Sunday, May 31, 2015

ሥነ-ስርዓት! የአቤል ማስታወሻ ከቅሊንጦ

“they say that time heals all things,they say you can always forget;
but the smiles and the tears across the years
they twist my heart strings yet!”
― George Orwell, 1984

የመታሰሬ ምክንያት መናገሬ ነው ፡፡ መንግሰት በሬ ወለደ “ሽብር” የሚል ክስ ሳይመስርትብኝ በፊት ይጠይቀኝ የነበረው በማህበረሰብ ሚዲያ የምጽፍበትን የምናገርበት አላማ ነበር፡፡ አላማዬ ተፈጥሮአዊ የመናገር መብቴን ማከናወን አንደሆነ ስናገር ከዚህ ተጨማሪ ሌላ ምክንያት ያለኝ ይመስል የተረፈኝ ድብደባ ነበር ፡፡ በዚህ ሂደት ወትሮም ገመምተኛ የነበረውን ግራ ጆሮዬን አጥቻለሁ፡፡ የሚቆጨኝ ነገር የለም፡፡ የሚያስቆጭ ነገር ካለም መቆጨት ያለብኝ የመናገር ነጻነት ያለውና ያን ነጻነቱን የሚጠቀም ሰው ሆኜ በመፈጠሬ ነው ፡፡


አላማዬ መናገር ነው ፡፡ አላማዬ መማር መማማር፣ ግድየለሽነትን በእውቀት ማስወገድ ነው ፡፡ ይህ አላማዬ ከማንም ያልተቀበልኩት ሰው በመሆኔ ብቻ ያገኘሁት ነው፡፡ ይህንን መሰረታዊ የሰውነት መብቴን ማንም አንዲነፍገው አልፈቅድለትም ፡፡ የመንግሰት ሹመኛ ይሁን ተራ ግለሰብ ፣ ተቋም ይሁን ማህበረሰብ የመናገር መብቴን ልሰጠው አልደራደርም ፡፡

የምናገረው በአደባባይ ፣ በገዛ ቤቴ ፣ በማህበራዊ ሚዲያ በእስር ቤት በፍርድ ቤት በፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል በአጠቃላይ በአካባቢዬ ያለውን ግለሰብና ቡድን ሳላውክ በሃላፊነት ነገር ግን በማንኛውም ቦታ ነው ፡፡ ይህንን እነዳላደርግ ቁጣ ፣ ማስፈራሪያ፣ የማሰቃየት ተግባር እስርና ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ  መብቶች መከልከል አላገደኝም ለወደፊትም እንዲያግደኝ አይሆንም ፡፡

ጓደኞቼም ሆነ እኔ አሁን ያለንበትን እስር ማስወገድ እንድንችል ስደትና ሌሎች መንገዶች አንድንመለከት ሥርዓቱ በደህንነት ሰራተኞቹ ጥቆማ ሰጥቶን ነበር፡፡ የመጨረሻዋ ሰአት ስትቃረብ ከልብ የሆነ አእምሮን የሚፈታተን ውይይት አድርገን ነበር፡፡ ከመታሰራችን ቀናት ቀድሞ ሚያዝያ 15/2006 በገጻችን ዞን9 አንዳስነበብነው“ ተፈጥሮአዊና ህገ መንግሰታዊ መብታችንን ማስረከብ “ እጅግ ስለበዛብን የምንከፍለውን ዋጋ እና የስርአቱን ቂመኝነት እያወቅን መናገራችንን አንደምንቀጥል አውስተን ነበር፡፡


የተራዘመው የእስር ጊዜም ይሄንን አቋም አልለወጠውም፡፡ አሁንም መናገር አሁንም ሃሳቤን መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡ ይህ ሰው ሆኖ የመወለድ መብት በምንም አይነት ላባክነው አልፈልግም፡፡ግንቦት 19/2007  በዋለው ችሎትም የተፈጸመውም ይሄ ነው፡፡


ይህንን ክስ የሚከታተል ሰው ሁሉ አንደሚያውቀው19ኛ ወንጀል ችሎት በቀረብንባቸው ጊዜያት ዳኞቹ ንጽህናችንን የምናረጋግጥበትን እድል የሚያጣብቡ ውሳኔዎቸን መወሰናቸው ፣ የራሳቸውን ውሳኔ መልሰው መካዳቸው ፣ አቃቤ ህግ በቸልተኝነት የፍትህ ሂደቱን አንዲያዘገይ መፍቀዳቸው ፣ ማረሚያ ቤት የሚደርሱብንን የመብት ረገጣዎች ሰምተው አጥጋቢ እርምጃ አለመውሰዳቸው ሳያንስ ከሁሉም የከፋው ደሞ ችሎት ውስጥ እነዳንናገርና ሃሳባችንን እንዳንገልጽ ማፈናቸው ነው ፡፡


ይህንን ተከትሎ መፍትሄ ይሆናል በማለት ሃሳባችንን በችሎት እንዳንገልጽ መታፈናችንን በመግለጽ የመሃል ዳኛው አንዲቀየሩ አቤቱታም አቅርበን ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ ጥያቄያችንን ውድቅ ቢያደርገውም መሃል ዳኛው በራሳቸው ፍቃድ ከእኛ ( ከነሶልያና ሽመልስ) የክስ መዝገብ ራሳቸው አግልያለው ብለው የነበረ ቢሆንም አሁንም ድረስ የሚሰየሙት ራሳቸው ናቸው :: ችሎቱም አንደተለመደው ለአቃቤ ህግ እንደፈቀደ ለእኛም ሆነ ለዳኞቹ ለራሳቸው የማይገቡ ነገሮች የሚናገርበት እኛም አንዳንዴ ካልሆነ በስተቀር እንዳንናገር የምንታፈንበት ሆኖ በኤሊ ፍጥነት እያዘገመ ነው ፡፡


ይህ መዘግየት አንደሚያሳስበን ዳኞቹ የተረዱ አይመስለኝም፡፡ በነጻነት ልናደርጋቸው የምንፈልጋቸው ነገሮች አንዳሉን ከሚወዱንና ከምንወዳቸው ሰዎች እስር ቤቱ አንደነጠለን ዘንግተውታል፡፡

የአገሪትዋን የማረሚያ ቤቶች ሁኔታ እና የማረሚያቤቶቹን የእስረኞች አያያዝ አያውቁት ይመስል፣ እኛ የተፈጠርንበትን የጉድ ዘመንና የምንተውንበት ወለፈንድ ድራማ አስገርሞን ፈገግ ማለታችንን አይተው እስሩ የተመቸን እየመሰላቸው በቀጠሮ ላይ ቀጠሮ መደራረባቸው አግባብ አለመሆኑን መናገር ነበረብኝ ፡፡ መታሰራችን ጤናማ መንፈሳችንን እያደከመ መሆኑን አቃቤ ህግ እስከዛሬ አለኝ ሲል ያልተደመጠውን በድንገት ያመጣውን አንድ ዶክመንተሪ ሲዲ (አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ላይ የቀረበ) ለማየት ሃያ ቀናት መውሰዱ ፣ በአጭር ቀናት ውስጥ አይተው በፍጥነት ወደቀጣዩ የፍርድሂደት እንድንሄድ አንዲደርጉ ለመግለጽ በፍርድ ቤቱ ሥርአት መሰረት እጄን አውጥቼ አውጥቼ አሳየሁ። አንደተለመደው እነዳንናገር ዳኞቹ እቀባ በማድረግ የመሰማት እድላችንን ነፈጉን ፡፡ ለመናገር ፍቃድ ስንከለከል ሳይፈቀድልን መናገር ጀመርን ፡፡ “ የምጣዱ ሳለ የእንቅቡ ተንጣጣ” አንዲል ያገሬ ሰው ተበድለን በተናገርን “ስነስርአት አድርጉ” የሚል ትእዛዝ ከዳኞቹ መጣ፡፡ በዚህ ሰአት “እናንተ ራሳችሁ ሥነ-ስርዓት አድረጉ” በማለት ስርአት አልበኛ የሆነው የንጹሃን ዜጎችን መብት ለማፈን የተዘጋጁት እነሱ መሆናቸውን ተናግሬያለሁ፡፡ ይህንን ስናገር ስሜት ተጭኖኝ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በዚያ ችሎት የሚፈጸመውን በደል ትውልድ እንዲረዳው ታሪክም መዝግቦ አንዲያቆየው መዘከር ነበረብኝ፡፡
ሥነስርዓት ምን እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ወላጆቼ በገባቸው መጠን ጥብቅ በሆነ ስነስርዓት አሳድገውኛል፡፡ ይህ ታላቅን ብቻ ሳይሆን ታናሽንም ማክበር አንደሚገባ ሥነ-ስርዓትና ደንቦችን መጣስ አንደማይገባ ይጨምራል፡፡ ( በሁለት አመት የዞን9ሥራቸንም ለማንኛውም የአገሪቷንህግ ሳንጥስ ህጋዊ ሆነን የቆየነው ለዚያምጭምር ነው ) ነገር ግን መታፈንን በጻጋ መቀበልና በደልን መሸከምን አይጨምርም፡፡ የማንም ሰብአዊ መብት ተሟጋች ወይም ነጸ አውጪአይደለሁም ፡፡ የግለሰብ መብቴ ሲነካ ግን ዝም ማለት አልወድም ፡፡ በተለይም ደግሞ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብቴ አንዲከለከልአልፈልግም ፡፡ ስለዚህም ይህንነ ከዚህ በፌት ላደረገ ፣ ከአሁን በማድረግ ላይ ያለ ፣ ወደፌትም ለማድረግ የሚያስብን ሁሉ አስጠነቅቃለሁ………….ሥነ-ስርዓት !!


Ethiopia becomes a state of one party

Ethiopia falls down under dictatorial regime of one party called TPLF (Tigrea people liberation front) which is controlled by one minority ethnic group that make up only 6% of  96 million Ethiopian population. They were in power for 24 years. They are now deciding themselves to continue in power as a result of their fake election which was carried out on 24/05/2015. As expected, TPLF has already declared that they have got 442 parliamentary seats so far out of 547 seats, while the final result is slated to be announced on June 22nd. This leaves the opposition empty-handed. Such victory by the regime is a message of disgrace and shows that a multi-party system is over in Ethiopia and it seems as it is monopolized only by one party. We Ethiopians rather embarrassed than surprised by the election results. This is because the election was also carried out without having

Friday, May 29, 2015

በሃመር ወረዳ ከፍተኛ እልቂት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን በሃመር ወረዳ በዲመካ ከተማ እና አካባቢዋ የሚኖሩ አርብቶአደሮች ” እኛ ድምጽ ሳንሰጥ” እንዴት ኢህአዴግ አሸነፈ ይባላል በሚል ካለፈው
ሰኞ ጀምሮ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ሲታኮሱ መቆየታቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አንድ ሻለቃ ጦር እና የፌደራል አባላት ወደ አካባቢው በመንቀሳቀስ በወሰዱት እርምጃ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል። አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች አደጋ የደረሰባቸውን ሰዎች ቁጥር በመቶቶዎች ያደርሱታል።
የአካባቢው ሰዎች እንደሚሉት አርብቶ አደሮች 5 የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ያቆሰሉ ሲሆን፣ ቁስለኞችም በሄሊኮፕተር ተወስደዋል። በአርብቶ አደሮች በኩል የተገደሉትን ሰዎች በትክክል ለማወቅ እንደማይቻል የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች
አስከሬን በየቦታው ወደቆ እንደሚታይ እየገለጹ ነው።
በዞኑ የሚኖሩ አንድ ታዋቂ ግለሰብ እንደተናገሩት ደግሞ ትናንት አርብቶ አደሮች ዲመካን በሌሊት ለመያዝ ጥቃት በፈጸሙበት ወቅት የመንግስት ወታደሮች ከባድ መሳሪያ በመተኮስ በወሰዱት የአጸፋ እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች
እንደተገደሉ መረጃው እንደደረሳቸው ገልጸዋል። በሶስት ፒካፕ መኪኖች የተጫኑ ቁስለኛ ወታደሮች ጂንካ ሆስፒታል መግባታቸውንም አክለው ገልጸዋል። ሁለቱም ወገኖች ለወራት የጦርነት ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የሚናገሩት ግለሰቡ፣
የችግሩ ምንጭ ከምርጫ ጋር ብቻ ሳይሆን ከመሬት ጋር የተያያዘ መሆኑም ይገልጻሉ።
ሌላ የአካባቢው ነዋሪም እንዲሁ በተወሰደው እርምጃ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን መረጃ እንደደረሳቸው ተናግረዋል ። የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ በርጤ ዢላ መግለጫ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል።
ኢሳት በሁለቱም ወገን የሞቱትን ሰዎች ከገለልተኛ ወገን ለማጣራት ያደረገው መኩራ አልተሳካለትም።
ኢሳት ከሶስት ቀናት በፊት አርብቶአደሮች 3 ፖሊሶች ማቁሳለቸውን ዘግቦ የነበረ ሲሆን፣ ሆቴል ቤቶችና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አሁንም ድረስ እንደተዘጉ ነው።
ለወራት የዘለቀው ውጥረት ምርጫውን ሰበብ አድርጎ መጀመሩን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። ሰመጉ ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው ልዩ መግለጫ ከጥር 7 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በተከሰተ ግጭት 7 ሰዎች መገደላቸውንና 9 ሰዎች መቁሳለቸውን
በጥናት አረጋግጦ ይፋ አድርጓል።
ሰመጉ በሪፖርቱ ህዳር 7 ቀን 2007 ዓም አቶ ዑልዴ ሃይሳ በሐመር ወረዳ ሸንቆ ወልፎ ቀበሌ ውስጥ ነዋሪ የነበረ አርብቶ አደር ሲሆን፣ በድንገት በተነሣ አለመግባባት ምክንያት ባሌ ኢልዴ በተባለ የፖሊስ አባል ኩላሊቱ ላይ በከባድ
እርግጫ በመመታቱ የአቶ ዑልዴ ህይወት በእለቱ ህዳር 7 አልፏል። የሐመር ብሔረሰብ አባላት አቶ ዑልዴን የገደለው የፖሊስ አባል ሕግ ፊት ቀርቦ ባለመጠየቁ ከፍተኛ ቅሬታ አድሮባቸውና የመበደል ስሜት ውስጥ ገብተው እንደነበር
የሰብአዊ መብት ድርጅቱ አስታውቃል።
ማንጐ ተብሎ በሚጠራው ፓርክ ጎሽ የገደሉ የሐመር ብሔረሰብ አባላትን ለመያዝ ከደቡብ ኦሞ ዞን ፓሊስና ልዩ ኃይል የተውጣጡ አባላት ጥር 7/ 2007 ሥፍራው ሲደርሱ ለሽምግልና የተቀመጡ የአካባቢውን ሽማግሌዎች ጎሽ ገዳዮችን እንዲያወጡ በጠየቁዋቸው ጊዜ “በቅርቡ የተፈጸመውን የአቶ ዑልዴን ግድያ ሳታጣሩና ገዳዩን ይዛችሁ ለፍርድ ሳታቀርቡ፣ ከረዥም ጊዜ በፊት ጎሽ ገደለ የምትሉትን ሰው ለመያዝ እንዴት መጣችሁ?” የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውን ይሁን እንጅ ” የፖሊስና ልዩ ኃይል አባላቱ በወቅቱ የተሰጣቸው ግዳጅ ጎሽ የገደለን ሰው መያዝ ብቻ መሆኑን በመግለጽ፣ ፖሊስ የተላክሁበትን ግዳጅ እፈጽማለሁ በማለቱ የሐመር ሽማግሌዎችና የማኅበረሰቡ አባላት ደግሞ የአቶ ዑልዴ ሃይሳን ገዳይ ሳትይዙ
የጎሽ ገዳይ ልትይዙ አትችሉም በሚል አለመግባባት መፈጠሩን ሪፖርቱ ያስረዳል።
አለመግባባቱ እየተካረረ ሄዶ በዚያው ቀን ጥር 7 ቀን 2007 በሐመር ማኅበረሰብ አባላትና በፖሊሶች መካከል ተኩስ ተጀምሮ፣ ሰፋ ወዳለ ግጭት ያመራ ሲሆን በግጭቱም 7 ሰዎች ሲሞቱ 9 ሰዎች መቁሰላቸውን ማረጋገጡን የሰመጉ 134ኛ
ሪፖርት ያስረዳል።
ሰመጉ ባወጣው የሟቾች ስም ዝርዝር አብዛኞቹ የሞቱትና የቆሰሉት የደቡብ ኦሞ ዞን ፖሊስና የልዩ ሃይል አባላት ናቸው።
ሰመጉ በግጭቱ ተሳታፊ ከነበሩት የሐመር ብሔረሰብ አባላት በኩል ምን ያህል ሰዎች ጉዳት እንደደረሰ ለማወቅ አለመቻሉን በመግለጫው አስታውቋል።
በሃመር ወረዳ ከ45 ሺ በላይ ነዋሪዎች ይኖራሉ። ዲመካ የወረዳው ዋና ከተማ ናት።


