Saturday, January 30, 2016

“በአኮቦ ወረዳ ከ200 በላይ የሚሆኑ አኙዋኮች ህፃናት እና ሴቶች መጨፍጨፋቸው ተነገረ




ሁላችንም እንደምንገነዘበው ባለፋት 25 አመታት ወያኔ ሲጠቀምባቸው የነበሩ ስሌቶችና ጭካኔና በተሞላበት ድርጊቶች መካከል የኢትዮጵያን ህዝብ በዘር በሀይማኖት እና በክልል እየከፋፈለ አንዱን ብሄረስብ በሌላው ላይ እያነሳሳና እያስታጠቀ ለመቆየት በመቻሉ ነው። በተናጠል ሌላውን ብሄረሰብ እያጠቃ በጠቅላላው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚፈፅመው የኢሰብዓዊ ድርጊቶች ከማንኛውም ግዜ በላይ በመቀጠል ላይ ነው ያለሁ። ለዘመናት በሰላም እና በፍቅር ይኖር የነበሩትን ብሄረሰቦች እርስ በእርስ በማጋጨት በሌላው ብሔረሰብ ላይ የዘር ማጥፋት ዘመቻም እያወጀና እየጨፈጨፈ ሲያንስም የሕዝቡን ነፃነት እየሸረሸረ ዛሬ በበለጠ ግዜ የሀገሪቷን ሉዓላዊነት አወዛጋቢ ሁኔታ ላይ ጥሎዋታል።

የወልቃይት የአማራ ማንነት ኮሚቴ ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ታገቱ

የፈደራል መንግስት ፖሊስ አብዛኛዉ የህዝብ ብዛት ያላቸዉ የኦሮሞና አማራ ህዝቦች ድርሻ ከፍተኛ እያለ በትናንትናዉ የእንጦጦ ኬላ የጠባቡ የትግራይ አስተዳደር ተወላጂ የሆኑ
1. ም/ኮ/ ጥጋቡ ረዳ ህድሩ
2. አኒስፔክተር ፍስሃ ተ/ ሃይማኖት
3. ኮንስታብል አረጋዊ ሃጎስ
ተመልከቱ ፊደራል መንግስትን ያህል የብሄር ብሄረሰቦች ስብስብ በጠባቡ ቡድን መዳፍ ስር መሆኑ ታዘቡ የወልቃይት የአማራ ብሄር ማንነት ጥያቂያችን በትግራይ አስተዳደር መልስ ማግኘት ሲገባን ጥያቂያችነን አፍነዉ የተዛባ አስተሳሰብ ይዘዉ ህብረተሰቡን ህገመንግስታዊ መብቱን ፍትሃዊ መልስ የተሳነዉን ጠባቡና ትምክህተኛዉ የትግሪ አስተዳደር የደረሰዉን እንግልትና ግፍ ለፊደራል መንግስት ቅሪታቸዉን ለማስገባት ሲጎዙ በማን አለብኝነት እነዚህ ተራ የፖሊስ አባላት ፖለቲካዊ ወገንተኝነት ተላብሰዉ የህዝቡን አደራ በልተዉ ጸረ ዲሞክራሲ እንቅስቃሴ ተለብሰዉ በወልቃይት ተወላጆች ላይ በ ደል ፈጽመዋል፡፡ ቅሪታ አቅራቢዉ የወልቃይት ህዝብ ተወካዩች አዲስ አበባ አጠገብ ጨንጮ በተባለ አከ ባቢ ተመልሰዉ አድረዉ የህግ ያለህ የመንግስት ያለህ እያሉ ነዉ፡፡ ኢትዩጽያ አገራችን በአናሳና ጠባብ ትምክህተኛ የትግራይ ቡድን መዳፍ ከወደቀች እነሆ 25 አመት የግፍ የመከራ ዘመን እያስቆጠርን ነዉ፡፡

የህዝባችን እንባ ለማቆም ሁላችንም አምርረን እንታገል

ኢትዮጵያ አገራችን ከፍተኛ የሆነ የህልውና ስጋት ተደቅኖባታል። ልጆቿ በያቅጣጫው ዋይታቸውን እያሰሙ ነው። የወያኔ የተበላሸ ስርዓት እና የስግብግብነት ተፈጥሮ ተደማምረው ህዝባችንን በቃላት ሊገለጽ በማይቻል ሰቆቃ ውስጥ ከተውታል። ህሊና ይዘው መፈጠራቸው ጥያቄ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ፣ ቅልብ የወያኔ ገዳይ ወታደሮች በኦሮሞ እናቶችና ህጻናት ላይ የፈጸሙት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በረጅሙ ታሪካችን ያላየነውና ያልሰማነው ነው። ባለፉት መንግስታት ለነጻነታቸው የጮሁ ወጣቶች በስርዓቱ የጸጥታ ሃይሎች መገደላቸው ታሪክ የመዘገበው ሃቅ ነው፣ ነገር ግን ህጻናትና ታዳጊዎች እጅግ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ግንባራቸውንና ደረታቸውን በጥይት እየተመቱ ሲወድቁ ስንመለከት ይህ በታሪካችን የመጀመሪያ ነው። አለም በፍጥነት እየተለወጠ ባለበት በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ መወሰዱ ደግሞ የአገዛዙ ቁንጮዎችንና እነሱን ተከትለው ወደ ጥፋት አረንቋ የሚተሙትን ሁሉ ከሰው መፈጠራቸውን እንድንጠይቅ የሚያደርግ ነው። የኦሮሞ ህዝብ በአጋዚ ወታደሮችና በፌደራል ፖሊሶች በግፍ ለተነጠቀው ልጆቹ ድምጹን ከፍ አድርጎ አልቅሷል፤ ቁጭቱን በቻለው መንገድ ሁሉ ሊገልጸው ሞክሯል። ነገር ግን እስካሁኗ ሰአት ድረስ መገደሉ፣ መታሰሩ፣ መሰደዱ፣ መዋረዱ አለቆመም። አገዛዙ ለአንድ ቀን በስልጣን ላይ ውሎ እስካደረ ድረስ ይኸው ግፍ ይቀጥላል።

Friday, January 29, 2016

የአቶ ደብረጽዮንን ማስፈራሪያ ወደኋላ ያሉ የኦህዴድ ባለስልጣናት ከስልጣናቸው ሊነሱ ነው * ሙክታር ከድር ሊሰናበቱ ይችላሉ (ሪፖርታዥ)

ከጥቂት አመታት በፊት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር የኦህዴድ ባለስልጣናት ሲያስቸግሯቸው በፓርላማ ወጥተው “ባለስልጣናት ሃብታቸውን ማስመዝገብ አለባቸው” በሚል የጸረሙስና ክስ ሊመሰርቱ እንደሚችሉ ተናገሩ:: በወቅቱ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ አባዱላ ገመዳ ነበሩ:: አባዱላ በሙስና ልታሰር እችላለው በሚል መሸማቀቅ አዲስ አበባ ላይ በሙስና የሰሩትን ቭላ ቤት ለኢህ አዴግ ጽህፈት ቤት አስረከቡ::
ሰሞኑን ታሪክ ራሷን ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብ ተቃውሞ በመላው ኦሮሚያ ሲናኝ አመጹን ለማስቆም የኦህ ዴድ ባለስልጣናት ምንም ሥራ አልሰሩም በሚል ሕወሃቶች በክፍተኛ ግምገማ ውስጥ ወድቀው ስንብተዋል ይላሉ የዘ-ሐበሻ ምንጮች:: አመጹ ከተቀጣጠለ በኋላ በኦህ ዴድ አመራር ላይ እምነት ያጡት ሕወሓቶች ልዩ አስተዳደር አቋቁመው ኦሮሚያን እየመሯት ይገኛሉ::

የጋምቤላ ክልል በፊዴራል መንግስት ስር ወደቀ

በጋምቤላ ሙሉ በሙሉ በፌዴራል መንግስት ቁጥጥር ስር ወደቀች። ከአርብ ጥር 20 2008 ጀምሮ ፕሬዚደንቱን ጨምሮ የክልሉ ባለስልጣናት ከስራ ውጭ መሆናቸውን የተረጋገጠ ሲሆን፣ የክልሉንም ጸጥታ የፌዴራል መንግስት ተረክቧል።
በአካባቢው የተቀሰቀሰውን የጎሳ ግጭት ተከትሎ በክልሉ ውጥረት የጨመረ ሲሆን የጋምቤላ ወህኒ ቤት ዛሬ መሰበሩ ታውቋል። በርካታ ሰዎች በዛሬው የወህኒ ቤት ጥቃት መገደላቸው ተገልጿል።
የፌዴራል መንግስት የክልል ባለስልጣናትን ከስራ ውጭ ያደረገው የጸጥታን መቆጣጠር አልቻላችሁም በሚል ምክንያት ቢሆንም በክልል ውስጥ የእርስ በዕርስ ግጭት እንዲከሰት በገዢው ስርዓት በኩል ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ።
በጋምቤላ በቀጠለው ግጭት የሟቾች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን፣ በአካባቢው መጠለያ የተሰጣቸው የደቡብ ሱዳን መንግስት ተቃዋሚዎች ተሳታፊ መሆናቸው ተሰምቷል።

በጋምቤላ በቀጠለው ግጭት 7 ሰዎች ተገደሉ

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል ዳይሬክተር አቶ ኒካው ኦቻላ ለኢሳት እንደገለጹት የንዌር ተወላጆች የጋምቤላ እስር ቤትን ሰብረው በመግባት 7 የአኝዋክ ተወላጆችን ሲገድሉ፣ 7ቱን ደግሞ አቁስለዋል። 4 የሌሎች ብሄረሰቦች አባላት መቁሰላቸውምን ዳይሬክትሩ ገልጸዋል።
በሁለቱ ብሄረሰቦች መካካል እንዲህ አይነት ደም የሚያፋሰስ የመረረ ግጭት ተቀስቅሶ እንደማያውቅ የገለጹት አቶ ኒካው፣ ለአሁኑ ግጭት መባባስ የሪክ ማቻር ወታደሮችንና ከደቡብ ሱዳን የተሰደዱ ንዌሮችን ተጠያቂ አድርገዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የሚያስታጥቃቸው የሪክ ማቻር ወታደሮች መሳሪያ እንደልባቸው በማግኘታቸው ጥቃት እየፈጸሙ ነው የሚሉት ዳይሬክተሩ፣ ብዙዎቹ የደቡብ ሱዳንን ግጭት እየሸሹ የሚመጡት የሪክ ማቻር ደጋፊዎች ኑዌሮች በመሆናቸውን ችግሩን አባብሶታል ብለዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና የፌደራል ፖሊስ አባላት በከተማው ቢሰማሩም ግጭቱን ሊቆጣጠሩት አልቻሉም።
በከተማዋ የሚገኙ መንገዶች ፣ ትምህርት ቤቶችና ባንኮችን የመሳሰሉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተዘግተው መዋላቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በደቡብ ጎንደር በመቶወች የሚቆጠሩ ሰዎች ከርሃብ ጋር በተያያዘ በሽታ መሞታቸው ተሰማ

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በላይጋይንት ወረዳ ከታች ነጋላ ነዋሪዎች መካከል በቀበሌ 23፣24 እና 26 በከፍተኛ ሁኔታ በድርቅ ከመጎዳታቸው ጋር ተያይዞ በተነሳ በሽታ ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ አባዎራዎች ለሞት መዳረጋቸውን በርካቶችም የበሽታ ሰለባ ሆነው እንደሚገኙ የአካባቢው ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከ1100 በላይ የቤት እንስሳት ማለቃቸውንም አክለው ተናግረዋል።
የአካባቢው ነዋሪዎች ሰሞኑን እርዳታ ለመጠየቅ ወደ ዛጎቻ ከተማ አምርተው ጥያቄ ሲያቀርቡ የሚያሳይ ምስል ኢሳት ደርሶታል። ነዋሪዎቹ አፋጣኝ እርዳታ ካልደረሰላቸው በስተቀር እስካሁን ከደረሰው የከፋ ጉዳት ሊደርስባቸው እንደሚችል ተናግረዋል።
ኢሳት ስለሞቱት ሰዎች የአካባቢውን ባለስልጣናት ለማናገር ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።
የኢትዮጵያ ረሃብ የአለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃንን ትኩረት እየሳበ ሲሆን፣ የተለያዩ የውጭ ድርጅቶች አፋጣኝ እርዳታ እንዲቀርብ መወትወት ጀምረዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አንድ አምስተኛ የሚሆነው ወይም ከ20 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን በያዝነው አመት በረሃብ ሊጠቁ ይችላሉ ሲል ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ ባንኪ ሙን በድርቅ የተጎዱ አንዳንድ አካባቢዎችን የፊታችን እሁድ ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ ዜና ደግሞ ቤዛ እንሁን የበጎ ፍቃደኞች ስብስብ በድርቅ ለተጎዱ ኢትዮጵያዊያን እርዳታ ለግሷል።
በበጎ ፈቃደኛ ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች አነሳሽነት የተቋመው ቤዛ እንሁን የበጎ ፈቃደኞች ስብስብ ለወገን ደራሽ ወገን ነው በማለት ያሰባሰቡትን 15 ሽህ ብር ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር በጋራ በመተባበር በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን ሲሬ ወረዳ በአካል በመገኘት ለተጎጂዎች አድርሰዋል።
የማኅበሩ አባላት ይህ የመጀመሪያ ዙር የረድኤት ልገሳቸው ሲሆን ቀጣይም ለችግረኛ ኢትዮጵያዊያንን ማገዙን እንደሚቀጥሉበት ወጣቶቹ አስታውቀዋል። የእርዳታ አሰጣጡን በተመለከተ በነገው ዕለት በ‹‹ቤዛ እንሁን›› ህዝብ ግንኙነት በኩል መረጃዎችን በዝርዝር እንደሚያቀርቡ ኤሊያስ ገብሩ በፌስቡክ ገጹ ዘግቧል።
በኢትዮጵያ ያለው የእርሃብ ሁኔታ አሳሳቢ በመሆኑ ዜጎች በማኅበሩ ጥላ ስር በመሰባሰብ በተግባር ለወገን ደራሽ አለኝታ መሆናቸውን ያሳዩ ዘንድ ወጣቶቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

የመሬት መንቀጥቀጥ ሸሽተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲሄዱ የነበሩ የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የመኪና አደጋ ደረሰባቸው

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ለአስራ አምስት ቀናት ትምህርት መቋረጡን የዩንቨርሲቲው አስተዳደር መግለጹን ተከትሎ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል። በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ተጭነው ከግቢው በመውጣት ወደ ወላጆቻቸው በመሄድ ላይ ከነበሩት ተማሪዎች ውስጥ ወደ በመቂ እና ሞጆ ከተሞች መዳረሻ አካባቢ የመኪና አደጋ ደርሶባቸዋል። የአደጋው መንስኤ የሚጓዙበት ተሽከርካሪ ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ሲጓዝ ከነበረ ኤፍ ኤስ አር አይሱዙ የጭነት መኪና ጋር በመጋጨቱ ምክንያት አምስት ተማሪዎች ወዲያውኑ ሕይወታቸውን ማጣቸውን ዘ ኢትዮጵያነር ድረገጽ በምስል አስደግፎ ጉዳተኞችን አውጥቷል።
በሃዋሳ የደረሰውን ርዕደ መሬት ሸሽተው ሲሄዱ የመኪና የሞት አደጋ ከደረሰባቸው ተማሪዎች በተጨማሪ ከፍተኛና ዝቅተኛ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ታውቋል።
በሃዋሳ ከተማ በዛሬው ዕለት ከሰዓት በኋላ በተደጋጋሚ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። የመሬት መንቀጥቀጡ በተለይ በሃዋሳ መምህራን ኮሌጅ ተማሪዎች ላይ የተወሰነ አካላዊ ጉዳት አስከትሏል። በመንግስት በኩል ስለ አደጋውና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምንም ዓይነት መግለጫ አለመሰጠቱ በተማሪዎቹና በወላጆቻቸው ላይ ከፍተኛ ስነልቦናዊ ጫና ፈጥሯል።
በተጨማሪም በአዋሳ ያሉ የሱቅ በረንዳቸው የፈረሰባቸውን ነጋዴዎችን ንብርት የክልሉ ፖሊስ በመኪና በመጫን ዝርፊያ ፈጽሟል። ንብረቶቻቸው የወደሙባቸው ነጋዴዎች አቤቱታቸውን ሰሚ አካል አላገኙም። የዓይን እማኞች ከስፍራው እንዳስታወቁት ፌስታል አዙረው እራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩ ወጣትና ታዳጊ የጎዳና ላይ ነጋዴዎችንም ጭምር ፖሊስ የያዙት በመቀማት ድብደባ በመፈጸም ላይ ነው።

በኢትዮጵያ በአዮዲን የበለጸገ ጨው የሚጠቀመው ህዝብ እጅግ ዝቅተኛ ነው ተባለ

ጥር ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያ በአዮዲን የበለጸገ ጨው የሚጠቀመው ህዝብ 23 በመቶ ያህል መሆኑን ከኢትዮጵያ የምግብ መድሀኒትና ፋርማሱዪቲካል ልማት ኢንስቲትዪት የተገኘ ጥናት አመልክቷል።
አብዛኛው ህዝብ በአዮዲን የበለፀገ ጨው ማግኘት ባለመቻሉ የእንቅርት በሽታን ጨምሮ የህጻናት አእምሮና እድገት ዝግመትን፣ ነፍሰጡር ሴቶች ላይ ውርጃንና የመሳሰሉ ችግሮችን በማስከተል ላይ ይገኛል።
መንግስት ቁጥሩን ወደ 70 በመቶ ለማሳደግ እየሰራሁ ነው ብሎአል። በአሁኑ ወቅት በአዮዲን የበለፀገ የጨው ማምረቻ ፋብሪካ በ220 ሚሊየን ብር በአፍዴራ ለመገንባት የታቀደ ቢሆንም የፋይናንስ ችግር መኖሩ ግን እቅዱ በቅርቡ እንዳይተገበር እንቅፋት ሊሆን ይችላል ተብሎአል።
በአዮዲን የበለፀገ ጨው እጥረት ጋር በተያያዘ አብዛኛው የገጠር ህዝብ በእንቅርት ህመም እንደሚሰቃይ ጥናቱ ይጠቁማል።

Thursday, January 28, 2016

የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኦሮምያን ሙሉ በሙሉ አረጋግተናል ባለ ማግስት ተቃውሞ ተነሳ

ጥር ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ፣ በኦሮምያ የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን በመገናኛ ብዙሃን ባስታወቀ ማግስት በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞዎች ተነስተዋል። የተቃውሞዎች ዋነኛ አጀንዳ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስረዛ ወደ ሌሎች የመብት ጥያቄዎች ተሸጋግሯል። በጉጂ ፣ ሰሜን ሸዋና ምስራቅና ምዕራብ ሃረርጌ በተካሄዱት የተቃውሞ ሰልፎች፣ ነዋሪዎች የታሰሩት እንዲፈቱ፣ ለወራት በዘለቀው ተቃውሞ ግድያ፣ ድብደባና ሰቆቃ የፈጸሙ ወታደሮችና አዛዦቻቸው ለፍርድ እንዲቀርቡ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት ክልሉን ለቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
መንግስት የአገር ሽማግሌዎችን በማናገር ተቃውሞው እንዲበርድ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያድርግም፣ ተቃውሞውን ለማብረድ አልቻለም። በአንዳንድ አካባቢዎች ነዋሪዎች ኦህዴድ አይወክለንም የሚል መፈክር ሲያሰሙ ተሰምተዋል።
ለሁለት ወራት ያክል በዘለቀው ታሪካዊ በተባለው ተቃውሞ ከ150 በላይ ዜጎች በመንግስት ወታደሮች ተገድለዋል።ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎች ቆስለዋል። በሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ታስረዋል።
የአውሮፓ ህብረትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ግድያውን አውግዘዋል። ጋዳዮችም ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል።
ኦህዴድ ለተቃውሞው መነሻ ነው የተባለውን አዲስ አበባ ማስተር ፕላን መተውን ማስታወቁ ይታወሳል። የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ተቃውሞው ማስተር ፕላኑን ሰበብ አድርጎ ቢነሳም፣ የህዝቡ ጥያቄ ግን ሌሎች መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎችን ያካተተ ነው።

በጋምቤላ በቀጠለው ግጭት ሰዎች ተጎዱ

ጥር ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት በሁለት የአኝዋክና ንዌር የመንግስት ባለስልጣናት መካከል የተነሳው ጸብ ወደ ብሄረሰብ ግጭት በማምራቱ የከተማዋና አካባቢው ነዋሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በከተማዋ ውስጥ እንደልብ መንቀሳቀስ አለመቻሉን የገለጹት ነዋሪዎች፣ እስካሁን ምን ያክል ሰዎች እንደሞቱ ለማወቅ አለመቻሉን ገልጸዋል።
በከተማዋ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችና የመንግስት መስሪያቤቶች ተዘግተዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላት በከተማዋ ቢሰማሩም ግጭቱን ሊያስቆሙት አለመቻላቸውንም ነዋሪዎች አክለው ተናግረዋል።
የአኝዋ ሰርቫይቫል ዳይሬክተር አቶ ኒይካው ኦቻላ በአንድ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ በደረሰው የቦንብ ፍንዳታ አንድ ሰው መቁሰሉን፣ ኦሜንጋ በተባለ አካባቢ የሚገኙ አኙዋኮች መፈናቀላቸውንና አንድ ፖሊስን ጨምሮ 4 ሰዎችም መሞታቸውን ገልጸዋል።

በሃዋሳ ከተማ ያሉ የበረንዳ ዳስ ሱቆች ካለምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ እንዲፈርሱ እየተደረገ ነው

ጥር ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በደቡብ ክልል ዋና ከተማ ሃዋሳ በተለምዶ አረብ ሰፈር አሮጌ ገበያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ የበረንዳ ዳሶችን ካንድ ቀን በፊት ብቻ ማሰጠንቀቂያ በመስጠት አፍራሽ ግብረ ኃይል በማሰማራት ሕገወጥ ግንባታ በሚል ሱቆቹን ማፍረሱ ቀጥሏል።
ሕጋዊ የቫትና ቲኦቲ ግብር ከፋይ የሆኑት ነጋዴዎች ሁኔታውን በመቃወም ተቃውሟቸውን ቢገልፁም፣በአፀፋው የክልሉ ፖሊስ ሰላማዊ ሰልፈኞቹን በመደብደብ አካላዊ ጉዳት ከመፈፀሙ በተጨማሪ የተቃውሞው መሪ ያሉዋቸውን ነጋዴዎች ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደው ስማቸውን መዝግበው ለቀዋቸዋል።
የከተማውን ውበት ያበላሻል በሚል አጥጋቢ ባልሆነ ምክንያት ቀድሞ ተፈቅዶላቸው የሰሩዋቸው የንግድ ቦታዎች የፈረሱባቸው ከ200 በላይ የሚሆኑ ነጋዴዎች ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ተጋጭተዋል። የአካባቢው ነዋሪዎችም ድጋፋቸውን ለነጋዴዎች ሰጥተዋል።
ነጋዴዎቹ በብረትና በጣውላ የከለሉዋቸውን ቦታዎች በአፍራሽ ግብረ ኃይሉ በመፍረሱ እቃዎቻቸው በዝናብና በፀሃይ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በዚህም ምክንያት እጅግ የከፋ ኪሳራና ጉዳት እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችሏል።
በሃዋሳ ከተማ በቅርቡ በሬክተር ስኬል መለኪያ 4.5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ መድረሱ ይታወቃል። በተለይ በከተማዋ ውስጥ ባሉት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የመሬት መንቅጠቀጡ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ በሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ዋናው ግቢና ሪፈራል ግቢ ውስጥ ብዙ ተማሪዎች ተጎድተዋል።
በንብረት ውድመት በኩልም የትምህርት ቤቶቹ ሕንጻ ግድግዳዎች ተሰነጣጥቀው መስታወቶቻቸውም ረግፈዋል። ዛሬ ተማሪዎቹ ለ15 ቀናት ትምህርታቸውን አቋረጠው ከግቢው ወጥተው ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ የዩንቨርሲቲው አስተዳደር ማስታወቂያ በመለጠፍ ትምህርት መቋረጡን ገልጿል።

