Friday, January 30, 2015

የአርበኞች ግንቦት7 ሴት አባላት የትግል ጥሪ አቀረቡ

ጥር ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዢውን ፓርቲ በሃይል ለማንበርከክ በትግል ላይ የሚገኙ የአርበኞች ግንቦት7 ሴት አባላት ጥሪያቸውን ያቀረቡት የመስክ ጉብኝት ለማድረግ ለተንቀሳቀሱት የኢሳት ጋዜጠኞች ነው።
ሴት አርበኞቹ በአገሪቱ ውስጥ እየተካሄደ ያለው አፈናና የመብት ጥሰት በስልጣን ላይ ያለውን የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት በሃይል ለማንበርከክ ነፍጥ እንዲያነሱ እንዳስገደዳቸው ገልጸዋል።
ለሁለት ወራት ያክል ከኢህአዴግ ታጣቂ የሰራዊት አባላት ጋር ጠንካራ ፍልሚያ ስታደርግ ቆይታ በመጨረሻ ምንም ችግር ሳያጋጥማት ሌሎች አርበኞችን ለመቀላቀል መቻሉዋን የገለጸችው አርበኛ ሃብታም ታደሰ፣ ወያኔ ደካማ መሆኑን በጫካ ህይወቴ ለማረጋገጥ ችያለሁ ብላለች።
አርበኛ ሃብታም ገዢውን ሃይል ለማንበርከክ በሚደረገው ትግል ሴቶች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርባለች
ሌላዋ አርበኛ ሰላማዊት ትኩ በበኩሏ ሴቶች የግድ በረሃ መውረድ እንደሌለባቸው ገልጻ፣ ለነጻነት ለሚደረገው ትግል ባሉበት ቦታ ሁሉ ሆነው ሊደግፉ፣ ሊታገሉ ይችላሉ ብላለች።
አርበኛ ሰናይት ወርቅነህም እንዲሁ በኢትዮጵያ ውስት የሚታየው ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መሄዱን ገልጻ በውጭና በአገር ውስጥ የሚኖሩ ሴቶች ትግሉን ተቀላቅለው ታሪክ የጣለባቸውን ሃላፊነት ይወጡ ስትል መልክት አስተላልፋለች።
የኢሳት የጋዜጠኞች ቡድን ተዘዋውሮ ለመታዘብ እንደቻለው በርካታ ሴቶች ገዢውን ሃይል በመሳሪያ ለማንበርከክ ወስነው እየታገሉ ነው። አርበኞች ግንባርና ግንቦት7 ውህደት ከፈጸሙ በሁዋላ ከሌሎች ሃይሎች ጋር ትብብር እና ጥምረት በመፍጠር ገዢውን ፓርቲ በሃይል ለማንበርከክ እንደሚሰሩ መግለጻቸው መዘገቡ ይታወሳል።
በሌላ በኩል ደግሞ የቀድሞ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አርበኞች ማህበር በአርበኞች ግንባርና በግንቦት7 መካከል የተፈጸመውን ውህደት በመደገፍ መግለጫ አውጥቷል። ማህበሩ በመግለጫው ኢትዮጵያን ከገባችበት ውድቀት ነጻ ለማውጣት የተናጠል ትግል እንደማያዋጣ በመግለፅ ድርጅቶቹ ያደረጉት ውህደት አስደሳች ነው ብሎአል።


Thursday, January 29, 2015

ሰበር ዜና ቦርዱ በአቶ ትዕግስቱ ለሚመራው የአንድነት ፓርቲ እና በአቶ አበባው ለሚመራው መኢአድ ፓርቲ ዕውቅና ሰጠ

አንድነት ዛሬ ተላለፎ መሰጠቱን ተረጋገጠ! የኢህአዴግ ምርጫ ቦርድ አንድነት በእነ ቱግስቱ እየተመራ ወደ ምርጫ እንዲገባ ተወሰነበት፤ እንዲህ ነው ጨዋታ

ሆደ ሰፊ ነኝ የሚለው የወያኔ ምርጫ ቦርድ በተደጋጋሚ በ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ እያሳረፈ ያለውን ሸፍጥ በመቀጠል ጭራሽ ህጋዊ ላልሆኑና ከአንድነት ና ከመኢአድ ፓርቲ ለተገነጠሉት ገንጣይ ወንበደዎች አሳልፎ ሰታቸዋል ሙልውን ዘገባ ከታች ያገኙታል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጽህፈት ቤት በአመራር ውዝግብ ውስጥ በነበሩት አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲና በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ዙሪያ ውሳኔ አሳለፈ።

አንድነትን በተመለከተ አቶ ትዕግስቱ አወሎ የፓርቲው ህጋዊ ሊቀመንበር ናቸው ብሏል።

በመኢአድ በኩል ለአቶ አበባው መሃሪ የፓርቲው የህጋዊ ፕሬዚዳንትነት ዕውቅናም ሰጥቷል።

ከመንግስታዊ አሸባሪው ወያኔ መልካም ነገር መጠበቅ ከእባብ እንቁላል ነጭ እርግብ የመጠበቅ ያህል ነው::

ወያኔ እንደ ኢዴፓ አይነቶችን ተለጣፊ ፓርቲዎች መቀፍቀፉን ተያይዞታል::በሰላማዊ ትግል ላይ የተሰማሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ እየደረሰ ያለው መንገላታት እና ወከባ በአሁኑ ወቅት ፓርቲዎቹን እስከማፍረስ እና አባላትን እስከመበተን ጉዞ ተይዟል::ይህ በፓርቲዎች ላይ የሚፈጸመውን መንግስታዊ ሽብርተኝነት እጅግ በከፋ መልኩ ቀጥሎ ይገኛል::

አንድነት ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የደረሰዉን ጉዳት በተመለከተ መግለጫ እየተሰጠ ሲሆን የተጎዱ አመራሮች እና አባላት ዝርዝር መግለጫ እየሰጡ ነው::መድረኩን የተከበሩ አቶ ተመስገን ስምረትይ አቶ ብሩ እና አቶ አስራት አብርሃም ሲመሩት ዝርዝር መግለጫ እየተሰጠ ነው:: የወያኔው ኢቢሲ ጣቢያ ለመግለጫው ሳይጠራ በቦታው ደርሶ እንዳይገባ የተደረገ ስለሆነ በደጅ ቀረጻ እያደረገ ነው::

Wednesday, January 28, 2015

(ሰበር ዜና) አንዳርጋቸው ጽጌ ወደ ቃሊቲ እስር ቤት መዛወራቸው ተሰማ

(ዘ-ሐበሻ) የመን ላይ በሕወሓት አስተዳደር ታግተው ኢትዮጵያ ከገቡ በኋላ እስካሁን የትኛው እስር ቤት ታስረው እንደነበር የማይታወቁት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ቃሊቲ እስር ቤት መዘዋወራቸው ተሰማ::

ምንጮች ለዘ-ሐበሻ እንዳስታወቁት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በቃሊቲ እስር ቤት ቀድሞ ስዬ አብርሃ የታሰሩበት ክፍል ታስረዋል::

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላለፉት 6 ወራት የት እንዳታሰሩ የማይታወቅና የብዙ ሕዝብ ጥያቄ የነበረ ሲሆን ከሳምንታት በፊት ከማይታወቀው እስር ቤት ከባለቤታቸው ጋር ማውራታቸውና ለልጆቻቸውም ያልሆነ ተስፋ እንደማይሰጡ መናገራቸውን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል::

በተለይም ሰሞኑን የ እንግሊዝ ፓርላማ አባላት ወደ አዲስ አበባ በአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ለመነጋገር እንደሚሄዱ ከተነገረ በኋላ አቶ አንዳርጋቸው ወደ ቃሊቲ እስር ቤት መዘዋወራቸው አነጋጋሪ ሆኗል:: አቶ አንዳርጋቸው ለሕዝብ ክፍት ሆነው እንዲጠየቁ የሕወሓት አስተዳደር ይፍቀድ አይፍቀድ የታወቀ ነገር የለም::


ሄሊኮፕተር በመያዝ ወደ ሶስተኛ አገር የጠፉት የአየር ሃይል ባልደረቦች በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገለጹ

ጥር ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ወር ሄሊኮፕተር ይዘው የጠፉት ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ እና ቴክኒሻን ጸጋ ብርሃን ግደይ በተረጋጋ እና በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለኢሳት ገልጸዋል።
ፓይለቶቹ በሚገኙበት ሶስተኛ አገር ውስጥ ሆነው ከኢሳት ጋር ግንኙነት የመሰረቱ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚደረገው የነጻነት ትግል አስተዋጽኦ ለማድረግ መዘጋጃታቸውን ተናግረዋል።
ሶስታችንም በአንድ ላይ የምንመደብበትን ጊዜ ስንጠብቅ ቆይተን ነበር ያሉት ፓይለቶቹ፣ አጋጣሚው ሲፈጠርላቸው ቀደም ብሎ ባወጡት እቅድ መሰረት መጥፋታቸውን ገልጸዋል።
ጉዞአቸውን ወደ ሶስተኛ አገር በሚያደርጉበት ወቅት ከራዳር እይታ ውጭ ለመሆን እስከ 10 ሜትር ድረስ ዝቅ ብለው መብረራቸውን የገለጹት ፓይለቶቹ፣ ካሰቡበት ቦታ ሲደርሱ ነዳጃቸው ማለቁን ተናግረዋል።
ለምን ወጣችሁ ተብለው የተጠየቁት ፓይለቶቹ፣ በአየር ሃይል ውስጥ የሚታየው ዘረኝነት፣ አድልዎና የአስተዳደር መበላሸት ይህን ውሳኔ እንዲወስኑ እንዳስገደዳቸው ገልጸዋል።
እድሉ ቢገኝ አብዛኛው የአየር ሃይል አባል ስርአቱን ትተው ለመውጣት ዝግጁ መሆናቸውን ፓይለቶቹ ገልጸዋል። ፓይለቶቹ ሁኔታዎችን አመቻችተው ለኢሳት ቃለምልልስ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
በሌላ ዜና ደግሞ የኢሳት የጋዜጠኞች ኤርትራ በተገኙበት ወቅት በተለያዩ ወራት ኤርትራ የተገኙነትን በርካታ የአየር ሃይል አባላት አነጋግረዋል።
የሱ 27 እና የሚግ 23 አብራሪዎችን ጨምሮ በርካታ የተዋጊ ሄሊኮፕተር ፓይለቶች ኤርትራ ከሚገኙ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በመቀላለቀል በመታገል ላይ ናቸው። ኢሳት ከፓይለቶች ጋር ያደረገውን ቀለምልልስ በቅርቡ ይለቃል።


ጋዜጠኞችና ጦማርያኑ ለጥር 26 ቀጠሮ ተሰጠባቸው። ∙ፍርድ ቤቱ ተሻሻለ በተባለው ክስ ላይ ብይን ሰጥቷል

ፍርድ ቤቱ ተሻሻለ በተባለው ክስ ላይ ብይን ሰጥቷልበነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተርየዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞች ዛሬ ጥር 20 ቀን 2007 ዓ.ም ለ16ኛ ጊዜ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ቀደም ብሎ ተሻሻለ የተባለውን ክስ አይቶ ብይን ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት ከአራቱ ነጥቦች መካከል አንዱን ብቻ ውድቅ ሲያደርግ ሦስቱን እንደተሻሻሉ ቆጥሮ በክሱ ውስጥ እንደተካተቱ እንዲቀጥሉ በብይኑ አመልክቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ በአቃቤ ህግ የክስ ማሻሻያ ላይ የሰጠውን ብይን በንባብ አሰምቷል፡፡ በዚህ መሰረት የፌደራል አቃቤ ህግ አሻሽየዋለሁ ያለውን ክስ ከአንዱ ነጥብ በስተቀር ቀሪዎቹ ሦስት ነጥቦች ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት አቃቤ ህግ አሻሽሏል በሚል ፍርድ ቤቱ በቀበሉን በብይኑ አመልክቷል፡፡

አንድነት ፓርቲ በድጋሜ የተቃውሞ ሰልፍ ጠራ

ጥር ፲፱(አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ህወሃት /ኢህአዴግ ጥር 17/2007 ዓም በአንድነት አመራሮችና አባላት ላይ ያደረሰውን አሰቃቂ ድብደባ ለማውገዝ እንዲሁም ፓርቲውን ለመቀማት የሚደረገውን ጥረት ለማውገዝ ለጥር 24 በአዲስ አበባና በሌሎች የተለያዩ የክልል ከተሞች ላይ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዱን ገልጸሏል።
አምባገነኑ የህወሀት/ኢህአዴግ መንግስት የዘንድሮውን ሀገራዊ ምርጫ ሂደቱንም ጭምር በማበላሸት ጠንክራ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከምርጫው ውጪ እንዲሆኑ ለማድረግ ላይ ታች እያለ ነው የሚለው አንደነት ፓርቲ፣ በምርጫ ቦርድ፣ በኢቲቪ እና በሬዲዮ ፋና የሶስትዮሽ ግንባር በመክፈት በህዝቡ ዘንድ ብዥታ እንዲፈጠር፣ ምርጫው ያለጠንካራ ተዋዳደሪ እንዲካሄድ በማድረግ የምርጫውን ዋጋ ቢስነት አረጋግጧል ብሎአል።
አንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ሰልፍ ደብዳቤ ማስገባቱን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አስራት አብርሃ ገልጿል። መስተዳድሩ በእለቱ የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መኖሩን ገልጾ ሰልፉን አለመፍቀዱን ቢያስታውቅም፣ አንድነት ፓርቲ የመስተዳድሩን ሃሳብ አለመቀበሉን አቶ አስራት አክለው ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫ ቦርድ የምዝገባ ጣቢያዎች በሰዎች ድርቅ በተመቱበት በዚህ ወቅት ይመዘገባል ብሎ ከሚጠብቀው 35 ሚሊየን መራጭ ውስጥ ባለፉት 14 ቀናት ብቻ ከ28 ሚሊየን በላይ ተመዘገበ ማለቱ አነጋጋሪ ሆኗል።
አንድነትና መኢአድ በምርጫ ቦርድ በተሰራባቸው ሴራ ምክንያት በመጪው ምርጫ የመሳተፋቸው ነገር አጠራጣሪ ሆኖአል፡፡ በመጪው ረቡዕ ወይም ሐሙስ ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎቹን ባስቀመጥኩት ቀነ ገደብ መሰረት ማሟላት የሚገባቸውን ነገሮች አላሟሉም በሚል ከምርጫ ተሳትፎ የሚያግድበትን እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል መረጃዎች ያመለክታሉ።


በኢትዮጵያ መንግስት በጥብቅ የሚፈለጉ 3 አርቲስቶች

ከሮቤል ሔኖክ

እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ ሃሳብን በነፃነት ያለመግለጽ መብት አለመከበሩ ያጠቃው ጋዜጠኞችን ብቻ አይደለም። አርቲስቶችም ጋዜጠኞች ከሚከፍሉት መስዋእትነት ያልተናነሰ ትግል እያደረጉ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳለመታደል ሆኖ የሃሳብን የመግለጽ ነጻነት በመገደቡ ዛሬ እንደ ታላቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙና ተመስገን ደሳለን ያሉ ጋዜጠኞች ያልሆነ ክስ ተልጠፎባቸው በእስር ላይ ይገኛሉ። የእነዚ ታላላቅ ጋዜጠኞች ‘ወንጀል’ መንግስት እንደሚለው ሳይሆን የሕዝብን በደልና ብሶት ማሰማታቸው ብቻ ነው።

ዛሬ ዛሬ ደግሞ ላለፉት 23 ዓመታት ሃሳባቸውን በነጻነት ከሚገልጹት ጋዜጠኞች ባልተናነሰ በመንግስት ጥርስ እየተነከሰባቸው የሚገኙት የጥበብ ባለሙያዎች እየሆኑ ነው።

እንደሚታወቀው በስደት ዓለም ከ150 በላይ ጋዜጠኞች እንዳሉ ሁሉ ዛሬ ቁጥራቸው በዛ ያሉ አርቲስቶችም በስደት ይህንን ስርዓት በመሸሽ በስደት ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ መካከልም የኢትዮጵያ መንግስት እንደታላቁ እስክንድር ነጋ አስሮ ለማሰቃየት ከሚፈልጋቸው ታላላቅ አርቲስቶች መካከል 3ቱ ዋነኞቹ ሲሆኑ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ገና መንግስት እያጎበጎበባቸው በመሆኑ የ3ቱን ገድል አሳይቻችሁ የሁለቱን እንስት አርቲስቶችን ማንነት አስተዋውቃችኋለሁ።

Tuesday, January 27, 2015

የሰላም በሮች ሲዘጉ የሁለገብ ትግል ስልት በሮች ይከፈታሉ!!!

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ አማካይነት እየደረሰበት ያለውን በደል ለሕዝብ ለማሰማት ጥር 17 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ጂንካና ሸዋ ሮቢት የተቃውሞ ሰልፎችን ጠርቶ ነበር። በተለይ በአዲስ አበባው ሰልፍ ላይ የተገኙ ወገኖቻችን ለህወሓት ፍጹም ታማኝ በሆነው የፓሊስ ክፍል ያለርህራሄ መደብደባቸው እና የተቃውሞ ሰልፉም በጉልበት መበተኑ ነፃነትና ፍትህ ናፋቂውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሳዘነ ብቻ ሳይሆነ ያስቆጨ ጉዳይ ነው። በመላው ዓለም በሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች ላይ የተለመደውን ድንጋይ ውርወራ እንኳን ሳይከጅሉ፤ የፓሊሶችን ሰብዓዊ ርህራሄ ለማግኘት “ፓሊስ የኛ ነው” እያሉ እየዘመሩ በፓሊስ ተደበደቡ። ሴቶችና አዛውንት ብቻ ሳይሆን ተላላፊ መንገደኞች እንኳን ከፓሊስ ዱላ አላመለጡም። ከሁሉም በላይ የሚዘገንነው ደግሞ የ 7 ወራት ነብሰ ጡር ሴትም በፓሊስ መመታትዋና ሆዷ መረገጡ ነው። ይህ እኩይ ተግባር የሚፈጥረው ቁጭት በህወሓት ላይ ብቻ አያበቃም። ትዝብቱ ለፓሊስም ተርፏል። ይህ የጭካኔ ተግባር ለፍትህና ለነፃነት በሚደረገው ትግል የሕዝብ አጋር ይሆናል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የፓሊስ ሠራዊትን የሚያዋርድ ነው።

የገነት ዘውዴ “ዶክትሬት”

‎አርአያ_ተስፋማሪያም‬
በህንድ ኒውዴልሂ ከተማ በሚገኘው ጄ.ኤን.ዩ (ጀበሃራል ነኸሩ ዩኒቨርሲቲ) በኢኮኖሚክስ ፒ.ኤች.ዲ ያገኘው አብዲ የወ/ሮ ገነት ዘውዴን የዶክትሬት ጥናት በመስራት እንዲመረቁ ማድረጉን ላረጋግጥ እወዳለሁ። በህንድ የነበርኩና ጉዳዩን በቅርብ ጠንቅቄ አውቃለሁ። አብዲ ከፍተኛ የትምህርት ችሎታ፣ እውቀትና ብቃት ያለው እንደሆነ ገነት ዘውዴ ጭምር ጠንቅቀው በማወቃቸው የእርሳቸውን የመመረቂያ ጥናቶች እንዲሰራ ካግባቡት በኋላ ጉዳዩ በሁለቱ መካከል እንዲቀር፣ ይህ ምስጢር ከወጣ ግን ሌላ ችግር አብዲ ላይ እንደሚከተል በማስጠንቀቅ ጭምር ነግረውታል። ለአብዲ የቤት ኪራይና መሰል ወጪዎች በገነት ዘውዴ ይሸፈኑ ነበረ። በጣም የሚገርመው የመመረቂያ ጥናቱን ለዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰሮች ፕረዘንት ያደረገው አብዲ ነበር። በህንድ እንዲህ አይነት ኮራፕሽን የተለመደ በመሆኑ ብዙም አያስገርምም። በወቅቱ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች « በአብዲ ጭንቅላት ስር ገነት ካባ አጥልቃ ተመረቀች» ሲሉ ከመሳለቃቸው ባሻገር ድርጊቱን ወንጀል ነው ሲሉ ኮንነውታል። በተለይ ወ/ሮ ገነት በህንድ የኢትዮጵያ ኢንባሲ ምክትላቸው ከነበረው የህወሀትና የደህንነት አባል ካህሳይ ገ/መድህን ጋር በመሆን የህንድ ሃብታሞችን ወደ ኢትዮጵያ በመላክና መሬት እንዲቀራመቱ በማድረግ ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን እንዲሁም ለዚህ ውለታቸው አብዲ የሰራውን ጥናት ወ/ሮ ገነት “ዶክተር” ተብለው እንዲመረቁ ተደርጓል። ካህሳይ ገ/መድህን የተባለው የህወሀት አባል እንግሊዘኛ ማንበብና መፃፍ የማይችል ሲሆን ነገር ግን ከዩኒቨርስቲው ዲግሪ እንዲያገኝ ተደርጓል።




Monday, January 26, 2015

ወያኔ ፀገዴ ላይ ያካሄደው ስብሰባ ከሸፈ

የትግራይ ነፃነት ግንባር /ህወኃት/ ገና ከፅንስሱ ሲነሳ ለሙን የሰሜን ወሎን፣ ምዕራባዊ ጎንደርን እና ምዕራባዊ ጎጃምን በማካተት ታላቁን የትግራይ ሪፐብሊክ መመስረት ግብ አድርጎ መመስረቱና ለዚህም አላማው ስኬት የቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ እንድሚገኝ የሚታወቅ ነገር ነው።
በተለይም በወልቃይት፣ ፀገዴና አርማጭሆ ያካሄደው መስፋፍት በአካባቢው ነዋሪ ህዝብ ላይ ትውልድ ይቅር የማይለው ግፍ ፈጽሟል፡ አሁንም የመስፋፋት ህልሙን እውን ለማድረግና ቀሪ የአማራን መሬት ለመቆጣጠር ያለማቁአረጥ ጥረት እያደረገ ነው። ከላይ በተጠቀሱት አካባቢወች የሚኖረውን የአማራን ህዝብ በማንበርከክ እኩይ ፍላጎቱን ለማስፈፀም ቀደም ሲል የጎንደር አስተዳደር ከተሞች በነበሩና አሁን በጉልበት ወደ ትግራይ በተወሰዱ ሁመራ፣ ማይካድራ፣ ማይፀብሬ፡ ዳንሻ፣ ማክሰኞ ገበያ/ ንጉስ ከተማ/ና ዲቪዥን የተባሉ ከተሞችን ማዕከል

ወደ ኤርትራ በማቅናት ላለፉት ሶስት ሳምንታት በኤርትራ ድንበር የሚገኙ የኢትዮጰያ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴ ሲቃኙ የቆዩት የኢሳት ጋዜጠኞች ትናንት እሁድ ተመለሱ።

ጥር ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን እና ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም የኢህዴግን መንግስት በትጥቅ ትግል ለመፋለም ብረት ያነሱ የኢትዮጰያ ተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴ በዓይን ለማየት እንዲሁም ስለ ኢትዮጰያና ኤርትራ የወደፊት ግንኙነት የኤርትራ ባለስልጣናትን ቃለ ምልልስ ለማድረግ ወደ ኤርትራ ያቀኑት ከሶስት ሳምንታት በፊት መሆኑ ይታወቃል።
ፋሲልና መሳይ ባለፉት ሶስት ሳምንታት የኤርትራ ቆይታቸው የሄዱበትን ዓላማ በሚገባ ማሳካታቸውን ጋዜጠኛ ፋሲል ገልጿል። በኤርትራ ቆይታቸው ፌስ ቡክን ጨምሮ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚሰጧቸው አስተያየቶች በሞራልም ሆነ በሀሳብ ሲያበረታቷቸውና ፍቅራቸውን ሲገልጹላቸው ለነበሩ ኢትዮጰያውያን በሙሉ ምስጋናቸውን ገልጿል።