Wednesday, May 27, 2015

ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙር!- የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

ምርጫ 2007 ተጠናቆ ተወዳዳሪም አወዳዳሪም የሆነው ህወሓት ይፋ ውጤት እስኪገልጽ እየተጠበቀ ነው። ሁሉ በእጁ ነውና ባለሥልጣኖቹ ምን ዓይነት ውጤት እንደሚስማማቸው እስከሚነግሩን ጥቂት ቀናት ይወስዱ ይሆናል። ከፈለጉ ሁሉን የፓርላማ ወንበሮች ሊወስዷቸው ይችላሉ፤ ካሻቸው ደግሞ ጥቂቱን ለተቃዋሚዎች ሊሰጡ ይችላሉ። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። በዚህ የፓርላማ ወንበሮች እደላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ አንዳችንም ሚና የለውም።

ምርጫ የሕዝብ የሥልጣን ባላቤትነት ማረጋገጫ ከሆኑ አቢይ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት አንዱ መሆኑ የታወቀ ነው። ሆኖም ግን ነፃ ተቋማት በሌሉበት፤ በአምባገነኖች አስፈፃሚነት የሚደረግ ምርጫ የመራጮች ነፃ ፍላጎት መግለጫ በመሆን ፋንታ የገዢዎች ሥልጣን ማረጋገጫ መሣሪያ ይሆናል፤ ከአገራችን እየሆነ ያለውም ይህ ነው።

ፍ/ቤቱ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ የቀረቡ የሲ.ዲ መረጃዎችን ውድቅ አደረገ

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሶስቱ ጋዜጠኞች ዛሬ ግንቦት 19/2007 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ መዝገቡ የተቀጠረው አቃቤ ህግ አሉኝ ባላቸው ሲ.ዲዎች እና ቀሪ ምስክሮቹን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ብይን ለመስጠት ነበር፡፡
በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡ ቀሪ ምስክሮቹን በተመለከተ ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ ምስክሮቹን ለማቅረብ ፍርድ ቤቱ በተደጋጋሚ የሰጠውን እድል ባለመጠቀሙ እና ምስክሮቹን ላለማቅረቡ የሰጠው ምክንያትም በቂ ባለመሆኑ አቃቤ ህግ ያቀረበውን የተጨማሪ ጊዜ ባለመፍቀድ ከዚህ በኋላ ምስክሮቹን እንደማይሰማ አመልክቷል፡፡
አቃቤ ህግ በኤግዚቢትነት ይዟቸው የቆያቸውን የ12ቱን ሲ.ዲዎች ጉዳይ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ሲ.ዲዎቹ በማስረጃ ዝርዝሩ ውስጥ ፕሪንት ተደርገው የተያያዙ ሰነዶችን እንደያዙ ስለተገለጸ ሲ.ዲዎቹ ከማስረጃነትም ሆነ ከኤግዚቢትነት ውድቅ መደረጋቸውን ገልጹዋል፡፡
አቃቤ ህግ በአንደኛ ተከሳሽ ላይ የሲ.ዲ ዶክሜንተሪ ማስረጃ ማቅረቡን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ እንዲመለከትለት የጠየቀ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ከሰዓት በኋላ አቃቤ ህግ ሲ.ዲውን በጽ/ቤት በኩል እንዲያስገባ በማዘዝ በአንደኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበውን ዶክሜንተሪ በቢሮ ዳኞቹና ጠበቆቹ እንዲመለከቱት ከተደረገ በኋላ ሲ.ዲው ሌሎችን ተከሳሾች ይመለከታል ወይስ አይመለከትም የሚለውን አይቶ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 8/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ተከሳሾች ጥያቄያቸውን ለፍርድ ቤቱ ለማስረዳት በሞከሩበት ጊዜ ፍርድ ቤቱ የመናገር እድል ሲነፈጉ የተስተዋለ ሲሆን፣ ተከሳሾቹ ፍርድ ቤቱ እንዲፈቅድላቸው ሲጠይቁ ‹‹ስነ-ስርዓት አድርጉ!›› ባለ ጊዜ ጦማሪ አቤል ዋበላ ‹‹እናንተ ራሳችሁ ስነ-ስርዓት አድርጉ....እንናገርበት! ይህ የመብት ጉዳይ ነው...በግልጽ ችሎት ላይ ህገ መንግስታዊ መብታችንን አክብሩ እንጂ...ጥያቄ አለን ተቀበሉን›› ሲል በመናገሩ ችሎት ደፍረሃል ተብሏል፡፡ በዚህም ፍርድ ቤቱ በአቤል ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለግንቦት 25/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡


በእሁዱ ምርጫ ላይ ታዛቢዎችና መራጮች ትዝብታቸውን እየተናገሩ ነው

ሚያዝያ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው እሁድ ግንቦት15 ፣ 2007 ዓም የተካሄደው ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንደተካሄደ መንግስትና ብቸኛው የውጭ ታዛቢ የአፍሪካ ህብረት ቢገልጽም፣ በምርጫው የተሳተፉ ታዛቢዎችና መራጮች ምርጫው በአሳዛኝ ሁኔታ መካሄዱን መስክርነታቸውን እየሰጡ ነው።
በአዲስ አበባ የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢ የነበረው አቶ መሰለ አድማሴ እንደገለጹት እርሳቸው በታዘቡበት የምርጫ ጣቢያ፣ የምርጫ ኮሮጆዎች ታዛቢዎች ሳይገኙ መከፈታቸውን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ካርድ ሲያስገቡ ማየታቸውንና ለምን ሲባሉ ” ለአባቴ ነው የምመርጠው” የሚል መልስ መስጠታቸውን እንዲሁም የደህንነት ሃይሎች ምርጫ ጣቢያ ውስጥ ገብተው ሲያስፈራሩ መታዘባቸውን ተናግረዋል

The youngest ever political prisoner, (age 3), went to jail

Her mother Ms. Nigist Wendifraw is an activist and member of the popular opposition Blue Party. The Ethiopian government violates the international law in the treatment of children in Prison, and the Convention on the Rights of the Child which Ethiopia has ratified in 1993.


Ill-treatment of children in the Ethiopian detention system appears to be systematic and institutionalized. The best interests of the child are to be used as the basis for decisions to allow children to stay with the mothers, and children in prison with their mothers shall never be treated as prisoners, and the environment for the children’s upbringing is to“be as close as possible to that of a child outside prison.” According to the Convention on the Rights of the Child. The prison conditions in Ethiopia are described as "horror and "hell on earth" by previous political prisoners, Human Rights Watch and Amnesty International.


Tuesday, May 26, 2015

ወያኔ ኢሓዴግ በምርጫ ተሸንፎ እያለ አጭበርብሮ በሥልጣን ለመቀጠል በሚያደርገዉ መፍጨርጨር ለሚከተለዉ ማንኛዉም ሕዝባዊ ተቃዉሞ ተጠያቂ ነዉ።

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን ይህን መግለጫ አውጥቷል።
በ 2007 ብሄራዊ ሀገር አቀፍ ምርጫ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ከምርጫው ቅስቀሳ ጊዜ ጀምሮ ያለው ሁኔታ ነፃና ፍትሃዊ አለመሆኑን ባወጡት ሪፖርት አረጋግጠዋል::ወያኔ በምርጫው ቅስቀሳ ሂደት ድብደባ፣ አፈና ፣እስራት ፣ግድያ እና እንግልት በግልጽ ፈጽሟል:: (በምዕራብ ሸዋ ዞን ሚዳቀኝ እና በአርሲ ኮፈሌ የተፈጸመው ግድያ ፤ በእነ በቀለ ገርባ ላይ በበደሌ፣ ጅማ እና በነቀምቴ የተፈጸመውን ድብደባ ልብ ይሏል)

Monday, May 25, 2015

እርምጃችሁ ትክክል መንገዳችሁ የድል መዳረሻ ነው

ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ዘመኑን የዋጀ የፖለቲካ መሪ

መጪው ጊዜ ከወያኔ ጋር ድቅድቅ ጨለማ መሆኑን በመገንዘብ በ1997 ዓ.ም ከምርጫ ማግስት ይህን አንባገነን መንግስት ሁሉን አቀፍ በሆነ  የሀይል ትግል ካልሆነ በሰላማዊ መንገድ ስልጣኑን በህዝብ ለተመረጠ የህዝብ ተወካይ እንደማያስረክቡ ከበቂ ትንታቴ ጋር አቅርቦ ስርዓቱ  ይወገድ ዘንድ ከሌሎች የለውጥ ሀይሎች ጋር ሌት  ከቀን የተቻለውን ብቻ ሳይሆን አይቻልም አይሞከርም የተባለውን ሁሉ እየሞከሩ በርካታ ለውጦችን በሚመሩት ንቅናቄ ዙራያ አስመዝግበዋል፡፡እያስመዘገቡም ይገኛሉ፡፡

በኦሮሚያ ሁለት የምርጫ ታዛቢዎች ተገደሉ “ምርጫ ሳይሆን ዘረፋ ነው የተካሄደው” – ዶ/ር መረራ ጉዲና

ትናንት እሁድ የተካሄደው ምርጫ በመሳሪያ የተደገፈ ዘረፋ እንጂ ምርጫ አልነበረም ሲሉ ዶ/ር መረራ ጉዲና አስታወቁ:: የመድረክ የወቅቱ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስም የምርጫውን ሂደት አወገዙ::

ምርጫው በፌደራል ፖሊስ እና በልዩ ሃይሎች የሕዝብ ድምጽ እንዲሰረቅ መድረጉን ያጋለጡት ዶ/ር መረራ ጉዲና በአምቦ አካባቢ የተቃዋሚ ፓርቲ 2 የምርጫ ታዛቢዎች መገደላቸውንም ለኢሳት ገልጸዋል:: ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስም በደቡብ ክልል በተለያዩ ቦታዎች በመንግስት ታጣቂዎች የምርጫ ኮሮጆ ከመሰረቁም በላይ በርካታ የምርጫ ታዛቢዎች መደብደባቸውና ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው አስታውቀዋል::

በአሪሲ ኮፈሌ እንዲሁም አምቦ ሚደጋን ቶላ ላይ ሁለት የምርጫ ታዛቢዎች መገደላቸውንና በሌሎች ላይም ጥቃት መፈጸሙን ዶ/ር መረራ ገልጸዋል:: ዶ/ር መረራ ጉዲና ሕዝቡ በሰላማዊ መንገድ የተሰረቀውን ድምጹን ለማስመለስ እንዲታገልም ጥሪያቸውን አቅርበዋል::


Saturday, May 23, 2015

ከእንግዲህ ቀልድ የሆኑ ምርጫዎችን አብረን ማፅደቅ የለብንም ብለን ስለወሰንን ነዉ። Ana Gomes

ኢትዮጵያ የፊታችን እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007ዓ,ም አምስተኛዉን ብሔራዊ ምርጫ ታካሂዳለች። ከአፍሪቃ በሕዝብ ብዛት ሁለተኛ ደረጃ ላይ በምትገኘዉ ሀገር በዘንድሮዉ ምርጫ ከ50 በላይ ፓርቲዎች ይሳተፋሉ።

በምርጫዉ ድምፁን ለመስጠትም ከ36,8 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ መመዝገቡን የሀገሪቱን የምርጫ አስፈፃሚ አካል የጠቀሱ ዘገባዎች ያመለክታሉ። ምርጫዉን ለመታዘብ ከሀገር ዉስጥ ምርጫ ቦርድ ከሚያሰማራቸዉ ሌላ ከዉጭ የአፍሪቃ ኅብረት ታዛቢዎች ብቻ እንደሚገኙ ተገልጿል። ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የተካሄዱ ምርጫዎችን የታዘቡ የአዉሮጳ ኅብረትም ሆነ የአሜሪካዉ ካርተር ማዕከል ታዛቢዎች አይገኙም። የ1997ቱን ምርጫ የታዘቡት የአዉሮጳ ኅብረት ልዑካን መሪ ታዛቢ መላክ አስፈላጊ አይደለም ይላሉ።

የዘንድሮዉ ምርጫ ከ1983 እስከ 2004ዓ,ም ድረስ በመንግሥት ስልጣን ላይ ከነበሩት ከቀድሞዉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈተ ሕይወት በኋላ የሚካሄድ የመጀመሪያዉ ምርጫ ነዉ። ዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ድምፁን ለመስጠት የተመዘገበዉ ሕዝብ ብዛት በሀገሪቱ የተሻለ ዴሞክራሲ ሰፍኖ እንደሁ የሚፈትንበት አጋጣሚ እንደሆነ መጠቆሙን የዜና ዘገባዎች ያመለክታሉ

ኢህአዴግ ሆይ ነቄ ነን ተቀየስ! – ርዕዮት አለሙ- ከቃሊቲ እስርቤት

ኢህአዴግ ሆይ ነቄ ነን ተቀየስ!

አራት ሆነን ወደምንኖርበት የአሁኑ የማግለያ ክፍል ከመግባቴ በፊት በርካታ እስረኞች በተለምዶ የአራድኛ ቃላት የሚባሉትን በመጠቀም ሲነጋገሩ የመስማት እድል ነበረኝ፡፡ ለርዕሴ የመረጥኳቸው ቃላትንም ያገኘሁት ከነሱው መሆኑን መግለፅ ይኖርብኛል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፤

አንዳንድ እስረኞች የሚፈልጉትን አንዳች ነገር ለማግኘት በጉልበታቸው ወይም ጤፍ በሚቆላ ምላሳቸው ይጠቀማሉ፡፡ ሀይልን በመጠቀም ያስገድዳሉ ወይም ያታልላሉ ማለት ነው፡፡ እንዲህ አይነቶቹ እስረኞች እንደለመዱት ለማድረግ ሲሞክሩ አንዳንዴ ደፋርና የማይታለሉ እስረኞች ላይ ይወድቃሉ፡፡ እናም ለማታለል ወይ ለማስገደድ የሞከረች ባለጌ የሚጠብቃት መልስ “ነቄ ነን እባክሽ! ተቀየሽ! ንኪው!”የሚል ይሆናል፡፡ እኛን ማታለልም ሆነ
ማስፈራራት ስለማትችይ ይቅርብሽ፡፡ ዞርበይልን እንደማለት ነው፡፡

Friday, May 22, 2015

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ለአማራው መፈናቀል ምክንያት የሆነው ክልሉ የፈረመበት ደብዳቤ ኢሳት እጅ ውስጥ ገባ

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ2005 ዓም ቁጥራቸው ከ20 ሺ ያላነሰ በአብዛኛው ከመስራቅና ምእራብ ጎጃም የመጡ ዜጎች፣ ክልሉን ለቀው እንዲወጡ በመታዘዛቸው ቁጥራቸው በውል ያልተወቁት መንገድ ላይ ሲሞቱ፣ ሌሎች ደግሞ ቤት ንብረታቸውን አጥተዋል።
በጊዜው ኢሳትና ሌሎች የመገናኛ ብዙሃን ባደረሱት ተጽኖ መንግስት ተፈናቃዮች እንዲመለሱ ቢያደርግም፣ አጥፊዎችን ለፍርድ የማቅረቡ ጉዳይ ለረጅም ጊዜ ሲጓተት ቆይቶ በመጨረሻ መንግስት የተወሰኑ የወረዳ ባለስልጣናትን ለፍርድ አቅርቧል።

ይሁን እንጅ ኢሳት ውስጥ የገባው ሰነድ እንደሚያሳየው የማፈናቀሉ ትእዛዝ የመጣው በቀጥታ ከክልሉ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ሲሆን፣ ትእዛዙ በመን መንገድ መፈጸም እንዳለበት እቅዱ በግልጽ ተቀምጧል።
የማፈናቀሉን ደብዳቤ የጻፉት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አብዱልናስር ሲሆኑ ድርጊቱን በዋናነት እንዲያስፈጽሙ ሃላፊነት የተሰጣቸው ደግሞ ምክትልዩ አምባሳደር ምስጋናው አድማሱ ናቸው። የክልሉ ፕሬዚዳንት በወቅቱ ትእዛዝ አለመስጠታቸውን ተናግረው ነበር።