በኢትዮጵያ አንድ አምስተኛ የሚሆነው ሕዝብ ለረሃብ ሊጋለጥ ይችላል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ

ጥር ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በአሳሳቢ የርሃብ አደጋ ውስጥ የሚገኙ ሲሆን በሚቀጥሉት ወራት አደጋው በእጥፍ እንደሚጨምር ቅድመ ጥናቶች አረጋግጠዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ግብረሰናይ የረድኤት ተቋማት በምስራቅ አፍሪካ ውስጥ ከተከሰተው የርሃብ አደጋዎች በኢትዮጵያ ያለው ርሃብ አድማሱን በማስፋቱ ከአጠቃላይ የአገሪቱ ሕዝብ ውስጥ አንድ አምስተኛ የሚሆነው ወይም ከ20 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ህዝብ በርሃብ አደጋ ውስጥ እንዳለና ሁኔታዎቹ እየከፉ መምጣታቸውን ድርጅቱ አስታውቋል።
በአገሪቱ በተከሰተው የአየር መዛባት ሳቢያ ወቅቱን ጠብቆ ዝናብ ባለመዝነቡ በተከሰተው ድርቅ ሚሊዮኖች ለርሃብ ሲዳረጉ ሕጻናት ያልተመጣጠነ ምግብ በማጣታቸው ምክንያት የጤና መታወክ ደርሶባቸዋል። በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በምግብ እጦት ምክንያት ልጆች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደዋል።
ዓለምአቀፍ የረድኤት ድርጅቶች አፋጣኝ እገዛ እንዲያደርጉና ርሃብተኞችን እንዲታደጉ የተባበሩት መንግስታት ጥሪውን አቅርቧል።
በድርቁ ሳቢያ ከ100 ሽህ በላይ ኢትዮጵያዊያንና ሶማሊያዊያን ባሕር አቋርጠው ወደ የመን መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ቢሮ ገልጿል። በድርቁ ምክንያት ዕድሜያቸው ያልደረሱ ታዳጊዎች ካለ ዕድሜ ጋብቻ እንዲፈጽሙ በቤተሰባቸው እየተገደዱ መሆናቸውንም ድርጅቱ አስታውቋል።

በአፍሪካ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እየተባባሰ መምጣቱ ተገለጸ

ጥር ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ተከትሎ አጠቃላይ በአሃጉሩ የሸቀጥ ዋጋ እየናረ ነው። የአፍሪካ ሕብረት የኤኮኖሚ ጉዳይ ኃላፊ የሆኑት ዶክተር አንቶኒ ሞንታይ እንዳሉት የሸቀጦች ዋጋ መውረድ፣ የዶላር የወለድ መጠን በአሜሪካ መናር፣ አሳሳቢ ድርቅና የጎርፍ አደጋዎች በሃጉሪቱ ያለውን ምጣኔሃብታዊና ማኅበራዊ ችግሮች ይበልጥ አባብሰውታል ።
ዶ/ር አንቶኒ “ችግሩ በመባባሱ ምክንያት የስራ አጡ ቁጥር እየጨመረ፣ የኑሮ ልዩነት እየሰፋ፣ ጤናማ ያልሆነ የንግድ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ፣ የዋጋ ግሽበት እያስከተለ ነው ” ብለዋል
ወደ ውጪ የሚላኩ የኤክስፖርት ምርቶች በማሽቆልቆላቸው ምክንያት ትርፍ ባለመኖሩ የሃጉሪቱ ገቢ ቀንስዋል። ድርጅቶችም ሰራተኞችን በመቀነሳቸው የስራ አጡ ቁጥር አሻቅቧል። የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ በማደጉ በሃጉሪቱ ኢንቨስትመንት ላይ አሉታዊ ጫና አሳድሯል።
የኤሊኖ አየር መዛባትን ተከትሎ በተለያዩ የአፍሪካ አገራትይ ውስጥ በአገር ውስጥና ወደ ውጪ በሚላኩ የግብርና ምርቶች ላይ አስከፊ የሆነ ተፅዕኖ ፈጥሯል።በሃይድሮ ኤሌትሪክ ኃይል ማመንጫዎች ረገድም በድርቁ ሰበብ ውሃ በወንዞችና በግድቦች ውስጥ ባለመኖሩ የኃይል አቅርቦቱ ተስተጋጉሏል።ይህም በማዕድን ማምረቻዎች፣ፋብሪካዎች በመስኖ እርሻዎችና በንጹህ ውሃ አቅርቦት ላይ የከፋ አደጋ እንዲደርስ ማድረጉን የአፍሪካ ሕብረት ተሰብሳቢዎች አስተውቀዋል።

‹‹ማዕከላዊ ነው እንዴ ያለነው?›› (ክፍል ፪) በናትናኤል ፈለቀ (ካለፈው የቀጠለ)

የማታው የመፀዳጃ ሰዓት አብቅቶ እስረኞችን ቆጥረው በሩን የሚቆልፉት ፖሊሶች መጡ፡፡ ሼህ ጀማል ዘወትር እንደሚያደርጉት የመጡት ፖሊሶችን ሰዓት ጠየቋቸው፡፡ አልፎ አልፎ በቁጣ ተሞልተው ከሚመጡት ፖሊሶች በስተቀር ሰዓት ለመናገር አብዛኞቹ ተባባሪዎች ናቸው፡፡ 12 ሰዓት ከ10 ደቂቃ እንደሆነ የተነገራቸው ሼህ ለመግሪብ ጸሎት የቀረው ግማሽ ሰዓት እንደሆነ ክፍሉ ውስጥ ለነበሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች አሳወቁ ኡመድ ለፈረሃን ተረጎመለት፡፡

Wednesday, January 27, 2016

በሰሜን ጎንደር በማንኛውም ጊዜ ግጭት ሊነሳ ይችላል ሲሉ ነዋሪዎች አስጠነቀቁ

ጥር ፲፰ (አሥራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ገዢው ፓርቲ ሆን ብሎ ፈጥሮታል በሚባለው በአማራና ቅማንት የሰሜን ጎንደር ተወላጆች መካከል ያለው ግጭት ለጊዜው ጋብ ያለ ቢመስልም፣ ድጋሜ ግጭት ለማስነሳት ውስጥ ለውስጥ የቅስቀሳ ስራ እየተሰራ መሆኑን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
አንዱ በሌላው ላይ የሚያካሂደው የማጥላላት ዘመቻ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በዚሁ የቅስቀሳ ስራ ላይ የኢህአዴግ ሹሞች ሙሉ በሙሉ እጃቸውን ማስገባታቸው ታውቋል። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገለጹት ከዛሬ ነገ ግጭት ይንሳል በሚል ስጋት የተረጋጋ ህይወት ለመምራት አልቻሉም።
በአንዳንድ አካባቢዎች ትምህርት ቤቶች ከተዘጉ ወራትን ቢያስቆጥሩም ሊከፈቱ አልቻሉም።

በኮንሶ የሚታየው ውጥረት እንደቀጠለ ነው

ጥር ፲፰ (አሥራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኮንሶ ህዝብ ራሱን ችሎ በዞን እንዲተዳደር ያቀረበው ጥያቄ ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ በርካታ ሰዎች ለእስር ከተዳረጉ በሁዋላ አሁንም አካባቢው በልዩ ሃይል ፖሊሶች እንደተከበበ መሆኑን ነዋሪዎች ከስፍራው ገልጸዋል። የልዩ ሃይል አባላት ከጥያቄው ጀርባ አርበኞች ግንቦት7ቶች አሉበት በማለት ቅስቀሳ ሲያደርጉ እንደነበር የገለጹት ነዋሪዎች፣ አሁን ደግሞ ” ጥያቄው የእኛ አይደለም” ብላችሁ ፈርሙ በማለት በግድ ለማስፈረም ሙከራ እያደረጉ ነው። የልዩ ሃይል አባላትና የወረዳው ሹሞች መግባባት አለመቻላቸውን፣ አስተዳዳሪዎቹ ጥያቄው የህዝብ ነው የሚል አቋም በማራመዳቸው አንዳንዶች ከሃላፊነት እንዲነሱ ተደርጓል።
የህዝቡን ጥያቄ አቅጣጫ ለማስለወጥ ሆን ብለው በማቀነባበር ቡርጂዎች ግጭት እንዲቀሰቀስ ለማድርግ የተሞከረ ቢሆንም፣ በሁለቱም ወገን የሚገኙ ነዋሪዎች ይህ ሆን ተብሎ ግጭት ለመፍጠር የተቀነባበረ ነው በማለት ወደ ግጭት አለመግባቱን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ከቡርጅና ከኮንሶ የሆኑ 2 ሰዎች መገደላቸውን፣ ግድያው የተፈጸመው ሆን ተብሎ ግጭት ለመቀስቀስ ታስቦ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል፤ ግድያውን የልዩ ሃይሎች እንዳቀነባበሩት ሲታወቅ ግን ህዝቡ ወደ ግጭት አለመግባቱን ነዋሪዎች አክለው ተናግረዋል።
የኮንሶ አገር ሽማግሌዎች ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያምን ለማነጋገር ወደ አዲስ አበባ መሄዳቸውና ለዛሬ ቀጠሮ ተይዞላቸው እንደነበር ቢታወቅም፣ ስለተሰጣቸው ምላሽ ይህን ዜና እስካቀናበርንበት ሰአት ድረስ ለማወቅ አልቻልም።
በአካባቢው አሁንም ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ነው። አንዳንድ የመንግስት መስሪያቤቶችም አገልግሎት መስጠት አቁመዋል።

የውጭ ምንዛሬ እጥረት ማዳበሪያ በበቂ እንዳናስገባ አግዶናል ሲሉ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ጥር ፲፰ (አሥራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የእር ሻና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው በውጪ ምንዛሪ ችግር ምክንያት ለእርሻ ግብአት የሚውል ማዳበሪያ በበቂ መጠን መግዛት እንዳልተቻለ ለፖርላማው ገልጸዋል፤፡
ለመስኖና እና ለበልግ እርሻ ማዳበሪያ በወቅቱ ለአርሶአደሩ እንዲቀርብ ለማድረግ 832 ሺህ 400 ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ለመግዛት ታቅዶ በውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ችግር ጋር ተያይዞ በመተማመኛ ሰነድ (ሌተር ኦፍ ክሬዲት) አከፋፈት ላይ መዘግየት በመፈጠሩ መግዛት የተቻለው 19 ሺህ 315 ሜትሪክ ቶን ብቻ ነው። ሚኒስትሩ እንዳሉት እንደእቅዳቸው ቢሆን ኖሮ እስካሁን ወደሀገር ውስጥ መግባት የነበረበት 200 ሺህ ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ነበር።
የማዳበሪያ ግዥው በመንግስት ቅድሚያ ማግኘት አለመቻሉ የዝናብ መሻሻል የሚያሳዩ አካባቢዎች አርሶአደሩ የእርሻ ግብአቶችን ተጠቅሞ በቂ ምርት እንዳያገኝ እንቅፋት በመሆን የድርቁን ችግር ያባብሳል በሚል በብዙዎች ዘንድ ስጋትን አሳድሮአል።
የምንዛሬ እጥረቱ በመድሃኒቶች ዋጋ ላይም ጭማሪ እንዲታይ አድርጓል። መንግስት የምንዛሬ እጥረት የለም በማለት በተደጋጋሚ ማስተባበያ ይሰጣል። ይሁን እንጅ የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ በአጠቃላይ የንግድ እንቅስቃሴው ላይ ተጽእኖ እያሳረፈ መምጣቱን ነጋዴዎች ይናገራሉ።

ባለፈው አመት በምስራቅ አፍሪካ ጭቆናው ተባብሶ መቀጠሉን ሂውማን ራይትስ ወች ገለጸ

ጥር ፲፰ (አሥራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ታዋቂው የሰአብዊ መብት ድርጅት ባወጣው ዘገባ የምስራቅ አፍሪካ መንግስታት የሰብአዊ መብት አያያዞችን ለማሻሻል ያደረጉት ጥረት አነስተኛ መሆኑንና በአንዳንድ አገሮች ተባብሶ የቀጠለበት ሁኔታ እንደነበር ገልጿል።
ኢትዮጵያ እና ቡሩንዲ በተወሰነ መጠን ደግሞ ዩጋንዳ ሃሳብን በማፈን፣ የሰዎችን የመሰብሰብ ነጻነት በመንፈግ እንዲሁም ከምርጫ በፊትና በሁዋላ በሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶች ቀዳሚዎች ሆነዋል።
ሩዋንዳ የተቃውሞ ሃሳቦች እንዳይስተናገዱ የያዘችውን አቋም የቀጠለችበት ሲሆን፣ ኬንያ ደግሞ የጸጥታ ሃይሎች ለሚፈጽሙት ወንጀል ተገቢውን እርምጃ መውሰድ አልቻለችም።በደቡብ ሱዳንም የሰአብዊ መብት ጥሰቱ እንደአዲስ ቀጥሎአል።
በፈንጆች አቆጣጠር በ2015 በቡሩንዲ የታየው የፖለቲካና ሰብአዊ ቀውስ የአመቱ ከፍተኛ ቀውስ መሆኑን የጠቀሱት በሂውማን ራይትስ ወች የአፍሪካ ዳይሬክተር ዳንኤል በቀለ፣ ኢትዮጵያ፣ ዩጋንዳና ኬንያም መሰረታዊ በሚባሉት የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ መሻሻል አለማሳየታቸውን ገልጸዋል። በምስራቅ አፍሪካ ምርጫና ጸረ ሽብር ትግል የሚሉት ጉዳዮች በፖለቲካና ሰብአዊ መብቶች ላይ ተጽኖ የሚያደርጉ ጉዳዮች መሆናቸውን የድርጀቱ ዳይሬክትር ኬንዝ ሮዝ በሪፖርቱ መግቢያ ላይ ገልጸዋል።
ዳንኤል በቀለ በበኩላቸው በምስራቅ አፍሪካ የሚገኙ የምስራቅ አፍሪካ መሪዎች ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ ሲሉ የሚፈጽሙትን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እንዲያቆሙ፣ እንዲሁም የሰብአዊ መብት ድርጅቶችና ሚዲያውን በመውቀስ ከተጠያቂነት ለመሸስ ከመሞከር ይልቅ የጸጥታ ሃይሎቻቸው ለሚፈጽሙት ህገወጥ ግድያዎች ተገቢውን ምርመራ በማድረግ ለፍርድ እንዲያቀርቡዋቸው ጠይቀዋል።

Tuesday, January 26, 2016

‹‹ማዕከላዊ ነው እንዴ ያለነው?›› (ክፍል ፩) - በናትናኤል ፈለቀ

እራሳቸውን ድንገት ስተው ‹‹ኮማ›› ውስጥ የገቡ ወላጅ አባቱን ለማስታመም እና በቅርቡ ሕይወታቸው ያለፈውን አሳዳጊ ሴት አያቱን እርም ሊያወጣ ከ15 ዓመት በላይ ወደተለያት ሀገሩ እየተመለሰ ነው፡፡ ለጉዞው ቀና ብሎ ያሰበው መንገድ ከሚኖርበት ሴንት ፖውል፣ ሚኒሶታ ወደካናዳዋ ቶሮንቶ አቅንቶ ከዛ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አዲስ አበባ ለመግባት እና በማግስቱ አውቶቢስ ተሳፍሮ አባቱን ወደሚያገኝበት የሱማሌ ክልል ከተማ ጎዴ ማምራትን ነበር፡፡
 
ወደ ሀገሩ ተመልሶ አባቱን ለማግኘት እጅግ ቸኩሏል፤ ተጨንቋል፡፡ ጭንቀቱን የሚያሳብቀው ገና ከተወለደች ሁለት ሳምንት ያልሞላትን ሁለተኛ ልጁን እና የሦስት ዓመት ወንድ ልጁን አራስ ባለቤቱ ላይ ጥሎ ጉዞውን መጀመሩ ነው፡፡ ነገሮች ሁሉ እንዳቀደው ከሄዱለት በአንድ ወር ግዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ቆይታውን አጠናቆ ዜጋዋ አድርጋ ወደተቀበለችው አሜሪካን ይመለሳል፡፡

ኢንሳ የአየር ላይ ፎቶ በማንሳት ላይ የሚገኘው ለሱዳን ተሰጥቷል የሚባለውን አልፋሽጋ ተብሎ የሚጠራውን አካባቢ መሆኑ ታወቀ

ጥር ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው ጥር ወር መግቢያ ጀምሮ የአየር ላይ ፎቶ እየተነሳ ያለው አካባቢ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ” ኢትዮጵያ መሬቱ የእኛ መሆኑን እውቅና ሰጥታለች” በማለት ለአልጀዚራ የተናገሩት አልፋሽጋ እየተባለ የሚጠራው ቦታ መሆኑ ታውቋል።
ትናንት ኢሳት የመረጃና ደህንነት ኢንፎረሜሽን ባለሙያ በማናገር በሰራው ዘገባ ላይ በአሁኑ ሰአት የአየር ላይ ፎቶ ለማንሳት ምልክቶችን መሬት ላይ የማስቀመጡ ስራ የሚከናወነው 365 ኪሜ ርዝመት ባለው ቦታ ላይ መሆኑን ቢዘግብም፣ ይህ ርቀት ግን የአየር ላይ ርቀትን የሚያመለክት እንጅ የመሬትን እርቀት የሚያመለክት ባለመሆኑ ማስተከከያ እንዲደረግበት ጠይቀዋል። በመጀመሪያው ሂደት ድንበር የማካለሉ ሂዳት የሚከናወነው 725 ኪሜ ርዝመት ላይ ባለው መሬት ላይ ሲሆን፣ ይህም አካባቢ ሱዳን የኢትዮጵያ መንግስት የእኔ መሬት መሆኑን አምኖልኛል በማለት የገለጸችው አልፋሽጋ እየተባለ የሚጠራውን ለም መሬት የሚያካትት ነው።

የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበሩት ዮናታን ተስፋዬ ላይ ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ

ጥር ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባልፈፀመው ወንጀል በሽብር ክስ ተወንጅሎ በደኅንነት ኃይሎች ከመንገድ ታፍኖ ተወስዶ በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ የአራዳ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለ2ኛ ጊዜ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል፡፡
በአራዳ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጥር 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በዋለው ችሎት አቃቤ ሕግ ምርመራዬን አልጨረስኩም ተለዋጭ ቀጠሮ ይሰጠኝ በማለት ያቀረበውን ምክንያት ፍርድ ቤቱ ተቀብሎ ለየካቲት 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የዋስትና መብቱ ይከበርለት ዘንድ አቶ ዮናታን ተስፋየ ጥያቄውን ቢያቀርብም ፍርድ ቤቱ ግን አቤቱታውን ውድቅ አድርጎታል። ፓሊስ በተከሳሹ ላይ ያልተያዙ ግብረ አበሮቹና የቴክኒክ መረጃዎችን መሰብሰብ ይቀረናል ማለታቸውን ጠበቃው ተናግረዋል።
ጠበቃው አክለውም ደንበኛቸው በሕገ መንግስቱ የተፈቀደለትን ከጠበቃው፣ከቤተሰቡ ጋር መገናኘት መብቱን መከልከሉንና በታፈነ ክፍል ውስጥ በመታሰሩ የጤና መታወክ ቢደርስበትም ወደ ጤና ማዕከላት እንዳይሄድ መከልከሉን ለፍርድ ቤቱ አስታውቋል።
ፍርድ ቤቱም አቶ ዮናታን ያቀረባቸውን አቤቱታዎች አድምጦ በጠበቃውም ሆነ በቤተሰቦቹ እንዲጎበኝ እንዲፈቀድለትና ህክምናም ዕርዳታም እንዲያገኝ ሲል ለእስር ቤቱ ትእዛዝ ሰጥቷል።
አቶ ዮናታን ተስፋዬ ከችሎቱ ሲወጣ በስፍራው ለነበሩት ቤተሰቦቹና ወዳጆቹ ያለውን ፍቅርና አክብሮት ገልጾ ”ነጻነት ይሰማኛል!›› በማለት ጮክ ብሎ መናገሩን ነገረ – ኢትዮጵያ ዘግቧል።

በአንዳንድ አካባቢዎች ነዋሪዎች መብራትና ውሃ ከተቋረጠባቸው 5 አመታትን ማሳለፋቸውን ተናገሩ

ጥር ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምእራብ ጎጃም ዞን የየስማላ ከተማ ነዋሪዎች መብራት ከተቋረጠባቸው 5 አመታትን ማሳለፋቸውን፣ በሰሜን ጎንደር ሃሙሲት ከተማ ደግሞ የከተማው ነዋሪዎች የቧንቧ ውሃ ከተቋረጠባቸው 5 አመታትን ማሳለፋቸውን ዘጋቢያችን ነዋሪዎችን አነጋግሮ የላከው ዘገባ ያሳያል። ነዋሪዎቹ ችግሮቻቸው እንዲፈቱላቸው በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም ሰሚ አካል አላገኙም።
በሞጣ ከተማ ደግሞ መብራት ከተቋረጠ 2 ወር ያለፈው ሲሆን፣ በቁንዝላ ከተማ ውሃ ከተቋረጠ 2 ሳምንት አልፎታል። የቁንዝላ ነዋሪዎች የጣናን ውሃ በመጠጣት ለበሽታ እየተዳረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የስኳርና የዘይት እጥረት መከሰቱንም ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ታንዛኒያ ከመቶ በላይ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ወደ አገራቸው ልትመልስ ነው

ጥር ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት ሲሞክሩ በድንበር ጠባቂዎች ባለፈው ወር በፖሊስ ተይዘው በእስር ሲንገላቱ የነበሩ 40 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ጨምሮ በዋና ከተማዋ ዳሬሰላም ካለ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ይኖሩና ይሰሩ ነበሩ ያላቸውን ኢትዮጵያዊያ ስደተኞችን ወደ ትውልድ አገራቸው ለመለስ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የታንዛኒያ የአገር ውስጥ ሚንስቴር አስታወቁ።
የአገር ውስጥ ሚንስቴሩ ቻርለስ ኪታዋንጋ እንዳሉት ”ካለ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ በአገራችን ውስጥ የሚኖሩ ብዙ የውጭ አገር ዜጎች አሉ። ካለ ምንም ጥርጥር ሁሉንም አስረን ወደ አገራቸው እንመልሳቸዋለን።”
ስደተኞቹ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት በአማካኝ ከ1 ሽህ እስከ 2 ሽህ የአሜሪካ ዶላር ለሕገወጥ ደላሎች እንደሚከፍሉ የአገሪቱ የስደተኞች ጉዳይ ቢሮ አስታውቋል።በ2012 እንደ አውሮፓዊያን ዘመን አቆጣጠር 45 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሻገር ሲሞክሩ በኮንቴነር ውስጥ ታፍነው ሕይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ ባለ ሁለት አሃዝ የምጣኔ ሃብት እድገት አምጥታለች እየተባለ በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ቢለፈፍም ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ግን አሁንም የትውልድ ቀዬያቸውን በመተው መፍለሳቸውን አላቋረጡም።