Sunday, January 25, 2015

የስርዓቱን አረመኔያዊ እርምጃ እናወግዛለን! ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አብሮ ስለመስራትና ሌሎቹም ትብብሩን እንዲቀላቀሉ በየጊዜው የሚወተውተው አገራችን በዚህ ዘመን በማይመጥን አምባገነንና የጭካኔ ስርዓት ውስጥ የምትገኝ መሆኑን በመረዳቱ ነው፡፡ ይህ የህወሓት/ኢህአዴግ አምባገነንና ጨካኝ ስርዓት ህዳሩ 27/28 2007 ዓ.ም የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በወጡት አመራሮቻችን፣ አባላቶቻችን፣ ደጋፊዎቻችንና በየጎዳናው የተገኙት ንፁሃን ላይ ከፍተኛ ድብደባና የጅምላ እስር በመፈፀም ስርዓቱን ለመታገል የተነሳነበትን አላማ ትክክለኝነት አረጋግጦልናል፡፡
በዛሬው ዕለትም ገዥው ፓርቲ በፓርቲያቸው የውስጥ ጉዳይ ገብቶ የሚፈፅመውን ደባ፣ ምርጫ ቦርድንና የህዝብ ሚዲያን ተጠቅሞ ፓርቲውን ለመከፋፈልና አሳንሶ ለማሳየት የሚያደርገውን እኩይ ተግባር በመቃወም ሰልፍ የወጡ የአንድነት አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና የፓርቲው ጽ/ቤት ፊት ለፊት የሚገኘው ቤተ ክርስትያን አካባቢ የነበሩ አዛውንት ምዕመናንን ሳይቀር በመደብደብ ጭካኔውን ዳግመኛ አሳይቶናል፡፡ ፖሊስ በትዕዛዝ በአንድነት አባላት ላይ ከፍተኛ የጭካኔ እርምጃ ወስዷል፡፡ አብዛኛዎቹንም በጅምላ አስሯል፡፡
ስርዓቱ በእነዚህ ሰላማዊ ዜጎች ላይ አሁንም የጭካኔ እርምጃውን መድገሙ ስልጣኑን የማጣት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዳለ እና ከይስሙላ ያለፈ ለሰላማዊ ትግሉ ዝግጁ አለመሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ ትብብራችን የስርዓቱን ጨካኝነት እያወቁም ቢሆን በሰላማዊ መንገድ ጥያቄያቸውን ለማቅረብ በስርዓቱ የማይከበረውን ህገ መንግስታዊ መርህ ተከትለው ሰልፍ ለወጡ ቆራጥ የአንድነት አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች አድናቆቱን መግለጽ ይወዳል፡፡ መስዋዕትነታችሁ ለነገ ድላችን ስንቅ በመሆኑ ይበልጡን ተጠናክራችሁ በጋራ ትግላችን እንደምናጠናክርም እምነታችን ነው፡፡
በተቃራኒው ገዥው ፓርቲ ህግ የማክበርና የማስከበር ሚናውን ረስቶ ፖሊስ፣ ደህንነትንና ሌሎች ተቋማትን ለራሱ ስልጣን ማስጠበቂያ በማዋል በአንድነት አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች ላይ የፈፀመውን ለዘመኑ የማይመጥንና በሰላማዊ መንገድ መብታቸውን ለጠየቁት ኢትዮጵያውያንም የማይገባ የጭካኔ እርምጃ በጥብቅ እናወግዛለን፡፡
ኢትዮጵያውያንን የማስተዳደር አቅምና ሞራል ያጣው ገዥው ፓርቲ የዜጎችን ጥያቄ በኃይል ማዳፈን የማይቻል መሆኑንና አገራችን ወደባሰ ችግር እንደሚከታት ተረድቶ ከዚህ የጭካኔ እርምጃው እንዲቆጠብ፣ እርምጃውን የወሰዱትን አካላት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑና የታሰሩትን በአስቸኳይ እንዲፈታ እናሳስባለን፡፡ ፖሊስ፣ ደህንነት፣ መከላከያና ሌሎች ተቋማት ገዥው ፓርቲ አላፊ መሆኑን በመገንዘብና ከገዥው ፓርቲ ታዛዥነት በመውጣት ወገኖቻቸሁ ላይ እንዲህ አይነት የጭካኔና አሳፋሪ እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥባችሁ ከህዝብ ጎን እንድትቆሙ ጥሪያችን እናቀርባለን፡፡
ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!
ጥር 17/2007 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የደደቢት ጉዞ መዘዝ፤ ከሰራዊት ፍቅሬ እስከ ታገል ሰይፉ

ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

በመጀመርያ ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ደጋፊና ተደጋፊ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን በሙሉ ጠሯቸው። ሰበሰቧቸው። እንዲህም አሏቸው። “ወደ ደደቢት አብራችሁን ትሄዳላችሁ፤ እዛ እንደደረሳችሁም አመጣጣችንንና አካሄዳችንን በደንብ አድርጋችሁ ታጤናላችሁ። ከዚያ ስትመለሱ ሁሉንም ነገር ለህዝቡ ትናገራላችሁ።…”      
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የሃገር መሪ ሆነው የሚሰሩት እኝህ ሰው መልዕክታቸውን በዚህ አላበቁም። አይናቸውን ፈጠጥ፤ ጉሮሯቸውንም ጠረግ-ጠረግ አደረጉና ንግግራቸውን ቀጠሉ “ስለረጅሙና መራራው ትግላችን፤ ከጅምራችን እስከ አያያዛችን የታዘባችሁትን ሁሉ ንገሩን። ጥሩውንም ይሁን መጥፎውን ነገር ሳትደብቁ ተናገሩ።…”

ድምጻዊው በዝማሬ፣ ጸሃፊው በድርሰት፣ ተዋንያኑ በተውኔት ስለ ህወሃት የአርባ አመት ጉዞ እንዲመሰክሩ የተሰጠች ትእዛዝ መሆንዋ ነው። አጭር፣ ግልጽ እና ቀጭን መልዕክት ነበረች።

የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ባለቤት ስለሺ ሃጎስ በሕወሓት ፖሊሶች ክፉኛ ተደበደበ

(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ አንድነት በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ያስደነገጠው የሕወሓት መንግስት በዜጎች ላይ አሰቃቂ ድብደባ ሲፈጽም መዋሉን ቀደም ብለን መዘገባችን ይታወሳል:: አሁንም ከሰልፉ በኋላ በአንድነት አመራሮችና አባላት ላይ የመንግስት ተላላኪዎች እጅጅ አሳዛኝ ጭፍጨፋ ማድረጋቸውን የቀጠሉ ሲሆን ከነዚህም መካከል የጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ባለቤት ጋዜጠኛ ስለሺ ሀጎስ እጅግ አሳዛኝና አሰቃቂ ድብደባ ተፈፅሞበታል::
አሁን ባለው ሁኔታ የአንድነት አመራርና አባላት በሰላማዊ ትግሉ እራሳቸውን አሳልፈው እየሰጡ፤ በኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል እንደማያዋጣ እያሳዩን ያለበት ሁኔታ ነው ያለ ሲሆን በዚህም በደማቸው ደማቅ ታሪክ እየጻፉ ይገኛሉ::ይህ በ እንዲህ እንዳለ የሚሊዮኖች ድምጽ እንደዘገበው በአንድነት ሰልፍ የተገኙ ዲፕሎማቶች በሆነው ነገር በጣም አዝነዋል። የተጎዱትን ሁኔታ ለመከታተል ወደ ሆስፒታልም ሄደዋል።የተጎዱ ወገኖቻችን ፣ «ከዚህም የበለጠ ዋጋ ለነጻነታች እንከፍላለን። እነርሱ ያላቸውን የመጨረሻ ዱላ ነው የተጠቀሙት፣ እርሱም ኃይል” ያሉ ተጎጂዎች ይህ የትግል ወኔያቸውን የበለጠ የሚያጠናከር እንጂ የሚቀንሰው እንዳልሆነ እያረጋገጡ ነው። ታጣቂዎቹ በተለይም በአቶ ስለሺ ሐጎስ እና በአቶ አሰራት አብርሃ ላይ፣ ከሌሎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ ድብደባ ፈጽመዉባቸዋል። የሰባት ወር ነፍሰ ጡር ሴት ሆዷ ላይ ተመታለች። የሰባ አመት እናት፣ አባት ሽማግሌ ተደብደበዋል።

Saturday, January 24, 2015

Breaking News: UK diplomats clash over Briton on death row in Ethiopia

UK diplomats clash over Briton on death row in Ethiopia: Officials’ fury after Foreign Secretary claims he couldn’t ‘find time’ to help father-of-three facing executionAndargachew Tsege was snatched by officials at Yemen airport last JuneThe 59-year-old was transferred to Ethiopia where he is thought to remainHe was dubbed ‘Ethiopian Mandela’ after exposing government corruptionLeaked emails revealed British officials’ frustration at political inactionPhilip Hammond said he could not ‘find time’ for phone call on issue

From left Andargachew Tsige’s wife Yemi Hailemariam, Andargachew Tsige and UK Foreign Secretary Philip Hammond.

አንዳርጋቸው ጽጌ ከሆንን እስከ ምን? ከAbraham Z,Taye

የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ የነበረው ጀግናው አቶ አንዳርጋቸው  ጽጌ በፋሺስት ወያኔ እጅ ከወደቀ  ወዲህ “እኔምአንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ” “ሁላችንም አንዳርጋቸው ነን” የሚሉ ተተኪ ሰዎች ተበራክተዋል። አንዳንዶች እንደፌስቡክ ባሉድረገጾች ሳይቀር ስማቸውን አንዳርጋቸው ጽጌ ብለው  ስሙንም ፎቶውንም በመጠቀም አንዳርጋቸው ነን ሲሉይታያሉ።አንዳርጋቸው ጽጌ ነን ስንል ስሙን ይዘን በማህበራዊ ድረገጾች በመጥራት ሲቀጥልም ፎቶውን በትልቅ ፍሬም አስርተንበየአደባባዩ ሰልፍ በመውጣት ባለፈ መሆን እንዳለበን ለማሳሰብ ከወጣትነቱና ከ አረጋዊነቱ ሁለት ጉልህ ክስተቶቹን በመምረጥ እንድንማርበት  ይሄ ጽሁፍ ተዘጋጅቷል።

እንኳን ደህና መጡ ወደ ወያኔ 2007 የምርጫ ጨዋታ!

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ እኔ ዳኛ ነኝ እያለ ቢለፍፍም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የምርጫ ቦርድ የወያኔ/ኢህአዴግ የመሃል ተጫዋች እንደሆነ ይገነዘባል። ይህ የዳኝነት ካባ ለብሶ የወያኔን የአጥቂ መስመር የሚመራ አካል በአሁኑ ሰዓት ዋነኛው ስራው የዳኝነት ካባውን ተጠቅሞ ጨዋታው ሲጀመር ለቡድኑ ወያኔ የሚያሰጉትን ጠንካራ ተቃዋሚዎች እና ፖለቲከኞች ሰበብ አስባብ እየፈለገ (Disqualify) እያለ ምርጫው ውስጥ እንዳይገቡ መከላከል ነው። በመኢሕአድ እና አንድነት ፓርቲ ላይ እያደረገ ያለውን ልብ ይበሉ።

የወያኔው ቋሚ ተሰላፊ ምርጫ ቦርድ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ ምርጫ ውስጥ እንዳይገቡ ቢከለክል ምርጫ ተብዬው ጨዋታ ሊኖር አይችልም፣ ስለዚህ ወያኔን በምርጫው ወቅት የሚያጫውቱት ቡድኖች ስለሚያስፈልጉ አንዳንዶችን ያሳትፋል።

የምርጫው ቦርድ ጨዋታው በሚካሄድበት ወቅት ቡድኑ ወያኔ ሲጠቃ የዳኝነት ካባውን ደርቦ ከች ይልና ባሰማራቸው የምርጫ ድምጽ ቆጣሪዎች እና ታዛቢዎች (ሁሉም የወያኔ ካድሬዎች ናቸው) አማካኝነት ኮሮጆ ዘቅዝቆና ቀመሩን አስተካክሎ ቡድኑ ወያኔ 99.6% ድምጽ በማግኘት እንዳሸነፈ ያውጃል።

‘Ethiopia’s media crackdown is bad news for Africa

Without a free press in Addis Ababa, Africans are being locked out of the important decisions being made in their de facto capital, writesSimon Allison

It’s not easy being a journalist in Ethiopia. In fact, it’s nearly impossible, according to a new 76-page Human Rights Watch report that documents the scale of the state’s censorship apparatus. As a journalist, it makes for highly disturbing reading.

“Ethiopia’s government has systematically assaulted the country’s independent voices, treating the media as a threat rather than a valued source of information and analysis,” says Leslie Lefkow, the organisation’s deputy Africa director.

“Ethiopia’s media should be playing a crucial role in the May elections, but instead many journalists fear that their next article could get them thrown in jail.”

የሕወሓት አስተዳደር 4 የአንድነት አመራሮችን አሰረ * አንድነት ጥር 17 የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ስርዓቱን እንቅልፍ ነስቶታል

(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት አስተዳደር ጉዳይ አስፈጻሚ መስሪያ ቤት እንደሆነ ላለፉት 23 ዓመታት ሲነገርለት የቆየው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አንድነት ፓርቲን ለማፍረስ የሚያደርገው ሴራ ከተጋለጠ በኋላ; አሁን ደግሞ ሌላኛው የሕወሓት አስተዳደር ጉዳይ ፈጻሚ የሆነው ፖሊስ 4 የአንድነት አመራሮችን ማሰሩን ከአዲስ አበባ የመጡ መረጃዎች አመለከቱ::
ከሚሊዮኖች ድምጽ ባገኘነው መረጃ መሰረት የታሰሩት 4 የአንድነት ፓርቲ አመራሮች:
1. አቶ አስራት አብርሃ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ
2. አቶ ሰለሞን ስዩም የፍኒትና ሚሊዮኖች ድምጽ ኤዲቶሪያል ሃላፊ
3. አቶ ስንታዩ ቸኮል የአዲስ አበባ ምክር ቤት የወጣቶች ክፍል ሃላፊ
4. አቶ ንዋይ ገበየሁ የህዝብ ግንኙነት ረዳት ሃላፊ እንዲሁም ሌሎችም ወደ አልታወቀ ቦታ በፖሊስ ተይዘው ተወሰደዋል።

እንደ ሚሊዮኖች ድምጽ ዘገባ ከሆነ ወያኔ/ኢሕአዴግ የኃይል የአዲስ አበባ ሰልፍ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት የኃይል እርምጃ መዉሰድ ጀምሯል። የአንድነት አመራሮች ፖሊስ እየጎተተ በማሳሰር እየሰራ ያለው፣ ከአቶ ትግስቱ አወል ጋር ከምርጫ ቦርድ ጋር አብሮ እየሰራ ያለው የማነ አሰፋ እንደሆነ ታወቋል።

በዚህ ሰዓት ትግሉ ወደ አንድ ምዕራፍ ተሸጋግሯል አስራት፤ ነዋይ ፤ስንታየሁና ሰለሞን ቢታሰሩም እንኳ የሶሻል ሚዲያውን ከሀገር ውጪ ያሉ የአንድነት ምዕራፍ 2 ሶሻል ሚዲያ ቡድን አባላት እየመሩት ነው ምዕራፍ 3 እና 4 ከሰዓታት በኋላ የተጀመረው ትግል ግቡን እስኪመታ እረፍት አይኖራቸውም፡፡

አንድነት ጥር 17 በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የጠራው ተቃውሞ ሰልፍ ስር ዓቱን እንቅልፍ እንደነሳው ለዘ-ሐበሻ የሚደርሱ መረጃዎች ያመለክታሉ::


Friday, January 23, 2015

ሕወሃት በመንግስት ስልጣን ባለቤትነትና በወንበዴነት መሐል ያለው ልዩነት ተምታቶበታል

ኢትዮጵያን በግፍና በዝርፊያ የሚገዛው የህወሀት ጉጅሌ በመንግስትነትና በወንበዴነት መሀል ያለውን ልዩነት ከ፪፫ ዓመት ስልጣን ዘመን ብኋላ እንኳን ሊገለጥለት አልቻለም። ወይም እንዳመችነቱ ሁለቱን እያምታታ መቀጠሉን እንደብልህነት ቆጥሮታል። መንግስት መሆንንና ባለህገመንግስት መባልን ከመቆነጃጃ ኩልነት ባልተናነሰ በለጋሾቻቸው ባዕዳን ፊት ይጠቀሙበታል እንጂ ለኛ ለዜጎቹማ ወንበዴነታቸውን ሊደብቁን እንኳን አይጨነቁም።

በቅርቡ ህወሀት የትግራይ ሪፐብሊክ ለማቋቋም የክህደት ተግባሩን የጀመረበትን ፵ኛ ዓመት በዓሉን ትግራይ ውስጥ በማክበር ላይ ሳለ የቀድሞው የህወሀት ታጋይ ያሁኑ የሀገሪቱ ጦር ሎች ኤታማዦር ሹም ተብዬው ሳሞራ የኑስ የህወሀት መንግስት ያገራችን ገበሬ ወፎችን ከማሽላው ለመከላከል እንደሚጠቀምበት መስፈራሪቾ የሚጠቀምበት ሕገ መንግስት ላይ የተጠቀሰውን የሀገሪቱን ሰራዊት የፖለቲካ ገለልተኝነት ድንጋጌና ሰራዊቱ “ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ ይሆናል” የሚለውን የይስሙላ ህግ ባደባባይ አውልቆ ጥሎ ተቃዋሚዎችን የሚወነጅል ሰፊ ንግግር ሲያደርግ ተደምጧል። ሳሞራ ይህን ንግግር በሚደረግበት ቦታ አፋቸውን ከፍተው ከሚያደምጡት ውስጥ የሀገሪቱን መንግስት እንዳሻቸው የሚዘውሩት የወያኔ ሹማምንት ነበሩ። በዚህ ንግግር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የባዕዳን መሳሪያ ሆነው የሀገሪቱን ሉዓላዊነት እንደሚፈታተኑ ሀይሎች በመቁጠር ፍጹም ሀሰትና ጅምላ ፍረጃ ሲያደርግ

መጪው ምርጫ በአድማ ብተና ስም እየተሰጠ ያለውን ስልጠና የተቃወሙ 97 የፌዴራል ፖሊስ አባላት እርምጃ ሲወሰድባቸው፤ 119 ፖሊሶች በግዳጅ እረፍት እንዲወጡ ተደረገ። ደረጀ ነጋሽ

ጥር ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራል ፖሊስ ዋና ዳይሬክተር የተባረሩት አብዮታዊ ዲሞክራሲን መቀበል ያልቻሉ ናቸው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት በመላ ሀገሪቱ ፖሊሶችና ሚሊሻዎች ከምርጫው ጋር በተያያዘ ሊነሱ ይችላሉ የተባሉ ህዝባዊ አመጾችን ለማክሸፍ ያስችላል የተባለ የተኩስ ልምምድ እያደረጉ እንደሚገኙ ከየክልሎቹ የመጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በፌድራል ፖሊስ አድማ ብተና አደረጃጀት በየክልሉ የሚካሄደውን ይህን ስልጠና፦ << የፖሊስን ተልእኮና ዓላማ የሳተ ነው>> በማለት በርካታ የፌዴራል ፖሊስ አባላት እንደተቃወሙት በፌዴራል ፖሊስ ውስጥ ያሉ የኢሳት ምንጮች ጠቁመዋል። ተቃውሞ ካነሱት መካከል 206 የፌዴራል ፖሊስ አባላት ተገምግምው ከስልጠናው እንዲወገዱ መደረጋቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል። ከነዚህ መካከል በ97ቱ ላይ እርምጃ ሲወሰድ፤119ኙ እስከ ምርጫው መጠናቀቅ ድረስ የግዳጅ እረፍት እንዲወጡ ተደርጓል።
የፌዴራል ፖሊስ ዋና ዳይሬክተር ጄነራል አቶ አሰፋ በዩ እርምጃ የተወሰደባቸውንና የግዳጅ እረፍት እንዲወጡ የተደረጉትን የፌዴራል ፖሊስ አባላት አስመልክተው ለኢህአዴግ የምርጫ ጊዚያዊ ኮሚቴ በላኩት ደብዳቤ ፦<<አብዮታዊ ዲሞክራሲን መቀበል ያልቻሉ ናቸው>> ማለታቸውም ተመልክቷል። በመሆኑም በምርጫው ዸህንነት ጥበቃ ላይ እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ዳይሬክተሩ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል።
ምንጮቻችን እንደሚሉት ግን <<አብዮታዊ ዲሞክራሲን መቀበል ያልቻሉ>> በሚል ምክንያት ከስራቸው እንዲታገዱም ሆነ በግዳጅ እረፍት እንዲወጡ የተደረጉት በብሄራቸው እየተመረጡ <<ለስርዓቱ ታማኝ አይደሉም፣ ግርግር ከተነሳ ሊከዱን ይችላሉ>>ተብለው የተጠረጠሩ ፖሊሶች ናቸው። ይህ በእንዲ እንዳለ በአማራ ክልል በከፍተኛ የስራ እርከን ላይ የሚገኙ የስራ ሂደት ሃላፊዎችና ካድሬዎች ትናንት ሀሙስ እና እና ዛሬ በምርጫው ዙሪያ ስብሰባ ማድረጋቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና ያመለክታል።


ኢትዮጵያ የማን ነች? አርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ

“ኢትዮጵያ የማን አገር ነች” የሚል ጥያቄ ከዚህም ከዚያም እየተሰማ ነው። ህወሃቶች ከፈጠሯቸው ቀውሶች መካከል አንዱ ይሄው ነው። ዜጎች የአገር አልባነት ስሜት ውስጥ ገብተው የገዛ አገራቸውን “የማን ነች” ብለው እንዲጠይቁ መገደዳቸው።

ለኢትዮጵያዊያኑ ኢትዮጵያ አገራቸው እየሆነችላቸው አይደለም። ኢትዮጵያዊ መሆን ወንጀል እስኪመስል ድረስ በዜጎች ላይ ግፍ እየተፈፀመ ነው። የሚፈፀመው የግፍ ዓይነት ወሰን የለውም። ግማሹ በጠራራ ፀሃይ ደሙ እንዲፈስ ይደረጋል። ሌላው ለቁም ስቃይ ወደ ወይኒ ይጋዛል። ቀሪውም እትብቱ የተቀበረበትን አገር ትቶ ለመሰደድ ይገደዳል። በአገሪቷ ውስጥ የሚፈፀመውን ወሰን አልባ በደል የተመለከቱ ኢትዮጵያን ከውዳቂ መንግስታት ተራ መድበዋታል። በኢትዮጵያችን የዜጎችን መብት አስከብሮ ለመምራት ብቃት ያለው መንግስት ባለመኖሩ እጣ ፈንታችን እንዲህ ከውዳቂ አገራት ተርታ መግባት ሁኗል።

ኢትዮጵያን ለመምራት ብቃት ያለው መንግስት ቢኖር ኑሮ ለረዥም ዘመን በሰላም ተጎራብተው ይኖሩ በነበሩ ህዝቦች መካከል ግጭት ተፈጠረ መባልን ባልሰማን ነበር።ህወሃት አገሪቷን ከተቆጣጠረ ዘመን ጀምሮ ሆን ተብሎ በሚፈጠር ግጭት ብዙ ደም ፈሷል። አማራው ከኦሮሞው፤ ትግሬው ከአማራው እና ከአፋሩ፤ ሶማሌው ከኦሮሞ፤ኦሮሞው ከጉጂው፤ ኑዌር ከአኙዋክ፤ ዲዚ ከሱርማ፤ ሌሎችም ብዙ ግጭቶች በየቀየው ተፈጥረው አይተናል። የብዙ ዜጎችም ህይወት ተቀጥፏል። ይሄ ሁሉ ደም መፋሰስ የሚከሰተው ህወሃት ከህዝብ ፈቃድ ያልሆነ እና ከህዝቡ የተለየ በመሆኑ ነው።

“ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም” የነፃነቱ ታጋይ አንዳርጋቸው ፅጌ


ከልጅ አያሌው

ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ትግል እስከወዲያኛው ከዳር ለማድረስ ቆርጦ ልጆቼን ቤተሰቦቼን ሳይል ከራሱ በላይ በሀገሩ ፍቅር ተበልጦ የተሻለ ነው የሚለውን፣ አማራጭ የሌለውን፣ የኤርትራን ጫካ መርጦ የማይቻል የሚመስለውን ችሎ ብዙዎች ፈቀቅ ማድረግ ያቃታቸውን የመተባበር የመያያዝ በአንድ ገብቶ ለአንድ አላማ የመታገልና ኢትዮጵያን እንደቀደመው ታላቅ ሀገር የማድረግ ውጥን የተሻለና የሚያግባባ ሀሳብ በመሸከፍ ከሚመራው ንቅናቄ ከግንቦት 7 ጋር እጅግ እውነት የማይመስሉ ድንቅ ስራዋችን በመስራት ጠማማውን በማቅናት ኮረብታውን በመደልደል አንድ መሆን ሳይችሉ ለአመታት ሲኳትኑ የነበሩትን በኢትዮጵያዊነት እንዲተሳሰሩ በማድረግ ፍቅር የሰራ ትልቁን መሰረት የጣለ ምርጥ የኢትዮጵ የቁርጥ ልጅ አንዳርጋቸው ፅጌ።

ዛሬ እሱ በማረፍያው ሰዓት አግባብ ባልሆነ መንገድ ከአውሬዋች እጅ ወድቆ ይህን መልዕክት አስተላልፏል። ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም።

“ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም”

የሰብዓዊ መብት ተመልካች የሆነው ድርጅት (ሂዩማን ራይትስ ዎች) “ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” በሚል ርዕስ ያወጣል ተብሎ የተጠበቀውን ዘገባ ማምሻው ላይ ይፋ አድርጓል፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “ያለ ነጻ ሚዲያ – ምርጫ ወይስ ቁማር?” በሚል ርዕስ ባተመው ዜና ላይ ዘገባው እንደሚወጣ በተናገረው መሠረት ባለ 76 ገጽ ሪፖርቱ በሚዲያ አፈና ዙሪያ ዝርዝርና ወቅታዊ መረጃዎችን አውጥቷል፡፡ኢህአዴግ በሚያደርስባቸው ስልታዊ አፈና፣ ማስፈራሪያ፣ ህይወት የማጥፋት ዛቻ፣ … ምክንያት በአሁኑ ጊዜ በትንሹ 22 የሚሆኑ ጋዜጠኞች በእስር ላይ እንደሚገኙ፤ ከ30 በላይ የሚሆኑ ደግሞ አገር ጥለው መኮብለላቸውን በዘገባው ተጠቁሟል፡፡ እንዲህ ያለው ገለልተኛ ሚዲያን የሚያፍን እና ከሜዳው የሚያስወጣ አሠራር ከወራት በኋላ ይካሄዳል ከሚባለው “ምርጫ” አኳያ የውድድሩን ሜዳ ከማጥበብ አልፎ እንዳይኖር እንደሚያደርገው የዘገባው ሃተታ ያስረዳል፡፡ድርጅቱ ካወጣው ዘገባ ጋር በተሰራጨው የዜና መግለጫ ላይ የድርጅቱ የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር የሆኑት ሌስሊ ለፍኮው ሲናገሩ “በመጪው ግንቦት በሚካሄደው ምርጫ የኢትዮጵያ ሚዲያ ወሳኝ ሚና መጫወት ይችል ነበር፤ ሆኖም ግን ብዙዎቹ ጋዜጠኞች ሊያወጡ የሚፈልጉት ጦማር ወደ እስርቤት እንደሚያስወረውራቸው ስለሚፈሩ” ሙያዊ ተግባራቸው ከመወጣት እንደሚቆጠቡ ተናግረዋል፡፡ዘገባው ከ70 የሚበልጡ አገር ውስጥና በስደት ከሚገኙ ጋዜጠኞች ጋር ቀጥተኛ ቃለምልልስ በማድረግ የወጣ የአንድ ወገን ሰነድ ሳይሆን ለኢህአዴግ ባለሥልጣናትም ጥያቄዎችን በማቅረብ የሰጡትን ምላሽ ለማመጣጠኛ አቅርቧል፡፡ በመጨረሻም ይበጃሉ ያላቸውን የምክር ሃሳቦች ጠቁሟል፡፡

4 መኮንኖች ታሰሩ * የመከላከያ ሰራዊቱ ጥያቄ ወደ አመጽ ሊሸጋገር ተቃርቧል

የደቡብ ምስራቅ እዝ የመከላከያ ሰራዊት ካልደፈረሰ አይጠራም እያለ ነው

ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው:-

ጨፍጫፊው ሌ/ጄነራል አብረሃ ወልደ ማርያም (ኩዋተር) የሚመራው ለሶማሌ ክልል ሰላም በሚል በአከባቢው የሰፈረው የደቡብ ምስራቅ እዝ የሕወሃት የጦር አዛዦች በራሳቸው የሚወሥዱት ውሳኔ የመከላከያ ሰራዊት ላይ የሚያደርሱት ጫና እና እንዲሁም ሰራዊቱ ያቀረበውን ሕገ መንግስታዊ ጥያቄ ወደ አመጽ ማምራቱ ተሰምቷል::በጎዴ ከሚገኙ የመከላከያ ደህንነት ምንጮች የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ካልደፈረሰ አይጠራም በሚል የተነሳውን አመጽ የተመለከቱ የሕወሓት የጦር አዛዦች የመከላከያ ሰራዊት ጥያቄ እና አመጻ ተከትሎ አነሳስተዋል የተባሉ አራት ወታደራዊ መኮንኖች መታሰራቸው ታውቋል::

ገጣሚ ታገል ሰይፉ ወደ ደደቢት ያልሄደው አላማውን በመቃወም እንደነበር ገለጸ (ከአስገራሚ ትንታኔ ጋር)

(ኢ.ኤም.ኤፍ) በቅርቡ የህወሃት 40ኛ አመት ሲከበር፤ በርካታ የኪነ ጥበብ ሰዎች የተደረገላቸውን ግብዣ ተቀብለው ወደ ትግራይ ማምራታቸው ይታወሳል። ሁሉም አርቲስት ግን… ፖለቲካዊ ይዘት ያለውን ጉዞ አልተቀበለም። ሁሉም የየራሳቸው ምክንያት ሊኖራቸው ይችላል። ህዝቡ ወደ ደደቢት የሄዱትን ያወገዘውን ያህል ጥሪውን ሳይቀበሉ የቀሩትንም ማመስገን ይገባው ነበር። ወደ ደደቢት ካልሄዱት መካከል፤ እነአብርሃም ወልዴ፣ እነጆሲ፣ ላፎንቴን፣ ደረጄ ኃይሌ፣ ሰይፉ ፋንታሁን እና ሌሎችም ሊመሰገኑ ይገባል። ሁሉም በየራሳቸው መንገድ የራሳቸው ምክንያት ቢኖራቸውም፤ ለመጀመሪያ ግዜ ምክንያቱን በአደባባይ ለመግለጽ የበቃው ገጣሚ ታገል ሰይፉ ግን፤ “ጥሪ ቢደረግልኝም ስላላመንኩበት ቀርቻለሁ።” ብሏል።

የዚህ ሁሉ መነሻ፤ የኢዮፒካ ሊንክ ሬድዮ ጋዜጠኞች ያቀረቡት ቀለል ያለ የሚመስል ጥያቄ ነበር። እንዲህ ብለው ጠየቁት። “ሰዎች ስላንተ እንዲያውቁ የምትፈልገው ነገር ምንድነው?” አሉት። ገጣሚ ታገልም ሲመልስ፤“ከተፈቀደልኝ ሰዎች እንዲያውቁት የምፈልገው…” ብሎ ጀመረ።

Thursday, January 22, 2015

ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ልደቷ ሲከበር ከቃሊቲ እስር ቤት ያስተላለፈችው መልዕክት

በቅድሚያ የልደት በዓሌን ለማክበር እዚህ የተሰባሰባችሁትንና እዚህ ባትገኙም አላማዬን በመደገፍ ፍቅርና

ከብር የተሰጣችሁኝን ወገኖች ሁሉ ላመሰግን እወዳለሁ፡፡

በመቀጠል እኛም ራሳችን ሆንን ሌሎች ኢትዮጵያዉያን እንደሰዉ መኖር የሚችሉባትን ሀገር ለመፍጠር በየሙያ

ዘርፎቻችሁ፣ በፓርቲ ተደራጅታችሁም ሆነ በሌላ በማንኛዉም መንገድ እየታገላችሁ ላላችሁ በሀገር ዉስጥና

በዉጭ የምትኖሩ የማከብራችሁ ወገኖች በሙሉ ሶስት ዋና ነጥቦችን የያዘ አጭር መልዕክት ላስተላልፍላችሁ

ፈልጋለሁ፡፡

በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደር በተቃዎሟቸው ኢትዮጰያውያን ላይ የመሰረቱትን ክስ የስዊድን ፖሊስ ውድቅ አደረገው።

ጥር ፲፬(አስራ አራት ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቀደም ሲል የኢህአዴግ መንግስት ፤ በስዊድን-ስቶኮሆልም አዘጋጅቶት የነበረው የቦንድ ሽያጭ ዝግጅት ላይ ኢትዮጰያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ ማሰማታቸው ይታወቃል።
<<ከአባይ በፊት ዘረኝነት ይገደብ>> በሚል መርህ ተቃውሞውን ያደረጉት ኢትዮጰያውያን፤ ዜጎች ያለፍርድ እየታሰሩና እየተገደሉ ባለበት ሁኔታ ገንዘብ ለመሰብሰብ መሯሯጥ፤ በሀገርና በህዝብ ላይ መቀለድ እንደሆነ በመናገር ነበር- ተቃውሟቸውን ጫማና እንቁላል በመወርወር የገለጹት።
ኢትዮጰያውያኑ -አምባሳደሯን መኪና ላይ የ እንቁላል መዓት በመወርወር ተቃውሟቸውን ሲገልጹ፤አምባሳደር ወይንሽት ከመኪናቸው መውጣት ተስኗቸው ተስተውለዋል። በኦትዮጰያውያኑ ጫማና እንቁላል የተወረወረባቸው በስዊድን የኢትዮጰያ አምባሳደር ወይንሸት ታደሰ፤ <<ስራዬን መስራት እስከማልችል ድረስ በደል ደርሶብኛል>> በማለት ለስዊድን ፖሊስ ክስ ይመሰርታሉ።
የአምባሰደሯን ክስ ተከትሎ የስዊድን ፖሊስ ባቀረበላቸው ጥሪ መሰረት ቃል ለመስጠት የሄዱት የኢትዮ-ስዊድን ግብረ-ሀይል አስተባባሪ አክቲቪስት መቅደስ ወርቁ እና የኢትዮጰያ ዲሞክራቲክ መድረክ ምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ሞላ፤ ኢትዮጰያ ውስጥ ስላለው የመብት ረገጣና በስፋት ለስዊድን ፖሊስ በማብራራት፤ ተቃውሞው የተደረገው የሰብዓዊ መብት ጥሰትን፣ዘረኝነትን እና ሙስናን ለመቃወም እንደሆነ አስረድተዋል።
ጉዳዩን የተመለከተው የስዊድን ፖሊስም በስዊድን ህግ መሰረት የዚህ ዓይነት ተቃውሞ ማድረግ መብት እንጂ ወንጀል እንዳልሆነ በመጥቀስ እና ክሱ ውደ ፍርድ ቤት የሚያመራበት አንዳችም የህግ ምክንያት እንደሌለ በማብራራት የአምባሰደሯን ክስ ውድቅ እንዳደረገው አክቲቪስት መቅደስ ተናግረዋል። የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን ከወራት በፊት በዋሽንግተን ዲሲ የልብስ መደብር ውስጥተቃውሞ ባቀረቡባቸው አክቲቪስቶች ላይ የመሰረቱት ክስ ሰሞኑን በአሜሪካ ፍርድ ቤት ውድቅ መደረጉ ይታወቃል።


የኢህአዴግ ሴራ ከሸፈ::የኢህአዴግና የምርጫ ቦርድ ድራማ ተዋናይ እያጣ ነው::እናት ፓርቲያቸውን ይቅርታ በመጠየቅ ተመልሰዋል፡፡

የኢህአዴግ ሴራ ከሸፈ::
አቶ አየለ ስሜና አቶ ኢሳይያስ ቱሉ እናት ፓርቲያቸውን ይቅርታ በመጠየቅ ተመልሰዋል፡፡

የኢህአዴግና የምርጫ ቦርድ ድራማ ተዋናይ እያጣ ነው::ምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ጻፍኩለት ያለውን አየለ ስሜን አጥቷል :: ምርጫ ቦርድ ለአቶ አየለ ስሜ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራ ደብዳቤ መስጠቱን የምርጫ ቦርድ ምክትል ሀላፊ አቶ አዲሱ ገ/እግዚአብሄር ከዚህ ቀደም መናገራቸው አይዘነጋም፡፡ዛሬ በምርጫ ቦርድ ደብዳቤ ተሰጥቷቸው የነበሩት አቶ አየለ ስሜና አቶ ኢሳይያስ ቱሉ እናት ፓርቲያቸውን ይቅርታ በመጠየቅ ተመልሰዋል፡፡ከእነ አቶ አየለ ቀደም ብለው የተወሰኑ ወጣቶች ከፓርቲው ውጪ ይሰበስቧቸው የነበሩ ሰዎችን የጥፋት ተልዕኮ በመረዳት መመለሳቸው አይዘነጋም፡፡
በእኔ እምነት ከዚህ ቀደም በፓርቲው ውስጥ በተደረገ ምርጫ ለራሳቸው የሰጡትን ድምጽ ብቻ ያገኙት አቶ ትዕግስቱ አወሉ ብቻቸውን ከመቅረታቸው በፊት እነ አየለ ስሜን በመከተል ይቅርታ እንደሚጠይቁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

Wednesday, January 21, 2015

ሥርዓቱ የምርጫ ካርድ ያልወሰዱትን ስኳር በመከልከል ማስፈራራት ጀምሯል

(ነገረ ኢትዮጵያ) በምስራቅ ጎጃም ዞን አነደድ ወረዳ የቦቀል ቀበሌ ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ ስልልወሰዳችሁ ስኳር አይሰጣችሁም መባላቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ በአካባቢው ስኳርን ጨምሮ ሌሎች አቅርቦቶች በስፋት እንደሚጠፉ የተናገሩት ነዋሪዎቹ ዛሬ ጠዋት የቀበሌ ካድሬዎች በድምጽ ማጉያ ‹‹ዛሬ ስኳር ስለመጣ ቀበሌ ድረስ መጥታችሁ እንድትወስዱ፡፡ የመጣው ስኳር ውስን በመሆኑ ሊያልቅ ስለሚችል ዛሬውኑ መጥታችሁ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡ ከዛሬ ውጭ ላታገኙ ትችላላችሁ፡፡›› እያሉ ሲለፉ እንዳረፈዱ ተናግረዋል፡፡

ሆኖም መጥቷል የተባለው ስኳር ለማግኘት ወደ ቀበሌው ያመሩት ነዋሪዎቹ ስኳሩን ለመውሰድ ሲጠይቁ ‹‹የምርጫ ካርድ ወስዳችኋል?›› የሚል ጥያቄ እንደሚቀርብላቸው ግልጸዋል፡፡ የምርጫ ካርድ የሚያሳዩ ነዋሪዎች ስኳሩ ሲሰጣቸው፤ ያላወጡት በአስቸኳይ ምርጫ ካርድ አውጥተው እንዲመለሱና ስኳር እንዲወስዱ ተነግሯቸዋል ተብሏል፡፡ በአንጻሩ ስኳር ለመውሰድ የምርጫ ካርድ ማውጣት የለብንም ያሉት ነዋሪዎች ስኳር እንደማያገኙ የተነገራቸው ሲሆን ‹‹እንደዜና የምርጫ ካርድ ወሰድንም አልወሰድንም ስኳር የማግኘት መብት አለን›› ያሉ ዜጎች በፖሊስ ተደብድበው እንደተባረሩ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

Who are Members of the Election Board that Perform the ruling party TPLF’s Dirty Job in Ethiopia?

By Muse Abebe

After virtual disappearance since the end of the ‘historic election’ of 2010 in which TPLF won 99.6 % of parliamentary seats, the National Election Board has once again resurfaced in the last few weeks in a bid to carry out the dirty job assigned to it by the TPLF for the upcoming general election. This time the Board resumed its client role by accusing Andinet and AEUP parties for violation of party rules in relation to the election of party leaders. It is an irony that the Board is attempting to enforce rule of law while it is an organ that willfully permitted the daylight robbery of the votes of millions of voters by TPLF in the last four general elections.

The role of the Election Board that aimed at rectifying violations of procedural rules within the opposition parties structures has been assigned to it by TPLF security apparatus for achieving two objectives. Primarily, the TPLF security apparatus instructed the Election Board to magnify the internal problems within the opposition parties so that the public may perceive them as weak and dysfunctional. The consideration of TPLF for such propaganda is that after the people watched all the divisions and disagreements in the opposition camp on government and party controlled media, the public will resort to support TPLF led regime. The other related motive of TPLF for instructing the Election Board to ‘advise’ opposition parties to resolve their internal problems is to appear to the public that TPLF is committed to multi-party democracy while the opposition parties are not ready to be competitors of TPLF. There are also clear indications that TPLF is financing and facilitating the dissenting groups from Andinet and AEUP conduct general meetings and get access to the media.

በባህር ዳር ሲካሄድ የነበረው የመምህራን ስልጠና ያለስምምነት ተጠናቀቀ፤ መንግስት ስልጣኑን እንዲያስረክብ ተጠየቀ።

ኢሳት ዜና ፦ በባህር ዳር ከተማ ለከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች መምህራን ሲካሄድ የቆየው ስብሰባ የታሰበለትን ዓላማ ሳያሳካ መጠናቀቁን በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ያጠናቀረው መረጃ ያመለክታል። መንግስት ሰሞኑን ትምህርት ቤቶችን ለአንድ ሳምንት በመዝጋት ለግልና ለመንግስት መምህራን ሲሰጠው የቆየው ስልጠና በሚጠናቀቅበት ጊዜ መምህራን በተሰጡት በሁሉም ርዕሶች ላይ ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ስልጠናው መጠናቀቁን በስብሰባው የተሳተፉ መምህራን ለዘጋቢያችን ገልጸዋል። በክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት በተዘጋጁት ሰነዶች ላይ የተወያዩት የኢኮኖሚክስ ምሁራን ፦ «ኢትዮጵያ ባለፉት 12 ዓመታት ባለ ሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ እድገት በማሳየት ካደጉ ሃገሮች ተርታ ተሰለፋለች።» በሚል ርእስ ያቀረቡትን ሰነድ አልተቀበሉትም። ኢትዮጵያ አሳየች የሚባለው እድገት ትክክለኛው እድገት ሳይሆን የመንግስት የቁጥር ጨዋታ መሆኑን ኢኮኖሚስቶቹ በምሁራዊ ትንተና አስደግፈው ለተሰብሳቢ መምህራን ሙያዊ ማብራሪያ መስጠታቸውን እና በድፍረት መናገራቸውን ፤ በስብሰባው የተሳተፉ መምህራን ለዘጋቢያችን ገልጸዋል።

ወያኔ አንድነትን ለማፍረስ ያቀደው ሴራ በሃብታሙ አያሌው አንደበት ከወህኔ ቤት

በአንድነት ፓርቲ ውስጥ የተከሰተውን ሰርጎ የመግባት ሙከራ እና በገዢው ፓርቲ የተደረገውን የተለጣ…ፊ ፓርቲ ምስረታ እጅግ የምቃወመው ሲሆን የአንድነት አመራሮች በጠቅላላ ጉባዬው የተመረጡ እና በአቶ በላይ ፍቃዱ የሚመራው ካቢኔ እንጂ ጥቂት ግለሰቦች በገዢው ፓርቲ ድጋፍ ተሰባስበው አንድነትን የፈጠሩ ተለጣፊ አይደሉም::እኔ ውስከማውቀው ድረስ የአቶ በላይ ፍቃዱ ካቢኔ ሕጋዊ እና በጠቅላላ ጉባዬ የተመረጠ አመራር ነው:: የአንድነትን አመራሮች የምነግራቹ መልእክት ቢኖር አንድነትን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱት ጋር ምንም አይነት ዝቅ ብላቹ ከነሱ ጋር በሚዲያም ሆነ በምንም ቃለ ምልልስ አታርጉ፡፡ እኔም ሆነ ቤስር ላይ የምንገኝ የአንድነት አባላት የአቶ በላይ አመራሮች የምንቀበል እና በኛ ስም ተለጣፊዎቹ እንዳይነግዱ ለማሳሰብ እወዳለሁ:: አሁን አንድነትን ለማፍረስ የሚንቀሳቀሱ የኢህኣዲግ ተላላኪዎች እንደሆኑ እና እኛ ለመታሰራችን ተጠያቂ እንደሆኑ አውቆ የአንድነት አባልም ሆነ ደጋፊ በጥንቃቄ እንዲከታተላቸው ለመናገር እወዳለሁ፡፡ ሃብታሙ አያሌው ከቂሊንጦ ወህኒ ቤት::

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ነፃነትን የማስመለስ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹በነፃነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› ዘመቻው ነፃነትን የማስመለስ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ፡፡ ትብብሩ ዛሬ ጥር 12/2007 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ኢህአዴግና ምርጫ ቦርድ አፈና እና ጫና እያደረጉ ቢሆኑም ነፃነትን ለማስመለስ የያዘውን ግብ ለማሳካት ወደኋላ እንደማይል ገልፀዋል፡፡ ‹‹የኢህአዴግ ጨካኝነትና የምርጫ ቦርድ አጋፋሪነት ሊቀጥል ይችላል›› ያሉት የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ሆኖም የትግሉ አላማ ኢህአዴግን ማጋለጥ በመሆኑ የሚያስፈልገውን መስዋዕትነት እየከፈሉ ትግሉን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ ‹‹ህዝቡ ካርድ እንዲያወጣ ጥሪ ስናደርግ የፖለቲካ ምህዳሩ ተስተካክሏል እያልን አይደለም፡፡ እኛ አሁንም እያነሳን ያለነው የትግል ጥያቄ ነው›› ያሉት የትብብሩ ም/ል ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርዴሎ የትብብሩ የትግል አላማ ይህን የተዘጋ ምህዳር ማስከፈት መሆኑን አብራርተዋል፡፡ትብብሩ ‹‹የትግሉ ቀዳሚና ዋነኛ ባለቤት የሆንከው መራጩ ህዝብ ነጻነትና ክብርህን ለማስመለስ በምናደርገው ትግል በንቃት እንድታሳተፍ፣ ዛሬውኑ

ወያኔ የሚመለመል ወታደር አጣ!

