Monday, April 24, 2017

በቻግኒ ከተማ የባጃጅ ታክሲ አሽከርካሪዎች ስራ የማቆም አድማ አደረጉ

ኢሳት (ሚያዚያ 16 ፥ 2009)

በአዊ ዞን ቻግኒ ከተማ የባጃጅ ታክሲ አሽከርካሪዎች ዛሬ የስራ ማቆም አድማ ጀመሩ። ከትራንስፖርት ታሪፍ ጋር በተያያዘ አሸከርካሪዎቹ በመቱት አድማ፣ የቻግኒ ትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡን ለኢሳት የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

የባጃጅ አሽከርካሪዎች የዋጋ ታሪፍ እንዲቀንስ በመንግስት የተወሰደውን ዕርምጃ ተከትሎ ነው የስራ ማቆም አድማውን የመቱት። ከ190 በላይ የባጃጅ አሽከርካሪዎች በተሳተፉበት በዚሁ ድርጊት፣ የቻግኒ ከተማ የታክሲ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ ማድረጉን የደረሰን ዜና ያስረዳል።

ከዚህ

በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት ጥረት ተጀመረ

ኢሳት (ሚያዚያ 16 ፥ 2009)

በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት የሃገር ሽማግሌዎች እንቅስቃሴ ጀመሩ።

በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅና በአትሌት ሃይሌ ገ/ስላሴ የተጀመረው ይህ ጥረት የአርበኞች ማህበር ሊቀመንበር/ ልጅ ዳንዔል ጆቴንም እንዳካተተ መረዳት ተችሏል።

በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) አመራር ውስት ረጅም ጊዜያት የዘለቀና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ገያድ እየወጣ የሚመጣውን ልዩነት ለመሰምገል ከራሱ ከህወሃት የተውጣቱ ገለልተኛ ቡድኖች ያደረጉት ጥረት አልተሳካም። ሆኖም ችግሩ ከህወሃት አጥር ወጥቶ በአደባባይ ምልክት እያሳየ መገኘቱን ተከትሎ እና ፕ/ር ኤፍሬም የሽምግልና ጥረቱን ጀምረዋል። ይህም ጥረት ከቀድሞዎቹ የሽማግሌ ቡድን አባላት ከ እነ አትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ በተጨማሪ የአርበኞቹ ማህበር ሊቀመንበር የሆኑትን ልጅ ዳንዔል ጆቴን እንዲሁም ነጋዲውዎችን እንደጨመረ መረዳት ተችሏል።

በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት ጥረት ተጀመረ

ኢሳት (ሚያዚያ 16 ፥ 2009)

በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት የሃገር ሽማግሌዎች እንቅስቃሴ ጀመሩ።

በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅና በአትሌት ሃይሌ ገ/ስላሴ የተጀመረው ይህ ጥረት የአርበኞች ማህበር ሊቀመንበር/ ልጅ ዳንዔል ጆቴንም እንዳካተተ መረዳት ተችሏል።

በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) አመራር ውስት ረጅም ጊዜያት የዘለቀና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ገያድ እየወጣ የሚመጣውን ልዩነት ለመሰምገል ከራሱ ከህወሃት የተውጣቱ ገለልተኛ ቡድኖች ያደረጉት ጥረት አልተሳካም። ሆኖም ችግሩ ከህወሃት አጥር ወጥቶ በአደባባይ ምልክት እያሳየ መገኘቱን ተከትሎ እና ፕ/ር ኤፍሬም የሽምግልና ጥረቱን ጀምረዋል። ይህም ጥረት ከቀድሞዎቹ የሽማግሌ ቡድን አባላት ከ እነ አትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ በተጨማሪ የአርበኞቹ ማህበር ሊቀመንበር የሆኑትን ልጅ ዳንዔል ጆቴን እንዲሁም ነጋዲውዎችን እንደጨመረ መረዳት ተችሏል።

ዶ/ር መረራ ጉዲና የቀረበባቸውን ክስ በመቃወም ለፍርድ ቤት መቃወሚያ አቀረቡ

ኢሳት (ሚያዚያ 16 ፥ 2009)

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተላልፈዋል ተብለው የታሰሩትና ህገ-መንስታዊውን ስርዓት በሃይል ለመናድ በሚል በእስር የሚገኙት ዶ/ር መረራ ጉዲና የቀረበባቸውን ክስ በመቃወም ሰኞ ለፍርድ ቤት መቃወሚያን አቀረቡ።