ፍ/ቤቱ በአቶ ዮናታን ተስፋየ ላይ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ

‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› ዮናታን ተስፋየ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለ2ኛ ጊዜ የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል፡፡
 ዛሬ ጥር 17/2008 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበው አቶ ዮናታን ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም በሚል የጠየቀበትን ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ ለየካቲት 15/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ አቶ ዮናታን ተስፋየ የዋስትና መብቱ እንዲከበርለት ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡
ፖሊስ በአቶ ዮናታን ላይ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ሲጠይቅ ‹‹የቴክኒክ መረጃዎችን መሰብሰብ ይቀረናል፤ ያልተያዙ ግብረ አበሮችንም አሉ›› የሚል ምክንያት ማቅረቡን የተጠርጣሪ ጠበቃ ገልጸዋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ በጠበቃ እና በቤተሰቦቹ እንዳይጎበኝ እንደተከለከለና ከታሰረበት ክፍል መታፈን የተነሳ የጤና እከል ቢገጥመውም ህክምና እንዳላገኘ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን አድምጦ በጠበቃውም ሆነ በቤተሰቦቹ እንዲጎበኝ እንዲፈቀድለትና ህክምናም እንዲያገኝ ትዕዛዝ መስጠቱን ከጠበቃው ለማወቅ ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ከችሎት ሲወጣ በስፍራው ለነበሩት ቤተሰቦቹና ወዳጆቹ ያለውን ፍቅር ገልጾ ‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› በማለት ጮክ ብሎ ሲናገር ተደምጧል፡፡

በሕወሓት የደሕንነት ሹሞች ትእዛዝ ኣራት እስረኞች መገደላቸው ታወቀ። የኦሮሞ ንቅናቄ ኣሁንም ከወያኔ ኣገዛዝ ኣቅም በላይ መሆኑ አየተነገረ ነው። ‪

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ከኬንያ ናይሮቢ ታፍነው ከሶስት ኣመት በፊት ወደ ኣዲስ ኣበባ ኣሮጌው ኣይሮፕላን ማረፊያ የጨለማ የግዞት እስር ቤት የታሰሩት የጎጃም ብቸና ተወላጅ የሆነው አና የደቡብ ምስራቅ እዝ ባልደረባ የመቶኣለቃ ኣበባው ነጮ እና ለኦብነግ የስለላና ሰራዊት ምልመላ ያደርጋሉ በሚል ጥርጣሬ ተይዘው የነበሩት ኣብዱ ኑር፣ ኢብራሂም ኣብዱላዚዝ እና ሁሴን ኣብዱልሙኒም የተባሉ ከ፳ ቀን በፊት ወደ ከደብረዘይት ኣየር ሃይል ጀርባ በሚገኘው ምስጢራዊ የግድያ ማእከል ተወስደው ከተገደሉ በኋላ መቀበራቸውን የደሕንነት ቢሮ መረጃዎች የጠቆሙ ሲሆን እንደ ምንጮቹ ገለጻ ይህ ለሕወሓት የተለመደ ስራ መሆኑን ገልጸው በተለያዩ የደህንነት ምስጢራዊ እስር ቤቶች ከስምንት ሺህ አስከ ኣስር ሺህ የሚደርሱ አስረኞች በጨለማ ክፍል ውስጥ አንደተቆለፈባቸው ኣስረድተዋል።

Monday, January 25, 2016

የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከካርታ ስራ ድርጅት ወጥቶ በደህንነት መስሪያ ቤት እንዲሰራ መደረጉ መሬት እንደፈለጉ ለመስጠት እንዲመች ነው ተባለ

በመረጃና ደህንነት ኤጀንሲ ( ኢንሳ) ውስጥ ተቀጥሮ የሚሰራ አንድ ከፍተኛ ባለሙያ ለኢሳት እንደገለጸው፣ የኢትዮጵያን የመሬት መረጃ የሚሰበስብ የኢትዮጵያ ካርታ ስራ ኤጀንሲ የተባለ መስሪያ ቤት ቢኖርም፣ መንግስት ፎቶ የማንሳቱ ስራ በኢንሳ ስራ ማድረጉ የተለያዩ አላማዎችን ለማስፈጸም ነው ይላል። የመረጃ ደህንነት ኤጀንሲ በአንድ ብሄር የተያዘ፣ ከመከላከያው ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው እንዲሁም ለወያኔ ድርጀቶችና ደጋፊዎች መሬት በመስጠት ፣ የወያኔን የፖለቲካ ኢኮኖሚ ደግፈው እንዲይዙ ለማድረግ ነው ይላል። እስካሁን 46 የፎቶ መቆጣጠሪያ ምልክቶች ተስርተው ያለቁ ሲሆን፣ የአየር ላይ ፎቶ የማንሳቱ ስራ እየተሰራ እያለ ለ2 ሳምንታት በአየር ጸባይ ምክንያት እንዲሁም በአካባቢው እየተነሳ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞ የተነሳ የአየር መቆጣጠሪያ ምልክት ለማቆም ባለመቻሉ እንዲቆም ከተደረገ በሁዋላ፣ ፎቶ የማንሳቱ ስራ እንደገና ተጀምሯል። በመጀመሪያው ዙር የሚካሄደው የፎቶ ማንሳት ስራ ከመተማ እስከ ቋራ ያለውን ወደ 365 ኪሜ እርዝመት ያለው መሬት የሚሸፍን ሲሆን ፣ በሂደትም በቤንሻንጉል ክልል አካባቢ ያለውን ፎቶ የማንሳቱ ስራ ይቀጥላል።
አሁን አንገብጋቢው ነገር ይላል ባለሙያው፣ በጎንደርና በሱዳን እንዲሁም በጎንደርና በምእራብ ትግራይ የሚሰሩ የአየር መቆጣጠሪያ ምልክቶች እንዳይሰሩ የአካባቢው ህዝብ በንቃት መጠበቅ እንዳለበት ባለሙያው ገልጿል

በኮንሶ ታጣቂ ሃይሎች ህዝቡን በማዋከብ ላይ ናቸው

ኮንሶ ራሱን ችሎ በዞን ደረጃ ሊተዳደር ይገበዋል በሚል ህዝቡ ከወራት በፊት ያነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የጸጥታ ሃይሎች የተለያዩ ወጣቶችና ጎልማሶችን ይዘው ካሰሩ በሁዋላ፣ ጥያቄው የአርበኞች ግንቦት 7 እንጅ የህዝቡ አይደለም ብላችሁ ፈርሙ በማለት ካለፉት 3 ሳምንታት ጀምሮ ቅስቀሳ ሲያካሄዱና ፊርማ ሲያሰባስቡ ቆይተዋል። ይሁን እንጅ ጥያቄው የአካባቢው ህዝብ በጉልበት ጥያቄያቸውን እንዲቀይሩ ለማድረግ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በመቃወማቸው፣ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌደራልና የደቡብ ክልል ልዩ ሃይሎች አካባቢውን ተቆጣጥረው ህዝቡን እየመረጡ ማሰር በመጀመራቸው፣ ነዋሪዎች ከአካባቢው እየሸሹ ነው።
የጸጥታ ሃይሎች የሚያደርሱትን ጫና በመቃወም ካለፉት ሶስት ሳምንታት ጀምሮ ትምህርት ቤቶች እና የተለያዩ መስሪያ ቤቶች መዘጋታቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል። በዛሬው እለት በፋሻ ፣ ዱሪያና ኮልሜ ቀበሌዎች የልዩ ሃይል አባላት በሌሊት በመግባት ህዝቡን በመክበብ በግድ እንዲፈርም ለማድረግ ቢሞክሩም አልተሳካላቸውም።
የወረዳው የኢህአዴግ አባላት ጥያቄው የህዝብ ነው ብለው ጽፈው በመላካቸው ወቀሳ የደረሰባቸው ሲሆን፣ የወረዳው አፈጉባኤና ሌሎች የወረዳው ባለስልጣናትም ከስልጣን መነሳታቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል

በስዊዘርላንድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ

ኢትዮጵያውያኑ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ጽ/ቤት ፊት ለፊት በመገኘት የመንግስት ወታደሮች በኦሮሞ እና በተለያዩ አገሪቱ ክፍሎች በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚወስዱትን እርምጃ አውግዘዋል።
የሰልፉ አስተባባሪ ከሆኑት መካከል ዶ/ር ዘውዱ ነቺሳ ለኢሳት እንደገለጹት፣ የተለያዩ ጥያቄያቸውን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለአፍሪካ ክፍል አቅርበዋል። ጉዳዩን እንደሚከታተሉት ባለስልጣናቱ መግለጻቸውንና የተመድ ከፍተኛ ኮሚሽነር በተገኙበት ደብዳቤ ቀርቦላቸዋል። ኮሚሽነሩም ጉዳዩን በቅርብ እንደሚከታተሉት ቃል መግባታቸውን ዶ/ር ዘውዱ ገልጸዋል
በተቃውሞ ሰልፉ ላይ የተገችው ጫልቱ ሙሃመድ በአገር ቤት የመንግስት ወታደሮች በህዝቡ ላይ የሚፈጽሙትን ግድያ ለመግለጽ ቃላት እንደሌላት ተናግራ፣ ተቃውሞዋን ለማሰማት ወደ አደባባይ መውጣቷን ተናግራለች።

ገዢው ፓርቲ የህዝብን ተቃውሞ ለማብረድ የሚወስደው እርምጃ የይስሙላ ነው ሲሉ አባላቱ ገለጹ

ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ ከሕዝቡ እየደረሰበት ያለውን ተቃውሞ ለማርገብ ከክልል አስከ ቀበሌ ባሉት መዋቅሮቹ
አባሎቹን ማባረር ቢጀምርም ከፍተኛ አመራሩን ያላካተተ መሆኑ ከወዲሁ በራሱ አባሎች ተቃውሞ እያስከተለበት ነው።
ኢህአዴግ በነሀሴ ወር 2007 ዓ.ም በመቀሌ ከተማ ባካሄደው 10ኛው ድርጅታዊ ጉባዔው የመልካም አስተዳደር
ችግሮች ከፍተኛ ደረጃ መድረሳቸውን በማመን የማጥራት ሥራው ከከፍተኛ አመራሩ ጀምሮ እንዲካሄድ ውሳኔ ያሳለፈ ይሁን
እንጂ ከፍተኛ አመራር ውስጥ በሙስና የሚጠረጠሩት ነባሮቹ የህወሀት አመራሮች ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ቁርጠኛ
እርምጃ ለመውሰድ ሳይችል ቀርቶአል፡፡
ግንባሩ ሕዝቡን በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ እርምጃ እየወሰድኩኝ ነው ለማለት ያህል የመልካም አስተዳደር
ንቅናቄ በሚል ትልልቆቹን ሙሰኞች በጉያው አቅፎ የወረዳና ቀበሌ አመራሮችን ወደማባረር ማዘንበሉ የግንባሩ ውሳኔ
መተግበር እንደማይችል ፍንጭ ያሳየበት ተጨባጭ ክስተት ነው ሲሉ አባሎቹ እየተቹት ነው።

ንግድ ሚኒስቴር በስኳር መሸጫ የችርቻሮ ዋጋ ላይ ጭማሪ አደረገ

ጭማሪው በኪሎ ግራም 3 ብር ከ40 ሳንቲም ሲሆን ከፍተኛ ነው በሚል እየተተቸ ነው፡፡
ሚኒስቴሩ ለዚህ ጭማሪ የሰጠው ምክንያት የማምረቻ ዋጋ ጭማሪ አሳይቶአል የሚል ቢሆንም ለስኳር ኮርፖሬሽን ቅርበት
ያላቸው ምንጮች ግን መንግስት ከድርቁ ችግር ጋር በተያያዘ ከፍተኛ የሆነ የፋይናንስ ቀውስ ውስጥ በመግባቱና
ስኳር መሠረታዊ ፍላጎት አይደለም በሚል እንዲጨመር መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
የስኳር የማምረቻ ዋጋ በኪሎግራም ከ 7 ብር እንደማይበልጥ የጠቀሱት ውስጥ አዋቂዎች፣ ነገር ግን ዋጋ እንዲያረጋጉ በተቋቋሙ
ሸማች ማህበራት በኩል ለአዲስአበባ ነዋሪዎች አንድ ኪሎ በ15 ብር እንዲሸጥላቸው ሲደረግ ቆይቶአል፡፡ ካለፈው ሳምንት
ጀምሮ በድንገት የአንድ ኪሎ ስኳር ዋጋ 18 ብር ከ40 ሳንቲም እንዲሆን ተደርጎአል፡፡ ጭማሪውን
ተከትሎ በመደበኛ ሱቆች የአንድ ኪሎ ግራም ስኳር የችርቻሮ ዋጋ እስከ ብር 25 አሻቅቦአል፡፡
ይህ ያልተጠበቀ የዋጋ ጭማሪ በተለያዩ የምግብ ውጤቶች ላይ ሊንጸባረቅ ስለሚችል በቀጣይ በምግብ ነክ ውጤቶች
ላይ የማይናቅ የዋጋ ንረት ያስከለትላል የሚል ስጋት አሳድሮአል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ የነዳጅ ምርትም በኣለም አቀፉ ገበያ በከፍተኛ ሁኔታ ቢጨምርም፣ አሁንም መንግስት የተለያዩ
ምክንያቶችን በመደርደር የዓለም ገበያን ተከትሎ ዋጋ ለመቀነስ እምቢታ ማሳየቱ የሚታወስ ነው፡፡
የመንግስት ሰራተኞች የኑሮ ውድነቱን መቋቋም እንደተሳናቸው በተለያዩ ጊዜዎች ሲገልጹ ቆይተዋል።

ዛሬ በሐዋሳ ለ6ኛ ግዜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ | #ለሐዋሳ እንጸልይ!

(ዘ-ሐበሻ) ዘ-ሐበሻ ትናንት እሁድ በዘገበችው መሰረት ለ3 ጊዜያት የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር:: ዛሬ ከአዋሳ አካባቢ ያነጋገርናቸው ወገኖች እንደገለጹልን ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በ24 ሰዓታት ውስጥ ለ6ኛ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጡ ተከስቷል::
ይህ ዜና ከተጠናከረበት 20 ደቂቃ በፊት ለ6ኛ ጊዜ የመሬት መንቀጥቀጡን ያስታወቁት ዘ-ሐበሻ ያነጋገረቻቸው ወገኖች በደረሰው አደጋ በርካታ ወገኖች ወደ ሆስፒታል እንደተወሰዱ… በፎቅ ላይ የሚኖሩ ወገኖችም ወደ ምድር መወረዳቸውን ነግረውናል::
በሐዋሳ ነዋሪው በከፍተኛ ሁኔታ ተደናግጦ ይገኛል::
ለሐዋሳ እንጸልይ!

Sunday, January 24, 2016

ወይ አቶ አባይ ፀሐዬ ሸመጠጠው – አድ አዳማ

አቶ አባይ ፀሐዬ በኦሮሚያ ውስጥ የተነሳውን ሕዝባዊ ተቁዋሞ አስምልክቶ በተደጋጋሚ የድንፋታ ቃላት ሲናገሩ መቆየታቸው ከማንም የተሸሸገ አይደለም ይሁንና ዛሬ ዛሬ ደሞ የኦሮሞ ሕዝባዊ አመፅ ተጠናክሮ መቀጠሉ ስላሰጋው ለማስተባበል የት እንደሆነ በማይታወቅ ቦታ ቃለመጠይቅ ብጤ ለማድረግ ሞክሮ ነበር። ይህ ቃለ መጠቅ ከማስተባበል ይልቅ የተባሉት የትምህከት ቃላት በትክክል አውዲኦና ቪዲዎ የታከለበት ማረጋገጫ በራሱ በአቶ አባይ ፀሐዬ የተሰጠ መግለጫ ነው።በመጀመሪያ የጠያቂውን ሁኔታ ስንመለከት ዋ ከተሰጠህ ጥያቄ ትንሽ ዝንፍ ብትል ዋጋህን ታገኛለህ ስለተባለ ከመጠየቅ ይልቅ በመርበትበትና ሕዝባዊ አመፁን በመወንጀል ግዜውን የጨረሰ ይመስላል።ታዲያ የአቶ አባይ ፀሐዬ መልስ ልክ አፈትልኮ እንደወጣው ድምፅ በድንፋታ ታጅቦ ባይሆንም ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ ማስተር ጥፋቱን ገና ከጥንስሱ የተቃወሙት የኦህዴድ አባላት ላይ ጣታቸውን ከመጠቆም ወደሗላ አላሉም።በቃለ መጠይቁ ላይ እንደሰማሁት ከሆነ አቶ አባይ ፀሐዬ አፈትልኮ የወጣው ድምፅ የኔ አይደለም ከማለት ይልቅ እኔ ጎንደር አልነበርኩም, እስቲ ቪዲዮውን ያምጡ , እስቲ የተናገርኩትን ሙሉ አረፍተ ነገር ያሰሙ እያሉ ግዜያቸውን ጨርሰውታል። አቶ አባይ አክሎም ህወሓት ወይም የፌደራል መንግስት በኦሮሚያ የተነሳው ሕዝባዊ ተቁዋሞ ውስጥ እጁን አላስገባም ብሎ ለማስተባበል ሞክራል። ለዚህ መልስ ይሆን ዘንድ ኦህዴድ ውስጥ ያሉትን ውድ የኦሮሞ ልጆችን ማስተር ጥፋቱን ስለተቃወሙ ብቻ ከኦህዴድ ባለስልጣናት ይልቅ የህወሓትና የፌደራል መንግስቱ ቱባ ባለስልጣኖች አባይ ፀሐዬንና ጌታቸው ረዳ ነበሩ ሲደነፉባቸው የነበሩት። በተጨማሪም የኦሮሚያ ፖሊስ የሕዝቡ ጥያቄ አግባብና ተገቢ ነው ባለ ወቅት የኦሮሚያ ፖሊስን ትጥቅ አስፈትተው ኦሮሚያ ውስጥ ከፈተኛ  ጭፍጨፋ ያካሔዱት የአጋዚ ጦርና የፌደራል ፖሊስ ናቸው። ይህም ጭፍጨፋ ሲካሔድ  under direct command of TPLF መሆኑ ከማንም የተሸሸገ አይደለም። ታዲያ ከዚህ በላይ ጣልቃ ገብነት ከየት ይምጣ።
ዘንድሮ ይሁን አምና ወይም ካቻምና ጎንደር ሔጄ አንድም ስብሰባ ብቻዬንም ሆነ ከሌሎች ሰዎች ጋር  አላካሔድኩም  ሙሉ ቪዲዮዋን ከነምስሌ ከነንግሬ ያምጡዋት  ያለው የዚሕ የድምፅ ተቀርፆ መውጣት ስለተደጋገመበት ምናልባት ከቪዲዮ አቀራረጽ ማን ድምፁን ቀርፆ እንዳወጣው ማወቅ በቀላሉ ይቻላል ከሚል ግምት እንጂ ስለድምፁ የሱ መሆን ቅንጣት ታህል ጥርጣሬ እንደሌለ አባይ ፀሐዬም ሆነ መላው ሕዝብ በደንብ ያውቃል። እሱም አልካደም።

የአቶ አባይ ፀሐዬ ንግግር እኔን እንደገባኝ ከሆነ  ቢያንስ ሁለት ነገር ጠቆም አድርገውን አልፈዋል
1ኛ. ከሁከትና ግርግር ለመጠቀም ከሚያስቡ ብለው ካሉ በሗላ ጥቆማው ያነጣጠረው አንዳንድ የኦሮሚያ ልዩ ዞን አስተዳደሮችና አንዳንድ የአዲስ አበባ ሀብታሞች ብሎ ቀጠለና የኦሮሚያ ሀብታሞች አለ እዚጋ ልብ ማለት የሚያስፈልገው ሙሉ አዲስ አበባና ዙሪያዋን አፍነው በጉልበት ስለያዙት የህወሐት ቱጃሮች አንድም ነገር ያለው የለም ። ከዚህ አባባሉ የተረዳሁት ነገር ቢኖር ወያኔ ማስተር ጥፋቱን የተቃወሙትን የኦሮሚያ ልዩ ዞን  አስተዳደሮችና  የኦሮሚያ ሀብታሞች ላይ ልዩ የሆነ የማዋከብ ዘመቻ ለመጀመር እቅድ ውስጥ እንዳሉ  ነው። ለዚህም መረጃ የሚሆነው በቅርብ አፈትልኮ የወጣው የአባይ ፀሐዬ ድምፅ ውስጥ ለኦህዴድ ባለስልጣናት የተሰጣቸው ትእዛዝ ማስተር ጥፋቱን የተቃወሙትን የኦሮሚያ አስተዳደሮችን አባሩ የሚል ነው።

የሰላምን በር ጠርቅሞ የዘጋው ወያኔ ነው!!! – አርበኞች ግንቦት 7

የወያኔ አረመኔያዊ ያገዛዝ ስርዓት በህዝባችን ላይ የሚፈጽመው አፈና ግድያና ዝርፊያ በመጠኑም በዘግናኝነቱም ይበልጥ እያገጠጠ ስለመጣ ለወትሮው እንዳላየ አይተው የሚያልፉትን ምዕራባውያን ለጋሾቹንና ወዳጆቹን ሳይቀር በጅጉ ማሳስብ ጀምሯል።

Friday, January 22, 2016

የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ላይ ምልክት ማድረግ ሊጀመር ነው

ጥር ፲፫ (አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ወይም ኢንሳ አማካኝነት ሲካሄድ የከረመው የሁለቱን አጎራባች አገራት ድንበር የአየር ላይ ፎቶ ወይም erial photo acquisition የመስራቱ ስራ ለሁለት ሳምንት ከተቋረጠ በሁዋላ፣ ሰሞኑን እንደገና የተጀመረ ሲሆን፣ በድንበሩ ላይ ምልክት ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን የደህንት መስሪያ ቤት ምንጮች ገልጸዋል።
በአሁኑ ሰአት በድንበሩ ዙሪያ መሬት ላይ ምልክት የማድረግ በእንግሊዝኛ pre mark ground control points እንዲሁም የካርታ ስራውን ለመስራት እንቅስቃሴ ተጀምሯል። ኢንሳ በአማራ ክልል መንግስት ስም በአርሶ አደሮች የእርሻ እና የግጦሽ መሬት ላይ ምልክት የማድረጉን ስራ ለመጀመር የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአካባቢው ህዝብ እና የወረዳ ባለስልጣናት ምልክት በማስቀመጡ ስራ ላይ ትብብር እንዳያደረጉ የደህንነት ምንጮች ምክራቸውን ለግሰዋል።
የመለያ ምልክቶቹ ከአሸዋ፣ ስሚንቶና ጠጠር የሚሰሩ ሲሆን ፣ 3 ሜትር ቁመት እና 60 ሴንቲሜትር ስፋት ያላቸው በነጭና ጥቁር የተቀቡ ይሆናሉ። የቀለም አቀባባቸውም ነጭ፣ ጥቁር፣ ነጭና ጥቁር የሚሆኑ ሲሆን መሃሉ ነጭ ይሆናል።
ኢንሳ ተመሳሳይ የአየር ላይ ፎቶዎችን በወልቃይት ፣ አብደራፊ እንዲሁም ምእራብ አርማጭሆ አካባቢዎች የሚያነሳ ሲሆን፣ ሰፊ የሆነ መሬት ወደ ትግራይ ክልል በመውሰድ የወልቃይት የስኳር ፋብሪካ ፕሮጀክት እንዲጠቀምበት እያዘጋጀ ነው።
የስኳር ፋብሪካው አቮሪንጋ በሚባል የእስራኤል ኩባንያ የሚሰራ ይሆናል።

ድንገተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ ይነሳል የሚል ስጋት የገጠመው መንግስት ማረጋጊያ ያላቸውን እርምጃዎች ሊወስድ ነው

ጥር ፲፫ (አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በታህሳስ ወር መግቢያ ላይ በጦር ሃይሎች አካባቢ በሚገኝ አንድ የደህንነት ጽ/ቤት ውስጥ ከ50 በላይ የሚሆኑ የደህንነት አባላት በተሳተፉበት ስብሰባ ላይ ከማስተር ፕላኑ፣ ከኑሮ ውድነቱና ከሌሎችም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ጋር በተያያዘ ህዝቡ በድንገት ወደ አደባባይ ሊወጣ ይችላል የሚል መልእክት ተላልፏል።
በስብሰባው ላይ ለችግሩ መፍትሄ ያስገኛሉ የተባሉ በርካታ የመፍትሄ ሃሳቦች ቀርበዋል። የጦር መሳሪያዎች ያሉዋቸውን ሰዎች ተከታትሎ ከመቀማት ጀምሮ በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ስራዎችን መስራት እንደሚያስፈልግ ተሳታፊዎች ስምምነት ላይ ደርሰዋል። በእስር ላይ የሚገኙትን የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ አባላት በከፊልና በአጠቃላይ መፍታት ህዝበ ሙስሊሙ ከተነሳው ወላፈን እንዲርቅ እንደሚያደርገው የተነገረ ሲሆን፣ ይህን ለማስፈጸም በውጭ አገር የሚገኙ የሙስሊም ድርጅቶች እንዲጋበዙና በታሳሪዎች ስም ይቅርታ እንዲጠይቁ ማድረግ ፤ ይህን የሚያደርጉ ሰዎች ቢቻል ከማህበረሰቡ ጋር ግንኙነት ያላቸው ቢሆኑ እንደሚመረጥ ስትራቴጂ ተነድፏል።

የአለማቀፍ ድርጅቶች በኢትዮጵያ የተከሰተው ረሃብ ከአቅም በላይ ነው ቢሉም መንግስት እያጣጣለው ነው

ጥር ፲፫ (አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሪዩተርስ ዛሬ ባወጣው ዘገባ በኢትዮጵያ አስከፊ በተባለው ረሃብ 400 ሺ ህጻናት ከፍተኛ አደጋ አንዣቦባቸዋል። አንድ አስረኛ የሚሆነው ህዝብ ራሱን መመገብ በማይችልበት ደረጃ መደረሱን ዘጋባው አመልክቶ፣ የአለማቀፉ ማህበረሰብ የሚሰጠው ምላሽ አነስተኛ መሆን ችግሩን አሳሳቢ ደረጃ ላይ አድርሶታል።
በአሜሪካ የህጻናት አድን ድርጅት ፕሬዚዳንት ካሮሊን ማይልስ አፋርና አማራ ክልሎችን መጎብኘታቸውን ለዜና ምንጩ ገልጸው፣ በምግብ እጥረት የተነሳ ሆስፒታል የገቡ ህጻናትን ማየታቸውን ተናግረዋል።

በኦሮምያና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተፈጸሙ ወንጀሎችን የሚያወግዙ የተቃውሞ ሰልፎች ተደረጉ

ጥር ፲፫ (አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጥር 13 ቀን 2008 ዓም በአውስትራልያ ብሪዝቤን ከተማ የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በአይነቱ ልዩ የተባለለት ነው። ህብረ ብሄራዊነት በተንጸባረቀበት በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ተሳታፊዎቹ በጋራ የኢትዮጵያን መንግስት ያወገዙ ሲሆን፣ በተለይም ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ በዜጎች ላይ እየፈጸመ ያለውን ግድያ ማፈናቀልና እስራት፤ በጎንደር ገበሬዎችን በማፈናቀል ለሱዳን መሬት ቆርሶ ለመስጠት እያደረገ ያለውን ታሪካዊ ክህደትና በኢትዮጵያ ኦጋዴን ተወላጆች ላይ እየፈጸመ ያለውን ጭፍጨፋ በጋራ አውግዘዋል።
ከብሪዝቤን ኩዊንስ ፓርክ የተነሳው ሰልፍ እልህና ቁጣ የተቀላቀለበት መፈክር በማሰማት ወደ ኩዊንስላንድ ፓርላማ መቀመጫ ቦታ አምርቷል።በፓርላማው ፊት ለፊት በመሰባሰብ ድምጻቸውን በማሰማት ላይ የነበሩትን ሰልፈኞች ለማናገር ሁለት የመንግስት ተወካዮች የተገኙ ሲሆን፣ ሰልፈኞቹም በተወካዮቻቸው አማካኝነት መልዕክታቸውን አቅርበዋል። በኩዊንስላንድ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ማህበር፤ በኩዊንስላንድ የኦሮሞ ማህበረሰብ ማህበርና በኩዊንስላንድ የኦጋዴን ማህበረሰብ ማህበር ተወካዮች በየተራ የኢትዮጵያ መንግስት በዜጎቹ ላይ እየፈጸመ ያለውን ኢ ሰብአዊ ድርጊቶችን በዝርዝር አቅርበው። አውስትራልያ ያሏትን እድሎች ተጠቅማ ጫና መፍጠር እንድትችል ተመጽኗቸውን አሰምተዋል።

Thursday, January 21, 2016

Ethiopia’s Anti-Terrorism Law: A Tool to Stifle Dissent

A Legal Analysis by International Lawyers
“While legitimate anti-terrorism laws exist, Ethiopia's Anti-Terrorism Proclamation criminalizes basic human rights, especially freedom of speech and assembly. The law defines terrorism in an extremely broad and vague way so as to give the government enormous leeway to punish words and acts that would be perfectly legal in a democracy,” said Lewis Gordon, editor of the report and Executive Director of the Environmental Defender Law Center. “It also gives thepolice and security services unprecedented new powers, and shifts the burden of proof to the accused. Worse still, many of those charged report having been tortured, and the so-called confessions thathave been obtained as a result have been used against them at trial,” he continued.

የአውሮፓ ህብረት ጠንካራ የተባለውን ውሳኔ በኢትዮጵያ ላይ አሳለፈ

ጥር ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 7ቱ ዋና ዋና የአውሮፓ ህብረት የፖለቲካ ድርጅቶች ኢትዮጵያን በተመለከተ የቀረበውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ አጽድቀዋል። አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የቀኝ አክራሪዎች ብቻ ውሳኔውን ተቃውመውታል። ለህጉ መጽደቅ ከፍተኛ ትግል ሲያካሂዱ የሰነበቱት የህብረቱ የፓርላማ አባል ሚስ አና ጎሜዝ በውሳኔው መደሰታቸውን ተናግረዋል። “በጣም ጠቃሚ የሆነ ሰነድ ነው፣ በተለይ ዋና ዋና የሚባሉት የፖለቲካ ድርጅቶች የውሳኔው ሰነድ ሳይለወጥ እንዲቀጥል ማድረጋቸው ትልቅ ነገር ነው” ሲሉ አክለዋል።
የተላለፈው ውሳኔ ምን ያክል ጠንካራ ነው የተባሉት አና ጎሜዝ፣ በኦሮሞ እና በሌሎችም ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመውን ግድያ ያወግዛል፣ እስክንድር ነጋን የመሰሉ ጋዜጠኞች፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ ሌሎች ፖለቲከኞችም እንዲፈቱ ይጠይቀዋል ብለዋል። ባለፉት 10 አመታት በኢትዮጵያ ላይ ከተላለፉት ውሳኔዎች ውስጥ የአሁኑ ጠንካራ መሆኑን የገለጹት ሚስ አና ጎሜዝ በተለይ ዋና ዋና የሚባሉት 7ቱ የፖለቲካ ድርጅቶች እንዳለ መቀበላቸው ትልቅ ውጤት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የህብረቱ ባለስልጣናትንና አዲስ አበባ የሚገኙ የህብረቱን ተወካዮች ለማግባባት ቢሞክርም፣ የህብረቱ የፓርላማ አባላት ግን አንቀበልም በማለት ማጽደቃቸውን አክለዋል

በጋምቤላ በተነሳው ግጭት በርካታ ሰዎች ተጎዱ

ጥር ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የከተማዋ ምንጮች እንደገለጹት ጥር 11 ፣ 2008 ዓም 11 ሰዓት አካባቢ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ በተነሳው ግጭት በርካታ ተማሪዎች ተጎድተዋል።ግጭቱ ወደ ከተማው በመስፋፋቱ በርካታ ሰዎች ሲቆስሉ ፣ መኪኖችም ተሰባብረዋል። የግጭቱ መንስኤ በትክክል አልታወቀም።
የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና የፈደራል አባላት ከተማዋን መቆጣጠራቸውን የገለጹት ነዋሪዎች፣ ግጭቱ ለጊዜው የቆመ ቢመስልም በማንኛውም ሰአት ሊነሳ ይነሳ ይችላል በሚል ከፍተኛ ስጋት አለ። ከሁለት ሳምንት በፊት ንኝያንግ በሚባለው ወረዳ በተነሳው ተመሳሳይ ግጭት 15 ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ምንጮች አክለው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ያወጣችው የጸረ ሽብርተኝነት ህግ እንዲሰረዝ አለማቀፍ የህግ ባለሙያዎች ጠየቁ

ጥር ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኦክላንድ ኢንስቲቲዩት እና ኢዲኤል ሲ የተባሉት መንግስታዊ ድርጅቶች በጋራ ባስጠኑት ጥናት፣ የኢትዮጵያ የጸረ-ሽብርተኝነት ህግ አለማቀፍ መስፈርቶችን ያላሟላ በመሆኑ ለውጥ እሰከሚካሄድበት ጊዜ ድረስ ጥቅም ላይ እንዳይውል ጠይቀዋል።
ድርጅቶቹ ጥናቱን ያወጡት የአፍሪካ ህብረት 26ኛ ጉባኤ በሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ላይ ትኩረት አድርጎ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ መሆኑን ምክንያት በማድረግ ነው።
ጥናቱ በአለማቀፍ ህግ እውቅና ባተረፉ ባለሙያዎች የተጠና መሆኑን ተቋሞቹ ለኢሳት በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል።በኢትዮጵያ ያለው የፀረ-ሽብር ህግ መንግስት ሽብረተኝነትን እንደፈለገ በመተርጎም በዲሞክራሲያዊ አገሮች ተቀባይነት ያላቸውን ድርጊቶች ወንጀል አድርጎ በማቅርብ እርምጃ ለመውሰድ ይጠቅመዋል የሚሉት ጥናቱን የመሩት ሊዊስ ጎርዶን፣ ህጉ ለፖሊስና ለደህንንት ሃይሎች አዲስ ስልጣን በመስጠት፣ ንጽህናን የማረጋገጡን ሚና ለተከሳሽ ይሰጣል ብሎአል።
የጸረ ሽብርተኝነት ህጉ መሬታቸውን እንዳይነጡ በጠየቁ ዜጎች ላይ ሳይቀር ተፈጻሚ መሆኑን የኦክላንድ ኢንስቲቲዩት ዳይሬክተር አኑራዳሃ ሚታል ገልጸዋል። የአለማቀፉ ማህበረሰብ የፖለቲካ ንግግሮችን በወንጀልነት የሚያየውንና ና ነጻነትን የሚደፈጥጠውን ህግ በአስቸኳይ እንዲወገድ መጠየቅ እንዳለበት ሚታል አክለዋል።
ህጉ ከአለማቀፍ ህጎች ጋር በሚስማማ መልኩ እስኪቀየር ድረስ፣ የጸረ ሽብር ህጉ በስራ ላይ እንዳይውል ድርጅቶቹ በመግለጫቸው ጠይቀዋል።

መንግስት ከፍያ የተፈጸመባቸውን ቤቶች ሰርቶ ማስረከብ አልቻለም ሲሉ ደንበኞች ተናገሩ

ጥር ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በ2005 ዓም መንግስት 40 በ 60 በሚል ላወጣው መርሃ ግብር ከ163 ሺ በላይ ህዝብ የተመዘገበ ቢሆንም፣ እስካሁን ቤቶችን ሰርቶ ለማስረከብ አልቻለም። በፕሮግራሙ መሰረት 40 በመቶውን ቤት ፈላጊዎች ሲከፍሉ፣ ቀሪው 60 በመቶ በባንክ ብድር ይሸፈንላቸዋል።
ሆኖም መቶ በመቶ ለከፈሉ ቅድሚያ ይሰጣል በመባሉ ከ8 ሺ በላይ ነዋሪዎች የተጠየቁትን መቶ በመቶ ከፍለው ቤቱን ለመረከብ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።
የአ/አ ከተማ አስተዳደር የቤት አቅርቦቱ ከፍላጎቱ ጋር ያልተጣጣመ ነው ያለ ሲሆን፣ የግንባታ እቃዎች ዋጋ ጨምሮአል በሚል ሰበብ ቀደም ሲል ለቤቶቹ ከሰጠው ዋጋ እጅግ የላቀ ዋጋ ለመጨመር መዘጋጀቱ ቤቶቹን እየተጠባበቁ ያሉ ወገኖችን አስደንግጦአል።
አስተዳደሩ ባለፈው አመት ሰኔ ወር 1 ሺ 200 ቤቶችን አስተላልፋለሁ በሚል ቃል ገብቶ የነበረ ቢሆንም ከስድስት ወራት ተጨማሪ ጊዜ በላይ ይህንንም አነስተኛ ቁጥር ማስረከብ አለመቻሉን፣ በዚህም ምክንያት ከዘመድ አዝማድ ተበዳድረው ለቤቱ ከሁለት አመት በፊት ክፍያ የፈጸሙ ዜጎች ችግር ላይ መውደቃቸውን በተደጋጋሚ ቢገልጹም ሰሚ አላገኙም።
አንድ ቤት ፈላጊ ስለጉዳዩ ለዘጋቢያችን አስተያየቱን ሲሰጥ ከሁለት አመት በፊት ቤቶቹ በ18 ወራት ተገንብተው ይተላለፋሉ በተባለው መሰረት መንግስትን በማመን 300ሺ ብር መክፈሉን ነገርግን ከ24 ወራት ቆይታ በሁዋላም የቤቶች ግንባታ መጓተቱን ሲሰማ እጅግ ማዘኑን ተናግሯል።የ40 በ60 ቤቶች መቼና እንዴት እንደሚተላለፉ በአ/ አ አስተዳደር በኩል ግልጽ የሆነ መረጃ አለመሰጠቱን የጠቀሱት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ በአስተዳደሩ ችግር ምክንያት ገንዘባቸውንም አስይዘው ለቤት ኪራይ መዳረጋቸው ተጨማሪ ጉዳት አስከትሎባቸዋል።

Wednesday, January 20, 2016

በአንዳንድ አካባቢዎች የጥምቀት በአል የተቃውሞ መገለጫ ሆኖ ዋለ

ጥር ፲፩ (አሥራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የጥምቀትን በአል ለማክበር የወጡ ዜጎች የኢህአዴግ መንግስት በቅርቡ በኦሮምያ ክልል ነዋሪዎች ላይ የወሰደውን ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በማውገዝ የተለያዩ ተቃውሞችን አሰምተዋል። በአዲስ አበባ ጥቁር ልብስ ለብሰው ለመውጣት ዝግጅት በማድረግ ላይ የነበሩ ወጣቶች በደህንነቶች ጥቆማ እንዲያቆሙ ሲደረግ፣ በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ ወጣቶች የጸጥታ ሃይሎች የወሰዱትን እርምጃ የሚያወገዙ እንዲሁም ለትግል የሚያነሳሱ ባህላዊ ዘፈኖች ሲያቀነቅኑ ተደምጠዋል።
ገዢው ፓርቲ በአዲስ አበባ የሚገኙ ወጣት አባላቱን ለአንድ ሳምንት ያክል በመሰብሰብ በበአሉ እለት ተቃውሞ የሚያሰሙትን እንዲከታተሉ የሚያስችል ስልጠና ሰጥቶ ነበር።
ሳምንቱን በተቃውሞ ያሳለፈችውና የተቃውሞው ማእከልነቱን ከአምቦ የተረከበች የምትመስለው የምእራብ ሃረርጌዋ መኢሶ ከተማ፣ የጥምቀት በአልን የተቃውሞ ድምጿን ለማሰማት ተጠቅማበታለች። ተመሳሳይ ተቃውሞ በቡራዩ ከተማም ተካሂዷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ 9 ታዋቂ የትግራይ ተወላጆች ” ተደጋጋሚ ጭፍጨፋዎች እንዲቆሙ አስጨፍጫፊዎች መወገድ አለባቸው” በሚል መግለጫ አውጥተዋል።

የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን መንግስት ለማውገዝ በተዘጋጀው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ድምጽ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል

ጥር ፲፩ (አሥራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የህብረቱ አባላት አዘጋጅተው ባቀረቡት ሰነድ ላይ ህብረቱ ነገ ሃሙስ 11 ሰዓት ላይ ድምጽ ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ለህብረቱ የቀረበው የውሳኔ ሃሳብ የኢህአዴግ መንግስት በኦሮሞ ተወላጆች ላይ የወሰደውን ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እንዲሁም በመላ አገሪቱ የሚፈጽመውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ያወግዛል። በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲካኞችና ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እንዲፈቱ ይጠይቃል። ለኢትዮጵያ መንግስት የሚሰጠው እርዳታ በቅድመ ሁኔታ ላይ እንዲቀመጥም ያሳስባል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ራፖርተር በኦጋዴንና በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ወደ አገሪቱ ገብቶ እንዲያጣራ ከመንግስት ፈቃድ እንዲያገኝ በውሳኔ ሃሳቡ ላይ ተጠቅሷል።
ጠንካራ የተባለውን ውሳኔ ሃሳብ ለማሳለፍ ዛሬ በተለያዩ የፓርላማ አባላት መካከል ክርክር ተካሂዷል። የውሳኔ ሃሳቡ ሳይቀየር እንዳለ ከተላለፈ፣ በአውሮፓ ህብረትና በኢትዮጵያ መካከል ባለው ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ተጽኖ ይፈጥራል። የኢህአዴግ መንግስት የውሳኔ ሃሳቡ እንዳይጸድቅ በደጋፊዎቹ በኩል ከፍተኛ የዲፐሎማሲ ስራ እየሰራ ነው።
የህብረቱ አባላት በቅርቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖምን ጠርተው በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ጥያቄ አቅርበውላቸው ነበር፡፡ የአርበኞች ግንቦት7 ሊ/መንበር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋም ከወራት በፊት ከተለያዩ የህብረቱ ባለስልጣናት ጋር ተገናኝተው ስለኢትዮጵያ ውቅታዊ ሁኔታ ገለጻ ማድረጋቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያውያን ለምግብ ፍጆታ ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ የአለም አገራት በሁለተኛ ደረጃ ተቀመጠች

ጥር ፲፩ (አሥራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ተቀማጭነቱን እንግሊዝ ለንደን ያደረገው ሙቭኸብ የጥናትና ምርምር ተቋም በመላው ዓለም ባሉ አገራት በምግብ ወጪ ላይ ባደረገው ጥናት፣ ኢትዮጵያዊያን ኡጋንዳን በመከተል የሚያገኙት ወርሃዊ ደመወዝ አብዛኛውን ለምግብ ወጪ መሸፈኛ ያውሉታል።
ከአንድ እስከ ሶስት ያለውን ደረጃ የያዙት የምስራቅ አፍሪካ አገራት ሲሆኑ፣ በጥናቱ መሰረት ኡጋንዳውያን 275.86 ከመቶ ገቢያቸውን ለምግብ በማውጣት ቀዳሚ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን 257.24 ከመቶ ወጪ በማውጣት 2ኛ ፣ ኬንያውያን ደግሞ 215.04 ከመቶ በማውጣት 3ኛ ሆነዋል።
የምግብ ፍጆታ ወጪያቸው አነስተኛ ከሆነባቸው አገራት ውስጥ ኳታር በቀዳሚነት ደረጃ ላይ ስትቀመጥ፣ ማካዎ 2ኛ ኩዌት 3ኛ ደረጃን ይዘዋል ።

ለቤተ እስራኤላዊያን ማቋቋሚያ ልዩ በጀት ተመደበላቸው

ጥር ፲፩ (አሥራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የእስራኤል መንግስት በአገሩ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ቤተእስራኤላዊያን ማኅበረሰብ አባላት ማቋቋሚያ ይሆን ዘን 55 ሚሊዮን የእስራኤል ሻክል መመደቡን አስታውቋል።
ቁጥራቸው ከ 3 ሽህ 600 በላይ የሚሆኑት ቤተ-እስራኤላዊያን ከተቀረው የእስራኤል ማኅበረሰብ ጋር የውህደት መስተጋብር ያደርጉ ዘንድ ያስችላል የተባለውን ውሳኔ የአገሪቱ ፓርላማ በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል።
የቤተ እስራኤላዊያንን አቅም በመገንባት በትምህርትና በሥራ መስክ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማጎልበት ይረዳል የተባለው መርኅግብርን ለማስፈፀም አራት ዓመታት ሊፈጅ እንደሚችል የገንዘብ ሚንስቴሩ አስታውቀዋል ሲል ጄሩሳሌም ፖስት ዘግቧል።