ዳግማዊ አቤ ጉበኛ
ወያኔን የሚከዱ ወታደሮች በየቦታው እየተሰማ ባለበት ባሁኑ ሰዓት የሚመለመል ወታደር መጥፍቱ ምናልባትም ወያኔዎቹ ከፍተኛ የራስ ምታት ሳይሆንባቸው አይቀርም፡፡ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል በተደጋጋሚ የአዲስ ቅጥረኛ ወታደር ማስታወቂያ ቢያወጡም፣ አይደለም የሚመለመል ወታደር ቀርቶ የሚመዘገብ ጠፋ፡፡

እናም ይህንን ችግር ለመፍታት ወያኔ አዲስ ዘዴ ቀየሰ፡፡ ከከተማ እስከ ገጠር ቀበሌ፣ በብረታብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ስም አማላይ ማስታወቂያዎችን አስለጠፈ፡፡ ይህ በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የወጣው ማስታወቂያ የሚመለምለው በሚከተሉት የሙያ ዘርፎች እንደሆነ ይዘረዝራል፡፡
1. ጄኔራል መካኒክ
2. ኤሌክትሪክሲቲ/ ኢንዱስትሪያል ኤሌክትሪክ ሲቲ/
3. ኤሌክትሮኒክ /ማካትሮኒክ/
4. ማሽን ቴክኖሎኪ
5. አውቶ መካኒክ
6. አውቶ ኤሌክትሪክ

የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ከነሰማያዊ ቲሸርታቸው ጥምቀትን ሲያከበሩ ዋሉ

ጥር ፲፩(አስራ አንድ ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-በጎንደር ዙሪያ ወረዳ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) አስተባባሪ  የሆነው ወጣት ዘመነ ምረተአብ ትናንት ጥር 10 ቀን  11:00  አካባቢ  በማክሰኝት ከከተራ በዓል ላይ ባልታወቁ ሰዎች ተወስዷል። አፋኞቹ ዘመነ ምረተአብን ወዴት እንደወሰዱትና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ እስካሁን አልታወቀም።

ቀደም ሲል የታሰሩት  የመኢአድ የቀድሞ  ዋና ጸሃፊ አቶ ተስፋየ ታሪኩ፣ የድርጅቱ የደቡብ ጎንደር ዋና ጸሃፊ የሆነው አቶ ጥላሁን አድማሴ እና   የምራብ ጎጃም ዋና አደራጅ የሆነው መቶ አለቃ ጌታቸው  በማእከላዊ ወንጀል ምርመራ እየተገረፉና  እየተሰቃዩ እንደሚገኙ  ተመልክቷል።

Tuesday, January 20, 2015

”የቃሊቲ ማጎሪያ ውስጥ የታሰሩ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ንጹሃን ዜጎች፣ ስቃይ አሁንም ከፊቴ አለ፤ የሚሞቱት ሰዎች ሊረሱኝ አይችሉም” የስዊድን ጋዜጠኛ ማርቲን ሺብዬ

“በማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ ቶርቸር (አካላዊ ስቃይ) የሚፈጸምባቸው ጩኸታቸው ይሰማኛል፡፡ የቃሊቲ ማጎሪያ ውስጥ የታሰሩ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ንጹሃን ዜጎች፣ ስቃይ አሁንም ከፊቴ አለ፤ የሚሞቱት ሰዎች ሊረሱኝ አይችሉም፤ የእስር ቤቱ ጠረንና ሽታ ይከተለኛል፤ በአካል ደህና ብመስልም አእምሮዬ ግን አሁን ድረስ ሰላም የለውም” በማለት የስዊድን ጋዜጠኛ ማርቲን ሺብዬ በተለይለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ተናገረ፡፡

አንድ ዓመት ከሁለት ወር (14 ወራት) ከሥራ ባልደረባው ዮሐን ፔርሶን ጋር ኢህአዴግ አስሮት የነበረው ጋዜጠኛ ሺብዬ ለጎልጉል የአውሮጳ ዘጋቢ ይህንን የተናገረው በዖጋዴን ክልል የተፈጸመውን ጭፍጨፋ የሚያጋልጥ ዘጋቢ ፊልም መሰራጨቱን ተከትሎ ለቀረበለት ጥያቄ መልስ በሰጠበት ወቅት ነው፡፡

“በአካል ሰላም አለኝ፤ አእምሮዬ ግን አልዳነም፤ ሁሌም እረበሻለሁ፤ በዓይኔ ያየኋቸው፣ በጆሮዬ የሰማኋቸውና በበቂ ምስክሮች ያረጋገጥኳቸው ሁኔታዎች ዕረፍት ይነሱኛል” ሲል አስተያየቱን የጀመረው ሺብዬ በኢትዮጵያ እየተፈጸመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና ግፍ ከሙያው አስገዳጅነት በመነሣት ከተባባሪዎቹ ጋር በመሆን ለዓለም እንደሚያሳውቅ ግልጽ አድርጓል፡፡

የኢሕአዴግ የደህንነት መዋቅር መናጋቱን ምንጮች ጠቆሙ::

ተቃዋሚ ሃይሎች ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ሰብረው በመግባት ስርአቱን ማፍረስ ያለባቸው ወቅት ነው::
Minilik Salsawi : ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን የፖለቲካ የምጣኔ ሃብት እና የማሕበራዊ ቀውስ እና ውጥረት ተከትሎ የባለስልጣናት አረመረጋጋት ታክሎበት በገዢው መደብ የተዋቀረው የደሕንነት ተቋም መናጋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ የላኩት መረጃ ጠቁሟል::እንደውስጥ አዋቂ ምንጮች ዘገባ ከሆነ የደህንነት አባላቱ ቡድን እና ብሄር በመለየት በሃላፊዎቻቸው ላይ ያላቸውን ጥላቻ እና ተቃውሞ እያሰሙ ሲሆን ለአንድ ብሄር ብቻ ተለይቶ የሚደረገው የበላይነት አድሎአዊ አሰራር ፍትሃዊነትን ሳይሆን የበታችነታችሁን ያሳብቅባቹሃል የሚሉ ጠንካራ ቡድኖች ከኢሚግሬሽን እና ደህንነት መምሪያ አከባቢ መከሰታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል::

የደህንነት አባላቱ በዜጎች መካከል በሚደረግ አድሏዊ አሰራር ለሃገር ይጠቅማሉ የተባሉ አባላትን በየክፍለ ሃገሩ በማዘዋወር ከችሎታቸው እና ከሰለጠኑት የደህንነት ሙያ ጋር የማይገናኝ ስራ ላይ በመመደብ መረጃ አምጡ ማለት የስርአቱን ዝቅጠት ከማሳየቱም በላይ በቀበሌ ካድሬዎች እና በመንደር ጆሮ ጤቢዎች የሚሰበሰቡ መረጃዎችን አሜሪካ እና እስራኤል ሰልጥነው በመጡ የአማራ እኦሮሚያ እና የደቡብ ክልል የደህንነት አባላት ማሰለል ስር አቱ ምን ያህል መዋቅሩን እንደሳተ እና በሰለጠኑ ዜጎች ላይ ሃገራዊ እምነት እንዳሌለው ያሳያል ሲሉ ምንጮቹ ተናግረዋል::

በውጭ አገር ሰልጥነው የመጡ የደህንነት አባላት ወደ ሃገራዊ የደህንነት መረጃ ሃይሎች እና ጉዳዮች እንዳይጠጉ የሚደረግ ሲሆን በቦታው ከዚህ ቀደም የተመደቡም ቢሆኑ በመረጃ መውር ውስጥ እንዳይሳተፉ ሲደረግ የአንድ ብሄር ተወላጆች በዚህ ላይ እንዲቀሳቀሱ መደረጉ ለስር አቱ ሰዎች አደጋ እና የመዋቅር መናጋት የፈጠረ ሲሆን አንዳንድ የሕወሓት አባላት አብረውን ውጪ አግር ሰልጥነው የመጡ አባሎቻችን የት ሄዱ ለምን አብረውን አይሰሩም በማለት በመዋቅሩ ውስጥ አደጋ ሆነው በመገኘት መናጋቱን እንዳጦዙት ታውቋል::

እንደ ምንጮቹ ከሆነ በአሁኑ ውቅት በሰራዊት ውስጥ እና በደህንነቱ ውስጥ የመዋቅር መናጋት አለመተማመን እና የእርስ በርስ ፍትጊያዎች በስፋት እየታዩ በመሆኑ በሃገር ውስጥ እና በውጭ አገር ያሉ ተቃዋሚዎች ይህንን ክፍተት እና የመዋቅር መናጋት እንዲሁም የውስጥ ሽኩቻን ተገን በማድረግ ሰርገው በመግባት ለስርአቱ መውደቅ ተጨማሪ ሃይል ሊሆኑ ይገባል ሲሉ ምክራቸውን ለግሰዋል::

Friday, January 16, 2015

የወልቃይት ህዝብ ለመንግስት ጥያቄ አቀረበ።

የወልቃይት ህዝብ ለመንግስት ጥያቄ አቀረበ።
(ኢሳት ዜና)፦የወልቃይት ህዝብ እየደረሰበት ላለው የፍትህ መጓደል፣ የመልካም አስተዳደር እጦት፣ የከፋ በደል እና መገፋት ተገቢው ምላሸ በቶሎ እንዲሰጠው ጥያቄ መቅረቡን አስተባባሪዎቹ ገለጹ።
የአስተባባሪዎቹ ተወካይ ለኢሳት እንደገለጹት፣ የወልቃይት ህዝብ ከማንነቱ ጀምሮ በመልካም አስተዳደር እጦትና በፍትህ መጓደል የተጋረጡበት ፈተናዎች ምላሽ እንዲያገኙ፤ፌዴሬሽን ምክር ቤትንና የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤትን ጨምሮ ይመለከታቸዋል ለተባሉ በርካታ ድርጅቶችና መስሪያ ቤቶች፤ ባለፈው ታህሳስ ወር በደብዳቤ ጥያቄ ቀርቧል።
ባለ 18 ገጽ ደብዳቤ ከቀረበላቸው ድርጅቶች መካከል፦ ህወሀትና ብአዴን እንደሚገኙበት የጠቀሱት ተወካዩ፤እስካሁን ድረስ ከአንዳቸውም ምላሽ አለመገኘቱን ተናግረዋል።
(ድምጽከ5፤13 እስከ5፡37)
<<ስር የሰደደው ችግራችንና ገደብ ያለፈው በደላችን፤ በጥይትና በጠመንጃ ሳይሆን በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ መንገድ እንዲፈታና ምላሽ እንዲያገኝ እንፈልጋለን፤ የማንም ህይወት እንዲጠፋ አንፈልግም>>ያሉት አስተባባሪው፤ << ሆኖም መንግስት ምላሽ ካልሰጠን፣ ህዝቡ የራሱን ምላሽ ይሰጣል>>ብለዋል።
(ከወልቃይት ህዝብ አስተባባሪ ጋር የተደረገው ቃለ-ምልልስ በልዩ ፕሮግራም የሚቀርብ መሆኑን እናሳውቃለን)


Thursday, January 15, 2015

ሬዲዩ ፋና፣ ‹‹አንድነት ከአሸባሪ ቡድኖች ገንዘብ ይቀበላል›› በማለት ወነጀለ!!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ሬድዩ ፋና እና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ/ኢቲቪ) በአንድነት ፓርቲ ላይ የጠነሰሱት ሴራ ተጋለጠ፡፡
አንድነት፣ ‹‹ኢትዮጵያውያን ካልሆኑ ሰዎች ገንዘብ ያሰባስባል›› የሚል ውንጀላ እየቀረበበት እንደሚገኝ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ለፍኖተ-ነፃነት ገልፀዋል፡፡ በተለይ ራዲዮ ፋና ‹‹አንድነት ከግንቦት ሰባት ገንዘብ ይቀበላል፣ በውጪ ሀገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ካልሆኑ ሰዎች ገንዘብ ይሰበስባል›› የሚል ውንጀላ እያቀረበ መሆኑን የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አያይዘው ገልፀዋል፡፡
አንድነት እየቀረበበት የሚገኘው ውንጀላ

ፈረንሳይ ሌጋሲዮን በኢቦላ በሽታ ስጋት ተወጥራለች ☞ ከ10 በላይ ሰዎች ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ በፖሊስ ታግተዋል

ሴራሊዮን ውስጥ በአንድ ዓለም አቀፍ ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ ሲሰራ ቆይቶ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላ ህይወቱ ያለፈውና በሽታው ኢቦላ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ የደም ናሙናው ወደ ውጭ ለምርመራ የተላከው ኢትዮጵያዊ ጋር ግንኙነት አለው የተባለው የአምቡላንስ ሰራተኛና ከእሱ ጋር ተገናኝተዋል የተባሉ ሌሎች 10 ያህል ሰዎች የሚኖሩበት ፈረንሳይ ሌጋሲዮን አካባቢ የሚገኝ ጊቢ በፖሊስ ተከቦ ነዋሪዎች ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ ተደርገዋል።

ኢሳያስ የተባለና ህይወቱ ያለፈውን ኢትዮጵያዊ በአምቡላንስ ሲያመላልስ የነበር ወጣት ፈረንሳይ ሌጋሲዮን በተለምዶ ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተከራይቶ የሚኖር ሲሆን እሱን ጨምሮ ከእሱ ጋር የሚኖሩት እህቱና ባለቤቱ እንዲሁም ተከራይቶ በሚኖርበት ግቢ ውስጥ የሚኖሩ ሌሎች ከ10 በላይ ሰዎች ከህዝብ እንዳይገናኙ በፖሊስ ታግተዋል። ግቢው በፖሊስ ተከቦ ሰው ከግቢው እንዳይወጣና ወደ ግቢው እንዳይገባ መከልከሉን ተከትሎ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን አካባቢ የሚኖረው ህዝብ በኢቦላ በሽታ ስጋት ተወጥሯል።

ከፍተኛ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ጀኔራሎች ስርዓቱ በላያቸው ላይ የሚፈፀመውን ተግባር በመቃወም ወደ ጠቅላይ ሚኒስተር ደብዳቤ መላካቸው ተገለፀ፣

ከመከላከያ እስታፍ አፈትልኮ የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው በከፍተኛው የመከላከያ ሰራዊት እርከን ሲሰሩ የቆዩ ከፍተኛ መኮነኖች ሌተናል ጀኔራል አበባው ታደሰ፥ ሌተናል ጀኔራል ሰዓረ መኮነን፥ ሜጀር ጀኔራል ሞላ ሃይለማሪያም፥ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በላያቸው ላይ እየፈፀመው ያለውን ተግባር ትክክል አይደለም በማለት በዚህ ሳምንት ወደ ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማሪያም ደሳለኝ የቅሬታ ደብዳቤ እንደፃፉ ለማወቅ ተችሏል፣

በግላቸው ከፃፏቸው ደብዳቤዎች የተወሰኑትን ለመጥቀስ አበባው ታደሰ ለምን በዚህ አገባብ ከተባረርኩ የጡረታ መብቴ ለምን አይከበርልኝም የሚል ሲሆን ሰዓረ መኮነን ደግሞ ከዚህ ቀደም ከነበርኩበት የስራ ቦታ ለምን ተነሳሁ መመለስ አለብኝ አሁን ባለሁበት የስራ ቦታ ላይ በነፃነት መስራት አልቻልኩም የሚሉና ሌሎችም የሚገኙበት ሲሆን፤ ሞላ ሃይለማሪያም በበኩሉም እኔ ምን አጥፍቼ ነው እያሰራችሁ የምታሰቃዩኝ የሚል ቅሬታ የያዘ ደብዳብቤ እንደሆነ ታውቋል፣

ሃይለማሪያም ደሳለኝ በወገኑ እኔ የህይወት ታሪካችሁን አላውቅም በማለት አባይ ፀሃየንና በረከት ስምዖንን ጠርቶ ባቀረቡት አቤቱታ ጉዳይ እንደተወያዩ የገለፀው መረጃው፤ አንዳንዶቹ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴያቸው ስለተበላሸ መባረራችሁ የግድ ነው ሲሏቸው ለአንዳንዶቹ ደግሞ ገንዘብ አጠፋፍታችሁ ችግር እየተፈታተናችሁ በመሆኑ በተመደባችሁበት ዘርፍ ስሩ እንዳሏቸው ሊታወቅ ተችሏል


የኢትዮጵያ ምርጫ መቆመሪያ ተቋም ገመና

ያሳለፍነው ሳምንት በሕወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ተሰልተው፣ ታስቦባቸው ይፋ ከተደረጉና አሻንጉሊቱ ምርጫ ቦርድ እንዲፈጽመው በህወሃት ሰዎች ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጥቶት ገቢራዊ እንዳደረገው የሚጠረጠረው የፖለቲካ ጉዳይ ይፋ የተደረገበት ነበር፡፡ ይሄው ጉዳይ በአይረቤ ሰበብና በምክንያት አልባ ሁነት ግን ዳግም ከቤተ-መንግስት በወጣ ትዕዛዝ በሚመሰል መልኩ አንድነት እና መኢአድ ወደ ምርጫ ፍክክሩ እንዳይገቡ አይን ያወጣና የሰዎችን የስልጣን ብልግና ባጋለጠ መልኩ መግለጫ የሰጡበት ነው፡፡እንደዚህ ዓመቱ ምርጫ ቦርዱ የተጋለጠበት ጊዜ አለ ብዬ አላምንም፡፡ ይሄው የምርጫ መቆመሪያ ተቋም እንደ ጫጩት ፍፁም ጠቅላላ ጉባዔ አድርገው የሚያውቁ፣ ቢሮም ሆነ ስራ አስፈፃሚ የሌላቸውን ተቃዋሚ ተብዬዎች በጉያው ሸጉጦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ እያላገጠ መሆኑ ሳያንስ የገዥውን ፓርቲ ኃላፊነት የጐደለው ተግባር ተቋቁመው ለሃገራችን የዴሞክራሲ

ሰማያዊ ቲሸርት የለበሱ ወጣቶች ከስላሴ በዓል ላይ ተባረሩ

ዛሬ ጥር 7/2007 ዓ.ም የዓመቱን የስላሴ በዓል ለማክበር አራት ኪሎ የሚገኘው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን የተገኙ ወጣቶች ሰማያዊ ቲሸርት በመልበሳቸው በፖሊስ እንደተባረሩ የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ ‹‹ያመነ፣ የተጠመቀ ይድናል!›› የሚል ሰማያዊ ቲሸርት የለበሱትን ወጣቶች ቲሸርቱን እንዲያወልቁ ሲጠይቅ ወጣቶቹ አናወልቅም በማለታቸው ከበዓሉ ማባረሩን እማኞቹ ገልጸዋል፡፡ ከተባረሩት ወጣቶች መካከል አብዛኛዎቹ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚገቡትንና የሚወጡትን አማኞች በማስተባበር ላይ እንደነበሩ የተገለጸ ሲሆን የተባረሩት ወጣቶች ይታሰሩ አይታሰሩ የታወቀ ነገር የለም፡፡በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የመጡ ከፍተኛ ኃላፊዎች ለጥምቀት በዓል ሰማያዊ ቲሸርት ያዘጋጁትን የጃንሜዳ አካባቢው የጥምቀት በዓል አስተባባሪዎች፣ ያዘጋጁት ሰማያዊ ቲሸርት በዓሉ ላይ እንዳይለበስ በተደጋጋሚ እያስጠነቀቁ እንደሚገኙ ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በፖሊሶችና በደህንነቶች ተደጋጋሚ ጫናም ለጃንሜዳ አካባቢ ወጣቶች የተዘጋጀው ሰማያዊ ቲሸርትና ‹‹ያመነ፤ የተጠመቀ ይድናል›› የሚለውን ጥቅስ በነጭ ቲሸርት እና በሌላ ጥቅስ እንድንቀይር ተገደናል ብለዋል፡፡ በአንጻሩ የፈረንሳይና ቤላ አካባቢ ወጣቶች ሰማያዊ ቲሸርቱን እንዲቀይሩ ጫና ቢደርስባቸው አንቀይርም በሚል አቋማቸው መጽናታቸው ታውቋል፡፡በተመሳሳይ ጥር 6 የአዲስ አበባ መስሪያ ቤቶችና ወረዳዎች ኮሚኒኬሽን ኃላፊዎች አዲስ አበባ መዘጋጃ ቤት ባደረጉት ስብሰባ የየካ ክፍለ ከተማ ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን አካባቢ ‹የፈራ ይመለስ› የሚል ሰማያዊ ቲሸርት አስለብሶ ሲበጠብጠኝ ሰንብቷል፡፡›› ሲል ሪፖርት ማቅረቡን የስብሰባው ተሳታፊዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ‹‹ደህንነት፣ ፖሊሶችና ካድሬዎች እያንዳንዱን የህዝብ እንቅስቃሴ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር በማገናኘት ወቀሳ የሚያቀርቡት ህዝብ ውስጥ ብሶት እንዳለ፣ ሰማያዊም የህዝብን ብሶት እንደሚያሳማ ስለሚያውቁ፣ ከምንም በላይ ገዥው ፓርቲ የራሱን ጥላ የማያምንበት ደረጃ ላይ ስለደረሰ ነው›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ባነሱባቸው ጊዜያት ሁሉ ገዥው ፓርቲ ሰማያዊ ፓርቲን ‹‹የሙስሊም ፓርቲ ነው›› በሚል ሀሰተኛ ወሬ ሲያሰራጭ እንደነበርና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በሰጠው የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ሰማያዊ ፓርቲን ሲወቅስ እንደከረመ ያስታወሱት ኃላፊው አሁንም ፓርቲውን ከእያንዳንዱ የህዝብ እንቅስቃሴ ጋር እያገናኘ ቢበረግግ አያስገርምም ብለዋል፡፡

የአማራ ክልል አስተዳደር ምርጫውን ተከትሎ አመጽ ይነሳል በሚል የ‹‹ፀጥታ ኃይሎችን›› እያሰለጠነ መሆኑ ተሰማ

ፖሊሶች የደረጃ እድገት እንደሚደረግላቸው ቃል ተገብቶላቸዋል ‪
የአማራ ክልል መስተዳደር በግንቦት 2007 ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀውን አምስተኛው አገራዊ ምርጫ ተከትሎ አመጽ ከተከሰተ ለመቆጣጠር ያስችላል ያለውን ስልጠና ለክልሉ ፖሊስ፣ ለማረሚያ ቤት ፖሊስ፣ ለሚሊሻና ለመከላከያ ሰራዊት አባላት እየሰጠ መሆኑን ሰልጣኞቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ስልጠናውም፤ ለፖሊሶች በዞን እንዲሁም ለሚሊሻና ለፀጥታ ጉዳይ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌዎች እየተሰጠ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

የስልጠናው ዋና አላማ በቀጣዩ ምርጫ ሊከሰት ይችላል ተብሎ የሚፈራውን አመጽ መቆጣጠር እንደሆነ የገለጹት የፖሊስ ምንጮች በተለይ ፖሊስና ፀጥታ ጉዳይ ከ‹‹ማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ›› ጋር በመተባበር የደፈጣ ውጊያን ለመከላከል ‹‹የደፈጣ ውጊያ ስምሪት›› በሚል አጭር ስልጣና እየወሰዱ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ይህም አገር ውስጥ አመጽ ያነሳል ተብሎ ከሚፈራው ህዝብ በተጨማሪ መሳሪያ ያነሱ ተቃዋሚዎች በምርጫው ወቅት ጦርነት ይከፍታሉ የሚል ስጋት በመኖሩ ነው ሲሉ ሰልጣኞቹ ገልጸዋል፡፡ በደብረማርቆስ ውስጥ ስልጠናውን የሚወስዱት ሰልጣኞች ማታ ማታ የተኩስ ልምምድ እንደሚያደርጉ አንድ የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

Wednesday, January 14, 2015

የሰሜን ጎንደር የእስር ቤት አዛዥ ተገደሉ!!