የአየር ሃይልና የመከላከያ አባላት ክስ ተመሰረተባቸው

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል፤ አባላትን መልምለዋል፤ ለሽብርተኛ ቡድኑ መረጃ አቀብለዋል፤ እንዲሁም ወደኤርትራ በመኮብለል የሽብር ድርጅቱን ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ተሰናድተው ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ በሚል የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በ7 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መመሰርቱን ሰንደቅ ዘግቧል።ተከሳሾች መቶ አለቃ ማስረሻ ስጤ፣ መቶ አለቃ ብሩክ አጥናዬ፣ መቶ አለቃ ዳንኤል ግርማ፣ መቶ አለቃ ገዛኸኝ ደረሰ፣ ተስፋዬ እሸቴ፣ ሰይፉ ግርማ እና የሻምበል አድማው አዳሙ መሆናቸውን ጋዜጣው ዘግቧል።“ሕገ-መንግስቱን እና ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል የማፈራረስ ዓላማን ይዘው ለማስፈፀም እና በመንግስት ላይ ተፅዕኖ ለማሳደር፤ ህብረተሰቡን ለማስፈራራት፤ የአገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተቋማት ለማናጋትና ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሰውና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሽብርተኛ ከተባለው የግንቦት ሰባት ድርጅት አባል በመሆንና በሽብር ድርጅት ለመሳተፍ ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ” የሚል ክስ እንደቀረበባቸው

Wednesday, May 20, 2015

አቤል ኤፍሬም በደረሠበት ድብደባ ኩላሊቱ ተጎድቶ ምንሊክ ሆስፒታል ገብቷል፡፡

በትላንትናው እለት በገዢው ፓርቲ የደህንነት ሀይሎች ተይዞ ወደማዕከላዊ ተወስዶ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲው አቤል ኤፍሬም ማዕከላዊ በሚገኙ የገዢው ፓርቲ ደህንነቶች ከትላንት ከቀኑ 5 ሠዓት ጀምሮ እስከ እኩለሌሊት በተፈፀመበት ከፍተኛ ድብደባ ኩላሊቱ በመጎዳቱ ዛሬ ጠዋት 11 ሠዓት ላይ ወደምንሊክ ሆስፒታል እንደተወሰደ ለማወቅ ተችሏል፡፡
አቤል ከመያዙ ከአንድ ቀን ቀደም ብሎ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ በማስተማር ላይ የሚገኙ 13 መምህራን በፖሊስ ተይዘው በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን አቤል ማዕከላዊ በገባበት ቀንም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኙ መምህራንን በህቡዕ እንደምታደራጅ ደርሰንበታል የተባለ ሲሆን አቤል ስለጉዳዩ ምንም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ የገለፀ ሲሆን ብሔሩን ሲጠየቅ ብሔሬ ኢትዮጵያዊ ነው ማለቱ ያናደዳቸው የደህንነት ሀይሎች መታወቂያውን በመቀበል ብሔሩን ለማጣራት ሲሞክሩ ብሔር የሚለው ስፍራ ላይ ምንም ብሄር አለመጠቀሱን ተመልክተው ተያዥ በሚለው ስፍራ ላይ ግን ታማኝ በየነ የሚል ፅሁፍ በማግኘታቸው ለድብደባ እንደተዳረገ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ሌሊቱን በሙሉ ያለምግብ እና ውሃ ሲደበድቡት ያደሩት የደህንነት ሀይሎች የአቤልን መድከም ሲረዱ ምንሊክ ሆስፒታል የወሰዱት ሲሆን በስፍራው የነበሩ ሠዎች እንደገለፁልኝ ከሆነ Abel Ephrem ሆስፒታል ሲደርስ በድብደባ ብዛት ኩላሊቲ እንዳበጠ እና የለበሰው ልብስ ከጥቅም ውጪ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡
‪#‎ኤርሚያስ_አለማየሁ‬


ግንቦት 7ትን ለመቀላቀል ሲሄዱ ተያዙ የተባሉት እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ሚያዝያ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው ግንቦት 12/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት በሃያዎቹ የእድሜ ክልል የሚገኙት ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ እየሩሳሌም ተስፋው ፣ ፍቅረማርያም አስማማው እና ደሴ ካህሳይ ናቸው።ተከሳሾች “ኤርትራ ውስጥ መቀመጫውን ባደረገውና በሽብርተኝነት በተፈረጀው ግንቦት ሰባት ስር አባል ሆነው የሽብር ተልዕኮ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ወስነው ከድርጅቱ ጋር ለመቀላቀል የኢትዮጵያንና የኤርትራን ድንበር አቋርጠው ሊሻገሩ ሲሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን” በዚህም የተነሳ በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በአባልነት በመሳተፍ ወንጀል መከሰሳቸውን የክስ ቻርጁ ንደሚያመለክት ጋዜጣው ዘግቧል። ተከሳሾቹ ጠበቃ ማቆምን በተመለከተ ከፍርድ ቤቱ ለተነሳላቸው ጥያቄ ሁሉም ተከሳሾች፣ ‹‹ከተያዝን ጊዜ ጀምሮ በደል እየደረሰብን ነው፤ ይህ የብቀላ ስራ ነው ብለን ስለምናምን እና በዚህ ሁኔታ ተከራክረን ፍትህ እናገኛለን ብለን ስለማናምን የግልም ሆነ የመንግስት ጠበቃ አንፈልግም›› የሚል መልስ ሰጥተዋል፡፡አንደኛ ተከሳሽ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ለፍርድ ቤቱ ባሰማው አቤቱታ ‹‹የተከሰስኩበት ወንጀል በክሱ ላይ የተመለከተው ሆኖ እያለ በግድ ቀድሞ እሰራበት በነበረው ሰማያዊ ፓርቲ ጓደኞቼ ላይ በተለይም በፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እና በህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ የግንቦት ሰባት አባል እንደሆኑ ተደርጎ መስክር እየተባልኩ ስቃይ

Tuesday, May 19, 2015

“ለውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ” ከአንዳርጋቸው ጽጌ እህት (ወ/ሮ ብዙአየሁ ፅጌ)

ይድረስ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ እንዳሸዋ ተበትናችሁ የምትገኙ ወገኖቼ እኔ የተጎዳሁትን ያህል እናንተም የተጎዳችሁ መሆናችሁን በተለያዩ ሀገሮች በተደረጉ ሰልፎች ፤ የዉይይት መድረኮች ላይ በንዴት፤ በቁጭት እና በእልኸኝነት በእንባ ስትራጩ በመሃላችሁ ተገኝቼ ያየኻችሁ ሲሆን ይህም በጣም በኢትዮጵያዊነቴ እንድኮራ አድርጎኛል። አንዳርጋቸውም በወያኔ የጨለማ እስር ቤት እየከፈለ ያለውን መከራና መስዋትነት የትም እንዳልወደቀና እንዳልቀረ በማሰብ እጽናናለው።

ዛሬ አንዳርጋቸው ፅጌ በመላው ኢትዮጵያዊያን ዘንድ  “የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ” ወዘተ…. የሚሉ መገለጫዎችን እና መጠሪያዎችን የተጎናፅፈው ታናሽ ወንድሜ አንዳርጋቸው ፅጌ በእኔ እይታ ደግሞ የቤተሰባችን ልዩ ልጅ ነው።

አንዳርጋቸው የቤተሰባችን የመጀመረያ ወንድ ልጅ ስለነበረ ብርቅዬ መሆን  የጀመረው የካቲት 1 ቀን 1947 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው ቀዳማዊ  ኃይለ ስላሴ ሆስፒታል ከእናታችን ከወ/ሮ አልታዬ ተሰማ  ሮቢ እና ከአባታችን ከአቶ ፅጌ  ሀብተማርያም ጨሜሳ ከተወለደ ቀን ጀምሮ ነው።

As Ethiopia votes, what’s ‘free and fair’ got to do with it?

by Terrence Lyons | The Washington Post

Ethiopia, Washington’s security partner and Africa’s second most populous country, is scheduled to hold national elections on May 24. The ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) and its allied parties won 99.6 percent of the seats in the last round of elections in 2010. There is no doubt that the ruling party will win again.

የህወሓት አየር ኃይል ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገው ጉዞ መሰረዙ ተሰማ

ምኒልክ ሳልሳዊ ዘንደዘገበው

የህወሓት አየር ኃይል ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገው ጉዞ መሰረዙ ተሰማ፡፡በበረራ፣ ጥገና፣ ድጋፍ ሰጪ፣ ዘመቻና አስተዳደር ከ200 በላይ አባላቱን በከፍተኛ ወጪ ለ6 ወራት ሲያሰለጥን የባጀው አየር ኃይል የሰላም ማስከበሩ ተልዕኮ ወደሚከናወንበት ደቡብ ሱዳን ሊጓዙ የተመረጡት መንገደኞች ከየአየር ምድቦቻቸው ተነስተው ደብረ ዘይት ከከተቱ በኋላ ጉዞው ድንገት ተዘርዟል፡፡

ጉዞው የተሰረዘባቸው ምክንያቶች በአባላትና አባላት፣ በአባላትና አመራሮች እንዲሁመም በአመራሮችና አመራሮች መካከል አለመተማመን በመስፈኑ፤ ያለመጠን ስር ሰዶ የተንሰራፋው ጎሰኝነት ተባብሶ በትግርኛ ተናጋሪ የህወሓት ሰዎች መካከልም ውቅሮና አዲግራት ወደሚሉ የመንደር ቡድንተኝነት ቁልቁለቶች በመውረዱ፤ ልክ እንደከዚህ ቀደሙ አሁንም አብራሪዎች ተዋጊ ሄሊኮፕተሮችን ይዘው ሊኮበልሉ ይችላሉ ከሚል ስጋት በመነጨ፣ ከፍተኛ በሆነ የአቅም ማነስ ችግር፤ ከምርጫው ጋር በተያያዘና ብረት ያነሱ የነፃነት ኃይሎች ጦርነት ይከፍታሉ ተብሎ በመሰጋቱ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

በህወሓት ቁጥጥር ስር የሚገኘው አየር ኃይል ከዚህ በፊት በ2005 ዓ.ም በብቃት ማነስ ምክንያት ከዳርፉር ተባሮ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን ሳያሳካ ጓዙን ጠቅልሎ ውርደት በመከናነብ መመለሱ አይዘነጋም፡



መጭውን ምርጫ ተከትሎ በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል ከፍተኛ ውጥረት እየታየ ነው

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢሳት የሚደርሱት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በተለይ በሰሜን የአገሪቱ ክፍል አብዛኛው ህዝብ ረብሻ ይነሳል ብሎ ያምናል። በዚህም የተነሳ ቀድም ብለው ገንዘባቸውን ባንክ ያስቀመጡ ሰዎች ገንዘባቸውን እያወጡ ለምግብ የሚውሉ የእህል ዘሮችን፣ ጨውና ሌሎችንም እቃዎች እየገዙ ነው። ወፍጮ ቤቶች ሰሞኑን ተጨናንቀው ታይተዋል። አቅም ያለው ቤተሰብ ለሶስት ወር የሚበቃ እህል ሲያስፈጭ፣ ድሃው ደግሞ አቅሙ በፈቀደ መጠን ለማጠራቀም እየተሯሯጠ ነው።
“በየከተሞች የሚታየው የሰራዊት እንቅስቃሴና ጥበቃ በህዝቡ ውስጥ ተጨማሪ አለመረጋጋት እንዲፈጠር እያደረገ ነው” የሚለው ዘጋቢያችን፣ ” ህዝቡ መንግስት በከፍተኛ ሁከት እና ብጠብጥ ይወገዳል” የሚል ግምት ማሳደሩ አሁን ለሚታየው አለመረጋጋት ምክንያት ሳይሆን አልቀረም ይላል።
የኖርዌይ፣ ስዊድንና አሜሪካ ኢምባሲዎች ያወጡዋቸው መግለጫዎች ለአለመረጋጋቱ ተጨማሪ ምክንያት መሆናቸውን ይጠቅሳል።
በህዝቡ ብቻ ሳይሆን የመንግስት ባለስልጣናትም ተወጥረዋል። በየአካባቢው ሌሊቱን በውጠራ በተጠንቀቅ የሚያሳልፉ ወታደሮችን ማየት የተለመደ ክስተት ሆኗል።
በባህርዳር ከተማ የመከላከያን ዩኒፎርም የለበሱ ወታደሮች የመገናኛ ሬዲዮ፣ ከባድ መሳሪያና ሌሎችም ቁሳቁሶች በመያዝ በየቀኑ ከ11 ሰአት በሁዋላ በከተማይቱ የተለያዩ አቅጣጫዎች ይዞራሉ። ህዝቡ ማንኛውንም አመጽ በመሳሪያ እንቆጣጠራለን የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ፈልገው ነው በማለት አስተያየት ይሰጣል።
በባህርዳር የመሰናዶ ተማሪዎች ለቅስቀሳ በተላከው የኢህአዴግ ቡድን ላይ ጥቃት የሰነዘሩ ሲሆን፣ ኢህአዴግ ይወረድ የሚል መፈክሮችን አሰምተዋል።
ባህርዳር፣ ጎንደር፣ አዋሳ፣ አዳማ፣ አምቦና አዲስ አበባ አመጽ ሊነሳባቸው ይችላል ተብሎ ከተለዩት ከተሞች መካከል ናቸው።
ገዢው ፓርቲ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ወጣቶችን በስራና ስልጠና በመደለል እንዲሁም በረብሻ ስም እያፈሰ አዋሽ አርባ አካባቢ በሚገኝ በረሃማ ቦታ ወስዶ አስሮአቸዋል። በርካታ ወጣቶች ከእስር ቤት ሲያመልጡ መንገድ ላይ በአውሬ መበላታቸውን እንዲሁም በምግብና ውሃ ጥም መሞታቸውን የሚደረሱን ተከታታይ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በቅርቡ ከማእከሉ ጠፍተው ጎንደር የደረሱ 5 ወጣቶች በእስር ቤቱ ያለው አስከፊ ሁኔታ እንዲጠፉ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል። ብዙ ወጣቶች መንገድ ላይ ወድቀው ማየታቸውንም ተናግረዋል።
ከምርጫ ዜና ሳንወጣ የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች የንብ ምልክት ያለበትን ፖስተር በየሰዎች ቤት ግድግዳ ላይ የሚለጥፉ ሲሆን፣ ፖስተሩ ተቀዶ ከተገኘ የቤቱ ባለቤት ተጠያቂ እየሆነ ነው። አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አባት፣ “ንቧን እንዳይቀዷት ቁጭ ብየ ስጠብቅ አድራለሁ ” በማለት ያጋጠማቸውን ፈተና ተናግረዋል።