Tuesday, January 19, 2016

በሶማሊያ በአሸባሪዎች የተገደሉት የኬኒያ ወታደሮች አስከሬን በክብር ወደ አገሩ ተመለሰ

ጥር ፲ (አሥር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ሕብረት ጦር አሜሶን ስር በመሆን በሶማሊያ ሰላም ለማስከበር ተሰማርተው የነበሩ የኬንያ ወታደሮች ባለፈው ሳምንት በአሸባሪዎች በተሰነዘረ ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ አስከሬናቸው ናይሮቢ ደርሷል።
የኬኒያ መከላከያ ሚንስትር የሆኑት ራቼሎ ኦማሞ ”በጣም ወሳኝ ዜጎቻችን! የወደቁ ጀግኖቻችን” ሲሉ ሟቾቹን አሞካሽተዋል።መንግስት የሟች ወታደሮችን ስም ዝርዝር ለቤተሰቦቻቸው አስታውቋል። ካሳም መክፍሉ ታውቋል።
የአፍሪካ ሕብረት ጦር አሜሶንን በገንዘብና በትጥቅ ከሚያግዙት በቀዳሚነት ተርታ የሚሰለፈው የአውሮፓ ሕብረት በበኩሉ ጥቃቱን አውግዞ በሶማሊያ ዘላቂ ሰላምንና መረጋጋትን ለማስፈን ይቻል ዘንድ ከትጥቅ ትግል ይልቅ ፖለቲካዊ መፍትሔት ሊበጅለት ይገባል ብሏል።
በሶማሊያ ሰላም ለማስከበር ከተሰማሩት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ውስጥ ምን ያህሉ ሕይወታቸውን እንዳጡና የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው እስካሁን በግልፅ አይታወቅም። በተጨማሪም የሟች ቤተሰቦችና የኢትዮጵያዊያ ሕዝብ አሃዙን በውል ካለማወቁ በተጨማሪ አገራቸውን ወክለው ሰላም ለማስከበር ሲሉ የሞቱ የሰራዊቱ አባላት ብሄራዊ አቀባበል ሲደረግላቸው ታይቶ አይታወቅም። የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስቴር ሟቹ መለስ ዜናዊ መንግስት የሟች ወታደሮችን ቁጥር ለፓርላማ አባላት የማሳወቅ ግዴታ የለብንም ሲሉ መናገራቸው የሚታወስ ነው።

በዓለምአቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ ቢያሽቆለቁልም በኢትዮጵያ አሁንም የዋጋ ማሻሻያ አልተደረገም

ጥር ፲ (አሥር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመላው ዓለም የነዳጅ ዋጋ አሽቆልቁሏል። በኢራን ላይ የተጣለው የኢኮኖሚያዊ ማዕቀብ መነሳቱን ተከትሎ የነዳጅ አቅርቦት ምርት መትረፍረፉን የምጣኔ ሃብት ጠበብቶች እየገለፁ ነው። በየቀኑ ከግማሽ ሚሊዮን በርሜል በላይ ድፍድፍ የነዳጅ ዘይት የማቅረብ አቅሙ ያላት መሆኑን የኢራን ምክትል የነዳጅ ሚንስቴር የሆኑት ሮኬንዲ ጃቫዲ ማስታወቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
በአሁኑ ወቅት የአንድ በርሜል የነዳጅ ዘይት ዋጋ በአማካኝ 28 የአሜሪካን ዶላር ሆኖ ሳለ፣ በኢትዮጵያ ያለው ዋጋ ግን ቀድም ብሎ ሲሸጥበት በነበረበት ዋጋ እንዲቀጥል መደረጉ በህዝቡ የእለት ከእለት እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ጫናን ፈጥሯል።

የአዲስ አበባ መስተዳድር ማስተር ፕላኑን በግሉ ለመተግበር አቅም የለውም ተባለ

ጥር ፲ (አሥር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከ150 ላላነሱ ሰዎች ህይወት መቀጠፍ ምክንያት የሆነው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በኦህአዴድ በኩል ተቀባይነት እንደሌለው መገለጡን ተከትሎ የአዲስ አበባ መስተዳድር በአስተዳደር ክልሉ ስር በሚገኙ ቦታዎች ላይ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ ቢጀመርም፣ እንቅስቃሴው ከእልህና ከግራ መጋባት የመጣ በመሆኑ ውጤታማ አይሆንም ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወገኖች ይገልጻሉ።
ከመጀመሪያው ጀምሮ በእቅዱ የተለያዩ ደረጃዎች የተሳተፉ ምንጮች እንደሚሉት፣ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እቅድ ዋና አላማ፣ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ ለመጣው ቤት ፈላጊ ህዝብ የመኖሪያ ቤቶች መስሪያ ቦታ መፈለግ፣ ለዲያስፖራው መኖሪያ ቤት መገንቢያ እንዲሁም፣ የተለያዩ የዘመኑ ባለሃብቶች ለሚያቀርቡት የቦታ ጥያቄ መልስ መስጠት ነበር። በአዲስ አበባ ያለው ባዶ ቦታ፣ ከቦታ ፈላጊው ህዝብ ቁጥር ጋር ሲነጻጸር እጅግ አነስተኛ ነው የሚሉት ምንጮች ፣ መስተዳድሩ በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ ከተሞችን በግዛቱ ስር በማድረግ ፣ የመሬት ጥያቄዎችን ለመመለስ ያወጣው እቅድ፣የኦሮምያ ክልል እቅዱን ሊቀበለው ባለመቻሉ ሊሳካለት አይችልም። ሰፋፊ ቦታዎችን ከኦሮምያ ክልል እስካልወሰደ ድረስ ለሚቀርብለት የቦታ ጥያቄ መልስ ለመስጠት አየችልም፣ ከዚህ አንጻር ሲታይ ማስተር ፕላኑን በራሴ እተገብረዋለሁ ማለት ህልም ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

እነ አቶ ሃብታሙ አያሌው ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው

ጥር ፲ (አሥር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሽብር ወንጀል ተከሰው ነጻ የተባሉትና እንደገና ይግባኝ የተጠየቀባቸው አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሽ፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ እና አቶ አብርሃም ሰለሞን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቢቀርቡም እንደገና ሌላ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል።
ፍርድ ቤቱ ፣ አቃቤ ህግ በስር ፍርድ ቤት አልተመረመረልኝም ያለው ከብሄራዊ ደህንነትና መረጃ ማዕከል የተገኘው ማስረጃ፣ ማስረጃ ሳይሆን የመረጃ ትንተና የተሰጠበት ስለሆነ ‹ኦርጅናሉ› መረጃ ቀርቦ እንዲመረመር መስጠቱን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል።
ፍ/ቤቱ አቃቤ ህግ የታዘዘውን ማስረጃ ይዞ እንዲቀርብ ለጥር 24/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ለኪሳራ የተዳረጉ መለስተኛ ፋብሪካዎች ሰራተኞችን መቀነስ ጀመሩ

ጥር ፲ (አሥር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኤሌክትሪክ ሀይል መቆራረጥ ችግር እጅግ ተባብሶ ከመቀጠሉ ጋር ተያይዞ በተለይ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቁዋማት ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረጉ፣ ሰራተኞችም እየቀነሱ ነው።
የሃይል እጥረቱ ተባብሶ በአሁኑ ወቅት በእየለቱ ቢያንስ ለግማሽ ቀን ወደመጥፋት ደረጃ ተሸጋግሯል። ት/ቤቶች፣ሆስፒታሎች ፣ዳቦ ቤቶችና የመሳሰሉ ስራቸው እየተስተጉዋጎለ ሲሆን አምራች ተቁዋማት ሰራተኞችን እየቀነሱ ነው።
አንድ በዳቦ መጋገር ስራ የተሰማሩ ባለሀብት ሀይል ተቋርጦ የሚመጣበት ጊዜ የማይታወቅ በመሆኑ ምርት ለመቀነስ መገደዳቸውን፣ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ከነበሩዋቸው 10 ያህል ሰራተኞች ግማሽ ያህሉን ለማሰናበት መገደዳቸውን ገልጸዋል።ችግሩ በዚሁ ከቀጠለ ስራውን አቆማለሁ ብለዋል። አንዳንድ የፋብሪካ ውጤቶችም ባልተጠበቀ ሁኔታ የመሸጫ ዋጋቸው ላይ ጭማሪ እያሳዩ መሆኑ አስደንጋጭ ሆኖአል።
መንግስት በግልጽ በሚታይ ሁኔታ የሃይል እጥረት ቢያጋጥመውም አሁንም እንደ ጅቡቲ ላሉ ጎረቤት ሀገራት በርካሽ ዋጋ ሀይል መሸጡን ቀጥሎበታል።

Monday, January 18, 2016

“የሱዳን መሬት በኢትዮጵያ መያዙን የኢትዮጵያ መንግስት አምኖአል” ሲሉ የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ

ጥር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢብራሂም ጋንዱር ለአልጀዚራ እንደተናገሩት “ኢትዮጵያ አልፋሽጋ የሚባለው ግዛት የሱዳን መሆኑን እንደምትቀበልና ለማስረክብ መቁረጧን” ተናገሩ።

ለሱዳን ይሰጣል የተባለው መሬት 250 ካሬ ኪሎሜትር ስፋት ያለው ሲሆን፣ ለም የሆነ መሬትና በርካታ የውሃ ተፋሰሶች ያሉት ነው።

የአማራ ክልል ነዋሪዎች የተለያዩ ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው

ጥር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በህብረተሰቡ ውስጥ የሚነሱ ቅሬታዎች ዘርፈ ብዙ ናቸው።

በምዕራብ ጎጃም ዞን አስተዳደር ደምበጫ፣ ቡሬ ዙሪያ፣ ጃቢጠህናን እና ወምበርማ ወረዳዎች የቀበሌ አመራር የሆኑ የኢህአዴግ አባላት በወል ግጦሽ መሬት ወረራ ላይ በስፋት እየተሳተፉ ነው። በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ደግሞ የመሬት ችግር መፍትሄ የሚሰጠው አካል አልተገኘም፡፡ በደቡብ ወሎ ዞን በመሃል ሳይንት ወረዳ ደግሞ ለማዘጋጃ ቤት አገልግሎት ተብሎ የነዋሪዎች ቦታዎች ተወስደዋል፤ አትክልቶቻቸው ተጨፍጭፈውባቸዋል። ከ70 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መሬታችን ሲወሰድና ንብረታችን ሲወድም ካሳ አልተከፈለንም የሚል ደብደባ ቢጽፉም መልስ አላገኙም።

በዲላ ከተማ የነዳጅ እጥረት መፈጠሩን ነዋሪዎች ተናገሩ

ጥር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አሽከርካሪዎች ነዳጅ ለመግዛት ተቸግረናል ሲሉ ፣ የነዳጅ ማደያ ባለሃብቶች በበኩላቸው መንግስት ያለንን ትንሽ መጠንም ቢሆን ከመንግስት ፈቃድ ውጭ እንዳትሸጡ ተብለናል እያሉ ነው፡፡ አንድ ሳምንት በዘለቀው ችግር የባጃጅ ባለንብረቶች ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል።

የችግሩ መንስኤ በነዳጅ እጥረት ቢሳበብም በአለም ደረጃ በ12 አመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ዋጋ ከ30 ዶላር በታች በሚሸጥበት ወቅት በሃገር ውስጥም ሊቀነስ ሲገባው እንዴት እጥረት ይኖራል የሚል ጥያቄ ህዝቡ እየጠየቀ ነው።
በሰሞኑ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በተደረገውና የተማሪዎችን ህይወት በቀጠፈው የተማሪዎች ተቃውሞ፣ ብዛት ያላቸው ባጃጆች ተማሪዎችን ጭናችሁዋል ተብለው መቀጣታቸው ይታወቃል፡፡

በታንዛኒያ 83 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ተያዙ

ጥር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የታንዛኒያ ፖሊስ በሚቢያ ግዛት ማሂንቤ መንደር ውስጥ ሕገወጥ ስደተኞች ያላቸውን ተደብቀው የነበሩ ቁጥራቸው ከ83 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን መያዙን አስታውቋል።

የክልሉ የፖሊስ ኮማንደር የሆኑት ፒተር ካካምባ ስደተኞቹ በሕገወጥ መንገድ በከባድ መኪና በኮንትሮባንድ ተጭነው ወደ ማላዊ ለመሻገር ሲሞክሩ ተይዘዋል ብለዋል። ታንዛኒያዊ ሾፌርና ሕገወጥ ስደተኛ አዘዋዋሪ የሆነችው ሃና ሚካኖዮማ በአካባቢው ነዋሪዎች ጥቆማ አብረው መያዛቸውን አዛዡ ገልፀዋል።
ስደተኞቹ በመንገድ ላይ በደረሰባቸው እርሃብና እንግልት ሳቢያ በመጎዳታቸው ምክንያት ሆስፒታል ውስጥ በማገገም ላይ መሆናቸውን ኦል አፍሪካ ዘግቧል።

Sunday, January 17, 2016

ሰበር ዜና – በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች መኝታ እየተቃጠለ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የቀጠለው ሕዝባዊ ቁጣ እየተባባሰ በመጣበት ባሁኑ ወቅት በዛሬው ዕለት በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች መኝታ ቤት እየተቃጠለ መሆኑ ተሰማ::
ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የእሳት አደጋው አንዱን የተማሪዎች ህንፃ እያወደመው ይገኛል:: ተማሪዎች ከክፍላቸው ወጥተው እሳት አደጋውን ለማጥፋት እየተረባረቡ እንደሆነ የሚገልጹት የዓይን እማኞች እስካሁን የተጎዳ ተማሪ እንዳላዩ ገልጸዋል::
እሳት አደጋውን ያስነሳው ምክንያት እና ምን እንዳስነሳው የተረጋገጠ ነገር የለም:: ሆኖም ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን እያሰባሰበች ትገኛለች::

Saturday, January 16, 2016

የትዊተር አራማጅነት መሬት ይረግጣል? በፍቃዱ ኃይሉ

ግርማ ጉተማ የተባለ ሰው ታኅሣሥ 29/2008 የፌስቡክ ገጹ ላይ የጻፈውን ቀንጭቤ በማስነበብ ልጀምር፤ እንዲህ ይላል፣
“ባለፈው ክረምት ‹ለሆነ የፖሊሲ ትምህርት› ኔዘርላንድ በነበርኩ ጊዜ አንድ በመስኩ የአውሮጳ ኅብረት ሰዎችን የማማከር ሥራ የሚሠራ አንጋፋ ፕሮፌሰሬን የማናገር ዕድል አግኝቼ ነበር። ያ መልካም ሽማግሌ ፕሮፌሰር በአውሮጳ ኅብረት የፓርላማ አባላት ሁኔታ ተደናግጧል። እንደአባባሉ፣ ‹እዚያ ያሉ ፖለቲከኞች ደደቦች ናቸው፤… በፖሊሲ ጉዳይ እንድናማክራቸው ባዘጋጁልን ስብሰባ ላይ

Friday, January 15, 2016

በሽብር ሕግ የተከሰሰው ሙባረክ ይመር በቂሊንጦ እስርቤት አረፈ

ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ሆን ብሎ ባቀነባረው የሽህ ኑሩ ግድያ ላይ እጁ አለበት በማለት ተወንጅሎ ፍርዱን ሲጠባበቅ የነበረው ሙባረክ ይመር በቂሊንጦ እስርቤት ሕይወቱ አልፏል።
በእነ አሕመድ እንድሪስ መዝገብ 9ኛ ተከሳሽ የነበረው ሙባረክ ይመር ፍርድ ቤት ቀጠሮ ላይ በሰላም ደርሶ ከተመለሰ በኋላ በድንገት ታሞ ወደ ሕክምና ማእከል ቢወሰድም ሊተርፍ አልቻለም። ሙባረክ ይመርን ለሞት ያበቃው የጤና እክል እስካሁን አልታወቀም።
በነቀጀላ ገላና መዝገብ 4ኛ ተከሳሽ የነበረው አብደታ ኦላንሳ እስር ቤት በደረሰበት ድብደባና እንግልት ሕይወቱን ማጣቱ ይታወሳል።

“ያለንበት ዘመን ጨለማና መከራ የበዛበት ነው”ሲሉ አርሶአደሮች ተናገሩ

ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በድርቁ በተጎዱ የአማራ ክልል አካባቢዎች በመዘዋወር ተጎጂዎችን ለተመለከቱት የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ያለባቸውን ችግር የተናገሩት አርሶአደሮች ‹‹ አሁን ያለንበት ዘመን አስከፊ የሆነ አሰቸጋሪ ጊዜ ነው ፡፡››በማለት እየደረሰባቸው ያለውን የውሃ ችግር በምሬት ቢናገሩም እስካሁን ምንም መፍትሄ እንዳልተሰጠ ተጊጂዎች ቅሬታቸውን ተናግረዋል፡፡
‹‹ የደረሰብን ድርቅ ታይቶ የማይታወቅ እጅግ አሳዛኝ ነው ›› ያሉት ተጎጂዎች ዛሬ የደረሰብን ድርቅ አያቶቻችንም ‘እንዲህ አይነት ቀን አይተን አናውቅም !’ያሉት ዘመን ላይ ነው የደረስነው፡፡ ›› በማለት ሲናገሩ ተሰምተዋል፡፡
ከመኖ እጥረት ጋር ተያይዞ እንስሳቶች በሞት አደጋ ሲሆኑ ነዋሪውም በመሰደድ ላይ መሆናቸውን እና ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ በደረሰው ተደጋጋሚ ችግር እንስሶች እንኳን ስጋቸው ሊበላ ቆዳቸው ተገፎ የማይጠቅምበት ሁኔታ ላይ ነው ሲሉ ያሉበትን ዘመን አሳዛኝነት ገልጸዋል፡፡

ሂውማን ራይትስ ወች “መንግስት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን መሰረዙ ለተቃዋሚዎች ትልቅ ድል ቢሆንም ውሳኔው ዘግይቷል” አለ


ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሂውማን ራይትስ ወቹ ፍሊክስ ሆርን ፣ ደም አፋሳሽ ከሆነው የ9 ወራት ተቃውሞ በሁዋላ መንግስት ተቃዋሚዎች ላቀረቡት ጥያቄ ፣ የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመሰረዝ መልስ ቢሰጥም፣ ኦሮምያን ለማረጋጋት ግን የዘገየ ውሳኔ ነው ብሎአል።
መንግስት ተቃዋሚዎች ላቀረቡት ጥያቄ መልስ መስጠቱ ያልተለመደ ነው የሚለው ሆርን፣ ለተቃዋሚዎች ደግሞ ትልቅ ድል ነው መሆኑን ገልጿል።
በመጀመሪያ ተቃውሞው ስለ አዲስ አበባ መስፋፋት ነበር፣ይሁን እንጅ መንግስት ዜጎችን በስፋት ሲያስር፣ ሲገድልና ሌሎችን ጭካኔ የተሞላባቸው እርምጃዎች ሲወስድ፣ ተቃውሞው ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን አልፎ ሌሎችም ጥያቄዎች ማካተቱን ገልጸዋል።ምንም እንኳ የተወሰኑ ግጭቶች ቢኖሩም፣ አብዛኞቹ ተቃውሞዎች ሰላማዊ ናቸው።መንግስት ጭካኔ የተሞባለት እርምጃ መውሰዱ ተቃዋሚዎቹ ታሪካዊ ብሶቶችን ሁሉ እንዲያነሱ እንዳደረጋቸው ሆርን ገልጸዋል።

Thursday, January 14, 2016

በኦሮሚያ አንዳንድ ከተሞች ዛሬም ተቃውሞ ቀጥሏል

ከአምቦ ከተማ ባለፈው ሃምሌ ወር ታስሮ በአዲስ አበባ እስር ቤት ሳለ ታሞ ሆስፒታል ህይወቱ እንዳለፈ የተገለጸው ተማሪ አብደታ ኦላንሳ ቀብር ዛሬ በአምቦ ከተማ ተፈጽሟል። የጸጥታ ሃይሎች ቀብር ሥነ ስርዓቱን ለማስተጓጎል ድብደባና እስር ፈጽመዋል። ትናንት አስከሬኑን ለመቀበል ተኩሰው የገደሉትም አለ ብለዋል።
 
ባለፈው ሐምሌ ወር ከአምቦ ወደ አዲስ አበባ ተወስዶ ታስሮ እንደነበርና ታሞ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ህክምና ላይ ሳለ ህይወቱ እንዳለፈ የተነገረው ተማሪ አብደታ ኦላንሳ ቀብር ዛሬ አምቦ ከተማ ተፈጽሟል። በስልክ ያነጋግርናቸው ነዋሪ ትናንት ማታ የወጣቱን አስከሬን ለመቀበል በወጣ ህዝብ ላይ የጸጥታ ሃይሎች ድብደባ አድርሰዋል። ወደ ሰማይ ሲተኩሱም ነበር። አንድ ሰው በጥይት ተመትቶ ተገድሏል ብለዋል።

ገዢው ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች እያደረሰ ያለውን ጥፋት የሚያወግዙ የተቃውሞ ሰልፎች ተደረጉ

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በተለያዩ የኦሮምያ አካባቢዎች እና በሰሜን ጎንደር የገዢው ፓርቲ ታጣቂዎች በህዝቡ ላይ ያደረሱትን እልቂት የሚያወግዝ፣ በእስር ላይ የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች፣ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች እንዲፈቱ የሚጠይቅ እንዲሁም ከሱዳን ጋር በመሬት ዙሪያ የሚደረገው ድርድር እንዲቆም የሚጠይቁ የተቃውሞ ሰልፎች በአውሮፓ ህብረት መቀመጫና ብራሰልስ እና በሙኒክ ጀርመን ተካሂደዋል።

በረሃብ ምክንያት በሰሜን ወሎ ወረዳዎች የሚኖሩ አርሶአደሮች ቀያቸውን እየለቀቁ ወደ ባህርዳር በመፍለስ ላይ ናቸው

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአካባቢያቸው በተከሰተው ድርቅ የሚበሉትና የሚቀምሱት እንዳጡ የሚናገሩት ስደተኞች፣ ሰሞኑን ባህርዳር ገብተዋል፡፡ በየመንገዱ በመለመን የእለት ምግባቸውን ለማግኘት እየሞከሩ መሆኑን በፎቶ አስደግፎ ዘጋቢያችን የላከው መረጃ ያሳያል፡፡

የክልሉ መንግስት ምንም አይነት እገዛም አላደረገላቸውም፣ ማረፊያ ቦታም አላዘጋጀላቸውም ፡፡ አብዛኞቹ ስደተኞች ሴቶችና ህጻናት ናቸው። ህብረተሰቡ ለዜጎቹ እገዛ በማደረግ ላይ ቢሆንም፣የአለማቀፍ ድርጅቶችም ሊጎበኙዋቸው እንደሚገባ ዘጋቢያችን አስተያየቱን አስፍሯል።

በአዲስ አበባ ካለምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ የመንገድ ዳር ንብረቶች መወረሳቸው ተዘገበ

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የከተማዋ የመንገድ ባለስልጣን መስሪያ ቤት በመንገዶች ዳርቻ ያሉ ዓመታዊ ግብር ተከፍሎባቸው የቆሙ ቢልቦርድ የንግድ ማስታወቂያዎችን ለድርጅቶቹ ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ተለዋጭ ቦታ ሳይሰጣቸው ሳይሰጣቸው ከተለጠፉበት ማንሳቱን ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል። ንብረታቸው የተወሰደባቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንደዚህ ዓይነት ሕገወጥ ድርጊት በሕግ ሽፋን መፈፀሙ እንዳስከፋቸው እየገለፁ ነው። የመንገድ ባለስልጣኑ በበኩሉ በሬድዮ ለሶስት ቀናት ማስታወቂያ አስነግሬያለሁ በማለት ማስተባበያ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ አምባገነንነትን እንቢ ትበል!!!