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ESAT ዜና :-የኢሳት ዘጋቢዎች ከጎንደር እንደገለጹት ኮማንደር አለባቸው የተባሉት የሰሜን ጎንደር ዞን የወይኔ ቤት አዛዥ የተገደሉት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ ነው። ኮማንደሩ በጥይት መመታታቸው ቢገለጽም ዘጋቢያችን ማን እንደገደላቸው ለማወቅ ያደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። የግለሰቡ አስከሬን ወደ ተወለዱበት በየዳ ወረዳ መላኩ ታውቋል።

አወጋን እየተባለ የሚጠራው ድርጅት ግድያውን መፈጸሙን ገልጿል። ድርጅቱ በማህበራዊ ድረገጽ ላይ ባወጣው መረጃ ”የሰሜን ጎንደር የማረሚያ ቤት ሀላፊ ኮማንደር መተከል አያልሰዉ እርምጃ ተወሰደበት” ብሎአል። አርምጃዉ የተወሰደዉ ትናት ማታ ሰባት ሰአት ሲሆን በተደጋጋሚ ከግፍ ስራዉ እንዲቆጠብ መልክት ቢደረሰዉም አሻፈረኝ በማለቱ ተገድሏል ” ብሎአል።

የኢሳት ዘጋቢዎች ሟቹን ኮማንደር አለባቸው ሲሉት አወጋን ደግሞ ኮማንደር መተከል ብሎታል። በጉዳዩ ላይ የሰሜን ጎንደር የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊን ለማነጋገር ሙከራ ብናድርግም አልተሳካልንም።


በዞን 9 ጦማርያንና ጋዜጠኞች ላይ የቀረበው ክስ በድጋሜ ‹‹ተሻሻለ››

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

ጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ ጥር 6 ቀን 2007 ዓ.ም ለ15ኛ ጊዜ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የተሰየመው ቀደም ብሎ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ እንዲሻሻል ባዘዘው መሰረት የፌደራል አቃቤ ህግ ክሱን ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ያላሻሻላቸው ነጥቦች ስለነበሩ እነዚህኑ ነጥቦች በድጋሜ አሻሽሎ እንዲቀርብ ባዘዘው መሰረት የተሻሻለውን ክስ ለመስማት ነበር፡፡

በመሆኑም የፌደራል አቃቤ ህግ አሻሽየዋለሁ ያለውን ክስ ይዞ ቀርቧል፡፡ ክሱ ‹‹ሌሎች ብዙ ‹ኬዞች› ስላሉ›› በሚል ምክንያት በችሎቱ ላይ በንባብ እንዲሰማ አልተደረገም፡፡ ተሻሻለ የተባለው ክስ ለተከሳሾችና ለጠበቆች እንዲደርስ የተደረገውም እዚያው ችሎት ውስጥ ነው፡፡

ክሱ በንባብ ባለመሰማቱና ጠበቆቹና ዳኞቹም ስላላነበቡት በሚል ተሻሻለ በተባለው ክስ ላይ ምንም አስተያየት አልቀረበም፡፡ በመሆኑም ክሱ መሻሻል አለመሻሻሉን ለመመርመርና ብይን ለመስጠት ለጥር 20 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

የጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ጠበቃ የሆኑት አቶ አምሃ መኮንን እንዳሉት በቀጣዩ ቀጠሮ ላይ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ተሻሽሎ ካልሆነ ነጥቦቹን ፍርድ ቤቱ ውድቅ ያደርጋል ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል፡፡ ‹‹በእኛ በኩል ከዚህ በኋላ የማሻሻያ ሀሳብ አቅርበን ጊዜ አንፈጅም፤ ከሚቀጥለው የፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኋላ መደበኛ ክርክራችንን መቀጠል ነው የምንፈልገው›› ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በዛሬው የችሎት ውሎ ላይ በጣም ብዙ እስረኛ (ተከሳሽ) ችሎቱ ውስጥ በመገኘቱ ምክንያት ከፍተኛ የቦታ ጥበት ማጋጠሙ ተስተውሏል፡፡ በአጠቃላይ እስከ 70 የሚደርሱ እስረኞች በችሎቱ ተገኝተዋል፡፡ ስለሆነም ችሎቱን መታደም የቻሉት ጥቂት ጋዜጠኞችና ዲፕሎማቶች ብቻ ሆነዋል፡፡ የተከሳሽ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶች ችሎቱን መታደም አልቻሉም


በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣ ዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ መሀል የተደረገውን ውህደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በዛሬው ዕለት፣ ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ ለዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ፣ ድርጅቶች፣ ተዋህደን “አርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ”፣ በሚባል ሥም መጠራት መጀመራችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስናበስር፣ እጅግ ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ባለፉት በርካታ አስርተ አመታት፣ለፍትህ፣ ለእኩልነት፣ ለነጻነት፣ መብትና አንድነት፣ ከፍተኛ ትግል ሲያካሂድ ቆይቷል። በአደረገውም ትግል እጅግ ከፍተኛ መስዕዋትነት ከፍሏል። ለከፈለው ከፍተኛ ዋጋ የሚመጥን ግን ምንም ዓይነት ውጤት አላገኘም። እንዲያውም ከጊዜ ወደ ጊዜ የመብት ረገጣው፣ አድሎው፣ ማስፈራራቱና ማዋከቡ ተጠናክረው መቀጠል ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ልትቀጥል የማያስችል ከፍተኛ የመበታተን አደጋ አንጃቦባት ትገኛለች ።

Tuesday, January 13, 2015

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ፣ ግንቦት7 እና የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ የውህደት ስምምነት ተፈራረሙ

የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ወደ ውህደት የሚያደርሳቸውን ስምምነት  ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር፣ የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እንዲሁም የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ በጋራ ባወጡት መግለጫ ”ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ካሉበት አዘቅት በማውጣት ሕዝቡ የስልጣን ባለቤት የሚሆንበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የጋራ ትግልና መስዋዕትነት የግድ የሚለን ደረጃ ላይ ደርሰናል” ብለዋል። ድርጅቶቹ አያይዘውም ”አገራችንና ሕዝባችንን ከአዘቅት ለማውጣት በመጣመር ብቻ ሳይሆን በውህደት አንድ ሆነን አገራችንንና ሕዝባችንን አንድ በማድረጉ ረገድ አስፈላጊው መስዋዕትነት በመክፈል የትግል እድሜ እናሳጥር በሚል ለውህደት የሚያደርሰንን ውይይት ለመጀመር የሚያስችል ሂደቶችን አጠናቀን ወሳኝ ወደሆነው ሂደት ውስጥ መግባታችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ወዳጆች ማብሰር እንፈልጋለን።” ብለዋል።

የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመባት

የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመባትወይዘሪት ወይንሸት፣ ንፍስ ስልክ አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ ሁለት ሰዎች ከረፋዱ 5፡30 ላይ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመባት ለፍኖተ-ነፃነት የደረሰው መረጃ ያመላክታል፡፡ወይዘሪት ወይንሸት፣ ነፍሰጡር መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን ደብዳቢዎቹም ሆዷን በመርገጥ ድብደባውን ሲፈፅሙባት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ ደብዳቢዎቹ ድብደባውን ፈፅመው የተሰወሩ ሲሆን ወይዘሪት ወይንሸት፣ በአሁኑ ሰዓት ራሷን ስታ ሆስፒታል መግባቷን ለማወቅ ተችሏል፡፡ወይንሸት፣ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለማካሄድ በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በከፍተኛ ድምፅ የአስመራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆና በመመረጥ በምርጫው ላይ ጉልህ ሚና በመጫወት ድርሻዋን መወጣቷ ይታወሳል፡፡ በእለቱ በተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአንድነት ስም የሚነግዱትን ግለሰቦች በማውገዝ አስተያየቷን መሰንዘሯን ተከትሎ ድብደባው ሊፈፀምባት እንደተቻለ ለማወቅ ተችሏል፡፡ወይዘሪት ወይንሸት፣ በፓርቲው ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ያላት ወጣት ከመሆኗም በተጨማሪ የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ሀላፊ በመሆን በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ሳምንት ብቻ በአንድነት አባላት ላይ ድብደባ ሲደርስ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ባለፈው እሁድ በአቶ መሳይ ትኩ፣ ላይ ድብደባ መፈፀሙ ይታወሳል፡፡

ዶር ዳኛቸው አሰፋ ከ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ አለች ወይ?

አንድ የተማረ ሰው ከ አዲስ አበባ ወጥቶ ወደ ሌላ ክልል ሄዶ ስራ ሲሰራ ደሞዙ ተቆርጦበት ወይም ዘግይቶበት ሰለ መብቱ ቢጠይቅ የሚሰጠው ምላሽ እኔዴውም ከ አላገራቹህ መጥታቹህ ስራ ስላገኛቹህ ልታመሰግኑ ይገባል ይባላሉ፥፥ አሁን ያለንበት ደረጃ አሥከፊና አስቸጋሪ ነው፥፥ እነዴውም አሁን እየጠየቅን ያለነው፥ አገራችን አለች ወይ ነው? ኢትዮጵያ አለች ወይ? ልክ ከ አዲስ አበባ ወጣ ስትል ከየት ነው የመታኽዉ ትባላለህ፥፥ ልክ ሌላ አገር የሄድክ እስኪመስልህ፥፥ ምንም አይነት ፕሮቴከሽን የሌለባት አገር ሁናለች፥፥ መጀመሪያ የጠነሰሱት ቢህል አሁን እያበበ ነው፥፥ የ አገሪቱ ሁኔታ ኢዝ አት ስቴክ (is at stake)፥፥ አንተ ትቀልዳለህ ሶማሊያ :ጋምቤላ ተወው፥ እዚህ አምቦ እንኮ የኔ ተማሪወች ስራ ተቀጥረው የ እኛ ተማሪወች እስኪመጡ ብቻ ነው ስራ ሊኖራቹህ የምትችሉ ነው የተባሉት፥፥ አንተ ትቀልዳለህ! አገር የለንም ነው እንኮ የምልህ፥፥ ይህ ከ ሗላ ኪሴ አውጥቼ የምንገርህ እንድይመስልህ ልጄ፥፥

የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንድነት ፓርቲ በጠራው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ሳይገኝ ቀረ።ጠቅላላ ጉባኤውን ተካፍሎ ወደ ቤቱ ሲሄድ የነበረ የፓርቲው አባል በፖሊሶች ተደበደበ።

ጥር ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቦርዱ -አንድነት በአራት ቀናት ዉስጥ አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ አመራሮችን በምስጢር አሰጣጥ መምረጥ እንዳለበት ሲያሳስብና ሲያስጠነቅቅ መቆየቱ ይታወሳል።
ሆኖም፤ ይህን የቦርዱን ማስጥንቀቂያ ተከትሎ አንድነት ከትናንት አርብ ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤና የአመራር ምርጫ ታዛቢ እንዲልክ በደብዳቤ የተጠየቀው ምርጫ ቦርድ፤ “አየለ የሚባል ሰው ሌላ የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ይደረጋል የሚል ደብዳቤ ስላሰገባ፣ በሁለት ቦታ መገኘት አንችልም” የሚል ምላሽ በመስጠት በጠቅላላ ጉባኤው ሳይገኝ መቅረቱን ፓርቲው ገልጿል።
አንድነት ፓርቲን የማይወክል አንድ ግለሰብ ደብዳቤ ስለጻፈ፣ ምርጫ ቦርድ በአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ አልገኝ ካለ፣ ችግሩ የምርጫ ቦርድ ነው ያለው ፓርቲው፣ ምርጫ ቦርድ ተገኝም፣ አልተገኝም፤ ጠቅላላ ጉባኤው እንደሚካሄድ ለቦርዱ በደብዳቤ ማሳወቁንም ጠቅሷል።
ምርጫ ቦርድ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ራሱን እያጋለጠና እርቃኑ እየወጣ ባለበት ወቅት፣ ከመላው አገሪቱ የተሰባሰቡ የአንድነት አባላት በጠቅላላ ጉባኤው መገኘታቸውን የጠቀሰው ፓርቲው፤ << በአራት ቀናት ዉስጥ የጠቅላላ ጉባኤ አባላትን ሰብሰበን ጠቅላላ ጉባኤ መጥራት መቻላችን፤ የፓርቲያችንን ድርጅታዊ ጥንካሬም የሚያሳይ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ>>ብሏል።

Monday, January 12, 2015

በጣይቱ ሆቴል መቃጠል ህብረተሰቡ ቁጣውን እየገለጸ ነው።

ጥር ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ትናንት እሁድ ጥር 3-2007 ማለዳ ላይ ነበር በ ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሰመናዊ ሆቴል የሆነው ታሪካዊው ጣይቱ ሆቴል በእሳት የወደመው።
የዓይን ምስክሮች በወቅቱ እንደተናገሩት፤የእሳት አደጋ ብርጌድ መስሪያ ቤት በሆቴሉ አቅራቢያ ሆኖ ሳለ እሳቱ ከተነሳ በትንሹ ለአንድ ሰኣት ያህል አንድም የ እሳት አደጋ መኪና አለመታዬቱ፣ሰግይተውም ከመጡት ሶስት መኪኖች መካከል አንድኛው ወሃ የለኝም ብሎ እንዲሁ መቆሙ ነው ለአደጋው መክፋትና ለሆቴሉ መውደም ዋነኛው ምክንያት የሆነው። ይህም በርካቶችን አስቆጥቷል። ሌላው የህስብን ቁጣ የቀሰቀሰው ደግሞ የሀገር ቅርስ ከሆነው ታሪካዊ ሆቴል ይሶታ በትንሹ 80 በመቶ ያህሉ ከወደመ በኋላ የኢትዮጵያ ቴሌቪጽንን ቸምሮ ሌሎች የመንግስትና የድርጅት ሚዲያዎች “በጣይቱ ሆቴል የተነሳው አደጋ በ አደጋ ብርጌድ ሰራተኞችና በፖሊስ በተደረገ የተቀናጀ ሰመቻ በቁጥጥር ስር ውሏል” የሚል ሴና ማወጃቸው ነው። ጣይቱ ሆቴል – የአርት ጋለሪው፣የመመገቢያው አዳራሹ፣እንግዳ መቀበያ ክፍሎቹ፣ እና በዛ ያሉ መኝታ ክፍሎቹ በእሳት አደጋው መሉ በሙሉ በ እሳት ወድመዋል።

ሕወሃት በመንግስት ስልጣን ባለቤትነትና በወንበዴነት መሐል ያለው ልዩነት ተምታቶበታል

ኢትዮጵያን በግፍና በዝርፊያ የሚገዛው የህወሀት ጉጅሌ በመንግስትነትና በወንበዴነት መሀል ያለውን ልዩነት ከ፪፫ ዓመት ስልጣን ዘመን ብኋላ እንኳን ሊገለጥለት አልቻለም። ወይም እንዳመችነቱ ሁለቱን እያምታታ መቀጠሉን እንደብልህነት ቆጥሮታል። መንግስት መሆንንና ባለህገመንግስት መባልን ከመቆነጃጃ ኩልነት ባልተናነሰ በለጋሾቻቸው ባዕዳን ፊት ይጠቀሙበታል እንጂ ለኛ ለዜጎቹማ ወንበዴነታቸውን ሊደብቁን እንኳን አይጨነቁም።በቅርቡ ህወሀት የትግራይ ሪፐብሊክ ለማቋቋም የክህደት ተግባሩን የጀመረበትን ፵ኛ ዓመት በዓሉን ትግራይ ውስጥ በማክበር ላይ ሳለ የቀድሞው የህወሀት ታጋይ ያሁኑ የሀገሪቱ ጦር ሎች ኤታማዦር ሹም ተብዬው ሳሞራ የኑስ የህወሀት መንግስት ያገራችን ገበሬ ወፎችን ከማሽላው ለመከላከል እንደሚጠቀምበት መስፈራሪቾ የሚጠቀምበት ሕገ መንግስት ላይ የተጠቀሰውን የሀገሪቱን ሰራዊት የፖለቲካ ገለልተኝነት ድንጋጌና ሰራዊቱ

ትናንት ከዉጭ ወራሪዎች የታደገን መከላከያ ሠራዊታችን ዛሬም ከአገር ዉስጥ ወራሪዎች ይታደገናል

አስተዋዩ የኢትዮጵያ ህዝብ እድገቱን ለሚመኙ አስተዋይ መሪዎች እለታደለምና ደሃ ነዉ፤ ረሀብተኛ ነዉ አልተማረም ወይም ኋላ ቀር ህዝብ ነዉ ማለት ይቻል ይሆናል፤ ሆኖም የኢትዮጵያ ህዝብ ያሰኘዉን ያክል ቢደኸይ ወይም ኋላ ቀር ቢሆን ለነፃነቱ፤ ለአንድነቱና ለግዛት አንድነቱ መከበር ያለስስት ደሙን የሚያፈስ ጀግና ህዝብ ነዉ። ይህ ጀግንነት ደግሞ አንደተረት በአፍ ተነግሮ የሚያበቃ ሳይሆን በመተማ፤ በአድዋ፤ በማይጮዉ፤ በወልወል፤ በፊልቱና በጎዴ የጦር ሜዳዎች ሊወጉትና ሊወሩት የመጡ ጠላቶቹ ጭምር የመሰክሩለት የታሪክ ሐቅ ነዉ።የኢትዮጵያ ህዝብ ከጀግንነቱ ጋር አርቆ አስተዋይና ታጋሽ ህዝብ ነዉ፤ ሆኖም ይህንን ህዝብ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ በተከታታይ የገዙት የገዢ መደቦች ጀግንነቱን ለራሳቸዉ ክብርና ዝና ታጋሽነቱን ደግሞ ለስልጣን ዘመናቸዉ ማራዘሚያ አድርገዉ የመከራ ዘመን እያስቆጠሩ ኖረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ታጋሽ ህዝብ ቢሆንም እርግጫዉና ጭቆናዉ በበዛበት ቁጥር አምርሮ የሚነሳ ለገዢ መደቦች የማይመች ቁጡና እልህኸኛ ህዝብ መሆኑንም በተከታታይ አሳይቷል። ይህንን ደግሞ በ1966 ዓም ከዳር ዳር ባቀጣጠለዉ ህዝባዊ አብዮት በ1983 ዓም ደግሞ በአራቱም ማዕዘናት ባካሄደዉ ህዝባዊ አመጽ አሳይቷል። ሆኖም አብዮቱንና ህዝባዊ አመጹን ከትግል ሜዳ እስከ ፖለቲካ ስልጣን አደባባዮች ድረስ

Sunday, January 11, 2015

በቂሊንጦ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን አስታወቁ

በቂሊንጦ ከሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች መሃል የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው እና የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ለአዲሱ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ በላይ ፍቃዱ ድጋፋቸውን መስጠታቸውን ተከትሎ በወህኒ ቤት ውስጥ ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

አመራሮቹ ስቃይ እየደረሰባቸው የሚገኘው ለአቶ በላይ ፍቃዱ እውቅና ሰተው በሌላ በኩል በአንድነት ስም በተጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለተመረጡት የፓርቲው ሰዎች እውቅና መንፈጋቸውን ተከትሎ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአንድነት ፓርቲ አመራር የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከሃምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡


ታሪካዊው ጣይቱ ሆተል ተቃጠለ:: 

- በውስጥ እና በውጭ የተከሰተበትን የፖለቲካ ውጥረት አቅጣጫ ማስቀየሪያ ነው::
- ጣይቱ ሆቴል የ ስዬ አብርሃ የቅርብ ዘመድ አቶ ፍፁም ዘአብ ንብረት ነበር

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዘመናዊ ሆቴል የሆነውና ለሀገሪቱ እና ለሕዝቡ እንደ ታላቅ ቅርስ የሚታየው ጣይቱ ሆቴል ተቃጠለ። በቦታው የነበሩ የዓይን ምስክሮች እንዳሉት ሆቴሉ መሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ በእሳት ጋይቷል።

በሃገሪቱ ውስጥ የተከሰተው የፖለቲካ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ወያኔ በምርጫው ጉዳይ እና በተለያዩ የምእራባውያን ጫና የተወጠሩት በህዝብ ጥያቄ የተጨነቁት የወያኔ ባለስልጣናት የህዝቡን የአስተሳሰብ አቅጣጫ ለማስቀየር እና ሃሳብ ለመስረቅ ለማስደንገጥ እና አዲስ መወያያ ጉዳይ ለመፍጠር ያደረገው ተንኮል ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ::

ሰማያዊ ፓርቲ ይቅርታ እንደማይጠይቅ አስታወቀ


ሰማያዊ ፓርቲ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽሕፈት ቤትን እስከ ጥር 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ በጽሑፍ ይቅርታ ይጠይቅ በማለት የተላለፈው ውሳኔ ከሕግ አግባብ ውጪ ስለሆነ ተቃውሞውን በመግለጽ ይቅርታ እንደማይጠይቅ አስታወቀ፡፡

የቦርዱ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደምሰው በንቲ ባለፈው ሐሙስ በጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ፣ ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድን ስም አጥፍቷል ብለዋል፡፡ ‹‹በተሻሻለው የምርጫ ሕግ አንቀጽ 102 (4)ሀ፣ ለ እና ሠ እንዲሁም 102 (6) ሐ መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎች የቦርዱን ሥልጣን መቀበል፣ ሕጋዊ ትዕዛዙንና መመርያውን የማክበር ግዴታ እንዳለባቸው፣ እንዲሁም ቦርዱ በሚያዘጋጃቸው የጋራ የምክክር መድረኮች ወይም ሌሎች መድረኮች ላይ ወኪል የመላክ ኃላፊነት እንዳለባቸውና በሐሰት ስም ከማጥፋት መቆጠብ እንዳለባቸው ያመለክታሉ፤›› ብለዋል፡፡

Saturday, January 10, 2015

ኦኬሎ አኳይ እጅና እግራቸውን ታስረው ጨለማ ክፍል መታሰራቸው ተገለጸ

ኦኬሎ አኳይ እጅና እግራቸውን ታስረው ጨለማ ክፍል መታሰራቸው ተገለጸ
•እስክንድር ነጋ ከቤተሰብ ውጭ ጠያቂ ተከልክሏል
የቀድሞው የጋንቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ኦኬሎ አኳይ እጅና እግራቸው ታስሮ ጨለማ ክፍል መታሰራቸውን ምንጮች ገለጹ፡፡
አቶ ኦኬሎ ቂሊንጦ በእስር ላይ እንደሚገኙ የሚታወስ ሲሆን፣ ሰውዬው ከሰሞኑ የርሃብ አድማ ማድረጋቸውን ተከትሎ በእስር በሚገኙበት እስር ቤት እጅና እግራቸውን ታስረው ብቻቸውን ጨለማ ክፍል እንዲገቡ እንደተደረጉ ምንጮች ተናግረዋል፡፡
ዛሬ ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም ወደ ቂሊጦ ማረሚያ ቤት እስረኞችን ሊጠይቁ ሄደው እንደነበር የገለጹት ምንጮች፣ እዚያው በእስር ላይ ካሉ ሰዎች አቶ ኦኬሎ ያሉበትን ሁኔታ መረዳታቸውን አክለው ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የ18 አመት እስር ፍርደኛው ታዋቂው ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ከቤተሰብ ውጭ ሌላ ሰው መጠየቅ እንደተከለከለ ለማወቅ ተችሏል፡፡


የወያኔው ጁንታ አንድነት ፓርቲ በምርጫው እንዳይሳተፍ የፖለቲካ ውሳኔ አስተላለፈ::

አንድነት ፓርቲ በድጋሚ የምርጫ ቦርድን ደባ ለማክሸፍ ጠቅላላ ጉባዬ ጠርቷል::
– አንድነት ፓርቲን ከሰላማዊ ትግሉ ለማስወጣት የተደረገውን ደባ ተጋልጧል::

የወያኔው አምባገነን ጁንታ የአንድነት ፓርቲ በ2007 በሚደረገው ምርጫ ላይ እንዳይሳተፍ በሕወሓት/ኢሕአዴግ ፖለቲካዊ ውሳነ ተደርጎበት ወደ ምርጫ ቦርድ እንደተላለፈ እና ፓርቲውን ከምርጫው ለማስወጣት ደባ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተጠቆመ:: እንደ ምንጮቹ ከሆነ ሕወሓት/ኢሕአዴግ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችን እና አባላትን ከማሰር እና ከማንገላታት ጀምሮ እስከ ምርጫ ቦርድ ማሸማቀቀ እና ሰበብ ማብዛት ቢሞክርም አንድነት ፓርቲ ይህንን ሁሉ ተቋቁሞ በአሸናፊነት መገስገሱ ለገዢው ፓርቲ መደናገጥ በመፍጠሩ ፓርቲው በምርጫ እንዳይሳተፍ ውሳኔ ማስተላለፉን ተገልጿል::