Monday, May 18, 2015

ወጣት እስማኤል ዳውድን ጨምሮ 18 ተከሳሾች ላይ ክስ ተመሰረተ

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት አይኤስን ለማውገዝ ሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም በጠራው ሰልፍ ላይ ሁከትና ብጥብጥ አስነስተዋል የተባሉትና በወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት ተከሳሾች ላይ መደበኛ ክስ ተከፈተ። በዚህም መሰረት የሚሊዮኖች ድምፅ ጋዜጣ አምደኛና የአንድነት አባል የነበረው ወጣት እስማኤል ዳውድን ጨምሮ በሌሎች 18 ተከሳሾች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል።በወንጀል ዝርዝሩ ላይ ተከሳሾቹ ‹‹ቤተ መንግስት አካባቢ በቡድን በመሆን መፈክር በመያዝና በቃል በመናገር “ተነስ! በለው!”ጊዜው ዛሬ ነው አትነሳም ወይ፣ የሞተው ሬሳ ያንተ አይደለም ወይ? መንግስቱ ሀይለማርያም ይምጣልን! ከኢህአዴግ አይ ኤስ ይሻለናል!፣ ወያኔ ሌባ!፣ ውሸት ሰለቸን!፣ ዝምታ ይብቃ!፣ እናት ኢትዮጵያ ያደፈረሰሽ ይውደም!” በማለት ሁከትና ብጥብጥ ፈጥረዋል ተብሏል። እንዲሁም መፈክሮችን በመያዝ እና ወደ ፀጥታ ሀይሎች ድንጋይ በመወርወር ሰልፉን አውከዋል ያለው አቃቤ ህግ፤ “በዋና ወንጀል አድራጊነትና ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት ወንጀል- በቡድን ስብሰባን በማወክ ወንጀል›› መከሠሳቸውን አስረድቷል። ከአንደኛ እስከ አምስተኛ ያሉት ተከሳሾች ስድስት ክሶች የቀረቡባቸው ሲሆን፤ በሌሎቹ 14 ተከሳሾች ላይ ሁለት ክስ እንደቀረበባቸው የክስ ቻርጁ ያትታል። ዐቃቤ ህግ በተከሳሾቹ ላይ 21 የሰው ምስክር 6 የሰነድ ማስረጃና ሁለት ኤግዚቢቶችንም አቅርቧል።ከተከሳሾቹ ውስጥ ከ1ኛ ተከሳሽ፣ 2ኛ ተከሳሽ፣ 3ኛ ተከሳሽ፣ 6ኛ ተከሳሽ፣ 11ኛ ተከሳሽ 12ኛ ተከሳሽ የሰጡት የእምነት ቃል በሰነድ ማስረጃነት ቀርቧል።በኤግዚበትነት “ከአባይ በፊት የህዝብ እንባ ይገደብ” እና “ዝምታ ይብቃ” የሚሉ መፈክሮችን የያዙ ሳምፕሎችም በ ኤግዚቢትነት ተያይዘው ቀርበዋል።ይሁንና ከሚያዚያ 20 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ የሚገኘው ወጣት እስማኤል ዳውድ፣ ከትላንት በስቲያ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም ፒያሳ በሚገኘው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ዐቃቤ ህግ በሰነድ ማስጃነት ያቀረበው ቃል የእሱ አለመሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡‹‹የሰጠሁት ቃል የኔ አለመሆኑን በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ 3 መርማሪዎች ከማረፊያ ቤት ሌሊት 7፡30 አካባቢ ጠርተውኝ እዚህ ወረቀት ላይ ባትፈርም እየተፈራረቅን እናድርብሃለን በማለት በከዘራ እየመቱ ያስረሙኝ መሆኑን ፍርድ ቤቱ እንዲገነዝብልኝ›› ሲል እስማኤል ለፍርድ ቤቱ አቤቱታውን አቅርቧል።ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት በአንድ መዝገብ ውስጥ ከሚገኙት 19 ተከሳሾች ውስጥ ወጣት እስማኤልን ዳውድን ጨምሮ ሌሎች አራት ተከሳሾች በድምሩ አምስት ተከሳሾች የዋስትና መብት ተነፍጓል።እንዲሁም አስራ አራቱ ተከሳሾች የተጠየቀባቸውና የዋስትና ገንዘብ ብር 10000 በሲፒኦ አሰርተው ገቢ ቢያደርጉም አቃቤ ህግ በጠየቀው ይግባኝ የተነሳ ተከሳሾቹ ገንዘቡን አስይዘው ወደ ማረፊያ ቤት እንደተመለሱ ለማወቅ ተችሏል፡፡


ካድሬዎች የምርጫ ካርድ ላይ ንብን እየለጠፉ ለመራጩ እያደሉ ነው

በጋሞጎፋ ዞን ቁጫና ቦርዳ ወረዳዎች የደኢህዴን/ኢህአዴግ ካድሬዎች የህዝቡን ካርድ እየተቀበሉ የምርጫ ካርዱ ላይ የንብን ምልክት በስቴፕለር በማያያዝ ኢህአዴግን እንዲመርጡ እያስገደዱ እንደሚገኙ በጋጎፋ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ አቶ ወንድሙ መኩሪያ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ካድሬዎቹ ህዝቡን 1ለ5 በማደራጀት የንብ ምልክት የተለጠፈበት ካርድ በማደል ‹‹የምትመርጡት ኢህአዴግን ነው›› እያሉ እያስገደዱ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የዞኑ፣ የወረዳውና የየ ምርጫ ክልሉ ምርጫ አስፈጻሚዎች ካድሬዎቹ የንብ ምክትን የምርጫ ካርዱ ላይ እያያያዙ ኢህአዴግን እንዲመርጡ እያስገደዱ መሆኑን ቢያውቁም ምንም እርምጃ እየወሰዱ አይደለም ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል በጋሞጎፋ ዞን ቦረዳ ወረዳ ሰማያዊ ፓርቲ እሁድና ቅዳሜን ‹‹የገበያ ቀን ስለሆነ›› በሚል ቅስቀሳ እንዳያደርግ መከልከሉን አስተባባሪው ገልጸዋል፡፡ ‹‹የምርጫ ህጉ የሚለው ቅስቀሳ መደረግ ያለበት ከገበያ 500 ሜትር ርቆ ነው እንጅ በገበያ ቀን ቅስቀሳ አይደረግም አይልም፡፡ እኛን ግን ገበያ በሌለባቸው ቦታዎች ሁሉ እሁድና ቅዳሜ ቅስቀሳ እንዳናደርግ ከልክለውናል›› ብለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ እየከለከሉ የሚገኙት የቦረዳ ወረዳ የፀጥታ አስተዳደር ኃላፊ አቶ ማርካ ማዶ እና የወረዳው ፖሊስ አዛዥ መቶ አለቃ ታምራት ናቸው ብለዋል፡፡


ኢትዮጵያና አሜሪካ (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ዱሮ ዱሮ ምዕራባውያን የሶቭየት ኅብረትን ኮሚዩኒዝም መስፋፋት ለመቋቋም ከእሥራኤል ሌላ አጋር ሊሆኑ የሚችሉ አገሮችን ሲያስሱ፣ ኢትዮጵያ፣ ቱርክና ፋርስ እየታጩ ነበር፤ አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የተወዳጀበትና በአስመራ ቃኘው ጣቢያን የተከለበት አንዱ ምክንያት ይኸው ነው፤ የፋርስ ጉዳይ ከንጉሠ ነገሥቱ መፈንቅለ መንግሥትና ሞት ጋር አበቃ፤ ቱርክ እያንገራገረም ቢሆን የሰሜን አትላንቲክ አገሮች ማኅበር ውስጥ አለበት፤ እሥራኤል በአረቦች አካል ላይ እሾህ እንደሆነች ጥጋበኛ የአሜሪካ ቅምጥል ሆናለች።

አንድ በ20ዎቹ የእድሜ ክልል የሚገኝ ወጣት አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ በዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ተገደለ

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ 22 እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖረው የ25 ዓመቱ ሲሳይ ተሾመ በቅጽል ስሙ ገብሬ ያለፉትን 8 ዓመታት በቃሊቲና በዝዋይ እስር ቤቶች እየተመላለሰ አሳልፏል።

በተለይ ወደ ዝዋይ እስር ቤት ከተላለፈ በሁዋላ ፣ ሃጎስ የተባለው የእስር ቤቱ ሃላፊ ” አንተ የነፍጠኛ ልጅ እንበቀለሃለን፣ በእኔ እጅ ነው የምትሞተው” እያሉ ይደበድቡትና ይዝቱበት ነበር። ባለፈው ቅዳሜ እናቱ ሊጠይቁት ሲሄዱ፣ ታሞ
ሚኒሊክ መወሰዱን ይነግሩዋቸዋል። ወደ ሚኒሊክ ሲሄዱ፣ በአንድ አምቡላንስ ውስጥ ጎንና ጎኑ በኤሌክትሪክ ተጠብሶ፣ ኩላሊቱ አካባቢ ተረጋግጦና በልዞ፣ አናቱ አካባቢ ያረፈበት ድብደባ ፊቱን ለማየት በማይቻል ሁኔታ በደም እንዲሸፈን
አድርጎታል።
የደረሰበትን ጉዳት ለመግለጽ ይዘገንናል የሚሉት ቤተሰቦቹ፣ ፖሊሶች አንዴ ታሟል፣ ሌላ ጊዜ ጉዳዩ በአቃቢህግ ተይዟል በማለት ለመደናገር እየሞከሩ ነው። የ22 አካባቢ ወጣቶች የሟቹ ቲሸርት ያለበትን ፎቶ እያሳተሙ ነው። ፖሊሶችና ደህንነቶች በድንካኑ አካባቢ እየተዘዋወሩ በመቆጣጠር ላይ ናቸው። የሟች የቤተሰብ አባላት የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደን እያሉ ነው ።


Friday, May 15, 2015

የኢትዮጵያ ብሮድካሲቲንግ ኮርፖሬሽን ለቴሌቪዥን ስርጭቱ ገንዘብ ለመሰብሰብ በተንቀሰሳቀሰባቸው ከተሞችህዝቡ የቴሌቪዥን ግብር አንከፈልም ሲል ተቃውሞውን እየገለጸ ነው

ሚያዝያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተጠናክሮ በደረሰው ሪፖረት ህዝቡ “እኛ ኢቲቪን (ኢቢሲን) አይተን አናውቅም ፤ ለውሸት ጣቢያ ፈፅሞ ክፍያ አንፈፅምም ፤ በአይናችን ያየነውን ለሚክድ ሚዲያ
እኛ ምንም ድጋፍ አናደርግም፡፡ እንደዚህ የሚባል ጣቢያ አለ እንዴ ፤ ኢቲቪ የሚባል ጣቢያ መኖሩን አናውቅም ነበር ” የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡ፣ አንዳንዶች ደግሞ “እኛ ከኢሳት ውጭ ምንም ጣቢያ ሰምተንም አይተንም አናውቅም ፣
ሶሰት አመታት አለፈን” የሚሉ አሰተያየቶች ሰጥተዋል።
ኢቲቪ በሀገሪቱ ያለውን የቴሌቪዥን ቁጥር ወደ ግብር ሰንሰለት ለማሰገባት ያደረገው ጥረትም እንደከሸፈበት በሙሉ ሪፖርቱ ተካቷል፡
አየር ላይ ያለሰሚ እና ተመልካች ከሚባክኑ ጣቢያዎች መሃከል አንዱ ነው የሚለው ሪፖርቱ፣ የኢሳትን መረጃ የሚጋፋ ሚዛን መያዝ እንደማይቻል ያትታል፡፡
ሀዝቡ ኢሳት ቴሌቪዥንን ለማገዝ ከፍተኛ መነሳሳት እንዳሳየ በዚሁ አጋጣሚ ከተሰበሰበው የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኢቲቪን ( ኢቢሲን) ግብር ለመሰብሰብ ከውሃ ፤ ከቴሌ እና ከመብራት ደረሰኝ ክፍያ ጋር ማቀናጀት እና አዲስ በሚገዙት ላይ የቴሌቪዥን ሽያጭ መደብሮች የውክልና ምዝገባ እንዲያ
ካሂዱ መስጠት እንደሚያስፈልግ የሚጠቁም የመፍትሄ ሀሳቦች በጥናቱ ተካተዋል ፡፡ የኢትዩጵያ ቴሌቪዥን በህዝብ በጀት የሚተዳደር ሲሆን በአመት እስከ 123 ሚልዩን ብር ከማስታወቂያ የሚሰበሰብ ተቋም ነው፡፡
በሌላ ዜና ደግሞ ኢሳት ስርጭቱን እንደገና በአሞስ ሳተላይት ጀምሯል።ገዢው ፓርቲ አገሪቱን አንጡራ ሃብት በከፍተኛ መጠን በማፍሰስ ኢሳትን ከአየር ላይ ለማስቀረት የሚያደርገውን ጥረት በቀጠለበት በዚህ ወቅት ኢሳት እንደገና በአሞስ
ሳተላይት ወደ አየር መመለሱን የድርጅቱ ማኔጅመንት አስታውቋል፡፡
ኢሳት ለ24 ሰዓታት በSES 5 አማካኝነት ያለማቋረጥ ለሁለት ዓመታት ሲያቀርበው የቆየው ፕሮግራም ከሰኞ መጋቢት 14/2007 ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከተቋረጠ በሁዋላ ፣ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተደራሽነቱን በማስፋት
በአዲስ ሳተላይት ስርጭቱን ቢቀጥልም፣ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ገጥሞት ከአየር ላይ ወርዷል።
ምንም እንኳ ድርጅቱ አፈናውን ለማስቀረት የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ቢሆንም ፣ በውጭ አገር ታላላቅ መንግስታት በሚደረግ ግፊት ፣ ለሳተላይት ኩባንያዎች በሚቀርብ የገንዘብ ስጦታና እና ከፍተኛ ጥቅም በሚያስገኙ ፕሮጀክቶች
በመደለል፣ የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ኢሳት በኢትዮጵያ ምድር እንዳይታይ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው።
ማኔጅመንቱ “እነሱ ለአፈና ካላቸው ቁርጠኝነት በላይ እኛም የኢትዮጵያ ሕዝብ የነጻነት ርሃብ ይሰማናል እና ማናችውንም መስዋዕትነት በመክፈል ኢሳት በኢትዮጵያ ውስጥ የኢትዮጵያውያን ድምጽ ሆኖ እንዲቀጥል እንደምንሰራ እያረጋገጥን በአዲስ ሳተላይት እንደገና ስርጭታችን ” መቀጠሉን እናስታውቃለን ብሎአል፡፡
አዲሱ ሳተላይት የሳህን አቅጣጫ በከፊል ማስተካከል የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ሕዝቡ የችግሩን ስፋት ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ይህንኑ እንዲፈጽም እንዲሁም በውጭ ሃገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ነጻነት ወዳዶች ሁሉ ኢሳት በተጨማሪ ሳተላይቶች ጭምር ስርጭቱን ለማስፋት የሚያደርገውን ጥረት እንዲደግፉ ማኔጅመንቱ አቅርቧል።
አዲሱ የሳተላይት ስርጭት
Amos,
Frequency 12335 vertical,
symbol rate 27500 (27.5) , FEC 3/4
17 degree east
ሲሆን ኢትዮጵያውያን መረጃውን በማሰራጨት ከኢሳት ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል።
ኢሳት በAB 7 ሳተላይት ላይ የ 24 ሰዓታት የራዲዮ ዝግጅት በማቅረብ ላይ መሆኑ ይታወቃል።



5 በሃይል አማራጭ የሚያምኑ ድርጅቶች በጋራ ለመታገል ውይይት ጀመሩ

በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ በማንኛውም አማራጭ ለማስወገድ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ የተቃዋሚ ሃይሎች በጋራ ለመታገል የሚያስችላቸውን ውይይት መጀመራቸውን ለኢሳት በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል። ውይይቱን የጀመሩት የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ( ትህዴን)፣ የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፣ የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፣ የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄና አርበኞች ግንቦት7 ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ናቸው። ድርጅቶቹ ” በሂደት ወደ አንድ የምንመጣበትን ሁኔታ እያመቻቸን፣ አሁን ግን አገርና ህዝብን የማዳኑን ስራ እንጀምር በሚል ውይይት እያደረግን መሆናችንን ለኢትዮጵያ ህዝብ መግለጽ እንወዳለን” ብለዋል። የኢህአዴግን አገዛዝ በሃይል እናስወግዳለን በማለት የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ ድርጅቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ በሰው ሃይልና በሎጂስቲክ እየተጠናከሩ መምጣታቸውን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። ስርዓቱ በአገር ውስጥ በሚገኙ ዜጎች ላይ እያደረሰ ያለው አፈና ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመር፣ ወጣቶች የትጥቅ ትግል አማራጭን የሚደግፉ ሃይሎችን እንዲቀላቀሉ እያደረጋቸው ነው።



Thursday, May 14, 2015

አይሲስን ስንቃወም ህወሓትን አለመርሳት!

በአይሲስ በግፍ በታረዱብን ወገኖቻችን የተሰማን ሀዘንና ቁጭት ከፍተኛ ቢሆንም እንኳን ከአዕምሮዓችን መውጣት የሌለበት ሀቅ አለ። ይህ ሀቅ “ያስጠቃን፣ ያሳረደን ወያኔ ነው” ከሚለውም ያለፈ ነው። መረሳት የሌለበት ሀቅ፣ ከአይሲስ የከፋ ጨካኝ በአገራችን የመንግሥት ሥልጣን የተቆጣጠረ መሆኑ ነው።

የህወሓት ፋሽስት ጦር በበደኖ፣ በአዋሳ፣ በሀረር፣ በጋምቤላ፣ በጎንደር፣ በኦጋዴን፣ በአዲስ አበባ፣ በሸካና መዠንገር፤ እንዲሁም በሚታወቁም በማይታወቁም የማሰቃያ እስር ቤቶች አይሲስ እየፈፀመ ካለው የባሱ ወንጀሎች በወገኖቻችን ላይ ፈጽሟል፤ አሁንም እየፈፀመ ነው። ባሳለፍነው ሣምንት እንኳን በሁመራ ወገኖቻችን የራሳቸውን መቀበሪያ ጉድጓድ ቆፍረው በጅምላ ተገድለዋል። በአይሲስና በህወሓት መካከል ያለው ልዩነት አይሲስ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሩን በቪዲዮ እየቀረፀ ለዓለም ሲበትን ህወሓት ግን እነዚሁኑ ነውረኛና አረመኔዓዊ ተግባሮችን እየፈፀመ መረጃዎች አፍኖ መያዙ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ግን ህወሓት ሰዎችን ከነሕይወታቸው ጉድጓድ ውስጥ የቀበረ አረመኔ፣ እኩይ ድርጅት ነው።

ፕሮፍ. መስፍን ወልደማርያም፡- አማራ የሌለው የት ሄዶ ነው?

