።በድብደባው ብልቱና ሆዱ ላይ ጉዳት የደረሰበት ፈረደ ወደ

የሕወሃት የስለላ ተቋማት አንድ በእስራኤል የሚገኝ ድርጅት የሚያቀርበውን የስለላ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክን፣አንድ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪንና የአንድ ጠበቃን ኮምፒዩተሮች ሲሰልል እንደነበር ሲትዝን ላብ የተባለው ተቋም አጋለጠ።

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 27/2010) የሕወሃት የስለላ ተቋማት አንድ በእስራኤል የሚገኝ ድርጅት የሚያቀርበውን የስለላ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክን፣አንድ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪንና የአንድ ጠበቃን ኮምፒዩተሮች ሲሰልል እንደነበር ሲትዝን ላብ የተባለው ተቋም አጋለጠ። በአሜሪካ በሚገኙ የኢትዮጵያውያን ነጻ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ላይ፣በግለሰቦችና ሌሎች ድርጅቶች ላይም የስለላ ተግባር መፈጸሙ ተጋልጧል። በሲትዝን ላብ የሚገኝ አንድ ግለሰብም የጥቃቱ ሰለባ መሆኑ ታውቋል። ሲትዝን ላብ እንደ ሕወሃት ያሉ አምባገነን መንግስታት በግለሰቦችና በተቋማት ላይ የሚያደርጉትን ስለላ እየተከታተለ የሚያጋልጥ ተቋም ነው። የሕወሃት መንግስት የኢንተርኔት የስለላ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በአሜሪካ በሚገኙ የኢትዮጵያውያን ነጻ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ላይ፣በግለሰቦችና ሌሎች ድርጅቶች ላይ የስለላ ተግባር መፈጸሙ ተጋልጧል። ሲትዝን ላብ የተሰኘውና እንደ ሕወሃት ያሉ አምባገነን መንግስታት በግለሰቦችና በተቋማት ላይ የሚያደርጉትን ስለላ እየተከታተለ የሚያጋልጥ ተቋም ዛሬ አገኘሁት ያለውን መረጃ ይፋ አድርጓል። እንደ ተቋሙ መረጃ የሕወሃት የስለላ ተቋማት አንድ በእስራኤል የሚገኝ ድርጅት የሚያቀርበውን የስለላ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክን፣አንድ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪን እንዲሁም አንድ ጠበቃን ኮምፒዩተሮች ሲሰልል እንደነበር ታውቋል። በሲትዝን ላብ የሚገኝ አንድ ግለሰብም የጥቃቱ ሰለባ መሆኑን አስታውቋል። ሲትዝን ላብ በምርመራ እንደደረሰበት ከሆነ የሕወሃት
የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ነባርና ታሪካዊ አካባቢዎችን ማፍረስ ጀመረ። ገዳም ሰፈርና ጌጃ ሰፈርን ጨምሮ አምስት ነባር ሰፈሮች ሙሉ ለሙሉ ይፈርሳሉ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2010 ከያዘው ከ40 ቢሊየን ብር አመታዊ በጀት ውስጥ 30 ቢሊየን ብሩን ከማዘጋጃ ቤትና ግብር ነክ ገቢዎችን ከሕብረተሰቡ በቀጥታ የሚሰበስበው መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ገቢ ውስጥ ከፍተኛ ድርሻውን የያዘው ነባር መሬቶችን በማስለቀቅ መሬቱን በመሸጥ የሚያገኘው እንደሆነ መረጃዎች ያመላክታሉ። የቀድሞ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከተማ ልማት ቢሮ አማካሪ ዶክተር ግዛቸው ቴሶ ለኢሳት እንደገለጹት አገዛዙ ነባርና ታሪካዊ አካባቢዎችን የሚያፈርሰው በዋናነት የነዋሪውን ማህበራዊ ትስስር ለመበጣጠስ በማሰብ ነው ብለዋል። የህብረተሰቡ ዲሞግራፊ በተቀየረ ቁጥር አዲስ አበባ የስርአቱ ተቃውሞ ማዕከል መሆኗ ሊቀንስ እንደሚችል አጋዛዙ እምነት እንዳለው ተናግረዋል።

ለኢሳት ቤተሰቦች/የቅርብ ደጋፊዎች የቀረበ ጥሪ!!!

ሁላችንም እንደምናውቀው፣ ኢሳት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነፃነትና ዲሞክራሲ የሚያደርገውን ትግል በማገዝ ረገድ ካለው ሚና አንፃር ያለው የፋይናንስ ምንጭ እና መጠን ውሱንነት አለው።
ይህንን በአግባቡ ስንመረምር፣ ኢሳት አስተማማኝ እና ተከታታይነት ያለው የፋይናንስ ምንጭ ኖሮት ወርሃዊ ወጪውን መሸፈን እንዲችል በአሁኑ ሰዓት በእጃችን ላይ የሚገኘው አስተማማኝ የፋይናንስ ምንጭ አማራጭ - ተቀባባይ/የማይቋረጥ (automated) ቋሚ የወርሃዊ ድጋፍ/ክፍያ ሆኖ እናገኘዋለን። ይህንን የኢሳትን ወርሃዊ ወጪ በአሁኑ ሰዓት የኢሳት ቤተሰቦች/የቅርብ ደጋፊዎች የሆኑ በሙሉ በሚያደርጉት ተቀባባይ/የማይቋረጥ (automated) ቋሚ ወርሃዊ ድጋፍ/ክፍያ ማሟላት ይቻላል የሚል ዕምነት አለን።

Tuesday, December 5, 2017

Ethiopia: German tourist killed in Afar

Tourists watching live volcano at Erta Ale PHOTOGRAPH BY TOM PFEIFFER / BARCROFT MEDIA LTD
A tourist killed on Sunday in Afar, Northern Ethiopia, is a German national, Germany’s foreign ministry confirmed today.
The German national, whose name is withheld, was among a group of tourists visiting Erta Ale volcanic site when they came under attack by unidentified gunmen. An Ethiopian tourist guide has sustained gunshot wounds, according to sources.
“The Foreign Office confirms one deceased German national during the attack at Erta Ale,” the statement from the Ministry said but did not provide additional details.