Friday, November 25, 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በወያኔ ጦር ላይ በተለያዩ ቦታዎች በተደጋጋሚ ጥቃት መፈፀሙን በመቀጠል ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ታወቀ፡፡

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)

የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ነበልባል የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ህዳር 10 ቀን 2009 ዓ.ም ለሊት ጎንደር ዳንሻ ከተማ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በተባለ ቦታ ሰፍሮ ከሚገኝ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ላይ በፈፀመው ድንገተኛ ማጥቃት ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ አጥቅቶ ተሰውሯል፡፡ በወሰደው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃም 15 የወያኔ ቅጥረኛ ወታደሮችን በመግደል ቁጥራቸው ያልታወቀ ደግሞ ማቁሰሉን አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ከስፍራው ባደረሰን ዘገባ አስታውቋል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ጥቃቱን በመቀጠል ህዳር 13 ቀን 2009 ዓ.ም በአብደራፊ ከተማ ዙሪያ በህወሓት መከላከያ ሰራዊት ላይ ተመሳሳይ የደፈጣ ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን ባደረገው ሰፊ የማጥቃት እርምጃም 25 በመግደልና 17 በማቁሰል በቅጥረኛው የህወሓት ጦር ላይ ጠንካራ ክንዱን በማሳረፍ የበላይነትን ተጎናፅፎ የህወሓት ቅጥረኛ ወታደሮችን እንቅስቃሴ በመግታት መበታተን እንደቻለ ሪፖረተራችን አክሎ ገልጿል፡፡
ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት እየፈፀመ ያለውን ቆራጥ ተጋድሎ ጥቃቱ በሚፈፀምበት ቦታ ሁሉ ሙሉ በሙሉ የህዝብን ድጋፍ እያገኘ ሲሆን የቆመለትን አላማ ከግብ ለማድረስ ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ትንሳኤ እስኪሆን ድረስም ጀግኖች የአርበኞች ግንቦት 7 ነበልባል ሰራዊት ወደፊት በመግፋት በተግባር የኢትዮጵያ አለኝታነታቸውን እያስመሰከሩ ይገኛሉ፡፡

Tuesday, November 22, 2016

Ethiopia: Amharas in Benishangul face displacement

ESAT News (November 22, 2016)
Amharas who have resettled and called it home in Benishangul Gumuz region since 30 years ago during the former Ethiopian regime have said  they are facing harassment and threat of displacement from their land.
The Amharas, who settled in Benishangul in a resettlement program in the former government are being threatened by authorities to leave the region, according to a source who spoke on the phone with ESAT.
Hundreds of Amharas in Asosa have been displaced after authorities gave their land to developers, forcing them to migrate to towns and other areas.
Meanwhile, security forces have detained several youth in Benishangul Gumuz following the martial law declared in October, sources told ESAT.
An estimated 80,000 Amharas live in Benishangul Gumuz region in western Ethiopia.

Monday, November 21, 2016

ማዕበል ከፋሲል የኔአለም

የትኛውም ለህዝብ ነጻነት የሚታገል ድርጅት ከውስጥም ከውጪም ማዕበል ያጋጥመዋል። በማዕ በል ሳይመታ ለውጤት የበቃ ድርጅት በታሪክ ያለ አይመስለኝም፤ ማዕበል የአንድ ድርጅት ተፈጥሮአዊ ባህሪው ነው ማለትም ይቻላል። የትኛውም ድርጅት ማዕበል እንዳይነሳ ማድረግ አይችልም፣ ውስጣዊ ማእበል እንዳይነሳ ማድረግ ቢችል እንኳን ውጫዊ ማዕበሉን በፍጹም ማስቀረት አይችልም። ትልቁ ነገር ድርጅቱ ማእበሉን እንዴት በጥበብ ያልፈዋል የሚለውን ጥያቄ መመለሱ ላይ ነው። ማእበል ለአንድ ድርጅት አወንታዊ ወይም አሉታዊ ነገሮችን ይዞ ይመጣል። አንዳንድ ድርጅቶች የተነሳባቸውን ማእበል በጥበብ ማለፍ ያቅታቸውና ይጠፋሉ ( የማእበል አሉታዊ ጎኑ መሆኑ ነው)፣ ሌሎቹ ደግሞ ማእበሉን ማለፍ ብቻ ሳይሆን ከማእበሉ ትምህርት ወስደውበት ተጠናክረው ይወጣሉ ( የማእበል አወንታዊ ጎኑ ነው)።

Thursday, November 17, 2016

CPJ renews calls to Ethiopian regime to release all journalists

Ethiopia should immediately release all journalists detained amid an intensifying crackdown on the media, the Committee to Protect Journalists said on Thursday.
In recent weeks, Ethiopian authorities have jailed Getachew Worku, newspaper editor, as well as two members of the award-winning Zone 9 bloggers’ collective, which has faced continuous legal harassment on terrorism and incitement charges.
A fourth journalist has been missing for a week; his family fears he is in state custody, CPJ said in a state
“Silencing those who criticize the government’s handling of protests will not bring stability,” CPJ Africa Program Coordinator Angela Quintal said from New York. “The constant pressure on Zone 9 bloggers with repeated arrests and court appearances is clearly designed to intimidate the remaining independent journalists in Ethiopia.”