ከመለክ ሐራ

እኔ ልናገረዎ የማይገባ ብላቴና ነኝ፡፡ በብዙ ነገር አድናቂዎ እና ብዙዎችን ጽሁፎችዎን ያነበብኩ ነኝ፡፡ አሁን ለያዝኩት ማንነትም የእርስዎ አስተዋጽኦ አለበት፡፡ ይሁንና በአማራ ጉዳይ ላይ ባለዎት አቋም ላይ ከረር ያለ ልዩነት አለኝ፡፡ ሰው መሆን አቅቶኝ እና የጎሰኝነት ስሜት አጥቅቶኝ ሳይሆን ይህ የለም እየተባለ መከራ የሚወርድበት ህዝብ ረፍት ስላጣና ዜግነቱን ስለተነጠቀ እንዲሁም አለሁልህ የሚለው ስላጣ አቅሜ በፈቀደው ሁሉ ልሟገትለት ራሴን ስላዘጋጀሁ እርስዎንም አሻቅቤ ለመናገር ተገድጃለሁ፡፡ ስለራሴ ስል የእርስዎ እምነትና ፍልስፍና ነው ያለኝ፡፡ ስለህዝቤ ስል ግን ከዚህ ሸሽቻለሁ፡፡ እንዳይቀየሙኝ፡፡

የክህደት ቁልቁልት በተባለው መጽሀፍዎ ምእራፍ 11 ላይ ያተቱት የአማራ አለመኖር

አማራ ማለት ሀይማኖት ነው ስላሉ በአለም ላይ ያሉ ትናንሽና ትላልቅ እምነቶች ውስጥ ዝርዝሩን ለማግኘት ብዙ ደክሜ ሳላገኘው ቀረሁ፡፡ አማራ ማለት ክርስቲያን ከሆነ አገው ለምን አማራ እንዳልተባለ እንዲያብራሩልኝ እጠይቃለሁ፡፡ ሁለቱም ቅዱስ ላሊበላ የምትሄዱ አልጋ ባልጋ ነው መንገዱ እያሉ ለዘመናት በአንድ የክርስትና ማእድ ሲሳተፉ ኖረዋል፡፡ አንዱ አገው አንዱ አማራ ሆነው፡፡ አማራው ታዲያ ለምን ሁለት የክርስትና ስም አስፈለገው–አማራ እና ክርስቲያን የሚል? ከተለያዩ ጸሀፍት እንደጠቃቀሱትም አማራ ማለት ነጻ የወጣ ህዝብ (ከአረማዊነት የተመለሰ) ማለት ነው፡፡ ታዲያ አገው ነጻ አልወጣም ማለት ነው? ትግሬ ነጻ አልወጣም ማለት ነው? ወይስ የተለያየ አይነት ክርስትና ነው ያለው–አንዱን ነጻ የሚያወጣ ሌውን ነጻ የማያወጣ? እንደገና በአማራ መሀል የሚኖሩት አርጎባዎች እስላም ናቸው፡፡ ከሌላው እስላም ተለይተው ለምንድን አርጎባ የሚል ስም የያዙት? እነሱ የአርጎባ ጎሳ እስላሞች ሲሆኑ ከአርጎባ ውጭ ያለው ምን ሊሆን ነው?

የዜጎች መታፈን ተባብሶ ቀጥሎአል

ሚያዝያ ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ካለፉት ሁለት ሳምንታት ጀምሮ አገዛዙን ይቃወሙ ይሆናል ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች በገፍ እየተያዙ በመታሰር ላይ ሲሆኑ፣ በርካታ ወጣቶችም ከእስር ለማምለጥ መሸሸጋቸውን ለኢሳት እየገለጹ ነው።
በተለያዩ ክልሎች የገዢው ፓርቲ አባል ለመሆን ፈቃደኛ ያልሆኑ ወጣቶች የሚታሰሩት ከምርጫው ጋር በተያያዘ ህዝቡን ለአመጽ ያነሳሳሉ በሚል ነው።
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መሪ የነበሩት አቶ ማሙሸት አማረ ዛሬ ግንቦት5 ረፋዱ ላይ በአዲስ አበባ ፖሊሶች ተይዘው ታስረዋል። አቶ ማሙሸት እጆቻቸው በካቴና ታስረው ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ታይተዋል።
በጎንደር ደግሞ አቶ አዋጁ አቡሃይ አደመ እና አቶ አዳነ ባብል ታደሰ የተባሉት ሁለት ግለሰቦች ጸጥታ ሃይሎች ታፍነው ተወስደዋል።
ሁለቱ ታዋቂ ሰዎች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ መታሰራቸው ይታወቃሉ። ከ5 ቀናት በፊት ደግሞ ጎንደር ከተማ አራዳ ቅዳሜ ገበያ አካባቢ 10 ሰዎች በፌደራል ፖሊሶች ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
በሰሜን ጎንደር አካባቢ የሚታየው ውጥረት መጨመሩን ተከትሎ ስርአቱን እየተዉ በትጥቅ ትግል የሚያምኑ የተቃዋሚ ሃይሎችን የሚቀላቀሉ ወጣቶች ቁጥረም ጨምሯል።


Wednesday, May 13, 2015

Hiber Radio የቀድሞ የመኢአድ የሕዝብ ግኑኙነት ሀላፊን ጨምሮ በርካታ ወጣቶች ኤርትራ ለትጥቅ ትግል መግባታቸውን ገለጹ

ወጣት ተስፋሁን አለምነህ

የቀድሞ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበረው ወጣት ተስፋሁን አለምነህ በአገር ቤት የወያኔን አገዛዝ በሰላማዊ ትግል ታግሎ መጣል አይቻልም ብሎ በመወሰን እሱና ሌላው የመኢአድ አባል ደሳለኝ ሲሳይ ከበርካታ ወጣቶች ጋር ኤርትራ የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ሰሞኑን መግባታቸውን ለህብር ሬዲዮ ከስፍራው በሰጠው አጠር ያለ ቃለ ምልልስ ገለጸ።

<<በአስቸጋሪ ሁኔታ አልፈን የቀድሞው መኢአድ ግማሹ ክንፍ ኤርትራ ገብተናል>> በሚል አርዕስት ለህብር የላከውን ማስታወሻ እውነተኛነት ለማጣራት ባቀረብነው ጥያቄ የኤርትራ ስልኩን ልኮልን እሱም ሆነ ሌሎቹ በትጥቅ ትግል ስርዓቱን ለመጣል ኤርትራ የገቡ ወጣቶች መኖራቸውንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አልፈው በአማራ ዲሞክራሲ ሀይል ንቅናቄ ታጋዮች ተጋድሎ ጭምር ወደ ኤርትራ መግባታቸውን ጠቁሟል።

በአገር ቤት በሰላማዊ ትግዩ አምንን በተደጋጋሚ ስንታሰርና መከራ ሲደርስብን ነበር ያለው ተስፋሁን ሰላማዊ ትግሉ መሪያችን ፕሮፌሰር አስራትን ጨምሮ ብዙዎችን ከማስበላት ያለፈ ስርዓቱን ለማዳከም ባለመቻሉ የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ኤርትራ መግባታቸውን አረጋግጦልናል ።

<<ወያኔን በሰላማዊ ትግል አይወድቅም ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ በትጥቅ ትግል መታገል ነው>> ያለው ወጣት ተስፋሁን አለምነህ ስርኣቱን በሰላማዊ መንገድ ብቻ ታግሎ መጣል አለመቻሉን ጠቅሷል።

ከወጣት ተስፋሁን አለምንህ ጋር ያደረግነውን አጠር ያለ ቃለ ምልልስ ዘግይተን እናቀርባለን።


Tuesday, May 12, 2015

EBC ስለ ደቡብ ኦሞ ህዝብ የሰራዉ ዶክመንታሪ ለፖለቲካ ፍጆታ ወይስ ከልብ መቆርቆር

የወንበዴዉ መንግስታችን ልሳን የሆነዉ EBC በሙያተኞች እይታ ለፖለቲካ፡ ለትምህርት፡ለመዝናኞ፡ ለልማት ተብሎ የተቋቋመ ሚዲያ አለመሆኑን ማንም ያዉቀዋል፡፡ ግንቦት 2/2007 ዓ.ም ከሁለት ሰዓት ዜና በኋላ በደቡብ ኦሞ ዞን በሚኖረዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ( ይቅርታ ህዝቦች አላልኩም) የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶ/ር ዬሴፍ ማሞ እና የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ዶ/ር ሽፈራዉ ተክለማሪያም ከሌሎች የደቡብ ክልል አገር ገንጣዩና ወንበዴዉ ህዉሀት እንደፈለገ የሚያሽከረክራቸዉ ቡችል ባለስልጣናት ጋር በመሆን በደቡብ ኦሞ ህዝብ ላይ ሲቀልዱበት ተመልክቸ ይህን አጭር መልእክት ልፅፍላቸዉ ወደድኩ፡፡በእኔ እይታ ለማህበረሰቡ የተቆረቆራችሁት Human Right Watch በህዝቡ ዘንድ እያደረሳችሁት ያለዉን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስተባበል ፈልጋችሁ እንጂ የማህበረሰቡ ችግር አሳስቧችሁ አይደለም ፡፡ የማህበረሰቡ ማህበራዊ፡ኢኮኖሚያዊ፡ ፓለቲካዊና ሰነ ልቦናዊ ችግር አሳስቧችሁ ከሆነ ለምትጠየቁት መልስ እየተንገሸገሻችሁ መልስ የምትሰጡት ማሰብ ጀምራችኋል ብየ ትርጉም ልስጠዉ ግን አይመስለኝም ለፓለቲካ ጠቀሚታ ይመስለኛል፡፡ ግን እስከመቸ ነዉ በህዝብ ላይ የምትቀልዱት ?…….. እስኪ ልጠይቃችሁ መልስ ካላችሁ?

ከተለያዩ ክልሎች የተሰበሰቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች አዋሽ አርባ በሚባል ቦታ መታሰራቸው ታወቀ

ሚያዝያ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፉት ሁለት ሳምንታት በውዴታና በግዴታ ከተለያዩ ክልሎች የተሰበሰቡ ወጣቶች አዋሽ አርባ አካባቢ በሚገኝ ካምፕ ውስጥ መታሰራቸውን አምለጠው የመጡ ወጣቶች ለኢሳት ተናግረዋል።
አንድ ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ ወጣት “በመጀመሪያ የወረዳው ባለስልጣናት ለስብሰባ ጠርተውን መንጃ ፈቃድና ልዩ ልዩ ስልጠና ስለምንሰጥ ከነገ ጀምሮ ተነሱ አሉን። እኔና 50 የምንሆን ጓደኞቼ በማግስቱ አዋሽ አርባ በሚባል ቦታ ተወሰድን። ከዚያ እንደደረስን ጸጉራችሁን
ተላጩ ተባልን። 1 ኪሎ ሜትር ርቆ በሚገኝ ሌላ ካምፕ እንደምንወሰድ ተነገረን። እስር ቤት መሆኑን ያወቅነው በሁዋላ ነው። ከተለያዩ ክልሎች የተሰባሰቡ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች አሉ። ከካምፕ ለማምለጥ ሲሞክሩ ውሃ የወሰዳቸው ወጣቶች አሉ።
ከእስረኞች መካከል ተማሪዎችም አሉበት” ብሎአል።
ከምርጫው ጋር በተያያዘ ረብሻ ሊፈጥሩ ይችላሉ ተብለን መታሰራችንን ያወቅነው በሁዋላ ነው የሚለው ወጣቱ፣ ከአካባቢው ጠፍተው የሚመጡ ወጣቶችን ለማደን እንቅስቃሴ በመጀመሩ ለመደበቅ መገደዱን ገልጿል።
በክልሎች ወጣቶች ለስልጠና በሚል ሰበብ የሚያዙ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ግን አብዛኞቹ ወጣቶች የተያዙት በሃይል ነው።


አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከውህደቱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን አርበኛ ታጋዮች ከትናንት በፊት እሁድ ግንቦት 2 2007 ዓ.ም ደማቅና ታሪካዊ በሆነ ስነ-ስርዓት አስመረቀ፡፡

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከውህደቱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን አርበኛ ታጋዮች ከትናንት በፊት እሁድ ግንቦት 2 2007 ዓ.ም ደማቅና ታሪካዊ በሆነ ስነ-ስርዓት አስመረቀ፡፡


እነዚህ በርካታ ቁጥር ያላቸው የመጀመሪያ ዙር ተመራቂ አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ተከታታይ ወራት የተሰጣቸውን የፖለቲካ፣ የወታደራዊ እና እንዲሁም የመረጃና ደህንነት ስፋትና ጥልቀት ያላቸውን ትምህርቶች በመውሰድ በብቃት የተወጡና በተግባር የተፈተኑ መሆናቸውን የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ታጋይ ተስፋሁን ተገኘ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ገልፀዋል፡፡

ወጣት ስንታየሁ ቸኮል ተፈረደበት



በህወሃት/ኢህአዴግ ትእዛዝ እና በምርጫ ቦርድ አስፈፃሚነት የፈረሰው አንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን የወጣቶች ጉዳይ ሀላፊ እንዲሁም አንድነት ለህገወጦች ከተሰጠ በኋላ አሁን የወያኔ እግር እሳት ወደሆነው ሰማያዊ ፓርቲ የተቀላቀለው ወጣት ስንታየሁ ቸኮል መንግስት በISIS በግፍ የተጨፉትን ወገኖች ለማሰብ እና አረመኔውን ቡድን ለማውገዝ በተጠራው ሰልፍ ላይ በመገኘቱ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ካዋለው በኋላ በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቀርቦ የሀሰት ምስክሮች ተሰምተው በ6 ወር እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል። ስንታየሁ ቸኮል የገዢው ፓርቲ በትር ሲያርፍበት ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በዚህም ምክንያት ባለቤቱ እና ሁለት ልጆቹ ችግር ላይ እንደወደቁ ለማወቅ ተችሏል።

Monday, May 11, 2015

በጋምቤላ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት ሰዎች ተገደሉ

ሚያዝያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጋምቤላ እና በደቡብ ክልል አዋሳኝ ከተሞች የሚታየው የጸጥታ ሁኔታ እየተበላሸ መሄዱን ተከትሎ ዜጎች እየተፈናቀሉና እየተገደሉ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።
ከሁለት ቀን በፊት ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በጎደሬ ወረዳ በየሪ ቀበሌ በፈጸሙት ጥቃት 6 ሰዎች ሲገደሉ አንድ ሰው ደግሞ በጽኑ ቆስሎ ሆስፒታል ገብቷል። ሌሎች ወገኖች ደግሞ የማቾች ቁጥር 7 ነው ይላሉ። ይህንን ተከትሎ ዛሬ በሚጤ ከተማ የተቃውሞ
ሰልፍ የተካሄደ ሲሆን፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ካልመጡ በስተቀር የቀብር ስነስርአት አንፈጽምም ብለዋል።
የተቃውሞ ሰልፉ ነገም እንደሚቀጥል የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ ግጭቱ እየተባባሰ ሲሄድ መንግስት ከዳር ቆሞ እያየ ነው በማለት ይወቅሳሉ። ግችቱን ተከትሎ በርካታ ዜጎች እየተፈናቀሉ ወደ ከተሞች በመፍለስ ላይ መሆናቸውንም ነዋሪዎች ይናገራሉ።
ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ በቴፒና አካባቢዋ ያለው ግጭት ተባብሶ በመቀጠሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ስጋት ላይ መውደቃቸውንም ተናግረዋል። ዛሬ በከተማዋ ውስጥ የጥይት ድምጽ ይሰማ ነበር የሚሉት ነዋሪዎች፣ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሸኮ መዠንገር ነዋሪዎች እየፈለሱ
ወደ ቴፒ ከተማ በመግባት ላይ መሆናቸውን ይገልጻሉ።
በአካባቢው የሚታየውን የእርሻ ቦታ ለመቆጣጠር ሲባል ግጭቶች ሆን ተብሎ እንደሚቀሰቀሱን የሚገልጹት ነዋሪዎች፣ በተለይም ጡረታ ወጡ ከፍተኛ የህወሃት የጦር መኮንኖች ሰፋፊ የእርሻ ቦታዎችን እየወሰዱ የአካባቢው ተወላጆች ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ማድረጋቸው
ግጭቱን አባብሶታል።
ባለፈው አመት በዚሁ አካባቢ በተፈጠረ ግጭት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ፣ የመንግስት አቃቢ ህግ ለግችቱ መንስኤ ናቸው ባላቸው የአካባቢው ተወላጆች ላይ በከፈተው ክስ 75 ሰዎች መገደላቸውን ገልጿል።
ግጭቱን አስነስተዋል በሚል ከ30 በላይ የአካባቢው ባለስልጣናት ቢታሰሩም፣ ግጭቱ ግን ሊቆም አልቻለም።