የአንድነት ፓርቲ አደገኛ የሆነበት ሕወሓት/እሕአዴግ ምርጫ ቦርድን ተገን በማድረግ ከምርጫ ለማስወጣት እንዲሁም ተለጣፊ አንድነት ፓርቲ ለመመስረት በመጣር ላይ ሲሆን ዓላማው በአባላት፣ በደጋፊና በህዝቡ ውስጥ ውዥንብር ለመፍጠር ታሰቦ የሚካሄድ ፖለቲካዊ ደባ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ ባስተላለፈው መግለጫ እንዳለው በሀገራችን አስተማማኝ ሠላም እና ዘላቂነት ያለው ደህንነት የሚያረጋግጠው እንደ ምርጫ ቦርድ ያሉ ተቋሞች ነፃ፣ ገለልተኛ እና በህዝብ ዘንድ አመኔታ ሲጣልባቸው ነው፡፡ ይህ ተቋም አሁን በያዘው ሁኔታ ከቀጠለ ከታሪክ ተጠያቂነት አይድንም፡፡ ገዢው ፓርቲም ጧት ማታ የሚያባንነው ሕዝባዊ እምቢተኝነት መምጣቱ አይቀሬ ነው፡፡

በመሆኑም አሁን ፓርቲያችንን ለመታደግ እና የቦርዱን የመጨረሻ ካርድ ለማስጣል አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለ2ኛ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ ጠርተናል፡፡ ይህ ማለት የትግሉ መጨረሻ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያደረሰብንን የሕግ ጥሰት ይዘን በፍርድ ቤት ክስ እንመሰርታለን፡፡ እስከ አሁን ያለውን ሂደት ስናየው የቦርዱ ፖለቲካዊ ደባ ቀጣይ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ስለሆነም መላው አባሎቻችን፣ ደጋፊዎቻችን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ለምንወስዳቸው ተከታታይ ፖለቲካው ውሳኔዎች እና እርምጃዎች ከጎናችን እንዲቆም ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፋለን፡፡ ብሏል አንድነት ፓርቲ::

እንደ ፓርቲው ምንጮች ምርጫ ቦርድ እና ኢህአዲግ ባሰማራው ጥቂት ቡድን አማካኝነት አንድነት ፓርቲን ከሰላማዊ ትግሉ ለማስወጣት የተደረገውን ደባ አቶ ብርሃኑ ይግለጡ እና አቶ መሳይ ትኩ ያጋለጡ ሲሆን ቭዲዮው ይለቀቃል ተብሎ ይጠበqaል::

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

Friday, January 9, 2015

ሁለት የኢሳት ጋዜጠኞች በድንበር አካባቢ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ለመዘገብ ወደ ኤርትራ መሄዳቸው የበርካታ ኢትዮጵያንን እያነጋገረ ነው።

ታኀሳስ ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት በትናንት በዘገባው እንዳስታወቀው ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን እና ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ወደ ኤርትራ ያቀኑት በኤርትራ ድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የ ኢት ጰያ ተቃዋሚዎች እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ በዓይን
አይቶ ለመዘገብ፤እንዲሁም ከተሳካላቸው በወደፊቱ የኢትዮጰያና የኤርትራ ግንኙነት ዙሪያ የኤርትራ ባለስልጣናትን ቃለ ምልልስ ለማድረግ ነው። ይህን ተከትሎ እጅግ በርካታ ኢትዮጰያውያን ለጋዜጠኞቹ ያላቸውን አክብሮትና አድንቆት በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
እነኚህ ወገኖች ፤ጋዜጠኞቹ- እንደ ጋዜጠኛ በተግባር መሬት ላይ ያለውን ነገር አይተው ለህዝብ ለማሳወቅ ወደ ድንበር ማምራታቸው ፤ ለሙያቸው የተሰጡ መሆናቸውን የሚያመላክት ከመሆኑም ባሻገር – ውሳኔያቸው በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል መልካም መቀራረብና ወንድማችነት እንዲኖር የሚያበረክተው አስተዋጻኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መንግስት ለኢህአዴግ ተላልፎ መሰጠቱ ያስቆጣቸው ኢትዮጰያውያን ደግሞ፤ በማህበራዊ ሚዲያዎችም ሆነ ወደ ኢሳት ስልክ በመደወል በሰጡዋቸው አስተያየቶች ፤ጋዜጠኞቹ የወሰዱትን ድፍረት በማድነቅ በሰላም እንዲመለሱ ምኞታቸውን ገልጸዋል። እነኚህኞቹ ጋዜጠኞቹ በሰላም እንዲመለሱ ምኞታቸውን እየገለጹ ያሉት ፤ በሀገር ቤት ያሉ ጋዜጠኞችን ለእስርና ስደት የዳረገውና በኢሳት ክፉኛ የሚበሳጨው የኢህአዴግ መንግስት እንደ አቶ አንዳርጋችው ጽጌ ጋዜጠኞቹን በመንገዳቸው ላይ በገንዘብ እንዳያስጠልፋቸው በመስጋት ነው።
በሌላ በኩል የገዥው ፓርቲ አባላት የሆኑ ካድሬዎች ደግሞ፤ የጋዜጠኞቹ ለዘገባ ወደ ኤርትራ ማቅናት ከተሰማ በሁዋላ ቁጣና ንዴታቸውን ያለመቋረጥ በመግለጽ ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን እና ፋሲል የኔዓለም በሰላም ኤርትራ ከመግባታቸውም በላይ በነጻነት በመንቀሳቀስ የሄዱበትን ስራ እየከወኑ ይገኛሉ።
ጋዜጠኛ መሳይ በፌስ ቡክ ገጹ አስመራ ከተማን ከሁዋላው አድርጎ በተነሳው ፎቶ ስር ባሰፈረው ጽሁፍ፦<<አስመራ፡ ተራራ ላይ የከተመች፡ ጥንታዊ ገጽታዋን ያለቀቀች ውብ ከተማ። ኢሳት አስመራ ገብቷል፡፡ ሰላማዊውን ትግል በሰፊው እየዘገብን ነው። ዱር ቤታቸው አድርገው በሃይል ህወሀትን ለማስወገድ የተዘጋጁትን ሃይሎች ደግሞ በአካል ተገኝተን ልናያቸው ነው፡፡ባልደረባዬ ፋሲል የኔዓልምም ከአምስተርዳም አስመራ ከቷል። ታሪካዊ ጉዞ ነው፡፡>>ብሏል።
በሚቀጥሉት ቀናት ወይም ሳምንታት ፋሲልና መሳይ በኤርትራ ቆይታቸው ከስፍራው የሚያጠናቅሯቸውን ዘገባዎች በቀጥታ የምናቀርብ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።


ለጥምቀት ሰማያዊ ቲሸርት እንዳይለበስ ተከለከለ

ሰበር ዜና

ለጥምቀት ሰማያዊ ቲሸርት እንዳይለበስ ተከለከለ

• ህዝብን ያነቃቃሉ የተባሉ መንፈሳዊ ጥቅሶች መጠቀም አይቻልም ተብሏል

የክርስትና እምነት ተከታይ ወጣቶች ጥምቀት በዓል ላይ ሰማያዊ ቲሸርቶችን እንዳይለብሱ መከልከላቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን ጀምሮ እስከ ጃንሜዳ አካባቢ የሚኖሩ ወጣቶች በተለያዩ ማህበራት ስር ለጥምቀት በዓል ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኙ የገለጹት ምንጮቹ ከዝግጅታቸው መካከል ቲሸርት አሳትሞ መልበስ አንዱ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ወጣቶቹ ለጥምቀት በዓል የተለያዩ የመጽሀፍ ቅዱስ ጥቅሶች የታተሙበት ሰማያዊ ቲሸርት ማሳተማቸውም ተከትሎም ደህንነትና ሲቪል የለበሱ ፖሊሶች በየ ቤታቸው እየዞሩ ‹‹ጥምቅት በዓል ላይ ሰማያዊ ቲሸርት መልበስ አይቻልም፡፡›› እያሉ እያስጠነቀቁ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በነገው ዕለትም ካድሬዎች ከፈረንሳይ ሌጋሲዮን እስከ ጃን ሜዳ አካባቢ የሚገኙ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር ስብሰባ መጥራታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ህዝብን ያነቃቃሉ ከሚል ስጋት አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በቲሸርት ላይም ሆነ ሌላ ለጥምቀት በዓል ላይ በማድመቂያነት በሚውል ነገር ላይ ማተም እንደማይቻል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ወጣቶቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ለጥምቀት በዓል ማድመቂያነት እንዳይውሉ ከተከለከሉት ጥቅሶች መካከል ‹‹የጌታ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን፣ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚያብሄር ትዘረጋለች፣ የአባቶቻችን ርስት አንሰጥም....›› የመሳሰሉት ይገኙበታል ተብሏል፡፡ እነዚህን መንፈሳዊ ጥቅሶች መጠቀም እንደሚያስቀጣም ደህንነትና ፖሊሶች የበዓሉ አዘጋጅ ወጣቶችን አስጠንቅቀዋል፡፡

ወጣቶቹ ሰማያዊ ቲሸርትም ሆነ የተከለከሉትን መንፈሳዊ ጥቅሶችን በሐይማኖታዊ ፋይዳቸው ምክንያት ባለፉት የጥምቀት በዓላት ላይ ሲጠቀሙባቸው እንደቆዩ፣ አሁን ደህንነቶች እነሱ ካላሰቡት ፖለቲካ ጋር ማገናኘታቸው እንዳሳዘናቸውና ከሐይማኖታዊ ፋይዳቸው ውጭ ምንም አይነት ትርጉም እንዲኖራቸው ታስበው የተሰሩ ባለመሆናቸው በበዓሉ ላይ እንደሚጠቀሙባቸው ገልጸዋል፡፡

ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ

Thursday, January 8, 2015

ወሎ ውስጥ በኦሮሞዎች ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመ ነው ተባለ

ታኀሳስ ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግ፤ ከአማራ ክልል ኦሮሚያ ዞን ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ ታስረው ከስምንት ወራት በላይ ፍርድ ቤት ያልቀረቡ ታሳሪዎችን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ።
ሊጉ የ 26 እስረኞችን ስም ዝርዝር በማያያዝ ባወጣው መግለጫ፤ ከወራት በፊት የአዲስ አበባን አዲስ ማስተር ፕላን በመቃወም ተነስቶ ከነበረው ሰላማዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ የወሎ ኦሮሞዎችን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ እየተፈፀመ ያለው ማዋከብና እስር ሊቆም አለመቻሉን አስታውቋል።
በዚህም የተነሳ አንዳንዶች የት እንደደረሱ ባልታወቀ ሁኔታ መሰወራቸውንና በርካቶች “አጋዚ”ተብሎ በሚጠራው የኮማንዶ አባላት ጥቃት እንደፈፀመባቸው የገለጸው ሊጉ፤ እነዚህ ታጣቂ ሀይሎች በማስተር ፕላኑ ምክንያት ከተነሳው ተቃውሞ ጋር በተያያዘ እስካሁን ድረስ ዜጎችን ከየቦታው ማሰራቸውን አላቆሙም ብሏል።
የሚጠብቃቸውን እስር በመፍራት በመቶዎች የሚቆጠሩ የዩኒቨርሲቲ፣የኮሌጅና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አለመመለሳቸውን በመግለጫው ያወሳው ሊጉ፤ አብዛኞቹ ለህይወታቸው አስጊ ወደሆኑ ወደ ሶማሊዩ ላንድና ወደ ፑንት ላንድ ለመሰደድ መገደዳቸውን ገልጿል።
የጥቃቱ ሰላባ ከሆኑት መካከል በአማራ ክልል የኦሮሚያ ልዩ ዞን ነዋሪ የሆኑ የወሎ ኦሮሞዎች እንደሚገኙበት የጠቆመው የሰብዓዊ መብት ሊጉ፤ ከተቃሞው ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች “የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አባል ናችሁ” ተብለው ያለፍርድ ቤት ማዘዣ መታሰራቸው እና ላለፉት ስምንት ወራት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በወህኒ እየተሰቃዩ እንደሚገኙ አመልክቷል።
እስረኞቹ በአሁኑ ወቅት በደሴ ወህኒ ቤት እንደሚገኙ ያመለከተው የሰብዓዊ መብት ሊጉ፣ ሰብዓዊ መብታቸው እንዲጠበቅላቸውና በሚታሰሩበት ጊዜ የተወሰደባቸው የእጅ ስልካቸውና ገንዘባቸው እንዲመለስላቸው እና ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ እንዲፈቱ ፤ ለጋሸ ሀገሮች፣ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማትና አክቲቪስቶች በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና ያሳድሩ ዘንድ ተማጽኗል።


በጎንደር አርማጭሆ የተቀሰቀሰው ግጭት ሊበርድ አልቻለም

በጎንደር አርማጭሆ የተቀሰቀሰው ግጭት ሊበርድ አልቻለም
ታኀሳስ ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ሳምንት ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያዎች በመታጀብ በጎንደር አርማጭሆ ውስጥ <<ሶረቃ>> የሚባለውን አካባቢ ወደ ትግራይ ለማካለል በወሰዱት እርምጃ የተነሳው ግጭት እስካሁን ሊበርድ እንዳልቻለ በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ያጠናቀረው ሪፖርት ያመለክታል።
ወኪላችን እንዳለው ታጣቂዎቹ፤ አርሶ አደሮችን በኃይልና በማን አለብኝነት አስነስተው ቦታውን ለማካለል ያደረጉትን ጥረት የአካባቢው ህዝብ ከዳር እስከዳር በመንቀሳቀስና ውጊያ ጭምር በመግጠም ነበር ያከሸፈው።በወቅቱ የታጣቂዎቹን እርምጃ ተከትሎ በተቀሰቀሰው ግጭት ከሁለቱም በኩል ጉዳት መድረሱ ታውቋል።
ውጥረቱ እስካሁን ያልበረደ ከመሆኑም ባሻገር የ አካባቢው ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር እየተጠራራ ንብረቱን ለማስጠበቅ በአንድ ተሰባስቦ መዘጋጀቱ፤ ሌላ ዙር የከፋ ግጭት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት አሳደሯል።


በምርጫ ቦርድ እና በአንድነት ፓርቲ መካከል የተፈጠረው ውጥረት እየተካረረ ነው። የአንድነት አመራሮች ለአባሎቻቸው ጥሪ እያቀረቡ ነው።

ታኀሳስ ፳፱(ሃያ ዘጠኖ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የውጥረቱ መካረር ምክንያት የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ዶክተር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር ከቦርዱ ውሳኔ ቀድመው ወደ ድርጅት ሚዲያ በመሄድ ” አንድነትና መኢአድ የውስጥ ችግራቸውን ካልፈቱ በምርጫ ላይሳተፉ ይችላሉ” የሚል መግለጫ መስጠታቸው ነው።
ዶክተር አዲሱ፤ ሁለቱ ፓርቲዎች በህገ- ደንባቸው መሰረት ውስጣዊ ችግራቸውን እንዲፈቱ በቦርዱ ቢነገራቸውም ችግራቸውን አለመፍታታቸውን በመጥቀስ፤ አሁን ባሉበት ሁኔታ በምርጫ ሊሳተፉ እንደማይችሉ ነው ያሳወቁት። “መስመሩን ያልጠበቀ ነው”ያለው የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ መግለጫ ያስቆጣው አንድነት ፓርቲ ትናንት ለኢሳት በሰጠው ምላሽ፤ ፓርቲው ምንም ያልፈታው ችግር እንደሌለ በመጥቀስ፤ ቦርዱ በምርጫው እንዳልሳተፍ ካገደኝ፤ ተመጣጣኝ የሆነ ፖለቲካዊ ውሳኔ ለመወሰን እገደዳለሁ ማለቱ ይታወሳል።

መታረም የሚገባዉ ማነዉ? ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስር ቤት

በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት " "ስህተቶችን" ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች" በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡

የኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደቢሮአችን ተደዉሎ ከኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የተደወለ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ለጽሑፌ ምላሽ የላኩ በመሆኑ በፍጥነነት እንድናወጣዉ ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጠን፡፡

በሰማያዊ አባል ላይ የአቃቤ ህግ ምስክር ተሰማ

•‹‹መንግስትን የሚቃወም ወረቀት ሲበትን ይዘነዋል›› የአቃቤ ህግ ምስክሮች
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ህዳር 27 እና 28/2007 ዓ.ም በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ተዘጋጅቶ ለነበረው የአዳር ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቅስቀሳ በራሪ ወረቅት ሲበትን ለእስር የተዳረገው የሰማያዊ ፓርቲ አባል በፌደራል አቃቤ ህግ ክስ እንደቀረበበት የሚታወስ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ ምስክር ያላቸውን አቅርቦ አስመስክሯል፡፡
ታህሳስ 30/2007 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መናገሻ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት የቀረበው የሰማያዊ ፓርቲ አባል አቶ ሲሳይ ዘርፉ ‹‹…‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ› ለመላው ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ሁሉ….ተብሎ የተጻፈበት በራሪ ወረቀቶች ለህብረተሰቡ ሲያከፋፍል እጅ ከፈንጅ በመያዙ በፈጸመው የሐሰት ወሬን በማውራት ህዝቡን ማነሳሳት ወንጀል…›› በፌደራል አቃቤ ህግ ተከስሶ ጉዳዩን እየተከታተለ እንዳለ ይታወሳል፡፡
በመሆኑም ታህሳስ 30 ቀን 2007 ዓ.ም የአቃቤ ህግ ሁለት ምስክሮች ቀርበው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡ አን

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል – አቶ ኪዳኔ አመነ – የመድረክ ወጣት አመራር

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡ ትርጉም ያለው የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ጥቂት ፓርቲዎች አንድነት አንዱ ነው፡፡ እናም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ና እውነተኛ ፍትህ ለማምጣት የአንድነት መኖር ከፍተኛ ትርጉም አለው፡፡ ፓርቲው የአንድነት ፓርቲ አባላትና የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሣይሆን የራሳችን አቋምና መስመር ይዘን በሌላ ፓርቲ ያለን ሰዎች እንኳ አንድነት እንዲኖር አጥብቀን እንፈልጋለን፡፡ ወደፊት አንድነትም እኛም ቤታችን እያፅዳን መንገድ ላይ መገናኘት አለብን፡፡

ያኔ ብቻ ነው ኢትዮጵያን የምናድናት፡፡ እንዳንራመድ ቀይዶ የያዘን ገመድ እየበጣጠስን፤ ፀረ-ለውጥና አድሃሪ አቋምን እየመከትንና እያፀዳን የዴሞክራሲ እና የሉዓላዊነት ፍለጋው ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል ፡፡ አንድነቶች አሁን ነው የፖለቲካ ፅናታቸው በጥበብ ማሳየት ያለባቸው፡፡ ወንድሞቻችን በርቱ!!!


“አሜሪካ በየቀኑ እየቀጠቀጠን በመሆኑ ብንችል ቪኦኤን ድምጥማጡን እናጠፋው ነበር” ሲሉ የብአዴን ዋና ጻሃፊ ተናገሩ

ታኀሳስ ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብአዴን ዋና ጸሃፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን ይህን የተናገሩት መጪውን ምርጫ አስመልክቶ ለተመረጡ የብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና ለባለድርሻ አካላት ባደረጉት ገለጻ ነው።
አቶ አለምነው ነጻ ሚዲያ በሌለበት አገር ኢሳትና ቪኦኤን የመሳሰሉ ነጻ ሚዲያዎችን ማፈን ተገቢ ነወይ የሚል የጽሁፍ ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን፣ ቪኦኤ በአሜሪካ መንግስት ሳንባ የሚተነፍስ ነው ፣ የአሜሪካ መንግስት አላማ ደግሞ የሊበራሊዝም አላማ ነው በዚህም የነተሳ የኢትዮጵያን መንግስት ሌት ከቀን እየቀጠቀጠው ነው ብለዋል። የውጭ ባለሃብቶች መጥተው የኢትዮጵያን ባንክ መምጠጥ ይፈልጋሉ ያሉት አቶ አለምነው፣ ቴሌም በውጭ ቱጃሮች እንዲያዝ ይፈልጋሉ ሲሉ አብራርተዋል። ቴሌ ማለት ገንዘብ የሚያመርት ማሽን ነው የሚሉት አቶ አለምነው፣ ደርጅቱ በየአመቱ 6 ቢሊዮን ብር ለአባይ ግድብ ድጋፍ እንደሚያደርግና የአባይ ግድብም በቴሌ ትርፍ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። ታዲያ ይህን ነው አሜሪካኖች ሊቀሙን የሚፍለጉት ሲሉ ለተሰብሳቢው አስረድተዋል። እነዚህ ሚዲያዎች ቢችሉ ምድር እንዲገለባብጥ ፣ አገሪቱ የተኩስ አገር እንድትሆን ይፈልጋሉ ያሉት አቶ አለምነው ፣ አቅም ስለሌለ ነው እንጅ አቅም ቢፈቅድማ ድምጥማጣታቸውን ማጠፋት ነበር ብለዋል።



Wednesday, January 7, 2015

Ethiopia: Ex-Mayor Arkebe’s Brother to Assume Top Position At ERA - Ethiopian Roads Authority

By Fasika Tadesse Fortune Staff WriterPosition had been vacant for two months after Prime Minister’s office removed Ziad WoldegebrielPrime Minster Hailemariam Dessalegn is considering to assign Getachew Equbay brother of Arkebe Equbay as director general of the Ethiopian Roads Authority (ERA) replacing the former director general Zaid Woldegebriel.Getcahew had been general manager of Mesfin Industrial Engineering Plc (MIE) for a couple of years. And he had also been general manager of Messebo Cement Factory Plc. Both companies Getcahew worked for are affiliates of the Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT), a group of companies established by Tigray People’s Liberation Front (TPLF).

የማለዳ ወግ … ሰሚ እስኪገኝ እያነባን እንጮሃለን ! – ነቢዩ ሲራክ

የማለዳ ወግ … አፈ ጉባኤ አባ ዱላ …ግን ለምን አልሰሙንም ?* የኮንትራት ሰራተኛዋ አይነ ብርሃኗን ማጣትና የስም የለሿ ሟች እህት መጨረሻ   !
*  ሰሚ እስኪገኝ እንጮሃለን  !

  ታህሳስ 27 ቀን 2007 ዓም ሰኞ በማለዳው ያገኘኋቸው ሁለት መረጃዎች የወጡት በሁለቱ አንጋፋ የሳውዲ ጋዜጦች በአረብ ኒውስ Arab News  እና በሳውዲ ጋዜት Saudi Gazette  ነው ። በአንዱን አይቸ ቢከፋኝ ፣  መፍትሔ ላይገኝ ይህን መርዶ ከንፈር ለማመስመጠጥ  ብቻ መረጃ ብየ ልለጥፍ ይሆን ?  እያልኩ ከራሴ ጋር ሙግት ገጥሜ ነፍሴን ሳስጨንቀት በሌላኛው ጋዜጣ የወጣውን ሌላ መረጃ አንድ ወዳጀ በጓዳው የመልዕክት መሰረጫ እንደኔው ማልዶ ያጋጠመውን የወገን መከራ አደረሰኝ ። ሁለቱንም አሳዛኝ መረጃዎች ተመለከትኳቸው ፣ ያማል ብቻ ተብሎ የሚታለፍ አይደለም  !