ዶ/ር መረራ ጉዲና በከሳሽ አቃቤ ህግ የተመሰረተባቸውን ክስ ለመቃወም ባለ 11 ገፅ የክስ መቃወሚያን ያቀረቡ ሲሆን፣ ቤልጂየም ለህዝባዊ ስራ በሄድኩበት ጊዜ የአስቸኳይ ጊዜ ዋጁን ተላልፏል ተብሎ የቀረበውን ክስ ተዋውመዋል። ከሳሽ አቃቤ ህግ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተላልፈዋል ካለው ክስ በተጨማሪ ህገመንስቱን በሃይል ለመናድ በመሞከር የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ እንዲባባስ አድርገዋል ሲል በክሱ አመልክቶ እንደነበር ይታወሳል።

የድርቅ አደጋ በመባባሱ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተጨማሪ ተረጂዎች ለምግብ ድጋፍ ተጋለጡ

ኢሳት (ሚያዚያ 16 ፥ 2009)

በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ መባባስን ተከትሎ በኦሮሚያና የደቡብ ክልሎች ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተጨማሪ ተረጂዎች ለምግብ ድጋፍ ተጋለጡ።

የመንግስት ባለስልጣናት የተረጂዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን በቅርቡ ይፋ ቢያደርጉም ቁጥሩን ግን ለህዝብ ከማሳወቅ ተቆጥበው ይገኛሉ።

ይሁንና በዚሁ የድርቅ አደጋ ዙሪያ አዲስ ሪፖርትን ያወጣው የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በቅርቡ በሁለቱ ክልሎች መጣል የነበረበት የበልግ ዝናብ በወቅቱ ባለፈው ባለመጣሉ ተጨማሪ ሰዎች ለምግብ ድጋፍ መጋለጣቸውን ይፋ አድርጓል።

Friday, April 21, 2017

U.S. troops in Somalia non-combat, says Pentagon

ESAT News (April 21, 2017)
The head of the US Africa Command (Africom) indicated on Thursday that the Pentagon is not initiating a major escalation of the US combat role in Somalia, according to a report b y Business Daily Africa.
Marine Corps Gen Thomas Waldhauser told reporters that the dozens of additional US soldiers being sent to Somalia are “logisticians” rather than infantry troops.
This “long-scheduled deployment” is primarily intended to help train Somali forces to become more effective in fighting al-Shabaab, Gen Waldhauser said.

Ethiopia: Five soldiers killed in ambush in Gondar

ESAT News (April 21, 2017)
Four soldiers were killed when their convoy came under attack in Gondar. The truck, carrying soldiers to the city of Gondar, overturned when the driver was shot in an ambush. Five others have sustained injuries.
No party claimed responsibility for the attack.
According to ESAT’s sources, the convoy was travelling from the Musie Bamb Military Camp to the city of Gondar, where the residence of an official of the ruling TPLF, Ambaye Amare, had come under a grenade attack, seriously injuring the official.

ሶስት የፖለቲካ ድርጅቶች ህዝባዊ ተቃውሞ እንዲባባስ አድርገዋል ተብለው ክስ ሊመሰረትባቸው መሆኑን ታወቀ


ኢሳት (ሚያዚያ 13 ፥ 2009)
ሶስት የፖለቲካ ድርጅቶች ከአንድ አመት በፊት በኦሮሚያና በሌሎች ክልሎች ሲካሄድ የቆየው ህዝባዊ ተቃውሞ እንዲባባስ አድርገዋል ተብለው ክስ ሊመሰረትባቸው መሆኑን ታወቀ።
ከቀናት በፊት በህዝባዊ ተቃውሞ ወቅት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ሲመረምር የቆየው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ሶስት የፖለቲካ ድርጅቶች ተቃውሞ እንዲቀሰቅስና እንዲባባስ የተለያዩ አስተዋጽዖ አድርገዋል ሲል ለፓርላማ ባቀረበው ሪፖርት አመልክቷል። የኮሚሽኑን ሪፖርት ያቀረበው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ ህዝባዊ ተቃውሞን አባብሰዋል በተባሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ላይ ክስ እንዲመሰረት ሃሙስ ውሳኔን ሰጥቷል።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሰማያዊ ፓርቲ እና የጌዲዮ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅቶች ክስ እንዲመሰረትባቸው የተወሰነ መሆኑን ሱዳን ትሪቢዩን ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ዘግቧል።