የተረጋጋ የትምህርት ፖሊሲ አለመኖር ወጣቱን ተስፋአልባ እንዲሆን አድርጎታል ተባለ፡፡

ሚያዝያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጅማ ዩኒቨርስቲ ሰሞኑ በተደረገ አውደጥናት ላይ ፣ በየዓመቱ በየጊዜው የሚቀያየረው የትምህርት ፖሊሲ ርእይ ያለው ወጣት እንዳይፈጠር ማድረጉ ተገልጿል ፡፡ ሀገሪቱ ወጥ የሆነ የትምህርት ፖሊሲ ይዛ ባለመማራቷ
ችግሩ መፈጠሩንም ምሁራን ተናግረዋል።
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ማምጣት የቻሉ ብዙ ተማሪዎች በምደባ ከፍላጐታቸው የራቀ ትምህርት እንዲያጠኑ በመደረጉ በአመት ከ12 ሺ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በውጤት መበላሸት ይባረራሉ፡፡
እየከሸፈ ባለው የትምህርት ፖሊሲ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ቅበላ 70 በ 30 ማለትም 70 በመቶ ተማሪዎች ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፎችን እንዲያጠኑ 30 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ የማኅበራዊ ሳይንስ ዘርፎችን እንዲያጠኑ ከተደረገ በኋላም
ተማሪዎች ባላሰቡት የትምህርት ክፍል መገኘታቸው ችግሩን አባብሶታል።
የተማሪዎችን ፍላጐት አለመጠበቅ ብቻ ሳይሆን እየተመደቡ ያሉት ተማሪዎች ስሙን እንኳ ሰምተውት በማያውቁት የትምህርት መስክ ወይም ዲፓርትመንት መሆኑ፣ ለውዝግብ መነሻና ለዲፓርትመንቶች መዘጋት ምክንያት ሆኗል።
ከ2001 -2007 ዓ.ም ባሉት አመታት በቀደምት ዩኒቨርስቲዎች 63 አይነት የትምህርት መስኮች ተከፍተው ከሀገሪቱ የስራ ቦታ ፍላጎት ጋር ባለመጣጣማቸው ተዘግተዋል፡፡
በኮርስ ስም ሳይቀር የትምህርት ክፍል ወይም ዲፓርትመንት የሚከፍቱ ዩኒቨርስቲዎች መፈጠራቸው በውይይቱ ወቅት ተነስቷል፡፡ ጅማ ፣ መቀሌ ፣ ባህርዳር እና ሀዋሳ ዩኒቨርስቲዎች በየጊዜው አዳዲስ የትምህርት ክፍሎችን ከፍተው የሚዘጉ ተቋማት ናቸው ተብሎአል፡፡
ለምሳሌ ያክል ይላሉ ጥናት አቅራቢዎች የመቐለ ዩኒቨርሲቲ አግሪ ካልቸራል ሪሶርስ በአግሪካልቸራል ሪሶርስ ሥር ከሚገኙ ባዮቴክኖሎጂ ፣ሆርቲካልቸር፣ ዋተር ሪሶርስና ኢሪጌሽን ፤ ፊሽሪ ፤ ዋተር ዲቨሎፕመንት እና በአጠቃላይ ከአሥራ አምስት ዲፓርትመንቶች አንዱን
እንኳን የመንግስት ስራ ቀጣሪው ሲቪል ሰርቪስ አያውቀውም ፡፡
በአገሪቱ ያለው የሰው ሃይል ገበያ የሚዘጉና የሚቀጥሉትን ዲፓርትመንቶች ይወስን የሚለው ፖሊሲ ዘንድሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፍልስፍና፣ታሪክና ጂኦግራፊ ዲፓርትመንቶች የተማሪዎች ቁጥር እንዲያሽቆለቁል መደረጉም ተወስቷል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጆርናሊዝም መምህር የሆኑት ዶ/ር አብዲሳ ‹‹ለተማሪዎች እያስተላለፍን ያለነው የገበያን የዋጋ እሴት ነው፡፡የሰው ልጅ በዕውቀት የመበልፀግና ምሉዕ የመሆን ነገር ዋጋ አልተሰጠውም፡፡ የሚጠየቀው ሥርዓተ ትምህርቱ በገበያ ዋጋ ስንት
ያወጣል? ተብሎነው›› ሲሉ ትችት አቅርበዋል።
የቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አቶ ወንድወሰን ታምራት 70 በ 30 የሚለውን የትምህርት ፖሊሲው ጥመርታ በየግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተፈፃሚ ማድረግ እንደማይቻል ተናግረዋል።
የግል ተቋማቱ ገንዘባቸውን ከፍለው ምናልባትም ሙያቸውን ለማዳበር ማጥናት የሚፈልጉትን የወሰኑ ተማሪዎችን የሚያስተናግዱ በመሆናቸው ፖሊሲውን ተፈጻሚ ማድረግ አይቻልም።
‹‹ተማሪዎቹ በገንዘባቸው የሚያዙ እንደመሆናቸው የምመርጥልህን ነው የምትማረው ቢባሉ ነገሩ የሚያስኬድ አይሆንም፡፡ በጥመርታው መሠረት 70% በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተማሪዎችን እንቀበል ብለን በሰው ኃይል በሌላም በሌላም ብንዘጋጅ በዝግጅታችን
መሠረት ተማሪዎች ባይመጡ ትልቅ ኪሳራ ይፈጠራ ሲሉ አክለዋል።
በ2011/ 2012 ብቻ 400 የከፍተኛ ትምህርት ተቌማት መምህራን ወደ ውጭ ሐገር ለትምህርት ሂደው በተለያየ ምክንያት ጥገኝነት ጠይቀው በዚያው ቀርተዋል።
ጅማ፣ መቀሌ እና ባህርዳር ዩኒቨርስቲዎች በምሁራን ፍልሰት ቀዳሚውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ 673 ከፍተኛ ልምድ ያላቸው መምህራንም ስራቸውን ጥለው ወጥተዋል።
በቂ ክፍያ ያለመኖር፣ የፖለቲካ ጫናዎች መበራከት፣ከትምህርት ጥራት ይልቅ ለትምህርት ሺፋን ትኩረት መስጠት፤ መምህራን ያለ እምነታቸው በግዳጅ የሚፈጽማቸው ስራዎች መበራከት፤ ለመምህራን ፍልሰት በምክንያትነት ይጠቀሳሉ።


በአማራ ክልል በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች የሲሚንቶ እጥረቱ ተባብሶ መቀጠሉን ነዋሪዎች ገለጹ፡፡

ሚያዝያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፉት ሁለት ወራት ጀምሮ በሲሚንቶ እጥረት ግንባታዎች እንዲቋረጡ መደረጉን በዘርፉ የተሰማሩ ነጋዴዎችና በግንባታ ላይ የሚገኙ የህብረተሰቡ ክፍሎች ለዘጋቢያችን አስታውቀዋል፡፡
ችግሩ የህወሃቱ ንብረት በሆነው መሰቦ ስሚንቶና የሼክ አላሙዲን ንብረት በሆነው ደርባን ስሚንቶ መካከል ባለው ውዝግብ የተፈጠረ ነው ይላሉ ነጋዴዎች። በዚህም የተነሳ ህብረተሰቡ ለአንድ ኩንታል ሲሚንቶ ከ80 እስከ 100 ብር ተጨማሪ ክፍያ እንዲከፍል
እየተደረገ ነው።
በባህርዳር ከተማ በሲሚንቶ ንግድ ስራ ተሰማርቶ ለረዢም ጊዜ የሰራው ወጣት ሱሌይማን አሊ ፤ በአማራ ክልልና በመላው ኢትዮጵያ ለረዢም ጊዜ ተጽኖ ፈጥሮ የነበረውን የመሶቦ ሲሚንቶ ዋጋ የደርባን ሲሚንቶ ፋብሪካ ምርት እንዲቀንስ አድርጎት ነበር ይላል።
ገዢው ፓርቲ ጥንታዊው የሙገር ሲሚንቶ ምርት ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ እንዳይገባ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ የውስጥ ትዕዛዝ መከልከሉ ያወሳው ነጋዴ ሱሌይማን ፣ በዚህ እገዳ ምክንያት በጥራቱ የታወቀውን የሙገር ምርት ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ
በሚያጓጉዙ መኪኖች ላይ ኮንትሮባንድ እቃ እንደጫኑ ተቆጥሮ እንዲቀጡ የሚደረግ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎ ህብረተሰቡ ሳይወድ በግድ የመሶቦ ምርቶችን እንዲገዛ ተገዶ ቆይቷል ብሎአል።
ከሁለት ወር በፊት ለመሶቦም ሆነ ደርባን ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ገንዘብ ገቢ አድርገው ምርቶቹ እንዲላኩላቸው ቢጠባበቁም መልስ ማጣታቸውን ነጋዴዎች ይናገራሉ።


Friday, May 8, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ አዲስ ድህረ ገጽ መልቀቁን ከድርጅቱ ጽ/ቤት ለማወቅ ተችሎል::

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ ባለፉት ወራቶች ውህደት ከፈጸመ በሆላ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተስፋ የጣሉበት ሲሆን፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ በአካባቢው መፈጠሩና ውጥረት መከሰቱ የሚታወቅ ሲሆን ብዙዎቹ የድል ሽታ መፍጠሩን ይስማሙበታል። ወያኔ በምንም ታምር በሰላማዊ መንገድ ከስልጣን እንደማይወርድ እና በስልጣኑ የመጡበትን ሁሉ መግደል ወይም ማሰር እና ማሰደድ ላይ ያተኮረው የህወሃት ድርጅትን ብቸኛው መንገድ በሁለገብ ትግል ማስወገድ ተገቢ መሆኑን አሁን ያለው ሁኔታ የሚመሰክር መሆኑን አስተያየት ሰጪዎች ይስማሙበታል።

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ ይህን ትግል ከግብ ለማድረስ የጀመረውን እንቅስቃሴ በማጠነከር ረገድ ስራውን እየሰራ ሲሆን በቅርቡ በርካታ ወጣቶችና የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ድርጅቱን መቀላቀላቸው ይታወቃል።
አዲሱ ድህረ ገጽ www.patriotg7.org ነው። እለታዊ ዜናዎችንና መረጃዎችን ዌብሳይቱን በመጎብኘት ሊያገኙ ይችላሉ።

በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን ከፍተኛ ግጭት ተከስተ

ለፈው ቅዳሜ ከወልቂጤ ከተማ ወጣ ብላ በምትገኘው አነስተኛዋ የዳርጌ ከተማ በፖሊሶች እና በአካባቢው ነዋሪዎች መካከል የተነሳው ግጭት ይህንን ዜና እስከፃፍኩበት ድረስ የቀጠለ ሲሆን በርካቶች ከተማዋን በመልቀቅ ወደወልቂጤ እና ወሊሶ ከተሞች በመሠደድ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአካባቢው ከሚኖር ግለሠብ ለማጣራት እንደሞከርኩት ግጭቱ የተቀሰቀሰው ቅዳሜ በ24/08/2007 ዓ.ም አንድ በአካባቢው በስራ ላይ የተሠማራ ፖሊስ በግብርና የሚተዳደር ግለሠብን በአጋጣሚ በተነሳ ፀብ ምክንያት በጥይት ተኩሶ በመገድሉ ሲሆን ይህንን የተመለከቱት የአካባቢው ነዋሪዎች በስፍራው ለሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ጉዳዩን ለማስረዳት እና ፍትህ ለማግኘት ባቀኑበት ሠዓት የወረዳው ፖሊስ ጣቢያ አስተዳዳሪ የአካባቢውን ማህበረሠብ “እናንተ መንግስቱ ሐይለማርያም አምጥቶ የኛ መሬት ላይ ያሠፈራሁ ናችሁ ፀጥ ብላችሁ የማትቀመጡ ካልሆነ ለቃችሁ ወደመጣችሁበት መሄድ ትችላላችሁ” በማለታቸው የተነሳ ነው፡፡ ይህንን የሠሙ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፖሊሶች ጋር በተፈጠረ እሰጣ ገባ ምክንያት ግጭቱ የተከሠተ ሲሆን ግጭቱ ተባብሶ ማክሠኞ እለት ተጨማሪ አንድ የዳርጌ ነዋሪ ህይወቱ ሲያልፍ የአንድ ፖሊስ ህይወትም እንዳለፈ ለማወቅ ተችሏል፡፡


ኢትዮዽያዊናን ያሳገቱ ካይሮ በሚገኘዉ የወያኔ ኢምባሲ የሚሰሩ የህወሀት አባል መሆናቸዉ ታወቀ

ኢትዮዽያዊናን ያሳገቱ ካይሮ በሚገኘዉ የወያኔ ኢምባሲ የሚሰሩ የህወሀት አባል መሆናቸዉ ታወቀ። በሰዎች ዝዉዉር ቢሊየነር የሆነዉ የህወሀት አባል በጣልያን መንግስት እየታደነ ነዉ።
ቀደም ሲል በኢሳት የድረሱልን ጥሪ ካቀረቡ ወገኖች ዉስጥ ለእርድ ታግተዉ የነበሩ 27 ወንድሞቻችን በኢሳት ልሳንነት የግብጽ መንግስት በተናዳፊ ያየር ሀይሉ ታሪካዊ ጀብድ ሰርቶ በፕሬዝዳንት አልሲሲ በሚመራ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ይፋዊ አቀባበል ተደርጎላቸዉ በክብር ግብጽ የገቡ ሲሆን ኢሳት ወገኖቻችንን የመታደግ የህዝብ ግንኙነትና የዲፕሎማሲያዊ ስራ ማካሄዱ አይታበይም።የታላቋ ግብጽ ታላቁ መሪ ፕሬዘዳንት አብዱልፈታ አል ሲሲ ጀግናዉ የግብጽ ሰራዊት በሊቢያ በአሸባሪዉ አይሴአይሴ የሰሜን አፍሪካ ክንፍ ታግተዉ ሞታቸዉን ሲጠባበቁ የነበሩትን 27 ኢትዩጵያዊያንን ከሞት መታደግ ለመንግስት አልባዋ ሀገራችን በቃላት የማይገለጽ ፣ታሪክ ሊፍቀዉናሊሽረዉ የማይችል የክፍለዘመኑ ከባድ ዉለታ አድርጎታል ።


በሌላ በኩል በደላላነት ወገኖቻችንን በግብጽና በሊቢያ ለእንደዚህ አይነት ዘግናኝ የሞት አደጋ የሚዳርጉ ደላሎች ግብጽ ኢምባሲ ዉስጥ የሚሰሩ የትግሬ ጉጅሌዎች መሆናቸዉ ታዉቋል።የወገኖቻንን ደም እየጠጡ በሁለት አመት ብቻ ቢሊየነር የሆነዉ የህወሀቱ ኤርሚያስ ግርማይ በጣሊያን መንግስት በተፈላጊ ወንጀለኛ ጥቁር መዝገብ(Most Wanted Balcklist) ላይ እንደሚገኝ አጃንፍራንስ ፕሬስ(AFP) ዘግቧል።ይህንን ዘራፊ የማፊያ ቡድን በዚሁ ሳይወሰን ሴት እህቶቻችንን በሙስና ዘንዶዋ አዜብ መስፍን ካምፓኒ በኩል የዉስጥ አካላቸዉ እየወጣ የሚሸጥበት ያለም ትልቁ የወንጀል እዝ ጋር ህብረት እንዳለዉ ይፋ ከሆነ ሰነባብቷል።ለዚህ ሁሉ ዉርደታችን ከጫካ በመጣ የደደቢት ወሮበሎች እጅ ላይ መውደቃችን ሲሆን አሁን ግን የፍርድ ቀን ቀርቧል ። የተዳፈነዉ ብሶታችን ሊፈነዳና ነጻነታችንን ልንጎናጸፍ በምንችልበት አስራ አንደኛዉ ስዓት ላይ ነን።ሁላችንም ለፊሽካዋን ድምጽ ነቅተን እንጠብቅ!!!

ድል ለጭቁኑ የኢትዮዽያ ህዝብ!!

Thursday, May 7, 2015

የቁልቁለቱን ጉዞ እናስቁም፤ ውርደት ይብቃን!!!

የህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።

አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።

ሶስተኛ ዙር የፌዴራል ፖሊሶች ግምገማ ሊካሄድ መሆኑ ተጠቆመ:: Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) 

ከዚህ ቀደም በሲቭል ደህንነት ሲያገለግሉ የነበሩ እና ካለፉት ሁለት አመታት ጀምሮ ወታደራዊ ካኪ በመልበስ ከወታደሩ ጋር ተመሳስለው በየሰራዊት እዝ ውስጥ የተሰገሰጉ ሰላዮች/ወታደራዊ ደህንነቶች ለስብሰባ አዲስ አበባ መክተማቸውን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል::

የሰራዊቱን አባላት እንዲሰልሉ እና በአባላቱ መካከል የጋራ አንድነት እንዳይፈጠር የመከፋፈል መርዝ እንዲረጩ በወታደራዊ ደህንነት ትጥቅ የተሰገሰጉ ሰላዮች የተመደቡበት ስራ አለመሳካቱ እንዲሁም ይሰራዊቱ አባላት በቡድን እየሆኑ ሰራዊቱን ጥለው መኮብለላቸው የሰላዮቹ ተልእኮ አለመስመሩን ተከትሎ የተጠራ ስብሰባ ከፍተኛ ፍጭት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል::ስብሰባውን ይመራሉ ተብለው የሚጠበቁት አቶ ኢሳያስ ወ/ጊ እና ብ/ጄ ገብረኪዳን ሲሆኑ ጎን ለጎን ከየእዙ የትወጣጡ የሕወሓት ወታደራዊ መኮንኖች ለስብሰባ የተጠሩትን ሰላዮች ይገመግማሉ ተብሎ ይጠበቃል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሶስተኛው ዙር የፌዴራል ፖሊሶች ግምገማ እንደሚካሄድ ለተቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ቢሮ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል::ባለፉት ግምገማዎች የተለያዩ የፌደራል ፖሊስ አባላቶች ተገምግምው ለእስር የተዳረጉ በደምወዝ የተቀጡ እና በማስጠንቀቂያ የታለፉ እንደነበሩ ሲታወስ በአሁን ግምገማ ባለፍው ወያነ በጠራውና ጸረ አይሲስ ተብሎ ለፖለቲካ ፎጆታ በዋለ እና በርካቶች በታፈሱበት ፌዴራል ፖሊሶች ባነቡበት ሰልፍ ዙሪያ እና በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚገመገሙ ታውቋል::በአሁኑ ወቅት በታማኝነት እየሰሩ ያሉት የፌዴራል ፖሊስ ካኪ የለበሱ የአግአዚ ወታደሮች እንደሆኑ እና ዋናዎቹ ፌዴራል ፖሊሶች በበላይ ትእዛዞች እየተሰላቹ እንደመጡ ቅርብ የሆኑ ምንጮች በመናገር ላይ ናቸው::


በመቶዎች የሚቆጠሩ የአዲስ አበባ ወጣቶች ታፍነው ወዳልታወቀ ስፍራ ተወሰዱ

ሚያዝያ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ተይዘው በወረዳ 5 ቀበሌ 08/09 በሚገኝ እስር ቤት ውስጥ እንዲቆዩ የተደረጉ ወጣቶች ዛሬ ጧት ላይ በሶስት አይሲዙ መኪኖች ተጭነው ወዳልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸውን የአይን እማኞች ተናግረዋል።

ወጣቶቹ በቅርቡ በአዲስ አበባ የተደረገውን ተቃውሞ ተከትሎ ከየስፍራው የተሰባሰቡ ሲሆን፣ ከምርጫው ጋር በተያያዘ ረብሻ ሊያስነሱ ይችላሉ በሚል በአደገኛ ቦዘኔ ስም የተያዙ ናቸው። ብዙዎች ሌሊት ሌሊት በሚደርስባቸው ድብደባ ክፉኛ ተጎድተዋል።

የአይን እማኞች እንደሚሉት እስረኞቹ ኩላሊታቸው የሚገኝበት የሰውነት ክፍላቸው አካባቢ በጫማ እየተረገጡ፣ በዱላ እየተደበደቡ እንዲሁም ውሃና ምግብ እየተከለከሉ “ተቃውሞውን ያነሳነው በሰማያዊ ፓርቲ ግፊት ነው” ብለው  እንዲመሰክሩ ጫና ተድርጎባቸዋል። የአዲስ አበባ እስር ቤቶች ሌሊት በሚታፈኑ ወጣቶች እየሞሉ መሆኑን የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ።


አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የተያዙበት ሁኔታ ለህይወታቸው አስጊ ነው ተባለ

ሚያዝያ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በከፍተኛ ህመም በመሰቃየት ላይ ሲሆኑ እስካሁን በዶክተሮች ለመጎብኘት አልቻሉም።

አያያያዛቸው የከፋ መሆኑን በማስመልከት የእንግሊዝ መንግስት አስቸኳይ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መጻፉንም ምንጮቻችን ገልጸዋል።

አቶ አንዳርጋቸው ያለፉትን ተከታታይ ወራት ጸሃይ የሚባል ነገር ሳያዩ ጨለማ ቤት ተዘግቶባቸው አሳልፈዋል; ከህመማቸው ጋር በተያያዘም ምግብ መመገብ በእጅጉ ቀንሰዋል።

በከፍተኛ የስነ ልቦና ጫና ውስጥ የሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው፣ አያያዛቸው አስከፊ እንደሆነ በቅርቡ ለጎበኙዋቸው የእንግሊዝ አምባሳደር  መናገራቸውን ምንጮች ገልጸዋል።  ይህንን ተከትሎም  የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ጠንከር ያለ ደብዳቤ  መጻፉን የአዲስ አበባ ምንጮች ገልጸዋል። የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ በአፋጣኝ የማይለወጥ ከሆነ፣ በህይወታቸው ላይ ያልተጠበቀ አደጋ ሊፈጠር እንደሚችል  ያስጠነቀቁት የእንግሊዝ ባለስልጣናት፣ አቶ አንዳርጋቸው የኮንሱላር ድጋፍ እንዲያገኙ፣

በመደበኛ እስር ቤት ውስጥ እንዲታሰሩና በጠያቂዎች እንዲጎበኙ ፣ ሃኪሞች እንዲያዩዋቸውና ሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር  ደብዳቤ መጻፋቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

ገዢው ፓርቲ ከአቶ አንዳርጋቸው የረባ መረጃ ለማግኘት ባለመቻሉ_የስነ ልቦና ጫና በማሳረፍና ህክምና በመከልከል ለመጉዳት ማሳቡን ምንጮች ገልጸዋል።

የእንግሊዝ ባለስልጣናት በሂደት ስለሚወስዱት እርምጃ ግልጽ ባያደርጉም፣ ጉዳዩን በቀላሉ እንደማያዩት ለኢህአዴግ ሹሞች እንደገለጹላቸው ታውቋል።

አቶ አንዳርጋቸው በየመን የጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ለኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች ተላልፈው ከተሰጡ በሁዋላ፣ ገዢው ፓርቲ ሁለት ጊዜ በቴሌቪዥን አቅርቧቸዋል። ተቆራርጦ የተላለፈውን ቪዲዮ  ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ትችት ሲቀርብብት ቆይቷል።

ኢህአዴግ  አቶ አንዳርጋቸውን ህዝብ ሊጎበኛቸው በሚችል እስር ቤት አለማሰሩና ሰብአዊ መብታቸውን ሁሉ መግፈፉ የገዢውን ፓርቲ የፍርሃትና የበቀል ደረጃ፣ እንዲሁም ራሱ ላወጣው ህግ እንኳን የማይገዛ መሆኑን የሚያሳይ ነው ተብሏል።

ፍ/ቤቱ በ‹‹በሁከትና ብጥብጥ›› ለተጠረጠሩ 17 ሰዎች ዋስትና ሲፈቅድ፣ በሰማያዊ አባላት ላይ ተጨማሪ ቀጠሮ ሰጥቶባቸዋል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስ ሊቢያ በሚገኙ ንጹሃን ኢትዮጵያውያን ላይ የፈጸመውን አሰቃቂ የሽብር ድርጊት ለማውገዝ ጠርቶት በነበረው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ አስነስታችኋል፤ ተካፍላችኋልም›› በሚል ፖሊስ ካሰራቸው ሰዎች መካከል ፍርድ ቤት 17ቱን በ3000 ብር የሰው ዋስ እንዲለቀቁ ሲወስን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ደግሞ ተጨማሪ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ዛሬ ሚያዝያ 28 ቀን 2007 ዓ.ም በቄራ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቀረቡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ሌሎች በዕለቱ የተያዙ ሰዎችን በተመለከተ ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን በሦስት መዝገቦች ስር እንደየተሳትፏቸው አደራጅቻለሁ ማለቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ከአሁን በፊት በሦስተኛው መዝገብ ላይ የተካተቱትን ሙሉ ለሙሉ መልቀቁን መግለጹ ይታወቃል፡፡ በሁለተኛው መዝገብ ላይ የተካተቱት 17 ሰዎች ደግሞ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው በዋስ እንዲወጡ ተወስኗል፡፡
አንደኛው መዝገብ ላይ በእነ ወይንሸት ሞላ መዝገብ 5 ሰዎች የተካተቱ ሲሆን አራቱ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሆኑት ወይንሸት ሞላ፣ ዳንኤል ተስፋዬ፣ ኤርሚያስ ጸጋየ እና ማስተዋል ፈቃዱ ናቸው፡፡ በዚሁ መዝገብ ላይ ፖሊስ የፓርቲው አባል እንደሆነች የሚገልጸው፣ እሷ ግን አባል አለመሆኗን የገለጸች ቤተልሄም አቃለወርቅ ተካትታለች፡፡ በዚሁ በአንደኛው መዝገብ ላይ የተካተቱት 5ቱም ተጠርጣሪዎች ዛሬ በዋለው ችሎት ተጨማሪ 3 ቀናት ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
5ቱም ተጠርጣሪዎች ፖሊስ እስካሁን የተሰጠው የምርመራ ጊዜ በቂ መሆኑንና ቋሚ አድራሻ ያላቸው መሆኑን በመግለጽ የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ፍርድ ቤቱን የጠየቁ ሲሆን፣ ፖሊስ በበኩሉ ተጠርጣሪዎች ምስክሮችን ያሸሹብናል፣ ያስፈራሩብናል በሚል ዋስትናውን ተቃውሟል፡፡ ፖሊስ ዋስትና ሲቃወም ‹‹ተጨማሪ አባላትን መያዝ ይቀረናል›› ሲል የገለጸ ሲሆን፣ ‹አባላት› ሲል ምን ለማለት እንደፈለገ ለፍርድ ቤቱ ግልጽ አላደረገም፡፡
በሌላ በኩል አሁን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች እንደገለጹት ጠዋት ፍርድ ቤት የ3000 ብር የሰው ዋስ የፈቀደላቸው 17 ሰዎች በፖሊስ ይግባኝ እንደተጠየቀባቸውና በአሁኑ ሰዓት ወደ ፍርድ ቤት መወሰዳቸው ታውቋል፡፡


Wednesday, May 6, 2015

በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ማየሉ ተገለፀ፡፡

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ
ዜና
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ማየሉ ተገለፀ፡፡
በአየር መንገዱ ውስጥ ጎሳንና የፖለቲካ አመለካከትን መሰረት ያደረገ የስራ መደብ፣ የስልጣን ድልድልና ትቅማጥቅም በመኖሩ፤ ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ በመንሰራፋቱ፤ የአንድ ቋንቋ ተናጋሪዎች ብቻ የኢኮኖሚና ስልጣን የበላይነት በመግነኑ፤ እና ፍህታዊ የሆነ አስተዳደር ፈፅሞ በመጥፋቱ ምክንያት ሰራተኞች በተለያዩ ጥያቄዎች የአመራር አካላትን ማፋጠጥ በመጀመራቸው ነው የሰፈነው ከፍተኛ ውጥረት ሊከሰት የቻለው፡፡
ከዚህ ቀደም ግለሰቦች በፖለቲካ አመለካከታቸው ልዩነት ምክንያት ብቻ ከስራ ታግደዋል፤ አሁንም በርካቶች ከፍተኛ መንገላታትና የመብት ረገጣ እየደረሰባቸው እንዳለ ከውስጥ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
በህወሓታዊዩ ተወልደ ወ/መድህን የሚመራው አየር መንገድ ልክ እንደ ኤፈርት ሁሉ የህወሓት የግል ድርጅት እየሆነ መምጣቱን ብዙዎች ሠራተኞች ይመሰክራሉ፡፡
ይህ የአየር መንገዱ አመራር አካል በሰራተኞች ላይ የሚፈፅመው ግፍና በደል ያንገፈገፈው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድን አበራ አውሮፕላን ይዞ በመጥፋት ስዊዘርላንድ-ጄኔቭ አሳርፎ ጥገኝነት በጠየቁና ተቃውሞውን ለዓለም ማሰማቱ የሁሉም የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡

በቅርቡ በተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የታሰሩት ወጣቶች በሃሰት እንዲመሰክሩ ጫና እየተደረገባቸው ነው

ሚያዝያ ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያና ደቡብ አፍሪካ በግፍ የተገደሉ ኢትዮጵያውያንን ለመዘከርና ቁጣቸውን ለመግለጽ ገዢው ፓርቲ በጠራው ሰልፍ ላይ የተገኙ ወጣቶች መንግስትን ሰድባችሁዋል በሚል ታፍሰው ከታሰሩ በሁዋላ፣ “ተቃውሞውን
ያስነሱት በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ናቸው” ብላችሁ ካልመሰከራችሁ አትለቀቁም መባላቸውን የእስረኞች ቤተሰቦች ገልጸዋል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ቤተሰቦች ለኢሳት እንደተናገሩት፣ ወጣቶች ማታ ማታ በደህንነት ሃይሎች እየተጠሩ በታሰሩ የሰማያዊ አባላት ላይ እንዲመሰክሩ ጫና እየተደረገባቸው ነው።
ወላጆች ልጆቻቸው በንጹሃን ላይ በሃሰት እንዳይመሰክሩ እንደመከሩዋቸው ተናግረዋል። ህዝቡ በኑሮውና በፍትህ እጦት ተማሮ በራሱ ጊዜ ተቃውሞውን ቢያሰማም፣ ገዢው ፓርቲ ተቃውሞውን ያስነሳው ሰማያዊ ፓርቲ ነው በማለት እየወነጀለ ነው። የገዢውን ፓርቲ ውንጀላ
አባሎቹ ሳይቀሩ አልተቀበሉትም።


Monday, May 4, 2015

የኢህአዴግ ከፍተኛ ካድሬዎች በድርጅታቸው ግራ ተጋብተዋል፡፡

ሚያዝያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያንን ለመዘከር የወጣው ህዝብ ተቃውሞውን ወደ ኢህአዴግ መንግስት ካዞረ በሁዋላ፣ ገዢው ፓርቲ ተቃውሞውን ያስነሳው በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ የሚታገለው ሰማያዊ ፓርቲ ነው በማለት የከፈተው ሰፊና አሰልቺ ፕሮፖጋንዳ የህዝቡን አመለካከት ሊቀይር አለመቻሉ ከፍተኛ ካድሬዎችን ስጋት ላይ ጥሎአቸዋል፡፡

በመስቀል አደባባይ የታየውን ህዝባዊ ቁጣ ሰማያዊ ፓርቲ የቀሰቀሰው የመንደር ሁከት ለማስመሰል በስሩ በሚገኙ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተደጋጋሚ ፕሮፖጋንዳ የሰራ ቢሆንም ፣ ፕሮፓጋንዳው ሕዝቡን ብቻ ሳይሆን የራሱን አባሎች ማሳመን አለመቻሉ ከፍተኛ ካድሬዎችን ድንጋጤ ላይ ጥሎአቸዋል። በአዲስአበባ አስተዳደር በተለያዩ የመንግስት ቢሮዎች ይህንኑ የሕዝብ ተቃውሞ በማስመልከት ሰማያዊ ፓርቲ ያቀነባበረው መሆኑን በመግለጽ ሁኔታውን ለማውገዝ ታስቦ ሰሞኑን ተከታታይ ስብሰባዎች የተካሄዱ ቢሆንም አጥጋቢ ውጤት ሊገኝባቸው አልቻለም፡፡

Saturday, May 2, 2015

ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ፕሬሱን ማዳከሙን ቀጥሏል

ሚያዝያ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ነጻ ፕሬሱን በማዋከብ፣ በማሳደድ፣ በማሰር ከሚያደርገው ቀጥተኛ ጥቃት በተጨማሪ ስልታዊ ጥቃትን በተጠናከረ መልኩ ስራ ላይ እያዋለ ነው።