12373403_184095175272945_8742457289203482535_nሁለት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኦሮሚያ ውስጥ ብቻ ከ150 በላይ ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል፤ በአማራ፣ በጋምቤላና በሶማሌ ቁጥራቸው የማይታወቅ በርካታ ወገኖቻችን ተገድለዋል፤ በሌሎችም ክልሎች ወገኖቻችን እየተገደሉ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተደብድበዋል፤ ታስረዋል። የህወሓት አገዛዝ ዜጎች መግደል፣ መደብደብና ማሰር መደበኛ ሥራው አድርጎታል።

የወጣቱ የህሊናና የፓለቲካ እስረኛ የሃብታሙ ሃብታሙ አያሌው መልእክት ‪#‎ከቂሊንጦ_እስር_ቤት‬።

እኔ ተስፋ አረጋለሁ ህዝብ ተሸንፎ አያውቅም።

እኔ ፅኑ እምነት አለኝ በመጨረሻ ህዝብ ያሸንፋል።
እዚህ የተገኝነው ብቸኛ አማራጭ በሆነው የሰላማዊ ተግል ሜዳ ላይ ተገኝተን ነው ለዚህ ግፍ የተዳረግነው።የመረጥነው ትግል ሌላ ቢሆን ኖሮ እዚህ አንገኝም ነበር። ይሁንና እኛ እዚህ እየከፈልን ያለነው መከራ በአሁኑ ሰአት እየተገደለ ካለውና…በርሃብ አለንጋ ከሚገረፈው ወገናችን አይበለጥብንም። ስለዚህ አሁንም በሰላማዊ መንገድ ትግሉ ይቀጥል ።

Wednesday, January 13, 2016

የአውሮፓ ህብረት በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደው ስላለው ተቃውሞ ከዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ማብራሪያ ጠየቀ

ኢሳት (ጥር 4 ፥ 2008)
የኢትዮጵያ ዋነኛ የልማት አጋር የሆነው የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በህብረቱ ዋና መቀመጫ ብራሰልስ ከተማ ተገኘተው በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ስላለው ተቃውሞ ማብራሪያን እንዲሰጡ ጠየቀ። ሆኖም የተዘጋጀላቸውም ጋዜጣዊ መግለጫ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ተሰርዟል።
የቀረበላቸውን ጥያቄ ተከትሎ በብራሰልስ የሚገኙት ዶ/ር ቴዎድሮስ በጉዳዩ ዙሪያ ከህብረቱ አባል ሃገራት በርካታ ጥያቄዎች ይቀርብላቸዋል ተብሎ በመጠበቅ ላይ መሆኑን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
በኢትዮጵያ የኦሮሚያ ክልል ኣየተካሄደ ያለው ተቃውሞ ስጋት እንደደረሰበት የገለጸው ህብረቱ፣ የጸጥታ ሃይሎች እየወሰዱ ያለው እርምጃ በአስቸኳይ እንዲቆም አሳስቧል።

የወያኔ ሰራዊት እርስ በእርሱ ተታኮሱ ከፍተኛም ጉዳት ደረሰ ተባለ

የመላዉ ኢትዮጵያ ህዝቦች ጠላት የሆነዉ እራሱን የትግራይ ነጻ አዉጭ ብሎ የሚጠራዉ የግፈኞች ስብስብ የሆነዉ ጎጠኛዉ ወያኔ በተለያዩ ከተሞች በዉትድርና ላይ ተሰማርተው የነበሩ የኦሮሞና የአማራ እንዲሁም የተለያየ ብሔር ያላቸዉን አባላት እና አርባ ምንጭ ላይ ከአሜሪካ ሰራዊት ጋር የነበረዉን መጠነኛ ብርጌድ በትግራይ ክልል ራማ ላይ በአንድነት አሰባስቦ! በካድሬዎቹ አማካኝነት፡
በኦሮሚያ ክልል ላይ የተነሳዉ ንቅናቄ የሚመራዉ በሽብርተኛ ሐይሎች በተለይም በኦነግና ! በርበኞች ግንቦት 7 ! ነዉ።
ዋነኛ አላማዉም ኢትዮጵያን አጥፍቶ ስልጣን በእጁ ማስገባት ብቻ ነዉ! 
ስለዚህም ይህን እንቅስቃሴ በማያዳግም እርምጃ መምታት አላማችን ነዉ!!

የወልቃይትን ህዝብ ትግል የሚያስተባብሩ ሰዎች በጸጥታ ሃይሎች እየተዋከቡ ነው

ጥር ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- “የወልቃይት ሕዝብ አማራነቱ ይከበርለት” በማለት ካለፉት ስድስት ወራት ወዲህ በፌዴራልና በአማራ ክልል እየቀረቡ አቤቱታ ሲያሰሙ የነበሩ የኮሚቴ አባላት ወደአካባቢቸው በሰላም ለመመለስ መቸገራቸው ታውቋል።
“የወልቃት ሕዝብ አማራ ነው፣ በትግራይ ክልል ሊተዳደር አይገባም” በማለት ጥያቄ ያነሱት ተወላጆች፣ የትግራይ ክልል አሁንም ጥያቄ የሚያቀርቡ ወገኖችን በተናጠልና በጋራ በማጥቃትና በማሳደድ ስራ በመጠመዱ ምክንያት የኮምቴ አባላቱ ያለስጋት ለመንቀሳቀስ አለመቻላቸው ታውቋል።
ባለፈው ህዳር ወር 2008 ዓ.ም የወልቃይት ተወካዮች በአዲስአበባ በመገኘት ቅሬታቸውን ለፌዴሬሽን ምክርቤት እና ለመንግስታዊው የሰብኣዊ መብት ኮሚሽን በጹሑፍ ያቀረቡ ሲሆን፣ በፌዴሬሽን ም/ቤት በኩል አቤቱታው በቅድሚያ ለትግራይ ክልል ቀርቦ በክልሉ በኩል ለፌዴሬሽን ም/ቤት መቅረብ እንዳለበት በቃል ምላሽ ማግኘታቸው ታውቋል፡፡
ሆኖም የኮሚቴ አባላቱ የማንነት ጥያቄውን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት አባልነት ጋር አያይዞ ከሚያየው የትግራይ ክልል ጋር ለመነጋገር የደህንነት ዋስትና ችግር ስለገጠማቸው አቤቱታውን ለማቅረብ እንዳልቻሉ እየገለጹ ነው።
የወልቃይት ሕዝብ አማራነቱ እንዲከበር ለአማራ ክልል በተደጋጋሚ አቤቱታ ያቀረቡ ቢሆንም፣ የክልሉ መንግስት ችግሩን ለመፍታት አቅም ማነስ ብቻ ሳይሆን ጥያቄያችሁን አንሱ በማለት እያሳደረ ያለው ጫና ይበልጥ አበሳጭቷቸዋል።
የአካባቢው ሹማምንቶች ህዝቡ ትግራዋይነቱን እንዲቀበል ለማድረግ የጠሩት ስብሰባ በተቃውሞ ተበትኗል። የአካባቢው ህዝብ ምንም አይነት ስብከት አንቀበልም፣ ጥያቄያችንን ብቻ መልሱልን ማለቱን የደረሰን ዜና ያመለክታል።
ወልቃይት በሰሜን ተከዜ፣ በደቡብ ጠገዴ፣በምስራቅ የተከዜ ወንዝ፣ በምዕራብ አርማጮህና ሱዳን የሚያዋስኑት ሲሆን የአካባቢው ሕዝብ ባለፉት 23 ዓመታት የማንነት ጥያቄ አጠንክሮ በማቅረቡ ምክንያት ለእስርና ለሰብዓዊ መብት ረገጣ መጋለጡን ተወላጆች ይገልጻሉ።

ኦህዴድ ማስተር ፕላኑን ትቼዋለሁ ቢልም ተቃውሞ ግን ቀጥሎአል

ጥር ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢህአዴግ አንድ ክንፍ የሆነው የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አዲሱን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን መተውን ባስታወቀ ማግስት በአምቦ፣ በአርሶ ኬፈሌና በሌሎችም የኦሮምያ ክፍሎች ተቃውሞው ቀጥሎአል።
በአምቦ የተካሄደው ተቃውሞ ደም አፋሳሽ የነበረ ሲሆን፣ አንድ ሰው መገደሉና በርካቶች መቁሰላቸው ታውቋል። ከቆሰሉት መካከል ህጻናትም ይገኙበታል።
ከአምቦ ከተማ በተጨማሪ በ ጃርሶ ወረዳ ቀሬ ጎሓ ከተማ ፣ በበደኖ፣ አርሲ፣ ሆድሮ ጉድሩና ሌሎችም ከተሞች ተቃውሞዎች ተካሂደዋል።
በሌላ በኩል ኦህዴድ ያወጣውን መግለጫ የኦፌኮው ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና አጣጥለውታል። ኦህዴድ ክልሉን የመምራት የሞራል ብቃት ስለሌለው ስልጣኑን ለህዝብ ያስረክብ ብለዋል።
ዶ/ር መረራ ፣ ዋናው ጥያቄ ” አዲስ አበባ ለምን ሰፋ አልሰፋ ሳይሆን፣ ለወደፊቱ አርሶደአሩ እንዳይፈናቀል ምን ዋስትና አለው” የሚለውን መመለሱ ላይ በመሆኑ፣ መግለጫው ይህንን ጥያቄ የሚመልስ አይደለም ይላሉ
በኦህዴድ የተሰጠው መግለጫ ተቃውሞውን ያስቆመዋል ወይ ተብለው የተጠየቁት ዶ/ር መረራ አይመስለኝም የሚል መልስ ሰጥተዋል። “ህዝቡ ይህ ድርጅት ወይም ያ ድርጅት ስለመራው ሳይሆን በራሱ ጊዜ ነው የተነሳው የሚሉት ዶ/ር መረራ፣ ጥያቄው ከመልካም አስተዳደር ችግር ጋር የተያያዘ መሆኑን፣ ዛሬ እንኳን ቢበርድ ነገ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።

Tuesday, January 12, 2016

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ሁሉም ዜጋ በኅብረት እንዲቆም አገራዊ ጥሪ አቀረበ

ጥር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያን ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ተግዳሮቶችን ለመቀየር እያንዳንዱ ዜጋ ይህንን ዘረኛ ስርዓት ለመጣል በአንድነት በፅናት መታገል እንደሚገባው ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በአቋም መግለጫውን ጠቅሷል።
“መብታቸው ለተረገጠ፤ ለተገፉ፤ አድሎ ለተፈጸመባቸው፤ ስብዓዊ መብታቸው ለተገፈፉ ዜጎች መቆም ያለብን ወቅት ላይ ነን። መደራጀትና የትኩረት አቅጣጫችንን የጋራ በሆኑ እሴቶችና ግቦች ላይ ማተኮር ያለብን ጊዜ ቢኖር ዛሬ ነው። እያንዳንዳችን እንደ ተሰጥዖአችንና እንደችሎታችን የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ ፈቃደኛ ከሆንን ጠባብና ዘረኛ አእምሮ የተቸራቸውንና ሃገራችንን በዘር ጥላቻ በመመረዝ ላይ ያሉትን የህወሃት ኢህአዴግ መሪዎችን ለመተካት የሚያስችል ሙያውም ፣እውቀቱም ፣ብቃቱም ያላቸው ዜጎች አሉን።” ብሎአል።
“ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሃዘንና በመለያየት አረንቋ ውስጥ ተዘፍቀን ተመልካች መሆን አይገባንም። ትኩረታችን ሁሉ ፊታችን በተደቀነው ግዙፍ እንቅፋት ላይ አድርገን በዘር መከፋፈላችንን ትተን ፣ በዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተን በጋራ ከቆምን ህወሃት እኛን ሊቋቋምበት የሚችልበት ምንም አቅም አይኖረውም” ሲል ንቅናቄው በመግለጫው ጠቅሷል።

በምስራቅ ሀረርጌ የተከሰው ረሃብ የህልውና ስጋት መደቀኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል

ጥር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከፍተኛ ረሃብ ገብቷል የሚሉት ነዋሪዎች፣ አስቸኳይ እርዳታ በፍጥነት ካልደረሰላቸው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ሊያልቅ ይችላል። በገጠር አካባቢ የሚኖረው ህዝብ ወደ ከተሞች መሰደድ ጀምሯል። ምንጮችና ወንዞች በመድረቃቸው ውሃ ለማግኘት አልተቻለም ሲሉ የውሃ እጥረት ለመሰደዳቸው ዋና ምክንያት መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ።
አንዳንድ አርሶአደሮች ከብቶቻቸውን እየሸጡ ችግሩን ለማሳለፍ እየሞከሩ ቢሆኑም፣ የከብቶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ በርካሽ ለመሸጥ ተገደዋል።
በዚህ አመት ከ10 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።

በጅማ ዩኒቨርስቲ ቦንብ ሲፈነዳ በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ ደግሞ ተማሪዎች ተደብደቡ

ጥር ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ተማሪዎች እንደገለጹት ፣ ትናንት ምሽት ላይ መብራት ከጠፋ በሁዋላ የእጅ ቦንብ የተወረወረ ሲሆን፣ ፍንዳታውን ተከትሎ የመንግስት ታጣቂዎች ወደ ተማሪዎች ማደሪያ ክፍል እየገቡ ደብድበዋቸዋል። በፍንዳታው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ተማሪዎቹ ፍንዳታውን ያደረሱት ወታደሮች ናቸው ይላሉ። ፍንዳታው ተቃውሞ ሊያሰሙ ይችላሉ በሚሉዋቸው ተማሪዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ ሆን ብሎ የተቀናበረ መሆኑን የሚያሳየው ከፍንዳታው በፊት መብራት መጥፋቱና ከመቅጽበት ተሰልፈው ይጠባበቁ የነበሩ ወታደሮች በተማሪዎች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸው ነው ይላሉ። ከክፍላችን እየደበደቡ ያስወጡን ወታደሮች፣ እየተቀባበሉ ደበደቡን ሲል አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ ተማሪ ተናግሯል።

በጅማ ዩኒቨርስቲ የእጅ ቦንብ ተወርውሮ 35 ተማሪዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል

በፍንዳታው የተጎዱ ተማሪዎች አብዛኛዎቹ የተለያዩ የአካል ክፍሎቻቸውን ማጣታቸውንም መረጃዎች ይጠቁማሉ ።

ህወሃት/ኢህአዴግ የዘር-ፍጅት በመቀስቀስ ላይ መሆኑን ታማኝ ምንጮች ገለጹ

ኢሳት (ጥር 3 ፥ 2008)

በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ ሁለት ወራት ባስቆጠረበት በአሁኑ ወቅት፣ የመንግስት የደህንነት ሃይሎች የዘር ፍጅት በመቀስቀስ የተቃውሞውን አቅጣጫ ለመቀየር በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውን ታማኝ የውስጥ ምንጮች ለኢሳት ገለጹ።
የዘር ፍጅት እቅዱ በኦሮሚያ ክልል በሚኖሩ የሌላ ብሄረሰብ ተወላጆች በተለይም በአማሮች ላይ የተነጣጠረና የተቀነባበረ ጥቃት በመሰንዘር፣ የሌላ አካባቢ ተወላጆች በስጋት ከመንግስት ጎን እንዲቆሙ በማድረግ ሁኔታውን ወደ እርስ-በእርስ ግጭት በመውሰድ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን መረዳት ተችሏል።
ወደ ኢትዮጵያ የሚሰራጩት የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) እና የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) በኢትዮጵያ ስርጭታቸው መታወኩ የመንግስት የደህንነት ሃይሎች የታቀደውን ጥፋት በቀላሉ ለማስፈጸም ይቻላቸዋል የሚል ግንዛቤ መያዙንም ለኢሳት የደረሰው መረጃ ያብራራል።
በመንግስት የደህንነት ሃይሎች የተቀነባበረው ጥቃት፣ በህዝቦች መካከል ግጭት ከመጋበዝ ባሻገር፣ በተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም ህዝብ በሚሰበሰብባቸው ስፍራዎች የተቀነባበሩ የቦንብ ፍንዳታዎች ጭምር ለማከናወን መታቀዱንና የቀደሙ ዕርምጃዎች የዚህ ውጤት መሆናቸው ተመልክቷል።
ድርጊቱን ለማስፈጸም የተመለመሉ የኦህዴድና የብአዴን ሰዎች ጭምር መዘጋጀታቸውንም ለመረዳት ተችሏል።
ለኢሳት መረጃውን ያደረሱት ወገኖች ህዝብን ለፍጅት ለመዳረግ በመንግስት የደህንነት ተቋም እየታቀደና እየተወሰደ ያለውን እርምጃ የሚመለከታቸው ወገኖች ሁሉ በትኩረት እንዲከታተሉና መረጃውን በማድረስ እንዲተባበሩም ጥሪ አቅርበዋል።

በአርባምንጭ ከተማ ወጣቶች በወያኔ ሃይሎች በገፍ እየታደኑ በመታሰር ላይ ናቸው ተባለ

በአርባምንጭ ከተማ ብዙ ወጣቶች የግንቦት 7 አባል ናችሁ በሚል ሰበብ ተጠርጥረው ዕርቃናቸውን ግርፋትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸሙባቸው ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። 20 አመት እድሜ ላይ የሚገኙ ዮሴፍ ይስሃቅና፣ እንዳሻው ወንድይፍራው ከዚህ በፊት በአርባምንጭ ከተማ ከጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ እያንዳንዳቸው በ2ሺ ብር ዋስትና እንደተለቀቁ፣ “ወያኔን ሰድበዋል፣ ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ግንኙነት አላቸው” በሚል ሰበብ እንደተደበደቡ በስፍራው የነበሩ እማኞች አስታውቀዋል።

Monday, January 11, 2016

በኦሮምያ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ህዝባዊ ተቃውሞውን ግንባር ቀድም ሆነው እየመሩት ነው

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከወር በላይ ያስቆጠረው በኦሮምያ የሚካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ እንደገና በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ሃይሉን ጨምሮ ሲካሄድ ሰንብቷል።

የወልቃይትን ህዝብ ለማሳመን የተላከው ቡድን እስካሁን አልተሳካለትም

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ያለፍለጎታቸውን ወደ ትግራይ ክልል በመጠቃለላችን ወደ አማራ ክልል እንዛወር በማለት የጠየቁ የወልቃይት ነዋሪዎችን ሲያግባባ የነበረው ከአማራ ክልል ከልዩ ልዩ መስሪያ ቤቶች የተወጣጣው ቡድን ለአንድ ወር ያክል ጊዜ በአካባቢው ተሰማርቶ የማሳመን ስራ ለመስራት ቢሞክርም እስካሁን ተልዕኮው ባለመሳካቱ ለተጨማሪ ጊዜ በወልቃይት ለመክረም ተገዷል፡፡

ኢትዮጵያ በተመድ የልማት ፕሮግራም መስፈረት የ174ኛ ደረጃን ያዘች

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተባበሩት የልማት ፕሮግራም UNDP ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያ ከ188 የአለም አገራት 174ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ገልጿል። ድርጅቱ የኢኮኖሚ እድገትን፣ ልማትን፣ የጸጥታ ጉዳዮችን ፣ የፖለቲካ ነጻነትንና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮችን በማጥናት የሚያወጣው ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ካለፈው አመት ከነበረችበት ደረጃ ዘንድሮ አንድ ደረጃ ዝቅ ብላለች። በአለማ ላይ ካሉት አገራት ኢትዮጵያ መብለጥ የቻለችው 14 አገራትን ብቻ ሲሆን፣ ሁሉም በአፍሪካ የሚገኙ ናቸው።

ወደ የመን በጀልባ ሲጓዙ ከነበሩ ስደተኞች ውስጥ 122 የሚሆኑት ሕይወታቸውን አጡ

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መነሻቸውን በሶማሌላንድ ሳናጋ ግዛት አድርገው በተጨናነቀ ጀልባ ሕይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው ባሕር አቆራርጠው ወደ የመንና የገልፍ አገራት ለመግባት ሲጓዙ ከነበሩት ኢትዮጵያዊያንና ሶማሊያዊያን ዜጎች ውስጥ አብዛኞቹ መሞታቸውንና ከሟቾቹ ውስጥ 122 የሚሆኑት አስከሬናቸው በባህር ዳርቻዎች መገኘቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።

በደቡብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የቀበሌ አስተዳደሮች የአማራ ክልል ባለስልጣናት በስብሰባ ጠምደው፣ አርበኞች ግንቦት 7 ጦርነት ከፍቶብናል ሲሉ መሰንበታቸው ተሰማ፡፡

ከታሃሳስ 24 ጀምሮ እስከ ታሃሳስ 28/2008 ዓ.ም በደቡብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የ48 የቀበሌ አስተዳደሮችንና የቀበሌ ሊቀመንበሮች የክልሉ ባለስልጣናት በወረታ ከተማ፣ለአምስት ተከታታይ ቀናት በስብሰባ ጠምደዋቸው ሰነበቱ፡፡ ‹‹የስብሰባው ዋና አጀንዳም አርበኞች ግንቦት 7 ጦርነት ከፍቶብናልና በየቀበሊያቹህ ያሉትን የሚሊሻ አባላት ለጦርነት እንዴት ዝግጁ እናድርጋቸው›› የሚል እንደነበር ከቦታው የደረሰን መረጃ ያሳያል፡፡

ምንም እንኳን ስብሰባው አምስት ተከታታይ ቀናት የፈጀ ቢሆንም የቀበሌ ሊቀመንበሮቹና አስተዳዳሪዎቹ በተነሳው አጀንዳ ዙሪያ ፈቃደኛ አለመሆናቸውንና በግልፅ ቅዋሜያቸውን አስቀምጠዋል፡፡
ይህን ተከትሎ የአገዛዙ ባለስልጣናት ለቀበሌ አመራሮቹ በዛቻ የታጀበ ትዕዛዝ ቢያስተላልፉም፣የቀበሌ አስተዳደሮቹና ሊቀመንበሮቹ የመጣ ይምጣ ሲሉ መደመጣቸው ታውቋል፡፡በዚህም ለአምስት ተከታታይ ቀናት የተደከመበት ስብሰባ ያለፍሬ ተጠናቋል፡፡
ህዝባዊ ዓላማ ታጥቆ የተነሳው አርበኞች ግንቦት 7 በፀረ-ህዝብ የወያኔ ሰራዊት ላይ እያደረሰ ያለውን ጠንካራ ምት ተከትሎ የአገዘዙ ሹማሙንቶች በግልፅ የፍርሃት ማዕበል ውስጥ መዘፈቃቸውን ያሳያል ሲሉ ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው አስተያየት ሰጭዎች ተናግረዋል፡፡

Sunday, January 10, 2016

ኃይለማርያም ልጃቸውን ከመዳራቸው አንድ ቀን አስቀድሞ ሙሽራው በፌደራል ፖሊስ ተገድሏል (ከብስራት ወልደሚካኤል)

ታሪክ ራሱን ሲደግም! የሌላውን ሰው ልጅ ደስታ አበላሽቶ በራስ ልጅ ሰርግ መደሰት…!
 ከብስራት ወልደሚካኤል
በምርጫ 1997 ዓ.ም. ወቅት የኢህአዴግን መሸነፍ ተከትሎ ሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ በሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ በአዲስ አበባ የ14 ዓመት ዕድሜ የነበራቸው ሴትና ወንድን በመንገድ ላይ እያሉ ገደሏቸው፡፡ በዛው ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ሰኔ 1997 ዓ.ም. መጨረሻ ህፃናት ያስገደሉት አቶ መለስ፤ ልጃቸው ሰመሃል መለስ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቷን በማጠናቀቋ በሸራተን አዲስ የእንኳን ደስ ያለሽ የእራት ግብዣ አድርገው ተደሰቱ፡፡ ከነበረው ተቃውሞ ጋ ምንም ንኪኪም ሆነ ግንኙነት ያልነበራቸው ሌሎችኢትዮጵያውያን ህፃናትን በአደባባይ አስገድለው የራሳቸውን ልጅ እንኳን ደስ ያለሽ ብለው ከተዝናኑ ባለፈው ሰኔ 10 ዓመታት አለፈው፡፡