የአቅም ችግር ታይቶባቸዋል የተባሉ የብዓዴን እና የኦህዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ ስልጠና ሊሰጣቸው ነው ተባለ


ኢሳት (ሚያዚያ 13 ፥ 2009)
በጥልቅ ተሃድሶው የአቅም ችግር ታይቶባቸው የተባሉ የብዓዴን እና የኦህዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ ስልጠና ሊሰጣቸው መሆኑን ተነገረ።
የመጀመሪያው ዙር ስልጠና ከብዓዴን የድርጅቱ የጽህፈት ቤት ሃላፊና አማራውን በመዝለፍ የሚታወቁት አቶ አለምነህ መኮንን ተከተዋል። የመጀመሪያው ዙር ስልጠና በመጭው ሰኞ ይጀምራል።

Ethiopia: Rights watchdog says impunity carries high price

ESAT News (April 21, 2017) 
Researches on atrocities committed against people in tyrannical regimes have demonstrated that  a decision to ignore atrocities and reinforce a culture of impunity carries a high price, and merely encourages future abuses, the Human Rights Watch said on Friday.
Felix Horne, Senior Researcher with the Human Rights Watch for Horn of Africa, writing about the report released by the Ethiopian Human Rights Commission, said “an international investigation would be a first important step in ending Ethiopia’s culture of impunity and would send a powerful and overdue message to the Ethiopian government that its security forces cannot shoot and kill peaceful protesters with impunity.”

Wednesday, April 19, 2017

Ethiopia: Diplomatic shuttle follows news that Eritrea grants Egypt military base

ESAT News (April 19, 2017)
Ethiopia’s Foreign Minister is in Cairo following news that arch foe Eritrea has given the nod to Egypt to establish a military base.
Details of the talks are scanty but Workeneh Gebeyehu has met his Egyptian counterpart and also president Abdel Fettah Al Sisi in Cairo.
A high level Egyptian delegation was in Asmara, Eritrea last week amid unconfirmed reports that the east African nation, which is under a UN sanction, has granted Egypt to establish a military base.

የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት በሰብዓዊ መብቶች ላይ የመወያያ መድረክ እንዲያዘጋጅ ተጠየቀ

ኢሳት (ሚያዚያ 11 ፥ 2009)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በሰብዓዊ መብቶች አካባቢ ላይ ልዩ የመወያያ መድረክ እንዲያዘጋጅ አሜሪካ ጠየቀች።
የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ለበርካታ ሃገራት አለመረጋጋት ምክንያት እየሆኑ መምጣቱን የገለጸችው አሜሪካ፣ ምክር ቤቱ የሰብዓዊ መብት መከበር ግጭትን ለመከላከልና ለአለም ሰላምና ደህንነት ያለው ሚና ትኩረት መስጠት እንዳለበት አሳስባለች።
በተባበሩት መንግስታት የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ኒኪ ሃሊ ቀጣዩ የአለም ቀውስና አለመረጋጋት የሰብዓዊ መብቶች ባልተከበሩባቸው ሃገራት ላይ ሊቀሰቀስ እንደሚችል ገልጸዋል።
የጸጥታው ምክር ቤት ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ የጠየቁት አምባሳደሯ፣ የብሩንዲንና የማይንማር መንግስታትን በምሳሌነት በመጥቀስ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚስተዋልባቸው ሃገራት መሆኑን አስታውቀዋል።

በሶማሌ ክልል የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በአመቱ የመደቡትን በጀት የኮሌራ ወረርሽንን ለመከላከል እንዲያውሉት ተጠየቁ