የኢሳት ጋዜጠኞች መሳይ መኮንን እና ፋሲል የኔዓለም አስመራ ገቡ

ከኢሳት እንደተገኘው መረጃ ከሆነ ጋዜጠኞቹ አስመራ የገቡት ትናንት ሲሆን በኤርትራ ቆይታቸውም እዚያ ያለውን ሃይል እንደሚጎበኙና ዘገባም እንደሚያቀርቡ በተጨማሪም የኤርትራ ባለስልጣናትን እንደሚያነጋግሩ ይጠቁማል::

የቀድሞው የጀርመን ድምጽ ጋዜጠኛና የአሁኑ የኢሳት ራድዮ ከፍተኛ አዘጋጅ መሳይ መኮንን; እንዲሁም የቀድሞው የአዲስ ዜና ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የአሁኑ የኢሳት ቲቭ ኤዲተር ፋሲል የኔዓለም በአስመራ ለስንት ጊዜያት እንደሚቆዩ እስካሁን የተገኘ መረጃ የለም::


ኮማንደር ቢኒያም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን በድቅድቅ ጨለማ ብርድ ላይ እያስተኛው በማሰቃየት ላይ ነው

ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ማን እንደሚመራት በማይታወቅባት ሁኔታ አንድ ደህንነት ወይም ወታደር የፈለገውን የማዘዝ ስልጣን ያለው ሲሆን እንገዛለታለን የሚሉትን ህገመንግስት ወደ ጎን በመተው የፈለጋቸውን እርምጃ እየወሰዱ በመሆኑ በስር ዓቱ ውስጥ ያለውን አለመደማመጥ ያሳያል የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች በቅርቡ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን በአንድ ደህንነት ት ዕዛዝ ብቻ ለ3 ሳምንታት ከሃገር እንዳይወጣ ፓስፖርቱን መቀማቱን ያስታውሳሉ።

በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ በዝዋይ እስር ቤት እየደረሰ ያለው ስቃይ ኮማንደር ቢኒያም በሚባል አዛዥ ሲሆን ተመስገንን በአንድ ምሽት ከ5 ጊዜ በላይ በድቅድቅ ለሊት በማስወጣት ብርድ ላይ እንደሚያስተኙት ከስፍራው የደረሰው መርጃ ያጋልጣል።

በተለይ ተመስገን ደሳለኝ “የመንግስት ገመና” በሚል ከእስር ቤት ከፃፈ በኋላ ደህነነቶች እና ይኸው ኮማንደር ቢኒያም የሚባል አዛዥ የእንግልሃለን ሬሳህን እዚህ ብንጠለው ዞር ብሎ የሚያይህ የለም በሚል እንደሚያስፈራሩት የጠቆሙት የዜና ምንጮቻችን ድብደባ እንደተፈጸመበትም ታውቋል።

ኢትዮጵያ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ግለሰቦች የሚያዙባት፤ በአንድ ግለሰብ ትዕዛዝም ሕይወት የሚጠፋባትና የሚበላሽባት ሃገር እየሆነች መምጣቱ የስርዓቱን ደጋፊዎች ሳይቀር እያስቆጣ እንደሚገኝ ከተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ባቀረበው ይግባኝ ላይ ክርክር አደረገ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በጠበቃው በአቶ አምሐ መኮንን አማካይነት፣ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበው ይግባኝ ላይ ክርክሩን አደረገ፡፡ ክርክሩን የተከታተለው የተወሰነበትን የሦስት ዓመታት የእስራት ቅጣት እየፈጸመ ባለበት በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ነው፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በከሳሽ ዓቃቤ ሕግ ቀርቦበት የነበረው ክስ፣ እሱ የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሲሠራ በጋዜጣው በቅጽ 5 ቁጥር 177፣ ቅጽ 04 ቁጥር 149፣ ቅጽ 04 ቁጥር 146፣ ቅጽ 5 ቁጥር 166 እና በቅጽ 5 ቁጥር 197 ዕትም ላይ፣ በራሱና በሌሎች ሰዎች አመንጭነት የተጻፉ ጽሑፎችን አትሞ አውጥቷል፡፡ በመሆኑም ሕዝቡ፣ ‹‹በመንግሥትና በሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ላይ እንዲያምፅ ቀስቅሷል፤ መንግሥትን በሐሰት ወንጅሏል፤ ስሙንም አጥፍቷል፤ የሐሰት ወሬዎችን በመዘገብና ለሕዝቡ በማሰራጨት የሕዝብን አስተሳሰብ እንዲናወጥ አድርጓል፤›› በሚል በቀረቡበት ሦስት ክሶች ከአሳታሚው ማስተዋል የኅትመትና ማስታወቂያ ሥራ ድርጅት ጋር ጥፋተኛ ተብለው ቅጣት ተወስኖባቸዋል፡፡ ተመስገን ሦስት ዓመት እስራትና ድርጅቱ 10,000 ብር ተቀጥተዋል፡፡

ከሬዲዮና ከቴሌቪዥን በተጨማሪ ድረገፆችን ለመቆጣጠር አዲስ ህግ ተዘጋጀ

በኢንተርኔት የሚሰራጩ ፅሁፎችን፣ ምስሎችንና ቪዲዮዎችን ለመቆጣጠር ታስቧል
የግል የሬዲዮ ጣቢያዎች ፈርሰው ከመንግስት ቻናል እንዲከራዩ ለማድረግ ታቅዷል

የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስርጭቶችን ለመቆጣጠር ከስምንት ዓመት በፊት በታወጀው ህግ ላይ አዳዲስ ቁጥጥሮችን የሚጨምርና እንዲሁም የኢንተርኔት ስርጭቶችንና ድረገፆችን የሚያካትት ህግ ተዘጋጀ፡፡
ከተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋር ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ውይይት የተካሄደበት ረቂቅ ህግ፣ ነባሩ አዋጅ ውስጥ የሰፈሩ የባለቤትነትና የፈቃድ አሰጣጥ ቁጥጥሮችን የሚዘረዝር ሲሆን፤ በኩባንያ መልክ እንጂ በግለሰብ የሬዲዮ ወይም የቴሌቪዥን ድርጅት ማቋቋም እንደማይቻል ይጠቅሳል፡፡ የዝምድና ወይም የጋብቻ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች ለብቻቸው ባለአክሲዮን የሆኑበት ኩባንያ ፈቃድ እንደማይገኝም ተደንግጓል፡፡
ምንም እንኳ እስከዛሬ ተግባራዊ ባይሆንም በ1999 ዓ.ም በወጣው ህግ፣ የግል የቴሌቪዥን ጣቢያ ለማቋቋም ፈቃድ እንደሚሰጥ ተገልፆ የነበረ ሲሆን፤ አሁን በተረቀቀው ህግ ግን የቴሌቪዥን ጣቢያ በግል ማቋቋም እንደማይቻል ይደነግጋል፡፡
መንግስት የቴሌቪዥን ማሰራጫ ኔትዎርክ እንደሚዘረጋ የሚገልፀው ይሄው አዲስ አዋጅ፤ የግል ኩባንያዎች ከመንግስት ቻናል እየተከራዩ ለመስራት ማመልከትና ፈቃድ መጠየቅ ይችላሉ ይላል፡፡
የግል ኩባንያዎች ለጊዜው የራሳቸው የሬዲዮ ጣቢያ ለማቋቋም ፈቃድ የሚያገኙበት እድል ሊኖር እንደሚችል አዲሱ ህግ ይጠቁማል፡፡

ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን!!!

በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የፌደራል ፓሊስ በእሁድ ታህሣሥ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ በግፍ እስር ላይ የሚገኘውን የግንቦት 7 ዋና ፀሐፊን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አቅርቦት ነበር። ይህ የ10 ደቂቃዎች ምስል ለቁጥር በሚያታክት ብዛት ተቆራርጦ የተቀጣጠለ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው ምን ተጠይቆ ምን እንደመለሰ ማወቅ አይቻልም። ስለሆነም በንግግሩ ይዘት ላይ አስተያየት መስጠት ይናገረው አይናገረው በአልታወቀ ጉዳይ ማብራሪያ መስጠት ይሆናል።  ስለዚህም፣ በንግግሩ ይዘት ላይ ጊዜ ከማጥፋት ህወሓት አንዳርጋቸው ጽጌን አሁን ማቅረብ ለምን እንደፈለገ መተንተን ይበልጥ ጠቀሜታ  አለው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል።አሁን ህወሓት በውስጥም በውጭም ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባበት ጊዜ ነው፤ በራሱ በድርጅቱ ውስጥም ሰላም የለም።

Tuesday, January 6, 2015

የምርጫ ቦርድ ምክትል ሃላፊ አንድነትን እና መኢአድ በምርጫው መሳተፍ እንደማይችሉ ገለጹ

የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ፣ አንድነት እና መኢአድ በምርጫ እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ለፋና ራዲዮ ገለጹ። የአንድነት አመራሮች ወደ ምርጫ ቦርድ ሄደው የምርጫ ቦርድን ዉሳኔ በጠየቁ ጊዜ ቦርዱ ነገ ማክሰኞ እንደሚሰበሰብና ቦርዱ እንደሚወስን ቢነገራቸውም፣ ቦርዱ ሳይሰበሰብ ምክትል ሃላፊው፣ ቀደመው በራዲዮ፣ የመኢአድ እና የአንድነት ፓርቲ እንደይሳተፉ መግለጻቸው፣ ከወዲሁ በሕወሃት ማእከላዊ ኮሚቴ የተወሰነና ተግባራዊ የሚሆነው ይሄ ዉሳኔ ይሆናል በሚል እንደሆነ ተንታኞች ይናገራሉ።
አንድነት ፓርቲ ከሶማሌ ክልል በስተቀር በሁሉም ክልሎች፣ ቢያንስ ከ480 ወረዳዎች በላይ ተወዳዳሪዎች ለማሰለፍ የተዘጋጀ በጥንካሬ ከአገዛዙ ጋር መፎካከር የሚችል ብቸኛ ድርጅት እንደሆነ ይታወቃል። አንድነት በዚህ ሳምንት ዉስጥ ብቻ በደሴና በመቀሌ ህዝባዊ ስብሰባዎች በባህር ዳር ሰላማዊ ሰልፍ ለማዘጋጀት እየሰራ የነበረ ድርጅት ሲሆን፣ አገዛዙ ሜዲያውን ቢዘጋም የማተሚያ ማሽን ገዝቶ፣ ሁለት ጋዜጦችን እያተመ ለህዝብ የሚያደርስ ድርጅት ነው።ከአንድነት ቀጥሎ ጠንካራ የሚባለውንና በብዙ ቦታዎች መዋቅር ያለው ሌላው ሁለተኛ ድርጅት መኢአድ እንደሆነ ይታወቃል።በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው ከፍተኛ የአንድነት አመራር፣ የቦርዱን ኦፌሳላዊ ዉሳኔ ነገ ከተሰማ በኋላ ምክክር ተደርጎ ምን መደረግ እንዳለበት ለሕዝብ እንደሚያሳወቁ ገልጸዋል። ምናልባትም የምርጫ ቦርድ ምክትል ሃላፊው ሆን ብለው ለማደናገር ብለው የተናገሩት ሊሆን እንደሚችል የገለጹት እኝሁ አመራር፣ ምርጫውን አትሳተፉም ቢሉም አንድነት ሰላማዊ ትግሉን እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ ዝዋይ የታሰሩ 16 የፖለቲካ እስረኞች ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ

• የሰማያዊ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ባልደረባ እንዳይጠይቁ ተከልክለዋልበነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተርጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ በዝዋይ የፌደራል ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙ 16 የፖለቲካ እስረኞች ባልታወቀ ምክንያት ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ፡፡ዛሬ ታህሳስ 28/2007 ዓ.ም የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ም/ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ የገናን ዋዜማ ዝዋይ ከሚገኙ እስረኞቹ ጋር ለማሳለፍ ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ዝዋይ አቅንተው የነበር ቢሆንም ሊጠይቋቸው ያስጠሯቸው የፖለቲካ እስረኞች ‹‹በማንኛውም አይነት ሰው መጠየቅ አይችሉም፡፡ ምግብም አይገባላቸውም፡፡›› ተብለው ሳይጠይቁ ለመመለስ ተገደዋል፡፡ጠያቂዎቹ ‹‹የመጠየቅ መብት አለን›› በሚል ወደ ውስጥ ለመግባት ግፊት በማድረጋቸው ፖሊሶች ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ አበበ ቀስቶ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ ጄኔራል አሳምነው ጽጌና ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጨምሮ ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው የተከለከሉትን የ16 የፖለቲካ እስረኞችን ስም ዝርዝር አሳይተዋቸዋል፡፡የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ባልደረባ ለእስረኞቹ ምግብና ጠያቂ እንዳይገባ የተከለከለበትን ምክንያት ለማጣራት ቢሞክሩም ፖሊሶች ‹‹የሚጣራ ነገር ስላለ ነው፡፡ እሱ እየተጣራ ነው፡፡›› ከማለት ውጭ ምክንያቱን በግልጽ ሊነግሯቸው አልቻሉም፡፡ክልከላው እስከመቼ እንደሚቆይ በውል የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን ከአዲስ አበባ ተነስቶ የገናን በዓል ዋዜማ ከእስረኞቹ ጋር ለማሳለፍ ወደ ዝዋይ ካቀናው የሰማያዊ ፓርቲ ልዑክ በተጨማሪ የእስረኞቹ ቤተሰቦችም በክልከላው ምክንያት ሳይጠይቁና ምግብ ሳያስገቡ ተመልሰዋለል፡፡

የወልቃይትን መሬት በተመለከተ በብአዴን አመራሮች መካከል አለመግባባት ተፈጥሯል

ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ የአማራ ህዝብ መሬት በግፍ እየተቀማ ለትግራይ ነዋሪዎች ከትግራይ ህዝብም ለህወሀት ደጋፊዎች መከፋፈሉ ይታወሳል ይህንን ተከትሎ ላለፉት በርካታ አመታት የራያ፣ የሁመራ እና የወልቃይት ህዝብ ለስደት እና ለጥፋት የተዳረገ ሲሆን ከሰሞኑም የትግራይ ክልልን ለማስፋፋት በተደረገው ጥረት ተቃውሞ ያሰሙ የክልሉ ነዋሪዎች ለድብደባ እና ለእስር መዳረጋቸውን ተከትሎ የአካባቢውን ህዝብ ለማነጋገር ወደስፍራው አቅንተው የነበሩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፍተኛ ተቃውሞ ድርሶባቸው ወደባህርዳር መመለሳቸውን ተከትሎ በዛሬው እለት ከፍተኛ የብአዴን አመራሮች እና የክልሉ ባለስልጣናት በጉዳዩ ላይ ለመወያየት ከቀኑ 4 ሰዓት ጀምሮ ባህር ዳር የክልሉ መስተዳደር የስብሰባ አዳራሽ ተገኝተው የነበረ ቢሆንም ስብሰባው ባለመስማማት እስከ 6፡30 ከተካሄደ በኋላ ተሰብሳቢው የተባለው መሬት የአማራ መሬት ነው የሚል አዝማሚያ በማሳየቱ ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ የገቡት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከምሳ በኋላ ስብሰባው ሲጀመር ከፌዴራል መንግስት መመሪያ መምጣቱን ተናግረው የሚቀጥለው ቅዳሜ ጥር 2 በአቶ አዲሱ ለገሰ እና በአቶ በረከት ስምኦን ሰብሳቢነት ስብሰባው ከእንደገና እንደሚካሄድ ተናግረው ስብሰባውን በትነውታል።

ይህንን ዜና ከባህር ዳር ያደረሰኝ ግለሰብ እንዳረጋገጠልኝ ከሆነ የወልቃይት መሬት ጉዳይ የክልሉን ካድሬ ቁጭት ውስጥ እንደከተተው የታወቀ ሲሆን ቅዳሜ የሚፈጠረውን ጉዳይ ለመገመት አስቸጋሪ መሆኑን ጨምሮ ገልጿል።


Monday, January 5, 2015

ጦማሪያኑ እና ጋዜጠኞቹ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው

በዛሬው እለት በልደት ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው፡፡

ችሎቱ በዛሬው እለት ተሰይሞ የነበረው ጦማሪያኑ እና ጋዜጠኞቹ ታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም ክስሳቸውን በማስመልከት ባቀረቡት አስተያየት ላይ አቃቤ ህጉ ክሱን አሻሽሎ እንዲቀርብ በተወሰነው መሰረት የነበረ ቢሆንም ዛሬ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በተሰየመው ችሎት ላይ አቃቤ ህጉ ክሱን አሻሽሎ ባለመቅረቡ ፍርድ ቤቱ ለጥር 6 ቀን 2007 ዓ.ም አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ እንዲቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ጦማሪያኑ እና ጋዜጠኞች ላለፉት ዘጠኝ ወራት በእስር ላይ መሆናቸው ይታወቃል፡፡


አንድ የአየር ሃይል አብራሪ ተቃዋሚዎችን መቀላቀሉ ተሰማ 

አንድ የአየር ሃይል አብራሪ ተቃዋሚዎችን መቀላቀሉ ተሰማ ባለፈው ረቡዕ ታህሳስ 15፣ 2007 ዓም ኢሳት 4 የአየር ሃይል አብራሪዎች ወደ ኬንያ ማምራታቸውን በሰበር ዜና ካቀረበ በሁዋላ፣ አንድ ተጨማሪ የአየር ሃይል ባልደረባ ጠፍቶ ተቃዋሚዎችን መቀላለቀሉ ተሰምቷል። ባለፈው ሮብ የጠፉት የሚግ 23 አብራሪ ሻምበል ገዛሃኝ ደረሰ፣ የኤም አይ 35 ተዋጊ ሄሊኮፕተር አብራሪ ሻምበል ዳንኤል ግርማ፣ የኤም አይ 35 ተዋጊ ሄሊኮፕተር አብራሪ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጠ፣ የኤም አይ 35 ተዋጊ ሄሊኮፕተር ብሩክ አጥናኤ በአጥሩ የደህንነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።

ከኢትዮጵያ ህዝብ ኣርበኞች ግንባር ዘብ እና የኢትዮጵያ ኣርበኞች ኣንድነት ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ

ጀግናው የኢትዮጵያ ህዝብ ከወራሪ ሃይሎች ጋር ተፋልሞ ድል ያስመዘገበው ለነጻነቱ በሚሰጠው ከፍተኛ ዋጋ ምክንያት ነው። የዚህ ታላቅ ህዝብ ተጋድሎ ለኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ኣፍሪካ ህዝብ የነጻነት ፋና ወጊ ሆኗል።

ይህ ለነጻነት የተከፈለ ትግልና ዉጤቱ እንዲሁ በቀላል ነገር የመጣ ኣልነበረም። ሁሉም የኢትዮጵያዊያን ልጆች ዘር ሃይማኖት ብሄር ቀለም ሳይለዩ ባንዲት ባንዲራና ባንዲት እናት ኣገር ኢትዮጵያ ስም ተሰባስበው ኣንድ ልብ ኣንድ ኣላማ ይዘው ስለታገሉ እንጅ። በዚህ ምክንያትም የኣገራችን መላው ህዝብ በየትኛዉም ቦታ እራሳቸዉን ቀና ኣድርገው የሚሄዱ ነበሩ። በኣሁኑ ወቅት ግን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከመቸዉም ጊዜ በከፋ ሁኔታ የነጻነት እጦት ዉስጥ ተዘፍቆ ይገኛል። ያ ነጻነት የለመደ ህዝብ !ያ ተባብሮ በሰላም መኖር ልማዱና ባህሉ ያደረገ ኩሩ ህዝብ! ዛሬ ግን በነጻነት እጦት ስር ወድቆ ከኣኩሪ ታሪኩ ጋር ወደታች እየሰጠመ ይገኛል። ወያኔ ኢህኣዴግ በዘራው መርዝ ምክንያት እርስ በርሱ ተለያይቶና ተፈራርቶ እንደጠላት እየተያየ ይገኛል።

Sunday, January 4, 2015

አማራ ፎርስ በሰሞኑ በወልቃይት ጠገዴና አርማጭሆ ስላለው ሁኔታ መግለጫ አወጣ ።

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ታጋዮች ከወልቃይት ጠገዴና አርማጭሆ ህዝብ ጎን በመሰለፍ በዘረኛውን ናዚ ወያኔ መከላከያና ከትግራይ ተስፋፊ ታጣቂዎች ጋር ከባድ ውጊያ አያካሄደ ይገኛል።አዴሃን ከኤርትራ/ሻቢያ/ ምድር ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለውጤት የሚያበቃውን የአደረጃጀት ስልት በመንደፍ /በመቀየስ/ ወደ ተጨባጭ ስራ መግባቱን ይፋ ማድረጋችን ይታወሳል።
አዴሃን በሁሉም የአገራችን አካባቢዎች የሚያደርገው እንቅስቃሴ እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም የወያኔ ስርአት አረመኔያዊ አገዛዝ ግፊት ቀማሽ ለሆነው ከወልቃይት ጠገዴና አርማጭሆ አካባቢ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተንቀሳቀሰን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም ህውሃት በወረራ የያዛቸውን የወልቃይት ጠገዴና የአርማጭሆ ሰፋፊ ለም መሬቶችን አስተማማኝ ለማድረግ እና አዳዲስ መሬቶችን ለመያዝ የነደፈውን እስትራቴጂ ተግባራዊ ሊያደርግ እየተዘጋጀ መሆኑንና ታላቋን ትግራይ ለማስፋት ባለው ህልም መሰረት ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን August 19 – 2014 ” ህወሃት በወልቃይትና ጠገዴ ህዝብ ላይ ተጨማሪ የዘር /ማጽዳት/ፍጅት ለማካሄድ እየተዘጋጀ ነው።” በሚል ርዕስ መረጃዎችን ይፋ አድርገን ነበር።

ስንቴ፣ በስንቱ እንታለላለን? -ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

ከብዙ ዓመታት በፊት ሪፖርተር ጋዜጣ የኢሳይያስ አፈወርቂና የድርጅቱ አቀንቃኝ ነበረ፤ ዛሬ ከሌሎች ብዙዎች ጋር በመቃብር ውስጥ ያለው የመጀመሪያው የሪፖርተር መጽሔት በሙሉ ውዳሴ ኢሳይያስ አፈወርቂ ነበር፤ የሞተው መለስ ዜናዊ እያለ የሪፖርተር መጽሔት ኢሳይያስን በመጀመሪያ እትሙ ሲያወድስ ነበር፤ በቅርቡ ደግሞ ደፋሩ የወያኔ አባት ስብሐት ነጋ ለኤርትራ ያለውን ልዩ ፍቅር በሚያስገርም ሁኔታ ገልጾ ነበር፤ ለኤርትራ ቆመን እንዋጋለን አስከማለት ደርሶ ነበር፤ መለስ ዜናዊ በልዩ ጥበቡ መጀመሪያ ኤርትራን ባዕድ አደረገ፤ ቀጥሎም ጠላት አደረገ፤ ክፉ ጦርነት ተደረገ፤ በጦርነቱ ያሸነፈ የለም፤ በፍርድ ግን ኤርትራ አሸነፈች ተባለ፤ ፍርዱ ዋጋ-ቢስ ቦሆንም!