የአርበኞች ግንቦት7 ሃይል ከህወሃት/ኢህአዴግ ወታደሮች ጋር በቀብትያ ሁመራ እና አጎራባች ቀበሌዎች እየተዋጋ ነው

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአርበኞች ግንቦት7 የሰሜን ጎንደር አስተባባሪ እንደገለጹት፣ አባሎቻቸው በሰሜን ጎንደር በተለያዩ አካባቢዎች ለወራት ሲደራጁና ሲያደራጁ ከቆዩ በሁዋላ፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ወታደራዊ ጥቃት በመፈጸም ላይ ናቸው። በተለይ ከትናንት ጀምሮ በቃፍታ ሁመራ እና በአከር አካባቢ ከፍተኛ ውጊያ እያካሄደ መሆኑንም ተናግረዋል።

በአባይ ግድብ አካባቢ ያለው የስራ እንቅስቃሴ መዳከሙን ጋዜጠኞች ገለጹ ።

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ‹‹ በአባይ ግድብ ላይ ያለው እንቅስቃሴ ቆሟል የሚል ወሬ በስፋት እየተወራ ነውና ወሬውን አክሽፉ!” ተብለው ለጉብኝት የተላኩት ጋዜጠኞች ምንም አይነት የስራ እንቅስቃሴ ባለማየታቸው የሚወራው ትክክል መሆኑን አረጋጋጥው መመለሳቸውን ለኢሳት ገለጹ።
ሰሞኑን ወደ አባይ ግድብ የተላከው የ መንግስት ጋዜጠኞች ቡድን ለጉብኝት በቆየበት አንድ ቀን፤ ምንም አይነት ስራ ሲሰራ አለመመልከቱን ገልጿል፡፡ ‹‹ ለአንድም ደቂቃ ስራው አይስተጓጎልም ›› የተባለለት ይህ የግድብ ስራ አልፎ አልፎ ከሚንቀሳቀሱ ተሸከርካሪዎች በስተቀር ምንም አይነት የስራ እንቅስቃሴም ሆነ ሰራተኞችን አለመመልከቱንና ስራው ተስተጓጉሏል የሚለው እውነት መሆኑን የቡድኑ አባላት ተናግረዋል።

በሶማሊያ ክልል በኮሌራ ወረሽኝ 35 ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በምስራቅ ኢትዮጵያ ኦጋዴን አካባቢዎች በኮሌራ በሽታ 35 ሰዎች መሞታቸውንና ድርቁን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊ ቀውስ እየተፈጠረ መሆኑን የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት አስታወቀ። በድርቁ ምክንያት እንስሳት እየሞቱ ነው። የምግብ እጥረት ተጠቂ የሆኑት የኦጋዴን ነዋሪዎች አፋጣኝ እርዳታ ካላገኙ አደጋው የከፋ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።

በኢንተርኔት አፈና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች ።

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በዜጎቻቸው ላይ አፈና በማድረግ የመረጃ እቀባ ከሚያደርጉ አገራት ውስጥ ቻይና፣ ሶሪያ እና ኢራንን በመከተል ኢትዮጵያ በዓለም አራተኛ፣ በአፍሪካ ደግሞ በአንደኝኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ፍሪደም ሃውስ አስታውቋል። በኢንተርኔት ስርጭት ሁዋላ ቀር የሆነችው ኢትዮጵያ በኢንተርኔት ተጠቃሚ ዜጎቿ ላይ በምታደርገው እቀባዎችና አፈናዎች ግን ቀዳሚ ሆናለች ብሎአል።

ዮናታን ተስፋዬ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት እንደሚታሰር ታውቋል

ፌስቡክ ላይ በጻፋቸው ፅሁፎች ምክንያት የሽብር ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በፍ/ቤት እየታየ የሚገኘውና በእስር ቂሊንጦ ያለው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ በሚገኝበት እስር ቤት ውስጥ ከአርብ ህዳር 2/2009 ዓ.ም ጀምሮ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት ታስሮ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለዚህ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የዳረገው ህዳር 2/2009 ዓ.ም የፍርድ ቤት ቀጠሮ የነበራቸው እነ አቶ በቀለ ገርባ ወደ ፍርድ ቤት አንሄድም በሚል ከቂሊንጦ እስር ቤት አስተዳደር ጋር አለመግባባት ፈጥረው ድብደባ ሲደርስባቸው አቶ ዮናታን ‹‹ለምን ትደበድቧቸዋላችሁ፤ በመግባባት ቢሆን አይሻልም ወይ›› በሚል ለግልግል ጣልቃ መግባቱን ተከትሎ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋዬ በተለይ አብሮት የታሰረው አቶ አዲሱ ቡላላ ላይ ድብደባ ሲደርስበት ‹‹ተው አትደባደቡ›› በማለቱ ‹‹ምን አገባህ›› ተብሎ በራሱም ላይ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞበት ከዚያ ወዲህ በሰንሰለት ለመታሰር እንደተዳረገ ታውቋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ ሰንሰለቱ የሚፈታለት ቤተሰቦቹ ሊጎበኙት ሲጠራ ብቻ እንደሆነም የመረጃው ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ አቶ ዮናታን መከላከያ ማስረጃዎችን ለማድመጥ ለህዳር 19/2009 ዓ.ም ተለዋጭ የፍ/ቤት ቀጠሮ ላይ እንደሚገኝ ይታወሳል፡፡

Wednesday, November 16, 2016

በቆላ ቃብቲያ ኹመራ ከፍተኛ ጦርነት ተቀስቅሷል

zehabesha
 ዛሬ ኅዳር 7 ቀን 2009 ዓ.ም ከቀኑ 11.00 አካባቢ ጀምሮ የወያኔ ጦር ከአማራ ገበሬዎች ላይ ጦርነት ከፍቷል። በአካባቢው የጎበዝ አለቆች የሚመራው የአማራ ገበሬዎች ጦር በአጋዚ ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ለማጥቃት የሄደው የወያኔ አጋዚ ጦር ከምልሻዎች እርዳታ መጠየቁን ሰምተናል።