ኢሳት (ሚያዚያ 11 ፥ 2009)
በሶማሌ ክልል በእርዳታ ስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለተለያዩ የሰብዓዊ ዕርዳታ ስራ የያዙትን በጀት እየተባባሰ ላለው የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ መከላከያ እንዲያዞሩ ተጠየቁ።
በሃገሪቱ መንግስታዊ ባልሆኑ አካላት ዘንድ የሚካሄዱ የዕርዳታ ስራዎችን የሚያስተባብረው Ethiopian Humanitarian Fund በክልሉ በመዛመት ላይ ያለው የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ ዕልባት ባለማግኘቱ ምክንያት ድርጅቶቹ በበጀታቸው ላይ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ጥያቄ ማቅረቡን አስታውቋል። በሰባት ዞኖች ውስጥ በሚገኙ በ40 ወረዳዎች ውስጥ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኮሌራ በሽታ ወረርሽኙ ለሰዎች ሞት ምክንያት መሆኑን ከቀናት በፊት ቢያረጋግጥም የሟቾችን ቁጥር ግን ከመግለጽ ተቆጥቧል።
በክልሉ በሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ላይ ተሰማርተው የሚገኙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ለተወሰነ ጊዜ ትኩረታቸውን ሙሉ ለሙሉ የበሽታውን ወረርሽኝ መከላከል ላይ እንዲያተኩሩ ተጠይቀዋል።

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ባልደርቦች ከ380 ሺ ብር በላይ ከተጠርጣሪ ወስደዋል ተብለው ክስ ተመሰረተባቸው

ኢሳት (ሚያዚያ 11 ፥ 2009)
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ሁለት ባልደርቦች ከአልሸባብ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተሰማሩ ጊዜ ከ380 ሺ ብር በላይ ከተጠርጣሪ ወስደዋል ተብለው ክስ ተመሰረተባቸው።
አቶ ባህሩ አዱኛና አቶ ደራ ደስታ የተባሉ የደህንነት ሰራተኞቹ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ጊኒር ከተማ ነዋሪ የሆኑትን አቶ ኡመር አብዶ የተባሉ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተሰማሩ ጊዜ 418 ሺ 500 ብር መያዛቸውን ከሳሽ አቃቤ ህግ በክሱ ማቅረቡን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ይሁንና የደህንነት ሰራተኞቹ የወሰዱትን ገንዘብ ሳያስመዝግቡ 30ሺ ብር ብቻ በኤግዚቢትነት ማስመዝገባቸው ተመልክቷል።
የፌዴራሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሁለቱ የደህንነት ሰራተኞች ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀም ወንጀልና በስራ ተግባር ላይ የሚፈፅም የመውሰድና የመሰወር ወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው ታውቋል።
ተከሳሾቹ ክስ ከተሰጣቸው በኋላ ጠበቃ ለማቆም አቅም እንደሌላቸው ለፍርድ ቤት በመናገራቸው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተከላካይ ጠበቆች ጽ/ቤት ተከላካይ ጠበቅ እንዲያቆምላቸው ትዕዛዝ አስተላልፏል። ክስ የመስማቱ ሂደትም ሚያዚያ 25 ቀን 2009 አም እንደሚሰጥ ታውቋል።

ወደ አራት ሚሊዮን አካባቢ የሚሆኑ የሞባይል ስልኮች አገልግሎት እንዳይሰጡ ሊደረግ መሆኑ ተነገረ

ኢሳት (ሚያዚያ 11 ፥ 2009)
ከተለያዩ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በተጠቃሚ እጆች የሚገኙ ወደ አራት ሚሊዮን አካባቢ የእጅ ስልኮች (ሞባይሎች) አገልግሎት እንዳይሰጡ ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ።
የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከወራት በፊት በተንቀሳቃሽ ስልኮች ላይ አዲስ የመመዝገቢያ ስርዓት ተግባራዊ እንዲደረግ መመሪያ አውጥቶ የነበር ሲሆን፣ ወደ ሃገሪቱ በህገወጥ መንገድ ገብተዋል የተባሉ ሞባይሎች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ በዚሁ መመሪያ ተደንግጓል።
አዲሱን መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግና ከጥቅም ውጭ የሚሆኑትን አራት ሚሊዮን ስልኮች እንዴት መተካት አለባቸው በሚለው ጉዳት በኢትዮ-ቴሌኮምና በሃገር ውስጥ የሞባይል አምራቾች መካከል ድርድር ቢካሄድም መግባባት ሳይደረስ መቅረቱን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
የእጅ ስልካቸው ከጥቅም ውጭ ለሚሆንባቸው ደንበኞች ተቀያሪ ስልኮች በሚሰጡበት ጊዜ የተቀያሪ ስልኮችን ወጪን ማን ይሸፍነው የሚለው ጉዳይ አለመግባባት ላለመደረሱ ዋነኛ ምክንያት መሆኑ ታውቋል።