Friday, January 8, 2016

ኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች ያነሱት የመብት ጥያቄ ተገቢ ነው፣ የትጥቅ ትግል የጀመሩትን መደገፍ አለብን ሲሉ ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ አስታወቁ

ኢሳት (ታህሳስ 29 ፣ 2008)
የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች ያነሱት የመብት ጥያቄ ተገቢና የሚግደገፍ ነው ሲሉ ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ምሁር ገለጹ። በከተሞች መስፋት ሃብታም የመሆን እድል የልተመቻቸለት አርሶ አደሮች ወደ ድህነት እየተገፉ፣ ባለጊዜ በዕርሱ መሬት እንዲበለጽግ መንገድ ሲጠርግ ተቃውሞ መጀመራቸው ትክክል ነው ያሉት ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ፣ ይህ በኦሮሞዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ላይ ሊደርስ የሚችል በመሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሊያወግዙት እንደሚገባ ለኢሳት በሰጡት ቃለምልልስ አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በሁሉም አካባቢ ችግሮች መኖራቸውን የጠቀሱት ታዋቂው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ፣ መፍትሄውም የጋራ እንደሆነ ለፖለቲካ ሃይሎች በአንድነትና በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ብዙ ብሄረሰቦችና ሁለት ትልልቅ ሃይማኖች ባሉበት ሃገር መቻቻልና መከባበር እንዲሁም ለጋራ ችግር በጋራ መቆም ያስፈልጋል ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። ግባችን ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሆንና መስዋዕትነቱ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሆን እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።
ስልጣን ላይ ያለው ቡድን ከእንግዲህ በምርጫም ሆነ በሰላማዊ ትግል ስልጣን ይለቃል የሚል ዕምነት የለኝም ያሉት ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ፣ የትጥቅ ትግል ለማድረግ የተነሱትንና የጀመሩትን መደገፍ ይገባል ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል። የትጥቅ ትግል ብለው የሚንቀሳቀሱ የምናውቃቸው ስለኢትዮጵያ ሲሉ የተነሱ ናቸው ሲሉም አክለው ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የአእምሮ በሽተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው

ታኀሳስ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከቅርብ ኣመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የአእምሮ ጤና መቃወስን ጨምሮ ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፉ መምጣታቸውን፣ መንግስትም ችግሩን ለመከላከል በቂ የሆነ ጥረት እንዳላደረገ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ አመለከተ፡፡
ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች መካከል የካንሰር ሕመም ፣ የአእምሮ ህመም፣ ከውፍረት ጋር የተያያዙ የጤና ችግሮች፣ ከአልኮልና የትምባሆ እንዲሁም ከአደገኛ ዕጾች ጋር የተያያዙ የጤና ቀውሶችና የመሳሰሉት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ችግሮቹን ከመሰረታዊ የጤና አገልግሎት ጋር አቀናጅቶ ለመስራት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም ችግሩ ካለበት ስፋት አንጻር ባለፉት ኣመታት የተገኘው ውጤት እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡
ሪፖርቱ ተላላፊ ያሆኑ በሽታዎች በቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራችን እየተበራከቱ መሆኑን አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ ካለ በኍላ፣በተለይ በከተሞች አካባቢ የሚኖሩ ሕዝቦች የውፍረት መጠን መጨመር፣ አልኮልና የትምባሆ እንዲሁም አደንዛዥ እጾች ተጠቃሚነት መበራከት፣ የአእምሮ ጤና መቃወስ (ድብርት፣ ጭንቀት) እንዲሁም የአየር ብክለት፣ ኬሚካሎች ልቀት እየተበራከቱ መጥተዋል ይላል፡፡
ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለማከም የሚወጣው ወጪም ሆነ የሚያስፈልገው አቅም ከፍተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ እነዚህ በሽታዎች እንዳይስፋፋ የተደረገው ጥረት አመርቂ እንዳልነበር ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡

አቶ በቀለ ነገአ በቁም እስር ላይ ናቸው

ታኀሳስ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦፌዴን ሊቀመንበር አቶ በቀለ ነገአ በደህንነት ሃይሎች ታፍነው ተወስደው ድብደባ ከተፈጸመባቸው በሁዋላ፣ ከቤት ወጥተው ስራቸውን ለማከናወን ባለመቻላቸው በቁም እስር ላይ እንደሚገኙ ከባልደረቦቻቸው የተገኘው መረጃ አመልክቷል። ሌላው የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ ባልታወቀ ስፍራ ተወስደው የታሰሩ ሲሆን፣ አቶ በቀለ ነገአ ግን ማንኛውንም አይነት መግለጫ ለመገናኛ ብዙሃን እንዳይሰጡ እንዲሁም ከቤታቸው እንዳይወጡ በመከልከላቸው ጓደኞቻቸው በስልክ ከመጠየቅ በስተቀር በአካል አላገኙዋቸውም።
አቶ በቀለ በደህንነት ሃይሎች ታፍነው ከተወሰዱ በሁዋላ፣ በጻፉት ጽሁፍ ” ከእንግዲህ ለየትኛውም ሚዲያ ብትናገር እንገልሃለን፣ ለቤተሰቦችም ብታሰብብበት ይሻላል” እንዳሉዋቸው ገልጸው ነበር። ኢሳት አቶ በቀለን ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም አልተሰካለትም።

በአርባምንጭ የሚገኘው የአሜሪካ ሰው አልባ አውሮፕላን ጣቢያ በኢትዮጵያ ጥያቄ የተዘጋ መሆኑ ታወቀ

ኢሳት (ታህሳስ 29 2008)
በደቡብ ኢትዮጵያ አርባ ምንጭ ከተማ ላለፉት 5 አመታት ያህል ሲያገለግል የቆየው የአሜሪካ የሰው አልባ የስለላና የውጊያ አውሮፕላን (ድሮን) ጣቢያ መዘጋት የሃገሪቱን ግንኙነት የሚጎዳ ዕርምጃ መሆኑ ተመልክቷል። ዩ ኤስ አሜሪካ የድሮን ጣቢያው አላስፈላጊ በመሆኑ መዘጋቱን በወቅቱ ብትገልጽም፣ የኢትዮጵያ መንግስት ቃለ አቀባይ ረቡዕ በሰጡት መግለጫ የድሮን ጣቢያው በኢትዮጵያ ጥያቄ መዘጋቱን ይፋ አድርገዋል።
በዓለም-አቀፍ ደረጃ በውጭ ግንኙነት ፖሊሲዎች ላይ የሚያተኩረው “ፎርየን ፖሊሲ” መጽሄት ያነጋገራቸው ኤክስፐርቶች የ”ድሮን” ጣቢያው መዘጋት የአሜሪካንንና የኢትዮጵያን መንግስታት ወዳጅነት እንደሚጎዳና እያሻከረው እንደሚሄድ የገለጹ ሲሆን፣ የአሜሪካ ባለስልጣናትም ጣቢያው በኢትዮጵያ ጥያቄ መዘጋቱን ዘግይተው አረጋግጠዋል።

እነ ሀብታሙ አያሌው ለጥር 10/2008 ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

አቃቤ ህግ በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብርተኝነት ክስ መስርቶባቸው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ ተበይኖላ...ቸው አቃቤ ህግ ለጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ጠይቆባቸው ጉዳያቸውን በእስር ላይ ሆነው እየተከታተሉ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በድጋሜ ለጥር 10/2008 ዓ.ም ተቀጥረዋል፡፡
ዛሬ ታህሳስ 29/2008 ዓ.ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በእነ ሀብታሙ አያሌው ላይ የተጠየቀው ይግባኝ ላይ ብይን ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም ዳኛ ዳኜ መላኩ ‹‹የምንመረምረው ነገር አለ›› በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡
ይግባኝ የተጠየቀባቸው ተከሳሾች ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሺ እና አብርሃም ሰለሞን ሲሆን፣ ሁሉም ተከሳሾች ነሀሴ 14/2007 ዓ.ም በስር ፍ/ቤት ነጻ ቢባሉም እስካሁን በእስር ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡

የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተከትሎ የተነሳው ህዝባዊ አመጽ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ኢሳት (ታህሳስ 29, 2008)
የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተከትሎ የተነሳው ህዝባዊ አመጽ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በኦሮሚያ ክልል የተጀመረው ተቃውሞ ትናንትም በተለያዩ አካባቢዎች ቀጥሎ መዋሉ ታወቀ። በትናንትናው ዕለትም በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች እና በአንዳንድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መንግስት እየወሰደ ያለውን ዕርምጃ በመቃወም የተለያዩ ህዝባዊ እምቢተኝነቶች መካሄዳቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
በትናንትናው ዕለት የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ 5 ኪሎ ካምፓስ ተማሪዎች ለገና በዓል የተዘጋጀውን ምግብ ባለመመገብ ተቋዉሞአቸውን አሳይተዋል።
በጅማና በተለያዩ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ በሚገኙ ከፍተኛ ተምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች የአውደ-አመት ምግብ ዝግጅቱን ትተው በመውጣት ትብብራቸውን አሳይተዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በምዕራብ ሃረርጌ አሰቦት እና ጡጢሳ ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ወደጎዳና በመውጣት ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የተቃዋሚ አመራሮች የሆኑና በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ ሰዎች ቤተሰቦቻቸው እየተለቀሙ መታሰር ጀምረዋል። በእስር ቤተ የሚገኙ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አመራር የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ እህት ወ/ሮ አበዙ ጣፋ በትናንትናው እለት በመንግስት ሃይሎች ቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል። ከሶስት ቀን በፊት የኦፌኮ ከፍተኛ አመራር አባል የሆነው በቀለ ገርባ ልጅ ከሚማርበት አዳማ ዩንቨርስቲ ተይዞ መታሰሩ የሚታወስ ነው።
ሁለተኛ ወሩን በያዘው በዚሁ ተቃውሞ፣ ከ140 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል። በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ታስረዋል።

በኒውዚላንድ የሚኖሩ ሴቶች ገንዘብ አሰባስበው ለአርበኞች ግንቦት7 ለገሱ

ታኀሳስ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኒዉዚላንድ ዌሊንግቶን የሚኖሩ ሴቶች ፣ በበረሃ ውስጥ ያሉ ሴቶችን ለመርዳት በሚል ተነሳስተው ለአርበኞች ግንቦት ሰባት የሴት ታጋዮች ፍጆታ የሚዉል ገንዘብ መለገሳቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመልክቷል።
ሴቶቹ ይህ ጅማሪ እንጂ የመጨረሻዉ እንደማይሆን፣ ለወደፊቱ ራሳቸዉን በማደራጀት ቀጣይ የሆነ እርዳታ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
በገና በዓል ቀን ሴት እሕቶቻችን በጫካ ለኛ ነፃነት ሲታገሉ እኛ የተመቻቸ አገር ላይ ሆነን ቢያንስ አስበናቸዉ ልንዉል ይገባል በማለት ድጋፍ ለማድረግ መነሳሳታቸውንም አክለዋል።

በትግራይ አርሶአደሮች የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

ታኀሳስ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታህሳስ 22፣ 2008 ዓም በመቶዎች የሚቆጠሩ አርሶአደሮች ተቃውሞውን ያካሄዱት የበለስ ምርታችን በተሳሳተ ምርምር ወድሞብናል በሚል ምክንያት ነው። አርሶአደሮቹ ከዋጅራት ተነስተው በእግራቸው ወደ መቀሌ የገሰገሱ ሲሆን፣ አዲግዶም ላይ ፖሊሶች በሃይል በትነዋቸዋል።
አርሶአደሮቹ እንደሚሉት ለምርምር በሚል የገባው በሽታ ፣ የበለስ ምርቱን በከፍተኛ ሁኔታ በመጉዳቱ በህልውናቸው ላይ አደጋ ፈጥሯል። መንግስት በሽታውን ያመጡትን ተመራማሪዎች ለፍርድ እንዲያቀርብላቸውና አስፈላጊው ካሳ እንዲፈላቸው ይጠይቃሉ።
የክልሉ መንግስት ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ጥያቄ ባቀረቡ አርሶአደሮች ላይ የሃይል እርምጃ መውሰዱ ይታወቃል።

በባህርዳር እስረኞች ለ2 ቀናት በቤተሰብ እንዳይጠየቁ ተደረጉ

ታኀሳስ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው እሁድ የእስር ቤቱ ሃላፊዎች ” በእስር ቤቱ ውስጥ ቦንብ ገብቷል” የሚል መረጃ ደርሶናል በሚል እስር ቤቱን በአድማ በታኝ ፖሊሶች አጥለቅልቀውና ዋናውን መንገድ በመዝጋት ጠያቂዎች እንዳይገቡ ከልክለዋል። በዚሁ ሰበብ በእስረኞች ላይ ከፍተኛ እግልት የደረሰ ሲሆን፣ ለሁለት ቀናት ያክል እስረኞች በቤተሰቦቻቸው እንዳይጠየቁ አግደዋል። በእስር ቤቱ ውስጥም ከፍተኛ ፍተሻ ተካሂዷል።
ዛሬ ታህሳስ 28 ከቀኑ 8 ሰአት ላይ እስረኞችን ለመጠየቅ መግባት እንደተጀመረ ድንገተኛ የተኩስ ድምጽ በመሰማቱ፣ ወታደሮች ጠያቂ ቤተሰቦችን ከአካባቢው በማባረር የተወሰኑትን አግደዋል።
የተኩሱ ትክክለኛ መንስኤ እስካሁን ባይታወቅም ፣ አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ ፖሊስ ግን በጣና ሃይቅ በኩል ለማምለጥ የሞከረን እስረኛ ለማስቆም በሚል ተኩስ መከፈቱን ለዘጋቢያችን ተናግሯል።
በባህርዳር ዋናው እስር ቤት መንግስትን ይቃወማሉ የሚባሉ በርካታ ወጣቶች ታስረው ይገኛሉ።

ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት መከሰቱን ነጋዴዎች ተናገሩ

ታኀሳስ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የንግድ ድርጅት ባለቤቶች ለኢሳት እንደገለጹት በአሁኑ ሰአት የተከሰተው የዶላር እጥረት ከምርጫ 97 በሁዋላ ከፍተኛው ነው። በአስመጭነትና ላኪነት ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በውጭ ምንዛሬ እጥረት ስራቸውን ለመስራት በማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። ፋብሪካዎች የመለዋወጫ እቃዎችን ለመግዛት በመቸገራቸው እንቅስቃሴያቸው በእጅጉ ተዳክሟል። በተለይ የግንባታ እንቅስቃሴው በእጅጉ መዳከሙን ነጋዴዎች ይገልጻሉ።
በአገሪቱ የተፈጠረውን ከፍተኛ ድርቅ ለማቋቋም መንግስት በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የእርዳታ እህል ለመግዛት ቢችልም፣ ከአለማቀፉ ማህበረሰብ የሚሰጠው ድጋፍ በመቀነሱ ተጨማሪ የእርዳታ እህል ለመግዛት አቅም አጥሮታል። ከዚህ ቀደም የተከሰተውን የዶላር እጥረት ለመቋቋም መንግስት ከአለማቀፍ የግል አበዳሪ ድርጅቶች 1 ቢሊዮን ዶላር ቢበደርም ፣ ሁለተኛው ዙር ብድር እስካሁን አለመለቀቁ ችግሩን አባብሶታል ሲሉ ምንጮች ይገልጻሉ።

በኦሮምያ የሚካሄደውን ተቃውሞ ተከትሎ የታሰሩት እንደፈቱ ሂውማን ራይትስ ወች ጠየቀ

ታኀሳስ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሰብአዊ መብት ድርጅቱ በምስራቅ አፍሪካ ተመራማሪው ፌሊክ ሆርን በኩል ባወጣው መግለጫ፣ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ መታሰራቸውን ተከትሎ ግጭቱ እየተባባሰ መምጣቱንና በእስካሁኑ ተቃውሞ 140 ሰዎች መገደላቸውን ጠቅሷል።
አቶ በቀለ ገርባና ሌሎችም እስረኞች እንዲፈቱ የጠየቀው ሂውማን ራይትስ ወች፣ ዜጎች ሃሳባቸውን በነጻነት እንዲገልጹ እንዲፈቀድላቸው፣ አርሶአደሮችን በዘፈቀደ ማፈናቀል እንዲቆምና በቂ ምክክር እንዲደረግ አሳስቧል።
መንግስት ሰላማዊ ተቃውሞዎች እንዳይካሄዱ ባፈነ ቁጥር ዜጎች የ ሃይል አማራጭን ለመጠቀም እንደሚያዘነብሉ ያሳሰበው ሂውማን ራይትስ ወች፣ ይህ ደግሞ አገሪቱን ወደ አደገኛ አዙሪት የሚከታት እንዲሁም የረጅም ጊዜ ደህንነቷን አደጋ ውስጥ የሚከተው ነው ብሎአል።
በሌላ በኩል በገና በአል እለት ሳይቀር በክልሉ የሚካሄደው ተቃውሞ ተጠንከሮ ቀጥሎአል። በአሰቦት ከተማ አርሶደሮችና የከተማው ነዋሪዎች ባሰሙት ተቃውሞ የእለቱ ገበያ ፈርሷል። በፈንታሌ፣ ጊምቢ፣ አምቦና ፍቼም ህዝባዊ ተቃውሞ መደረጉን መረጃዎች ደርሰውናል። በትናንትናው እለት በሂርና በነበረው ተቃውሞ ደግሞ ወደ ሃረርና አጎራባች ከተሞች የሚሄዱ ነዋሪዎች መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት የትራንስፖርት ችግር አጋጥሟቸው ነበር። አንድ ተሰፋሪ እንዳለው፣ በርካታ መንገደኞች ” የጸጥታ ችግር አለ በሚል” መንገድ ላይ ለማደር ተገደዋል።

Thursday, January 7, 2016

"የነጻነት ቀን ቀርባለችና ጸንታችሁ ቁሙ! እየሩሳሌም ተስፋው (ከቃሊቲ ማጎሪያ ቤት፣ አዲስ አበባ)

እነሆ በጨለማ ቤት ውስጥ ከታጎርን 311 ቀናት ሞሉን፡፡ ጊዜው እንዴት ይሮጣል ባካችሁ? የዛሬ አመት በዚህ ወቅት ከጓደኞቼ ጋር በዝዋይ እስር ቤት የሚገኙትን ጀግኖቻችንን ለመጠየቅና እንኳን አደረሳችሁ ለማለት የገና ዋዜማን በዝዋይ ወህኒ ቤት ተገኝተን ነበር፡፡ ግን ምኞታችን ቅዠት ሆኖ ያሰብነው ሳይሳካ አንድም የፖለቲካ እስረኛ ማግኘት ሳንችል በሩን ተሳልመን ተመለስን፤ መጠየቅ አትችሉም ተብለን፡፡

Tuesday, January 5, 2016

የአዳማ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በአጋዚ ወታደሮች ግድያ፣ ድብደባና ወከባ ደረሰባቸው

ኢሳት (ታህሳስ 26 ፥ 2008)
በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለውን የመሬት ዘረፋና የጅምላ ጭፍጨፋን  በመቃወም ላይ በነበሩ በአዳማ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ተቃውሞውን ለማስቆም በተሰማሩ የጸጥታ ሃይላት መካከል ግጭት እንደተፈጠረ የአይን እማኞች ከስፍራው አስታወቁ።
ሰኞ ጠዋት የተጀመረው ይህ ተቃውሞ፣ ተማሪዎቹ በአዳማ ዩንቨርስቲ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በኦሮሚያ ክልልና በሌላው የኢትዮጵያ ክልሎች ላይ እየደረሰ ያለው ጭፍጨፋና፣ ወከባና፣  እንግልትን እንዲቆም ሲጠይቁ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
አመጹን ለማስቆም ቀደም ብሎ በአካባቢው የሰፈረው ብዛት ያለው የአጋዚ ክፍለጦር እንደተሰማራ የተገለጸ ሲሆን፣ ተማሪዎችም ከመሬት ወረራና ከሰብዓዊ መብት ጥሰት በተጨማሪ የአጋዚን በትምህርት ማዕከል መስፈር በጽኑ ተቃውመዋል።

77 ኢትዮጵያዊያዊያን ስደተኞች በዛንቢያ ተያዙ

ታኀሳስ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የዛንቢያ የስደተኞች ጉዳይ ከፓሊስ ጋር በመተባበር በሕገወጥ መንገድ ወደ አገራችን ገብተዋል ያላቸውን ቁጥራቸው 77 የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን በዋና ከተማዋ ሉሳካ ካባንግዌይ አቅራቢያ በቁጥጥር ስራ ማዋሉን አስታውቋል።
በአንድ ቶዮታ ሬጉስ መኪና ላይ ተጭነው ሲጓዙ የነበሩ 10 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ለመያዝ አሰሳ ሲያደርጉ በስፍራው ሌሎች ተጨማሪ 67 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ከተደበቁበት መያዛቸውን ገልፀዋል።

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለአለም የጤና ድርጅት መሪነት ሊወዳደሩ ነው

ታኀሳስ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሚኒስትሩ የውጭ ጉዳይ ስልጣናቸውን በመልቀቅ ለአለም የጤና ድርጅት መሪነት ሊወዳደሩ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ታውቋል። ዶ/ር ቴዎድሮስ ሰሞኑን ወደ ጄኔቫ የሚመጡ ሲሆን፣ ለመመረጥ የቅስቀሳ ( ሎቢ) ስራ ይሰራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የድርጅቱ ሰራተኞች ዶ/ር ቴዎድሮስ የንጹሃን ዜጎችን ደም በማፍሰስ የሚወነጀለው የህወሃት/ኢህአዴግ አንዱ ከፍተኛ መሪ በመሆናቸው ኢትዮጵያውያን ተቃውሞዋቸውን ፊርማ በማሰባሰብና ለድርጅቱ ደብዳቤ በመጻፍ እንዲገልጹ ጥሪ አቅርበዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ ያለው ርሃብ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አሳወቀ

ታኀሳስ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዓለም የምግብ ድርጅት በኢትዮጵያ ያለው የድርቅ ሁኔታ እየከፋ መምጣቱንና ዜጎች አፋጣኝ እርዳታ ካልተደረገላቸው በአገሪቱ የሚደርሰው ሰብዓዊ ቀውስ እጅግ አደገኛ መሆኑን በሪፖርቱ ገልጿል።
በኢትዮጵያ በተከሰተው የአየር መዛባት ኤሊኖ ምክንያት ወቅቱን ጠብቆ ዝናብ ባለመዝነቡ በቂ ምርት መሰብሰብ ያልተቻለ ሲሆን እንስሳትም በድርቁ ሰበብ ሞተዋል።
ቁጥራቸው ከ10 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን አፋጣኝ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን የዓለም የምግብ ድርጅት 7.6 ሚሊዮን የሚሆኑትን በ2016 ዓ.ም ለመርዳት መዘጋጀቱንና ባለፉት ስድስት ወራቶች ውስጥ ከ5% ያነሰ የምግብ አቅርቦት ግብዓቶችን ማድረሱን የድርጅቱ ቃል አቀባይ እስቴፋን ጁሪክ አስታውቀዋል።