በነገው ዕለት የሚከበረው የዓለም የፕሬስ ቀን በኢትዮጵያ ታስቦ የሚውለው የፕሬሱ ስልታዊ አፈና በተጠናከረበት ወቅት መሆኑም ያነጋገርናቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ምንም ዓይነት ትችትና የተለየ አስተያየት ለመስማት  ዝግጁ ያልሆነው የኢህአዴግ መንግስት ከእስርና ከስደት የተረፉ፣ ጥቂት በሕትመት ላይ የሚገኙ የግሉ ፕሬሶችን ከብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት ጋር በመቀናጀት ጋዜጦች መውጣት ካለባቸው ቀናት እስከሶስት ቀናት

Friday, May 1, 2015

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ምክር ቤት የኢሳትን የመረጃ ጥንካሬ ገመገመ

ሚያዝያ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአቶ ሬድዋን ሁሴን የሚመራው የኮምኒኬሽን ምክር ቤት የኢሳት አባሎችን እና ቁልፍ የግንቦት ሰባት አመራሮችን የግል ላፕቶፓቸውን እና ለመረጃ መሰብሰብ የሚጠቀሙባቸውን ስልኮች ለማግኘት የሚያስችል እቅድ ማውጣቱ ታውቋል።
በግምገማው ወቅት ኢሳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ መሆኑ ተገልጿል። ኢሳት በመንግስት ላይ እየሰነዘረ ያለው ጥቃት ጉልህ ለውጥ የማምጣት አቅም ፈጥሯል ሲል በውይይቱን ላይ ተነስቷል፡ የኢሳት የማህበራዊ ሚዲያ እና የቴሌቪዥን ስርጭት ሀገሪቱን በማወኩ ሂደት በፕሮፓጋንዳ ስራው መንግስትን ቀድሟል የሚለው ግምገማ፣ ይህም በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት በማግኝት ተፅኖ እየፈጠረ ነው ብሎአል።
የኢሳትን እና የግንቦት ሰባት አመራሮች የአባላቱን የግል ስልክ ፤ ላፕቶፕ ፤ የሚስጢር ኢሜል አድራሻ ማግኝትን ተቀዳሚ አላማው ያደረገው ወይይት ፤ በኢንባሲ በኩል ያሉ ወኪሎች ቀጣይ ስራቸው የኢሳትን ጋዜጠኞች ላፕቶፖችና ስልኮች ማግኘት እንዲሆን ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
ውይይቱን ለመተግበር የተዘረጋውን እቅድ ኢሳት በአጽኖት የሚከታተለው ይሆናል። መረጃዎችን ለኢሳት የሚልኩ ኢትዮጵያውያን ደህንነታቸውን በተመለከተ በኢሳት በኩል አስፈላጊው ጥንቃቄ የሚደረግ በመሆኑ ምንም ስጋት እንዳይገባቸው ድርጅቱ አስታውቋል። መንግስት ኢሳትን ለማፈን ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ቢያደርግም እስካሁን ሊያስቆመው አልቻለም። ኢሳት ካለፉት ሶስት ሳምንታት ጀምሮ በተጠናከ ሁኔታና አብዛኛው ህዝብ ሊያየው በሚችለው በናይል ሳት ስርጭቱን በማስተላለፍ ላይ ነው።


አውነቱ ይውጣ! ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

ሴቶችን በወንዶች ፊት፣ ወንዶችን በሴቶች ፊት ልብስ እያስወለቁ የአካላቸውን ክፍሎች ሁሉ ለማየት የሚያስችል አንቅስቃሴ አንዲሠሩ ማስገደድ በሽተኞችን ያስደስታል፤ የምርመራ ዘዴ ግን አይደለም፤ ውርደት እንዲሰማቸው ከሆነ በወራዶች ሰዎች ፊት የምን መዋረድ አለ? ወራዶች እነሱ ደረጃ ላይ ከእነሱ ጋር ያስተካክላሉ አንጂ አያዋርዱም፤ በሌላ አነጋገር ወራዶች አያዋርዱም፤ ወራዶቹ ደንቆሮዎችም ሆነው ነው እንጂ ልብስ የሚያስወልቁ እነሱ ብቻ አይደሉም፤ ሀኪሞችም ልብስ አስወልቀው፣ አጋድመው በጣታቸውም ሆነ በመሣሪያ የፈለጉትን የአካል ክፍል አንደፈለጉ ያደርጉታል፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ከሚያደርጉት የሀኪሞቹ የሚለየው ሀኪሞቹ ሰዎችን ለማዳን ሲሉ ነው፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ግን የራሳቸውን ሱስ ለማርካት፣ የራሳቸውን ህመም ለማስታገስ ነው፤ ወራዶቹንና ደንቆሮዎቹን ከመለዮአቸው አራቁቻቸዋለሁ!
ከነውር በቃላት ወደነውር በተግባር፣ ያውም በመሥሪያ ቤት! ዱሮ ዱሮ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቲያትር ፊት ለፊት የአንድ ኢጣልያዊ ቡና ቤት ነበር፤ እዚያ ውጭ ተቀምጠን ቡና ስንጠጣ አንዲት ውብ ሴት ወደጸጉር መሥሪያው ቤት ስትመጣ የሁላችንም ዓይኖች እየዘለሉ እስዋ ላይ ዐረፉ፤ ከሦስታችን አንዱ ስለሴትዮዋ የወሲብ ችሎታ በዝርዝር መናገር ሲጀምር ሁለታችን ተያየንና አፈርን፤ ጨዋታው የጣመለት መስሎት ሲቀጥል የሕግ ባለሙያ የሆነ ጓደኛዬ አቋረጠውና ‹‹ስማ! ይህን ጊዜ እናትህ በአንድ ቦታ ስታልፍ አንዱ እንዳንተ ያለ ስለስዋ ችሎታ ያወራ ይሆናል!›› አለው፤ ሊጠጣ ወደአፉ ያስጠጋውን ስኒ ቁጭ አደረገና ተነሥቶ ሄደ፡፡

በሊቢያ ለደረሰብን ውርደት ምላሽ መንግስት የበቀል አርምጃ መውስድ አለበት በማለታቸው የጦር አዛዦች እየታሰሩ ነው

(የምዕራብ እዝ 7ኛ ሜካናይዝድ የሬጅመንት ምክትል አዛዥ ሻለቃ ሙሉአለም ባህርዳር ታስሯል)
ሊቢያ ውስጥ አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን በዜጎች ላይ የተፈፀመውን ግፍ የተሞላበት ግድያ መንግስት ፈጣን ግብረ መልስ መስጠት አለበት በማለት የጠየቁ የሰራዊት አዛዦች እየታሰሩ መሆናቸውን ምንጮች ገለፁ፣የደረሰን መረጃ እንደሚያመልክተው- የምዕራብ እዝ 7ኛ ሜካናይዝድ የሬጅመንት ምክትል አዛዥ ሻለቃ ሙሉአለም የተባለ መኮነን የኢህአዴግ ገዥው መንግስት በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በየመን በኢትዮጵያውያን ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ላለው አስቃቂ ግፍ መንግስት ፈጣን ግብረ መልስ መስጠት አለበት ብሎ ስለጠየቀ ብቻ ፀረ ሰላም ነህ ተብሎ ባህር ዳር መኮድ በተባለ ቦታ እንደታሰረ ምንጮቻችን አስታወቁ፣
ስርዓቱ በአይ ኤስ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ፍላጎት ስለሌለው የዜጎቻችንን ደም መመለስ አለብን የሚል ጥያቄ ለሚያነሱ ሰዎች እንደ ጠላት እያዬ ወደ እስር ቤት እያስገባቸው እንደሚገኝ የገለፀው ይህ መረጃ የመከላከያ ሰራዊትም በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ላለው የሚያሳዝን ተግባር ዋነኛ ተጠያቂው በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ ስርዓት መሆኑን በተደጋጋሚ እየገለፁ እንደሚገኙ ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ ገልጿል፣


በሱዳን በኩል ወደ ውጭ የሚወጡ ዜጎች ቁጥር በአስደንጋጭ ሁኔታ ጨምሯል

ሚያዝያ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመንግስት የጸጥታ ሃይሎች የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በዚህ ሳምንት ብቻ 9 ሺ 405 ወጣቶች ድንበር አቋርጠው ወደ ሱዳን ሲጓዙ በድንበር ጠባቂ ፖሊሶች ተይዘዋል።
ፋሲል የኔአለም ዝርዝሩን ያቀርበዋልበሰሜን ጎንደር ዞን ቆላማ ወረዳዎች በተደረጉ 2 የዳሰሳ ጥናቶች በቀን ከ150-250 በዓመት ደግሞ ከ 54,000 እስከ 90,00 ኢትዮጵያውያን ወደ ሱዳን ይሻገራሉ፡፡ ጥናቱ በመላው አማራ ወይም በመላው አገሪቱ ያለውን
የስደት ቁጥር አይዳስስም።
በዚህ ሳምንት ብቻ ወደ ሱዳን ለመሻገር የሞከሩ 9 ሺ 405 ግለሰቦች በጸጥታ ሃይሎች ሲያዙ፣ የጃን አሞራ ፖሊስ ጽ/ቤት ለኢሳት በላከው መረጃ መሰረት በቁጥጥር ስር የዋሉት ሁሉም ሴቶች ናቸው። ከእነዚህ ሴት ስደተኞች ውስጥ 66 በመቶው ከ18 እስከ 24
እድሜ ያላቸው ሲሆን፣ 32 በመቶው ደግሞ ከ14 አመት በታች ናቸው። ወደ ሱዳን በመፍለስ ከፍተኛውን ቁጥር የያዙት የአርማጭሆ፣ በየዳ፣ ጃናሞራና ወገራ ወረዳዎች ሲሆን፣ በአካባቢው ያለው ድህነት ከሁሉም አካባቢዎች የከፋ ነው፡፡
ስደትን ከድህነ

በኦስትርያ ቬየና ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ (የአብስራ ዳኛቸው)

                           
          ISIS፣ ደቡብ አፍሪካ፣ የመን እና አልሻባብ ወገኖቻችን ላይ እያደረሱ ያለውን በደል በመቃወም ኢትዮጵያዊያን፣ ኤርትራዊያን እና ሌሎች የአፍሪካ አገሮች አንድ ላይ በመሆን ነበር በ 29.04.2015 በቬየና ይህን ሰላማዊ ሰልፍ ያደረግነው። ይህ ሰልፍ ከሾቶንቶር ዩንቨርስቲ አንስቶ መዳረሻውን ስቴፈን ፕላትዝ ነበር። በዚህ ሰልፍ ላይ የተለያዩ መፈክሮች የተሰሙ ሲሆን ከነዚህም መካከል STOP GEWALT GEGEN IMMIGRANTEN, GEGEN MENSCHEN LÖTEN MENSCHEN, ISIS & TPLF ARE TERRORIST THEY KILLED INNOCENT ETHIOPIAN, EU STOP SUPPORTING TPLF, STOP ALSHABAB የሚሉት ይገኙበታል።

          ማንኛውም ህዝብ ከሀገሩ ተሰዶ በባዕድ ሀገር ኑሮውን ለመግፍት የሚገደደው፣ በባህር ላይ ህይወቱን እንዲያጣ የሚደረገው እንዲሁም በአሸባሪዎች አንገት ለመቀላት ምክንያት የሚሆነው በሀገሩ ላይ ያለው የፖለቲካ አለመረጋጋት እና በሀገሩ ላይ በነፃነት መኖር ባለመቻሉ ነው።

በርካታ ወጣቶችን በጨለማ እየታፈሱ ነው

በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን አሰቃቂ አደጋ ተከትሎ ለተቃውሞ የወጡ ኢትዮጵያውያን በፌደራል ፖሊሶች ተደብድበው እንዲታሰሩ በተደረገ ማግስት፣ የኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች የሚገኙ ወጣቶችን በምሽት በማፈን ወደ እስር ቤት እያጋዙ ነው።

የከተማዋ ነዋሪዎች እንደተናገሩት ባለፉት ሶስት ቀናት ብቻ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ተወስደው ታስረዋል መጪውን ምርጫ ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ረብሻ ይነሳል በሚል ፍርሃት ወጣቶችን እያፈነ በማጋዝ ላይ መሆኑን ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ሰዎች ገልጸዋል።

የአራት ኪሎ ወጣቶች ለሁለተኛ ጊዜ ታፈሱ


• ‹‹ከአሁን በኋላ በሽብር እንከሳችኋለን!›› ፖሊስ
አራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ወጣቶች ትናንት ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ መታፈሳቸውን ወጣቶቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ከአንድ ወር በፊት ፖሊስ ወጣቶቹን ቪዲዮና ኳስ የሚታይባቸው ቤቶች ውስጥ እያሉ ‹‹ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ግንኙነት አላችሁ›› በሚል ካሰረ በኋላ አስፈርሞና አሻራ ወስዶ እንደለቀቃቸው ገልጸዋል፡፡
በትናንትናው ዕለትም ፖሊስ በርከት ያሉ ወጣቶችን አስሮ የነበር ሲሆን ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ እንድትበጠብጡለት ምን ያህል ብር ይከፍላችኋል? ማን ነው ያደራጃችሁ? ደንጋይ ለመወርወር ምን ያህል ብር ይከፈላችኋል?›› በሚል ምርመራ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል፡፡ በስተመጨረሻም ምሽት ላይ አስፈርሞና አሻራ ወስዶ ከእስር ተለቀዋል፡፡ ወጣቶቹን ‹‹ከአሁን በኋላ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ግንኙነት እንዳላችሁ ካወቅን በሽብር ነው የምንከሳችሁ፡፡›› የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia


በእስር ላይ የሚገኙ የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች ከምርጫው በፊት ውሳኔ አያገኙም ተባለ

ሚያዝያ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከደህንነት ምንጮች የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ሚያዚያ 30 ፣ 2007 ዓም ከፍተኛው ፍርድ ቤት በእነ አቶ አቡበክር አህመድ በተከሰሱት ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም፣ ከደህንነት መስሪያ ቤት በተሰጠትእዛዝ፣ ውሳኔው ከምርጫው በፊት አይሰጥም። ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ የተባሉት የደህንነት ባለስልጣን ይህንኑ አቋም በቅርቡ ተደርጎ በነበረው የኢህአዴግ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።

ውሳኔው በተያዘለት ቀን እንዳይሰጥ የተፈለገው፣ ውሳኔውን ተከትሎ ሙስሊሙ ሊያሰማ የሚችለውን ተቃውሞ ለመቀነስ ነው። ለውሳኔው መራዘም ዳኞች ስልጠና ገብተዋል የሚል ምክንያት ሊሰጥ እንደሚችልም መረጃው አመልክቷል።

በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የሚፈፀመው ድብደባ ቀጥሏል

ነገረ ኢትዮጵያ

ምርጫውን ተከትሎ በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የሚፈፀመው ድብደባ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ትናንት ሚያዝያ 21/ 2007 ዓ.ም በምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ፀኃፊ የሆነው አቶ ሳሙኤል አወቀ በደህንነቶች ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመበት ኃላፊው ገልጾአል፡፡ አቶ ሳሙኤል ከምሽቱ 2 ሰዓት ላይ ወደ ቤቱ እየገባ በነበረበት ወቅት ሁለት ደህንነቶች አፍነው በመውሰድ ከሌሎች አራት ደህንነቶች ጋር በመሆን ከፍተኛ ድብደባ ፈጽመውበታል፡፡ ደህንነቶች ‹‹እንፈልግሃለን!›› ብለው ከወሰዱት በኋላ ‹‹ለምን አርፈህ አትቀመጥም?›› እያሉ ድብደባ እንደፈፀሙበትም አቶ ሳሙኤል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
በተመሳሳይ የደ/ጎ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢና የፎገራ ወረዳ የተወካዮች ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪ አቶ አለማየሁ አደመ ላይ ከፍተኛ የሆነ ድብደባ እንደተፈፀመበት ተገልጾአል፡፡ ደህንነቶች አቶ አለማየሁ በሚኖርበት ደራ ወረዳ አርብ ገበያ ከተማ ሚያዝያ 20/2007 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ደብደባ ፈጽመውበታል፡፡ አቶ አለማየሁ ድብደባው በተፈፀመበት አርብ ገበያ ጤና ጣቢያ እየተረዳ የነበር ቢሆንም ጉዳቱ ከፍተኛ በመሆኑ ወደ ባህርዳር ሪፈራል ሆስፒታል መዛወሩ ታውቋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተባባሪ የሆነው አቶ አዲሱ ጌታነህ መንግስት አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን ግድያ ለመቃወም ባህርዳር ከተማ ላይ በጠራው ሰልፍ ተገኝቶ ከተመለሰ በኋላ ምሽት ላይ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመበት መዘገባችን ይታወሳል፡፡