ጠ/ሚ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ለውጭ ጋዜጠኞች ሊሰጡ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰረዘ

ኢሳት (ሚያዚያ 11 ፥ 2009)
ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ረቡዕ በወቅታዊ የሃገሪቱ ጉዳዮች ዙሪያ ለውጭና ለሃገር ውስጥ ጋዜጠኞች ሊሰጡ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰረዘ። ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች ግን መግለጫ መስጠታቸው ተዘግቧል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ለተጋበዙ ጋዜጠኞች ባሰራጨው አስቸኳይ መልዕክት የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ ቀድሞ በተያዘለት ፕሮግራም እንዳማይካሄድ አስታውቋል። ይሁንና ጽ/ቤቱ መግለጫው በሌላ ጊዜ እንደሚካሄድ ቢገልፅም የረቡዕ ፕሮግራም በምን ምክንያት ሊሰረዝ እንዳቻለ የሰጠው ዝርዝር መረጃ የለም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ረቡዕ ከጋዜጠኞች ጋር ያደርጉታል ተብሎ በተጠበቀው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ማክሰኞ ለፓርላማ ቀርቦ የነበረው የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ሪፖርት ዋነኛ ትኩረት ሊሆን ይችል እንደነበር ጋዜጣ አስረድተዋል።

በሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ከቀናት በፊት በሶስት ወረዳዎች አዲስ ጥቃት መፈጸሙ ተነገረ

ኢሳት (ሚያዚያ 11 ፥ 2009)

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የደቡብ ሱዳን ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል የሚፈጽሙትን ጥቃት ለመከላከል በአካባቢው እንደሰፈረ መንግስት ቢገልጽም፣ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ከቀናት በፊት በሶስት ወረዳዎች አዲስ ጥቃት ፈጸሙ።
ቁጥራቸው ያልታወቀው የጎሳ ታጣቂዎች መጋቢት 25 እና ሚያዚያ 1 ቀን 2009 አም የኢትዮጵያ ድንበርን በመዝለቅ በጎድ ጆርና ዲማ ወረዳዎች ጥቃት ማድረሳቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበሪያ መምሪያ አስታውቋል። ይሁንና የሰብዓዊ ዕርዳታ ድርጅቱ ታጣቂዎች በሶስት ወረዳዎች ያደረሱትን ጉዳት ከመግለጽ ተቆጥቧል።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ባለፈው ወር በጋምቤላ ክልል ስር በሚገኘው የጎግና የጆር ወረዳዎች በፈጸሙት ጥቃት በትንሹ 28 ኢትዮጵያውያንን መግደላቸውና 43 ህጻናትን አፍነው መውሰዳቸው ይታወሳል።

Tuesday, April 18, 2017

በፒያሳ ከ10 ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች ለመልሶ ልማት ከመኖሪያ ቀያቸው ሊነሱ መሆኑ ተገለጸ

ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009)
በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ፒያሳ ሰራተኛ ሰፈር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የሚኖሩ 10ሺ ነዋሪዎች ለመልሶ ልማት ከመኖሪያ ቀያቸው ሊነሱ መሆኑ ተገለጸ።
ከተቆረቆረ ረጅም ጊዜ እንደሆነ በሚነገርለት በዚሁ አካባቢ በርካታ በቅርስነት መፍረስ የሌለባቸው ህንጻዎች ያሉ ሲሆን፣ የከተማዋ ነዋሪዎችና የታሪክ ምሁራን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
አካባቢውን በቀጣዮቹ ስድስት ወራቶች ሙሉ ለሙሉ ለማፍረስ ሃላፊነት የተሰጠው የአራዳ ክፍለ ከተማ፣ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጨምሮ 14 ቤቶች በቅርስነት በመታየታቸው እንደማይፈርሱ አስታውቋል።
ይሁንና የከተማ ነዋሪዎች አካባቢው ረጅም ዕድሜ ያስቆጠረ በመሆኑን ከ14 በላይ የሚሆኑ ይዞታዎች በቅርስነት መያዝ እንደሚኖርባቸው ጥያቄ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል።
በሰራተኛ ሰፈር በወረዳ 10 ቀበሌ 10 እና 13 ዙሪያ ያሉ 1ሺ 600 መኖሪያ ቤቶች በተያዘው አመት መጨረሻ ድረስ ሙሉ ለሙሉ እንደሚፈርሱና በድርጊቱ ወደ 10 ሺ አካባቢ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው እንደሚነሱ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

ከህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ 669 ሰዎች መሞታቸው መረጋገጡን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ገለጸ

ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009)
በኦሮሚያክ አማራና የደቡብ ክልሎች ሲካሄድ ከቆየው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ 669 ሰዎች መሞታቸው መረጋገጡን የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ማክሰኞ ገለጸ።
በጉዳዩ ዙሪያ ያካሄደውን ምርመራ አስመልክቶ ሪፖርቱን ለፓርላማ ያቀረበው ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል በቢሾቱ ከተማ ከእሬቻ  በዓል አከባባር ጋር በተገናኘ የደረሰውን የሞት አደጋ ጨምሮ በተለያዩ ዞኖች የተፈጸሙ ግድያዎችን አቅርቧል።
በኦሮሚያ ክልል 15 ዞኖች እና 91 ከተሞች በአማራ ክልል 5 ዞኖች እና 55 ወረዳዎች እንዲሁም በደቡብ ክልል ጌድዮ ዞን በሚገኙ ስድስት ከተሞች ምርመራው መካሄዱን የኮሚሽኑ ሃላፊ ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚያብሄር ለፓርላማው አስታውቀዋል።
በኦሮሚያ ክልል 462 ሰላማዊ ሰዎችና 33 የጸጥታ ሃይሎች ተገድለዋል ያለው የኮሚሽኑ ሪፖርት በአማራ ክልል 110 ሰላማዊ ሰዎችና 30 የጸጥታ አባላት መሞታቸውን ገልጿል።
በተመሳሳይ ሁኔታም በደቡብ ክልል የ34 ሰዎች ህይወት ማለፉን ያወሳው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽኑ በባሌ ሮቤና በምስራቅ ሃረርጌ 28 ሰዎች የሞቱበት እንዲሁም በዳዳሴ ከተማ የተካሄደው የጸጥታ ሃይሉ ዕርምጃ የተመጣጠነ አለመሆኑን አመልክቷል።
የፌዴራልና የኦሮሚያ ክልል መንግስት የእሬቻን በዓል በሚከበርበት ወቅት ችግሩ ሊፈጠር እንደሚችል በቂ መረጃ እያላቸው ጥንቃቄና በቂ ጥበቃ አለማድረጋቸው ሃላፊነት የጎደለው ነው ሲል ኮሚሽኑ በሪፖርቱ አስፍሯል።
የጸጥታ ሃይሎች በበዓሉ ማግስት የነበረውን ብጥብጥ ባለመቆጣጠሩ ሊጠየቅ ይገባዋል ያለው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የጸጥታ አባላት በበአሉ ወቅት ያሳዩት ትዕግስት የሚመሰገን ነው ብሏል።
የአይን እማኞችና በወቅቱ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች የጸጥታ ሃይሎች የተኩስ ዕርምጃ መውሰዳቸውን ቢያረጋግጡም ኮሚሽኑ በወቅቱ ከአስለቃሽ ጭስ ውጭ የተወሰደ የሃይል እርምጃ የለም ብሏል።
የመንግስት ባለስልጣናት በወቅቱ ከ50 በላይ ሰዎች ሞተዋል ቢሉም መንግስታዊው የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምን ያህል ሰው እንደሞተ የሰጠው መረጃ አለመኖሩን ለመረዳት ተችሏል።