Saturday, January 3, 2015

አርማጮ በአማራ ንቅናቄ ሰራዊት እና በወያኔ ሰራዊት በውጊያ ተወጥራለች

በአርማጮ አከባቢ በአማራ ንቅናቄ ሰራዊት እና በወያኔ ሰራዊት መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑን የንቅናቄው ምንጮች ከአከባቢው አስታወቁ። የህዝቡ ተሳትፎ በከፍተኛ ደረጃ እየታየ ባለበት እና ህዝቡ እና የንቅናቄው ወታደሮች በመቀናጀት ዱር ቤቴ ብለው ወደ ጫካ መግባታቸው ሲታወቅ በመተማ ሸዲ አከባቢ በትላንትናው እለት በወያኔው ጦር ላይ ጥቃት አድርሶ ወደቦታው የተመለሰው የአማራ ንቅናቄ ሰራዊት ከሕዝቡ ጋር በመተባበር እጅግ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እንደማረከ ምንጮቹ ተናግረዋል።

ካለፈው አርብ ጀምሮ የተነሳው ውጊያ በአሁን ወቅት ቀጥሎ ያለ ሲሆን በዛሬው ለሊት ከፍተኛ የቶክስ እሩምታዎች እና የከባድ መሳሪያ ድምጾች በአከባቢው እየተሰሙ መሆኑ ታውቋል። በአብድራፊ አብሃጂራ ሶረቃ ግጨው ማርዘነብ ማይጸማር ሃሙስ ገበያ ዳንሻ ማይካድራ እና አከባቢው ጦርነቱ ይስፋፋባቸዋል የሚል ከፍተኛ ስጋት ስላደረ በአከባቢው የወያኔ ሰራዊቶች በብዛት መስፈራቸው ሲታወቅ አዳዲስ ታንኮችን የጫኑ ከባባድ መኪኖች በቦታው ደርሰዋል። እንዲሁን ወደ ሱዳን ክልል ዘልቀው የገቡ እና ከሱዳን ወታደሮች ጋር አሰሳ የሚያደርጉ ወያኔዎችን እንዳጠቁ የአማራው ንቅናቄ ወታደሮች ተናግረዋል
በአርማጮ እና አከባቢው የተከሰተውን ግጭት በተመለከተ የአማራ ንቅናቄ ሰራዊት መግለጫ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ምኒሊክ ሳልሳዊ


Friday, January 2, 2015

በድሬዳዋ የአየር ሃይል ምድብ ሲካሄድ የነበረው የ3 ቀናት ግምገማ ሃሙስ እለት ተጠናቋል።

ታኀሳስ ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አራት ከፍተኛ ማእረግ ያላቸው የአየር ሃይል አብራሪዎች መጥፋታቸውን ተከትሎ በድሬዳዋ የአየር ሃይል ምድብ ሲካሄድ የነበረው የ3 ቀናት ግምገማ ሃሙስ እለት ተጠናቋል።
በግምገማው ላይ አብራሪዎች፣ አሰልጣኞች፣ ቴክኒሻኖችና ሰራተኞች የተገኙ ሲሆን፣ ሰራተኞቹ ስለጠፉት አብሪዎች የተሰማቸውን ስሜት እንዲናገሩ፣ የሚያውቁትን ሚስጢር እንዲያወጡ ሲገደዱ ሰንብተዋል። ብዙዎች ” ስለጠፉት አብራሪዎች ምን ትላላለችሁ?’ እየተባሉ ሃሳባቸውን እንዲናገሩ የተጠየቁ ሲሆን፣ በሚሰጡት ሃሳብ ተንተርሶ የደህንነት ሃይሎች ተጨማሪ ምርምራ እንደሚያካሂዱ በግምገማው ላይ የተሳተፉ ወገኖች ገልጸዋል።
በግመገማው ላይ የተገኙት አዛዦች በሙሉ እጅግ ተናደው መሰንበታቸውን የሚናገሩት ምንጮች፣ በግቢው ውስጥ ያለው ድባብ ውጥረት የበዛበት በመሆኑ ሰራተኞች ተረጋግተው ስራቸውን ለመስራት አልቻሉም። የእርስ በርስ ጥርጣሬውና አለመተማመኑ የከፋ ደረጃ ላይ መድረሱንም ሰራተኞች ገልጸዋል።
በዚህ ሳምንት ስርአቱን አናገለግልም ብለው ወደ ኬንያ የተሰደዱትን አብራሪዎች በተመለከተ ኢሳት ለወደፊቱ ዝርዝር መረጃዎችን እንደሚያቀርብ ለመግለጽ ይወዳል።


መላው ኢትዮጵያዊ አጋርነቱን የሚያሳይበት ሰዓት ላይ ደርሰናል!!! (የደብረ ማርቆስ ተማሪዎች የለኮሱት የለውጥ ችቦ)

የኢህአዲግ መንግስት 11ኛው ሰዓት ላይ የደረሰ ይመስላል፡፡ ካድሬዎቹ በመላው ሀገሪቱ የሚይዙት የሚጨብጡትን አጥተው፤ደም እንዳሰከረው ሰው መቅበዝበዙን ተያይዘውታል፡፡ ገሚሶቹ ካድሬዎች ከስርአቱ ሸርተት ማለት ጀምረዋል፤በህዝብ ላይ ለሰሩት ግፍም ማጣፊያ ይሆናቸው ዘንድ የስርአቱን ብልት ደህና አርገው እየተለተሉት ነው፡፡ …..በዚህ ሰዓት ኢህአዲግ ወዴት እንደሚገባ፣ምን እንደሚያደርግ ሁሉ አያውቅም፡፡ በየአቅጣጫው የሚነሱ ተቃውሞዎችና ለውጥ ለውጥ የሚሉ ድምፆች ተበራክተውበታል፤እንቅልፍ ነስቶታል፡፡ ስለዚህ በደመነፍስ የሚያደርገው ድርጊት፤በህብረትካልመከትነውና ካላስቆምነው፤ ጥቂቶችን ተጎጂ ማድረጉ የማይቀር ነውና የአንዱ መነካት የሌላውም ነውና ሁላችንም በጋራ በመነሳት የስርአቱን ውድቀት በይፋ እናብስርለት፡፡

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ ለታህሳስ 30 ተቀጠረ * ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ችሎቱን ተከታትሏል

(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ያስገባው የይግባኝ ጥያቄን ለመስመት ስድስት ኪሎ የሚገኘው ፍርድ ቤት ተሰይሞ የነበረ ሲሆን ጉዳዩን ተመስገን እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ተከታትሏል::

ከ’ፍሪ ተመስገን ደሳለኝ” የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ዛሬ ታህሳስ 23/2007 ጠቅላይ ፍረድቤት በዋለው ችሎት የጋዜጠኝ ተመስገን ደሳለኝን ይግባኝ ከሰማ በኋላ ጉዳዩ ለይግባኝ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለመወሰን ለታህሳስ 30/2007 ዓ.ም ቀጥሮ ሰቷል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ችሎቱን የተከታተለው ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ነው::


ምእራባዊያን ኢህአዴግን ከተቃዋሚዎች ጋር ለማቀራረብ ላይ ታች እያሉ ነው

ታኀሳስ ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ችግር እየከፋ መሄዱ ለህዝባዊ አመጽ በር ሊከፍት ይችላል የሚል ስጋት ያደረባቸው ምእራባዊያን በአሜሪካ ፊት አውራሪነት በአገር ውስጥና በውጭ ያሉትን ተቃዋሚዎች ከኢህአዴግ ጋር ለማቀራረብ እየተሯሯጡ መሆኑን የዲፕሎማቲክ ምንጮች ገለጹ።
እንደምንጮች ገለጻ በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ከሚታገሉት ድርጅቶች ውስጥ አንዳንዶችን በማካተት፣ በውጭ ከሚገኙ ገዢውን መንግስት በሃይል እናንበረክካለን ከሚሉ ወገኖች ጋር ለማቀራረብ አሜሪካውያን የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችን እያነጋገሩ ሲሆን፣ ኖርዌይ ውይይቱን ለማዘጋጀት እየተንቀሳቀሰች ነው።
ኢህአዴግ በድርድሩ ላይ ለመገኘት ፈቃደኝነቱን መግለጹ የተነገረ ሲሆን፣ በተቃዋሚዎች በኩል ግን አንዳንዶች ለውይይት ለመቀመጥ ፈቃደኝነታቸውን ሲገለጹ ሌሎች ግን እያንገራገሩ ነው።
ምርጫውን ተከትሎ ህዝባዊ አመጽ ቢነሳ ኢህአዴግ ሊወድቅ ይቻላል የሚል ስጋት የገባቸው ምእራባውያን፣ ምናልባትም ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች የተወሰኑ መቀመጫዎችን በመልቀቅ ውጥረቱ እንዲበርድ ሊያደርግ ይችላል የሚል እምነት ይዘዋል።
የአውሮፓ ህብረት ከሁለት ምርጫዎች በሁዋላ የኢትዮጵያን ምርጫ እንደማይታዘብ ባስታወቀ ማግስት የተጀመረው የአሜሪካ እና የኖርዌይ ጥረት ይሳካ አይሳካ ለወደፊቱ የሚታይ ነው። በጉዳዩ ዙሪያ የኖረዌይና የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቶችን ለማናገር የተደረገው ጥረት አልተሳካም።


ለምን ወለድናቸው? ፖሊስ የደብረ ማርቆስ ተማሪዎችን እየደበደበ ነው

ዳዊት ዳባ

ፖሊስ የደብረ ማርቆስ ተማሪዎችን እየደበደበ ነው፡፡ የትናንትናው ተቃውሞ በኢሳትና በሌሎች ሚዲያዎች መተላለፉን ተከትሎ ‹‹ማን ነው ከኢሳትና ከሌሎች ሚዲያዎች ጋር እየተደዋወለ መረጃ የሚሰጠው?›› እንዲሁም ‹‹የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ካለ ተናገሩ›› በሚል ተማሪዎቹን አሳልፈው እንዲሰጡ ከፍተኛ ደብደባ እየፈጸመ መሆኑን ከቦታው የደረሰን መረጃ ይጠቁማል፡፡ ፖሊስ አሁንም ተማሪዎችን እየፈለገ እያሰረ መሆኑም ተገልጾአል ይላል የዛሬ ዋና ዜና።

ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባል!

ኢትዮጵያ ሀገራችን በታሪኳ ከአስከፊ የፈተና አረንቋ ውስጥ ተገፍታ የገባችበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ዜጎችዋ ከፋሽስት ኢጣልያ በከፋ ሁኔታ ይህ ቀረሽ የማይባል የመከራ መአት የወረደባቸውና እየወረ ደባ ቸው የሚገኝበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመን ወያኔ ብቻ ነው፡፡ እስር ቤቶች ሞልተው ተጨማሪ እስር ቤቶች መገ ንባት ከልማት ተቆጥሮ የሚፎከርበት ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የሀገሪቱ ብሄራዊ ባንክ ንብረት የሆ ነው ወርቅ በባሌስትራ ለውጦ እስከ መዝረፍ የደረሰ በጠራራ ፀሀይ የህ ዝብና የሀገር ሀብት ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በጥቂቶች የሚዘረፍበት ዘመን ቢኖር የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የጅምላ እስር፤ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ ስደትና መፈናቀል፤ ይበልጡንም በታሪካችን ታይቶ በማያውቅ መልኩ ለሞት፤ ለእስር፤ ለመፈናቀልና ለስደ ት ምክንያቱ የተገኘንበት ዘውግ የሆነበት ዘረኛ ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ባጠቃላይ ላለፉት 23 አመታት ወያኔ ማድረግ የሚችለውን አስከፊ ነገር ሁሉ በሀገርና በህዝብ ላይ ሲፈፅም

አቶ በረከት እሱን መች ጠየቅንህ?

ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) የተመሠረተበትን አርባኛ ዓመት ለማክበር ሽር ጉድ እየተባለ ባለበትና በመጠኑ ከፍተኛ የሆነ የሀገሪቱ የገንዘብ ወጭ ተደርጎአስረሽ ምችው የሚደለቅበት ሰአት ላይ ያለን ሲሆን የዘድሮው በዓል አከባበር ደግሞ የተለየ ሆኗል አስቀድመው ነው የጀመሩት ያም ሆነ ይህ በዓሉ ለምን ይከበራል? የሚያከብረውስ ማን ነው? ብለን ስንጠይቅ ድርጅቱ በጫካ አሥራ ሰባት ዓመት በትረ ሥልጣኑን ከጨበጠ በኋላ በከተሞች ለሃያ ሦሥት ዓመታት ያህል የምሥረታ በዓሉን በከፍተ የገንዘብ ወጭ እያከበረ ዘልቋል።በዓሉ የሚከበርበት ምክንያት፦ ህወሃት ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የተነሳበት ዓላማ ግቡን እየመታ በመምጣቱ፤ ከዚህ ግቡ የማይባሉ ሰዎችን ለሀገር ሥልጣን በማብቃቱ፤ጥቂቶቹን ሚሊየነር በማድረጉ፤የድርጅቱን ዓላማ የሚቃወሙትን እያወደመና እየበላ በመምጣቱ፤ ከሀገር እንዲሰደዱ በማድረጉ እንዲሁም አሰቃቂና ጭካኔ በተሞላበት ድብደባና እንግልት በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ ድርጅት አመራሮች ፤ጋዜጠኞች፤ ጦማርያን፤ የሃይማኖት መሪዎች፤ ተማሪዎች፤አስተማሪዎች፤ ነጋዴዎች፤አርሶ አደሮች ወህኒ ቤት ወርደው እንደ ብረት እየተቀጠቀጡ

Thursday, January 1, 2015

‹‹እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም›› አብርሃ ደስታ

መልዕክት ከቂሊንጦ እስር ቤት!

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

‹‹እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም›› አብርሃ ደስታ

እዚህ እስር ቤት ውስጥ በሽብር ስም የገባ ሰው በፈጠራ ወንጀል እንደገባ ነው የሚታመነው፡፡ ስለዚህ የሽበር ክስ ተመስርቶባቸው የታሰሩትን ሰዎች ማንም ወንጀለኛ አድርጎ አይመለከታቸውም፡፡ በእርግጥም አሸባሪ የለም፤ የፈጠራ ክስ ነው ያሳሰራቸው፡፡ አሸባሪ አለ ከተባለም እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም፡፡

ነጻ መውጣት ያለበት ቡድን አለ፣ እሱም ኢህአዴግ ራሱ ነው፡፡ እኔ አልታሰርኩም፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እስር የአዕምሮ ነው፡፡ እኔ አዕምሮየ አልታሰረም፡፡ ነጻ ሰው ነኝ፤ ውስጤ በጣም ነጻነት አለው፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡

በጋምቤላ ክልል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት 79 ሰዎች መገላቸውን መንግስት ገለጸ

ታኀሳስ ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት በጋምቤላ ክልል በጎደሬ ወረዳ ከመጋቢት እስከ ጳጉሜ በነበሩት ግጭቶች የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከ12 አይበልጥም በማለት በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቢቆይም፣ አቃቢ ህግ የክልሉን ባለስልጣናት ለመክሰስ ባቀረበው የክስ ቻርጅ ላይ 79 ሰዎች መገደላቸውን ፣ 273 ቤቶች መቃጠላቸውን ከ13 ሺ በላይ ዜጎች እንዲፈናቀሉ ማድረጋቸውን ገልጿል።አንዳንድ ወገኖች የተገደሉት ሰዎች ቁጥር በመቶዎች እንደሚቆጠሩ ሲገልጹ፣ ኢሳት 60 ሰዎች መገደላቸውን የሞአቾችን ስም ዝርዝር ይፋ በማድረግ ዘገባ አቅርቦ ነበር።
አቃቢ ህግ መንግስት አምኖ የሾማቸው የክልሉ ባለስልጣናት ግድያውን እንዳስፈጸሙና ግጭት እንዲነሳ እንዳደረጉ በክስ ቻርጁ ላይ አምልክቷል። የክልሉ ልዩ ሃይል አዛዥ አቶ ያእቆብ ሸራተንና የመዠንገር ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትንሳኤ ራጃን ጨምሮ 35 የክልሉ ባለስልጣናት  ክስ ተመስርቶባቸዋል።  የክልሉ ባለስልጣኖች በሚጤ ህዝቡን ሰብስበው ከተለያዩ የሃገሪቱ ክልሎች የመጡ ሰዎች የእርሻ ቦታቸውንና የቡና ተክላቸውን ለክልሉ ተወላጆች እንዲያካፍሉ፣ ይህን የማያደርጉ ከሆነ ግን ከክልሉ እንዲወጡ ቅስቀሳ ማድረጋቸው በክሱ ላይ ተመልክቷል።የግጭቱ መነሻ በአካባቢው የሚታየው መሬት ወረራ መሆኑ በተደጋጋሚ ቢገለጽም፣ በዚህ በኩል ተጠያቂ የሆኑ የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ለፍርድ አለመቅረባቸው የፍርድ ሂደቱ ተአማኒነት እንዲያጣ አድርጎታል። የቀድሞ የህወሃት አዛዦች የአካባቢው መሬት በስፋት እየቀሙና ነዋሪውን እያፈናቀሉ መሆናቸው በተጨባጭ ማስረጃ ቢረጋገጥም እስካሁን ምንም አይነት እርምጃ ሳይሰወድባቸው መቅረቱ በዜጎች መካከል ያለውን ልዩነት የሚያሳይ መሆኑን አዲስ አበባው ዘጋቢያችን አስተያየቱን አስፍሯል።የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በመጪው ጥር አጋማሽ የክሱን ዝርዝር ለማዳመጥ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በአርማጮ አከባቢ በአማራ ንቅናቄ ሰራዊት እና በወያኔ ሰራዊት መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑን የንቅናቄው ምንጮች ከአከባቢው አስታወቁ::

በአርማጮ አከባቢ በአማራ ንቅናቄ ሰራዊት እና በወያኔ ሰራዊት መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑን የንቅናቄው ምንጮች ከአከባቢው አስታወቁ::የህዝቡ ተሳትፎ በከፍተኛ ደረጃ እየታየ ባለበት እና ህዝቡ እና የንቅናቄው ወታደሮች በመቀናጀት ዱር ቤቴ ብለው ወደ ጫካ መግባታቸው ሲታወቅ በመተማ ሸዲ አከባቢ በትላንትናው እለት በወያኔው ጦር ላይ ጥቃት አድርሶ ወደቦታው የተመለሰው የአማራ ንቅናቄ ሰራዊት ከሕዝቡ ጋር በመተባበር እጅግ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እንደማረከ ምንጮቹ ተናግረዋል:: ካለፈው አርብ ጀምሮ የተነሳው ውጊያ በአሁን ወቅት ቀጥሎ ያለ ሲሆን በዛሬው ለሊት ከፍተኛ የቶክስ እሩምታዎች እና የከባድ መሳሪያ ድምጾች በአከባቢው እየተሰሙ መሆኑ ታውቋል::በአብድራፊ አብሃጂራ ሶረቃ ግጨው ማርዘነብ ማይጸማር ሃሙስ ገበያ ዳንሻ ማይካድራ እና አከባቢው ጦርነቱ ይስፋፋባቸዋል የሚል ከፍተኛ ስጋት ስላደረ በአከባቢው የወያኔ ሰራዊቶች በብዛት መስፈራቸው ሲታወቅ አዳዲስ ታንኮችን የጫኑ ከባባድ መኪኖች በቦታው ደርሰዋል::
እንዲሁን ወደ ሱዳን ክልል ዘልቀው የገቡ እና ከሱዳን ወታደሮች ጋር አሰሳ የሚያደርጉ ወያኔዎችን እንዳጠቁ የአማራው ንቅናቄ ወታደሮች ተናግረዋል::
በአርማጮ እና አከባቢው የተከሰተውን ግጭት በተመለከተ የአማራ ንቅናቄ ሰራዊት መግለጫ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል:: Zehabesha.com

የደህንነት ሃይሎች ዜጎችን ለማደናገርና ለማስፈራራት የእጅ ስልኮችን መበርበር ሊጀምሩ ነው

ወያኔ ‘ሚስጥራዊ ‘ስብሰባዎች በተሰብሳቢዎች ሞባይል ስልኮች እየተቀረጹ በውጭ ባሉ መገናኛ ብዙሃን መቅረባቸውና የዘረኛው መንግስት ሚስጥርና የድርጅቱን ጉድፍ አጉልቶ በማሳየቱ ይህም ድርጊት የወያኔን አመራሮች እያበሳጨ በመምጣቱ በየቦታው በሚደረጉ ስብሰባዎች ላይ ተሰብሳቢዎች ምንም አይነት ሞባይል ስልክ ወደ አዳራሽ ይዘው እንዳይገቡ መከልከል ተጀምሯል። በሌላ በኩል ዛሬ ይፋ በተደረገው ዜና ላይ አራት ከፍተኛ ማእረግ ያላቸው የአየር ሃይል አብራሪዎች ከድሬዳዋ አየር ሃይል በመነሳት ኬንያ መግባታቸው እንደተሰማ የደህንነት ሃይሎችና የመንግስት ባለስልጣናት የበርካታ ሰዎችን የእጅ ስልኮችን ሲፈትሹ ውለዋል፣ ይህ የግለሰቦችን ስልክ መፈተሽ/ መበርበር ሰፋ ባለ ሁኔታ በየከተሞች ያሉትን ሰላማዊውን ሰው ለማሸበርና ለማሸማቀቅ ይረዳል ብለው በማሰብ የደህንነት ሃይሎች ከሰሞኑ በሰፊ ዘመቻ እንደሚጀምሩት የውስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቁመዋል።


በጋምቤላ ክልል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት 79 ሰዎች መገላቸውን መንግስት ገለጸ

ታኀሳስ ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት በጋምቤላ ክልል በጎደሬ ወረዳ ከመጋቢት እስከ ጳጉሜ በነበሩት ግጭቶች የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ከ12 አይበልጥም በማለት በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቢቆይም፣ አቃቢ ህግ የክልሉን ባለስልጣናት ለመክሰስ ባቀረበው የክስ ቻርጅ ላይ 79 ሰዎች መገደላቸውን ፣ 273 ቤቶች መቃጠላቸውን ከ13 ሺ በላይ ዜጎች እንዲፈናቀሉ ማድረጋቸውን ገልጿል።
አንዳንድ ወገኖች የተገደሉት ሰዎች ቁጥር በመቶዎች እንደሚቆጠሩ ሲገልጹ፣ ኢሳት 60 ሰዎች መገደላቸውን የሞአቾችን ስም ዝርዝር ይፋ በማድረግ ዘገባ አቅርቦ ነበር።
አቃቢ ህግ መንግስት አምኖ የሾማቸው የክልሉ ባለስልጣናት ግድያውን እንዳስፈጸሙና ግጭት እንዲነሳ እንዳደረጉ በክስ ቻርጁ ላይ አምልክቷል። የክልሉ ልዩ ሃይል አዛዥ አቶ ያእቆብ ሸራተንና የመዠንገር ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትንሳኤ ራጃን ጨምሮ 35 የክልሉ ባለስልጣናት ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የክልሉ ባለስልጣኖች በሚጤ ህዝቡን ሰብስበው ከተለያዩ የሃገሪቱ ክልሎች የመጡ ሰዎች የእርሻ ቦታቸውንና የቡና ተክላቸውን ለክልሉ ተወላጆች እንዲያካፍሉ፣ ይህን የማያደርጉ ከሆነ ግን ከክልሉ እንዲወጡ ቅስቀሳ ማድረጋቸው በክሱ ላይ ተመልክቷል።
የግጭቱ መነሻ በአካባቢው የሚታየው መሬት ወረራ መሆኑ በተደጋጋሚ ቢገለጽም፣ በዚህ በኩል ተጠያቂ የሆኑ የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ለፍርድ አለመቅረባቸው የፍርድ ሂደቱ ተአማኒነት እንዲያጣ አድርጎታል። የቀድሞ የህወሃት አዛዦች የአካባቢው መሬት በስፋት እየቀሙና ነዋሪውን እያፈናቀሉ መሆናቸው በተጨባጭ ማስረጃ ቢረጋገጥም እስካሁን ምንም አይነት እርምጃ ሳይሰወድባቸው መቅረቱ በዜጎች መካከል ያለውን ልዩነት የሚያሳይ መሆኑን አዲስ አበባው ዘጋቢያችን አስተያየቱን አስፍሯል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በመጪው ጥር አጋማሽ የክሱን ዝርዝር ለማዳመጥ ቀጠሮ ሰጥቷል።