በኦሮምያ ዜጎች በህወሃት ንብረቶች ላይ የኢኮኖሚ ማእቀብ እየጣሉ ነው

ታኀሳስ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ህዘባዊ ተቃውሞው እንደቀጠለ ሲሆን፣ ዜጎች በህወሃት ኩባንያዎች ላይ እርምጃ እየወሰዱ ነው። ትንናት በምስራቅ ሀረርጌ ቆቦ ከተማ የተጀመረው ተቃውሞ ወደ መሰላ ከተማም ተዛምቷል። የኢህአዴግ ወታደሮች በሚወስዱት ጭካኔ የተሞባለት እርምጃ እስካሁን 3 ሰዎች መገደላቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና ያመለክታል። የስርዓቱ ወታደሮች የሚወስዱት ጭካኔ የተሞላበት የሃይል እርምጃ ያሳሰባቸው የክልሉ ነዋሪዎች፣ የህወሃት ንብረት በሆነው ሰላም አውቶብስ ላለመሳፈር እንቅስቃሴ ጀምረዋል:፡ የክልሉ ወኪላችን እንዳለው ዜጎች በሰላም አውቶቡስ አንሳፈርም ማለታቸው ብቻ ሳይሆን፣ አውቶቡሱ በአካባቢው እንዳይንቀሳቀስ እየወሰዱት ያሉት እርምጃ ስጋት ላይ የጣለው ፣ ገዢው ፓርቲ፣ በእያንዳንዱ የሰላም ባስ ተሽከርካሪ ላይ ጠባቂ ወታደሮችን ለመመደብ ተገዷል።

Monday, January 4, 2016

የእኔና አየርመንገዳችን ክርክር - የኢ-ፍትሓዊነት ማሳያ?! - በአቤል ዋበላ


ያኔ ይደብረኝ ነበር፡፡ መሥሪያ ቤቱ ይደብረኛል፡፡ አለቆቼ ይደብሩኛል፤ የሚጠገ’ኑት አውሮጵላኖች ሽታ ይደብረኛል፡፡ አቧራ የጠገቡት የጥገና መሳሪያዎቼ ይደብሩኛል፡፡ ለምን ይህንን ስህተት ሠራሁ እያልኩኝ ራሴን እጠይቃለሁ፡፡ ለምን በኮሌጅ የተማርኩትን የመሀንዲስነት ሙያ ትቼ ስለምን የአውሮጵላን ጥገና ሙያ ውስጥ ገባሁኝ እያልኩኝ ራሴን እጠይቃለው፡፡ ከኮሌጅ እንደወጣሁኝ ሥራ የጀመርኩት በቢሾፍቱ ከተማ ነበር፡፡ በኋላ ደግሞ የተወሰኑ ወራት ጫንጮ የሚገኝ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሠርቻለው፡፡ ጥግ ጥግ ከመዞር ገላግሎ አዲስ አበባን እንድከትምባት ዕድሉን ያመቻቸልኝ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው፡፡ያኔ የትውልድ ከተማዬ ውስጥ፣ አዲስ አበባ መሆን እፈልግ ነበር፡፡ አራት ኪሎ ከቤተ መንግሥቱም፣ ከቤተ ክህነቱም መራቅ አልፈልግም ነበር፡፡ ምክንያቴ ደግሞ የማወቅ የመማር ነበር፡፡ ጫንጮ ብርዳማ ናት፡፡ እንደ አየር ንብረቷ የዐሳብ ገበያዋም ለእኔ ፍላጎት የሚያመረቃ አልነበረም፡፡ በወቅቱ በስስት የምትነበበውን አዲስ ነገር ጋዜጣን ለማግኘት እንኳን ወደ መዲናዋ የሚመላለሱ ሹፌሮችን መለማመጥ ግዴታዬ ነበር፡፡

የኢትዮጵያ ፖሊሶች ሁለት ኬንያዊያንን አግተው መውሰዳቸው ታወቀ

ታኀሳስ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ቅዳሜ እለት የኢትዮጵያ የደኅንነት ኃይሎች በኢትዮ ኬንያ ድንበር ቦሪ አቅራቢያ ተሻግረው ሁለት ኬንያዊንና ሁለት የእሳት አደጋ መከላከያ መሳሪያዎችን አግተው መውሰዳቸውን የቀጠናው ፖሊስ አስታውቋል።
የመርሳቤት ግዛት የፓሊስ አዛዥ የሆኑት ሞፋት ካንጋ እንዳሉት ግለሰቦቹ ምን እንዳደረጉ ያወቅነው ነገር የለም። በእርግጥ በኦሮሞ ሕዝብና በኢትዮጵያ መንግስት መሃከል ችግር እንዳለ እናውቃለን። የታገቱትን ዜጎቻችንን እንደሚለቁና የወሰዱብንን መሳሪያዎች እንደሚመልሱልን ተስፋ አደርጋለሁ በማለት መግለጫ ሰጥተዋል።
የኬኒያ የደህነት ባለስልጣናት ሁኔታውን እያጣሩ ሲሆን ባለፈው ወር በኢትዮጵያ የፀጽታ ኃይሎች ሶስት ፖሊሶች መገደላቸው ይታወሳል ሲል ስታንዳርድ ዲጅታል አክሎ ዘግቧል።

ድርቁ እየተባባሰ በመጣባቸው አካባቢዎች የትምህርት ሰራው እየተጎዳ መምጣቱ ተነገረ፡፡

ታኀሳስ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኙ ሰባት ወረዳዎች በተከሰተው ድርቅ ፣ የሚያስተምሩ መምህራን በየጊዜው ስራቸውን በመልቀቃቸው የትምህርቱ ስራ አደጋ ላይ መሆኑን የዞኑ ትምህርት ከፍተኛ ባለስልጣናት በጎንደር ከተማ በሰጡት መግለጫ ተናገሩ፡፡
በዞኑ ባሉት 280 አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ120 ሽህ በላይ ህጻናት ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማቆም በቋፍ ላይ መሆናቸወን የተናገሩት የዞኑ አመራሮች በተለይ በወገራ፣ምስራቅ በለሳና ጃናሞራ ወረዳዎች በሁለት ሳምንት ብቻ 265 መምህራን መልቀቃቸውን ሲናገሩ ተሰምተዋል፡፡
በጃናሞራ ወረዳ አሁን አሁን የመበተን አዝማሚያ እየታየ መሆኑን የዞኑ የትምህርት ከፍተኛ ኃላፊዎች ገልጸው፤ሰፊ የደርቅ አደጋ በታየባቸው 120 ቀበሌዎች የትምህርቱ ሂደት አደጋ ላይ መውደቁን ተናግረዋል፡፡

በዲላ ዩኒቨርስቲ ግጭቱ ተባብሶ ሊቀጥል እንደሚችል ተማሪዎች ስጋታቸውን ገለጹ

ታኀሳስ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሶስት ቀናት በፊት በዲላ ዩኒቨርስቲ ምሽት ላይ በተመሳሳይ ሰአት በፈነዱ 4 ቦንቦች አንድ ተማሪ ወዲያውኑ ሲሞት፣ አንደኛው ሆስታል ከገባ በሁዋላ መሞቱ መዘገቡ ይታወሳል። ፍንዳታውን ተከትሎ 10 ተማሪዎች በጩቤ የተወጉ ሲሆን፣ አንዳንድ ተማሪዎች ለዘጋቢያችን እንደገለጹት ጉዳቱን ያደረሱት የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አባላት አለመሆናቸውን ተናግረዋል። በፍንዳታው አንድ አዳማና ሌላ ደብረብርሃን ልጅ ሲገደሉ፣ አንድ አርባ ምንጭ ልጅ ደግሞ እግሩ ተቆርጧል። ይህን ተከትሎ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው ሲወጡ፣ የፌደራል ፖሊስ ወደ ግቢው እንዲገቡ ያስገደዳቸው ሲሆን፣ እንደገና 3 ተማሪዎች መጸዳጃ ቤት ውስጥ ታርደው ተጥለው ተገኝቷል።

የመንግስት ወታደሮች በኦሮምያ የሚፈጽሙትን ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እንደቀጠሉ ነው

ታኀሳስ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለተከታታይ ሳምንታት በኦሮምያ የተደረገው ህዝባዊ ተቃውሞ ደም አፋሳሽ ሆኖ ቀጥሏል። የመንግስት ወታደሮች ያለርህራሄ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እየወሰዱ ነው። እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መንገድ የተገደሉ ዜጎችን ምስል በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን ማየት የተለመደ ክስተት ሆኗል። መንግስት የሚወስደው ከልክ ያለፈ እርምጃ ተቃውሞን ከመባባስ ውጭ ሊገታው አልቻለም።

በዲላ ዩንቨርስቲ በተከሰተው ግድያ የተነሳ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፣ 2008)
ባለፈው ሐሙስና ቅዳሜ ጠዋት በዲላ ዩንቨርስቲ በእጅ በተወረወረ ቦምብ ጥቃትና በስለት ተወግተው 4 ተማሪዎች መሞታቸውን ከዲላ የአይን እማኞች ለኢሳት ተናግረዋል። ከተጎጂዎቹ ውስጥ በቦምብ ጥቃት የሞቱት በተለምዶ “ሰመራ” ተብሎ በሚጠራው ካምፓስ የሚኖሩ ሁለት ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ከ10 የማያንሱ ተማሪዎች ደግሞ በቦምብ ፍንዳታውና በጩቤ ተጎድተው በዲላ ሬፈራል ሆስፒታል ህክምና እያገኙ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
በተጨማሪውም ባለፈው ቅዳሜ ጠዋት ሶስት ተማሪዎች በስለት መጸዳጃ ቤት ውስጥ ታርደው መገደላቸውን በግቢው ውስጥ የነበሩ እማኞች ገልጸዋል። ጥቃቱን የሰነዘረው አካል  ማን እንደሆን እስካሁን ያልታወቀ ቢሆንም፣ ድርጊቱ ምን አልባትም በመንግስት ካድሬዎች የብሄር ግጭት ለማስነሳት ሆን ተብሎ ሳይፈጸም እንዳልቀረ ተገምቷል።
አርብ ማታና ቅዳሜ ጠዋት በተፈጸሙት በእነዚህ ዘግናኝ ድርጊቶች የተደናገጡት ተማሪዎች፣ እጅግ በመረበሻቸው የዩንቨርስቲውን ግቢ ለቀው ወጥተዋል ሲሉ የአይን እማኞች ለኢሳት ገልጸዋል።

በጋምቤላ ክልል 9 የልዩ ሃይል አባላት ከእነሙሉ ትጥቃቸው ሸማቂ ቡድንኑ መቀላቀላቸው ተሰማ

ኢሳት (ታህሳስ 25 ፥ 2007)
የጋምቤላ ልዩ ሃይል አባላት ከእነሙሉ ትጥቃቸው የህወሃትን መንግስት በመክዳት ተቃዋሚዎችን መቀላቀላቸው ከአገር ቤት የደረሰን ዜና አመለከተ።
የልዩ ሃይል አባላቱ የታጠቁትን የጦር መሳሪያ በመያዝ የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ጥምረት ግንባር የተባለው ሸማቂ ቡድን መቀላቀላቸውየኢሳት ምንጮች ከአገር ቤት ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች ብዛት ያላቸው የስርዓቱ መከላከያ ሃይል አባላት ስርዓቱን እየከዱ ሸማቂ ቡድኑን እየተቀላቀሉ ናቸው ተብሏል።
የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ጥምረት ግንባር ሊቀመንበር አቶ አቡላ ኦባንግ አሁን የተቀላቀሏቸው የልዩ ሃይል አባላት ለትግሉ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርጉ ለኢሳት ተናግረዋል።

በኦሮሚያ የመለስ ፓርኮችና የአደባባይ ፎቶግራፎች ተቃጠሉ


ኢሳት (ታህሳስ 25 ፣ 2008)
በኦሮሚያ ክልል ከማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ የተነሳው ተቃውሞ ሰሞኑን እንደገና አገርሽቶ በተለይም በምስራቁ የአገራችን ክፍል ከፍተኛ አለመረጋጋት መከሰቱን ከስፍራው የሚወጡ ዘገባዎች አመለከቱ።
በምዕራብ ሃረርጌ ዞን ሂርና ከተማ እና በምስራቅ ሃረርጌ ዞን በደኖ ወረዳዎች በህወሃት/ኢህአዴግ ታጣቂዎችና በነዋሪው ህዝብ መካከል ከፍተኛ ግጭትና ፍጥጫ እንደነበር የአይን እማኞች ከስፍራው ለኢሳት ተናግረዋል።
በበደኖና በሂርና አርብ የጀመረው ተቃውሞው እስከዛሬ ሰኞ ድረስ እንደቀጠለም ታውቋል። በሁለቱም አካባቢዎች አውራ ጎዳናዎች ተዘግተው እንደነበርና፣ ህዝቡም ተቃውሞ ሲያሰማ እንደሰነበተ እሳት ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በኤጀሬ ሰሜን ሸዋ የመለስ ዜናዊ ፓርክ ቅዳሜ ምሽት ሙሉ በሙሉ ተቃጥሏል። ከሁለት ሳምንት በፊትም በጀልዱ የሚገኘው የአቶ መለስ ዜናዊ ብሄራዊ ፓርክ መቃጠሉን ኢሳት ዘግቦ እንደነበር ይታወሳል። የአቶ መለስ ፎቶግራፎችም በአንዳንድ ኦሮሚያ አካባቢዎች እንደተቃጠሉ ለማወቅ ተችሏል። በአርሲም ሰሞኑን በአደባባይ የተሰቀሉ የአቶ መለስ ዜናዊ ፎቶዎች እንደተቃጠሉ በስፍራው የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ተናግረዋል።
የአቶ መለስ ዜናዊ ፓርክና ፎቶግራፍ ማቃጠል ላይ ህዝቡ ለምን እንዳተኮረ የተጠየቁት አንድ የኢጄሬ አካባቢው ነዋሪ፣ አቶ መለስ ዜናዊ በአገዛዝ ዘመናቸው ያመጡት ጎጠኝነት እና አገሪቷን በዘውግ በመከፋፈል ላይ የተመሰረተ የአስተዳደር ስርዓት ህዝቡን ለከፍተኛ ጭቆናና ብዝበዛ ኣንደዳረገው ገልጸው፣ ይህን ጭቆናና ብዝበዛ ለመቃወም በስማቸው የተሰየመውን ፓርክና ፎቶግራፍ አቃጥለነዋል ብለዋል።
“አገሪቷ በሙት መንፈስ መመራት የለባትም” ያሉት እኚህ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉት ሰው፣ “የመለስ ራዕይ ከሚሉት ቅዠት ህዝቡን ነጻ ማውጣት አለብን” ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
ሌሎች እሳት ያነጋገራቸው ሰዎችም በአቶ መለስ ዜናዊ የተሰየሙት ፓርኮችና በየአደባባዩ የተሰቀሉት ፎቶግራፎች እየተቃጠሉበት ያሉበት ምክንያት አሁን በሁሉም የአገሪቷ ክፍሎች በገሃድ እየታየ ያለውን ጭቆናና ግፍ ያመጡብን አቶ መለስ በመሆናቸው ይህንን ለመቃውም ነው ሲሉ አስተያየታቸውን አክለዋል።

Sunday, January 3, 2016

በቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ እየደረሰ ስላለው ሁኔታ ከለንደን ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

በአሁኑ ወቅት በቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያና በሕዝቧ ላይ እየደረሰ ስላለው ሁኔታ ከለንደን ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ።

“ጻድቃን ጮኹ፤ እግዚአብሔርም ሰማቸው፤ ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።” (መዝ፡ 34፡ 17)
ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ፈጣሪን በማወቅና የክርስትና ሃይማኖትን በመቀበል ቀደምት ከተባሉት የዓለም ሀገራት አንዷ ስትሆን ሕዝቧም በፈሪሃ እግዚአብሔር የታነፀ፤ ጨዋ ኩሩ እና ዘር ሃይማኖትና ቋንቋ ሳይከፋፍለው በመቻቻል፤ በመፈቃቀርና በመከባበር በሰላም አብሮ መልካም ምሳሌ ሆኖ የኖረ ነው።

የመጨረሻዉ መጀመሪያ — አሜሪካ ለምን የአርባ ምንጭ የሰዉ አልባ አይሮፕላን ማስነሻ ጣቢያዋን መተዉ አስፈለጋት?

ከሳዲቅ አህመድ
ወደ አለም አቀፉ የዲፕሎማሲ መንደር ቀረብ ቀረብ ማለት ከጀመሩ ወራት ተቆጥረዋል። ከሐያላኑ አገራት ጋር የቀጥታ ሳይሆን የእጅ አዙር የዲፕሎማሲ ጉዞን ሳይጀምሩ አልቀሩም የሚሉም አሉ። በጠመዝማዛዉ መንገድ የሚጓዙት የዲፕሎማሲ ጉዞ ከሚፈልጉበት ቦታ እስኪያደርሳቸዉ ድረስ እምብዛም አትኩሮት አልሳቡም። እርሳቸዉ ግን እየተጓዙ ነዉ። ፕሬዝዳንት ኢሳያስ  አፈርቂ።
ዜናዉ፦

አሜሪካ አርባ ምንጭ ዉስጥ ያላትን የሰዉ አልባ አይሮፕላን ማብረሪያ ጣብያ መጠቀም ማቆሟ ታወቀ

በሱማሊያ ያሉትን አል-ሸባቦች ለማጥቃት አሜሪካ እንደ ኢሮጵያዉያን አቆጣጠር ከ2011 ጀምሮ ትጠቀምበት የነበረዉን የሰዉ አልባ አይሮፕላን ማስነሻ ጣብያ መጠቀም ማቆሟን አሶሽየትድ ፕሬስ አዲስ አበባ ያለዉን የአሜሪካ ኤምባሲ ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።US shuts down drone operation in Ethiopia

Saturday, January 2, 2016

“መፍትሄ ያጣው የቡዳ ፖለቲካችን” – ዶ/ር መረራ ጉዲና


gudina zehabesha
 (“የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ህልሞች” በሚል ርዕስ አንጋፋው ፖለቲከኛና የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር ዶ/ር መረራ ጉዲና ሰሞኑን ለንባብ ካበቁት ሁለተኛ መጽሐፋቸው የተቀነጨበ

… የቡዳ ጉዳይ በሀገራችን ባሕል ውስጥ የታወቀ ስለሆነ ለማስረዳት ዝርዝር ውስጥ አልገባም፡፡ ቡዳና ፖለቲካችንን ምን አገናኛቸው ለሚለው ጥያቄ ግን ተገቢ መልስ መስጠት ስለአለብኝ አንዳንድ ጭብጦችን ላስቀምጥ፡፡ ተረቱ እንደሚለው፣ አንድ ቡዶችን ለይቶ የማያውቅ ሰው፣ የቡዶች መንደር ይደርስና፣ “እዚህ አካባቢ የቡዶች መንደር አለ ይባላል፣ የትኛው ነው” ብሎ ራሱን፤ ቡዳውን ይጠይቀዋል፡፡ ቡዳው ሰው፣ “ቡዶች የምንባለው እኛው ነን” ለማለት ድፍረት ስላጣ፣ “እኛ እዛ ማዶ ያሉት ናቸው እንላለን፣ እነሱ ደግሞ እኛን ይሉናል” አለ ይባላል፡፡

ዛሬ በዲላ ዩኒቨርሲቲ 3 ተማሪዎች በመጸዳጃ ቤት ውስጥ ተገድለው ተገኙ | ተማሪዎች ግቢውን ለቀው እየወጡ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከትናንት በስቲያ ቦምብ መፈንዳቱን ተከትሎ የተማሪዎች ሕይወት ማለፉን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም:: ዛሬ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ እንደሚጠቁመው 3 ተማሪዎች መጸዳጃ ቤት ሞተው ተገኝተዋል::
dilla
ዘ-ሐበሻ እንዳነጋገረቻቸው ተማሪዎች ከሆነ በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያለው አለመረጋጋት እጅጉን ከቁጥጥር ውጭ ሲሆን በርካታ ተማሪዎች ጊቢውን ለቀው ቢወጡም ሌሎች ደግሞ በፌደራል ፖሊሶች እንዳይወጡ መደረጋቸው ተሰምቷል::
እጅጉን ቆሳስለው በመጸዳጃ ቤት ውስጥ ሞተው የተገኙት ተማሪዎች በፌደራል ፖሊሶች መጨፍጨፋቸውን የገለጹት እነዚሁ ምንጮች በደም በመጨማለቃቸው በጥይት ብቻ ተመተው ሞቱ ለማለት ይከብዳል ይላሉ:: እንደምንጮቹ ገለጻ እነዚህ ሶስት ተማሪዎች ሳይወጉ አይቀሩም::
ከትናንት በስቲያ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፈነዳውን ቦምብ በተመለከተ መንግስታዊ ሚድያዎች ያልታወቁ ሰዎች ያፈነዱት ነው ቢሉም በአንጻሩ ሌሎች የመንግስት ወታደሮች በተማሪዎቹ ላይ ጥቃት ለማድረስ ሆን ብለው ያደረሱት ጥቃት ነው ሲሉ ይከሳሉ::

Friday, January 1, 2016

“የአዲስ አበባ ማስትተር ፕላን አልቆመም በሱሉልታ የመሬት ቅርምቱ ቅጥሏል” ይላሉ የሱሉልታ ነዋሪዎች።


ከመቶ ለሚበልጡ የኦሮሞ ተወላጆች ሞት ምክንያት የሆነዉ፣ አያሌ የኦሮሞ ተወላጆች ታስረዉ ለስቃይ አያያዝ የተጋለጡበት፣ እዉቅ የፖለቲካ መሪዎች፣ጋዜጠኞች፣ የሲቪክ ተቋማት አገልጋዮች ታፍነዉ የተወሰዱበት፣ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን የፈሰሰበት ደም ሳይደርቅ መመሪያዉ ወደ መሬት እየወረደ ነው ሲሉ የሱልልታ ነዋሪዎች ለቢቢኤን ገለጹ።
የሱሉልታ ማዘጋጃ ቤት የገበሬዉን መሬት ለመንጠቅ ማስትወቂያ አዉጥቷል የሚሉት ነዋሪዎች፤ የማዘጋጃቤት ሰራተኞች በድምጽ ማጉያ መሬት መዉሰድ የሚፈልግ ካለ መመዝገብ ይችላል በማለት በየመንደሩ እይዞሩ ማስተዋወቅ መጀመራቸዉንም ይገልጻሉ።
በአካባቢው ያለዉ ገበሬ ወደ ‘መሬት ለመተግበር የመጣ መመሪያ የለም’ በማለት የእርሻ ስራዉን ከመቀጠል በስተቀር ጉዳዩን እምብዛም በጥልቀት ያለተመለከተዉ መሆኑን የሚገልጹት የሱሉልታ ነዋሪዎች፤ የከተማዉ ህዝብ ‘እንጫረሳታለን እንጂ መሬታች አይወሰድም’ በሚል የትግል መንፈስ ዉስጥ መሆኑን ጨምረዉ ለቢቢኤን ገልጸዋል።