የኢትዮጵያ መንግስት የተመድና የአውሮፓ ህብረት በአገሪቱ የተፈጸሙ ግድያዎችን ለማጣራት ያቀረበውን ጥያቄ እንደማይቀበል አስታወቀ



ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅትና የአውሮፓ ህብረት በመቶዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ምክንያት የሆነውን ግድያ ለማጣራት ያቀረቡትን ጥያቄ እንደማይቀበል በይፋ ምላሽ ሰጠ።
ሁለቱ አለም አቀፍ ተቋማት ባለፈው አመት በኦሮሚያ ክልል ተቀስቅሶ ከነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች የሃይል ዕርምጃ በመውሰድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን ሲገልጹ ቆየተዋል።
ይኸው የጸጥታ ሃይሎች ግድያና የሰብዓዊ መብት ጥሰት በገለልተኛ አካል ምርመራ እንዲካሄድበትና ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት ለፍትህ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል።
ይሁንና ከቢቢሲ ጋር ቃለምልልስን ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ መንግስት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅትና ከአውሮፓ ህብረት የቀረበውን የምርመራ ጥያቄ እንደማይቀበለው አስታውቀዋል።
መንግስታዊው የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጉዳዩን በቸልተኝነት የሚመረምር አካል ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስታቸውን አቋም ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኮሚሽኑ ገለልተኛ ነው ቢሉም አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በመንግስት የሚካሄደው ምርመራ ነጻና ገለልተኛ እንደማይሆን ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛል።

የአህያ ቄራ ለመዝጋት የተወሰደውን ዕርምጃ በመቃወም የቻይናውን ኩባንያ ጉዳዩን ወደ አለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንደሚወስደው አስታወቀ

ኢሳት (ሚያዚያ 10 ፥ 2009)
የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር በከተማዋ የሚገኘውን የአህያ ቄራ ለመዝጋት የወሰደውን ዕርምጃ በመቃወም የቻይናውን ኩባንያ ጉዳዩን ወደ አለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንደሚወስደው ማክሰኞ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የፋብሪካው መዘጋትን በተመለከተ እስካሁን ድረስ የሰጠው ምላሽ ባይኖርም የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የአህያ ማረጃ ቄራው እንዲዘጋ መወሰኑ ተገልጿል።
ይሁንና የከተማው የአስተዳደር ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም የቄራው ባለቤት የሆነው የቻይናው ሻንዶንግ ዶንግ ኩባንያ ጉዳዩን ለአለም አቀፍ ፍርድ ቤት ለመውሰድ እያጤነ መሆኑን አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ የኩባንያውን ምንጮች ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።
በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር እንዲዘጋ የተወሰነው የአህያ ቄራው በየዕለቱ 200 አህዮችን ለእርድ በማቅረብ ስጋን ወደ ቬይትናም እንዲሁም የአህያ ቆዳን ደግሞ ወደ ቻይና ለመላክ እቅድ ይዞ እንደነበር ይታወሳል።

Ethiopian regime says 669 killed in protests, refuses to allow international investigators

ESAT News (April 18, 2017)
A government Commission says a total of 669 people were killed in anti-government protests last year in the Oromo, Amhara and South regions of the country. The Commission said the measure by security forces was “proportional.”
The results of the investigation by the Ethiopian Human Rights Commission was announced as the Prime Minister, Hailemariam Desalegn, said in a BBC interview that they would not allow international investigations into the killings.

Tuesday, April 4, 2017

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ስም እየተራቆተ መሆኑ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደ ሃገሪቱ ልማት ባንክ በብድር ስም እየተራቆተ መሆኑን ምንጮች ገለጹ። ለባንኩ ፕሬዚደንት በጉቦ መልክ እጅግ ዘመናዊ ቤት የተሰራላቸው ቢሆንም፣ እርሳቸው የሚኖሩበት ግን ባንኩ በዋስትና በወረሰው ቤት ውስጥ መሆኑንም መረዳት ተችሏል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የህወሃት ንብረት ለሆነው ኤፈርት ኩባንያዎች ብድር ምንጭነት በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት፣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ቅርበት ያላቸው ባለሃብቶችም ከህግና ደንብ ውጭ ከፍተኛ ገንዘብ እየወሰዱ ሲሆን፣ የአንዳንዶቹ ብድር ከ2 ቢሊዮን ብር መብለጡንም ለኢሳት በዝርዝር የደረሰው መረጃ ያስረዳል።

በኢትዮጵያ አህዮች እንዲታረዱ መደረጉ ተቃውሞ ሊቀሰቀስ ይችላል ተባለ

ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ አህዮች እንዲታረዱና ስጋና ቆዳቸው ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መወሰኑ በኢትዮጵያውያን ዘንድ እያነጋገረ ሲሆን፣ በአፍሪካዊቷ ቡርኪናፋሶም ያስከተለው ቁጣ በኢትዮጵያ ሊደገም እንደሚችል የፖለቲካ ተመልካቾች ይገልጻሉ። በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ድርጊቱ ተቃውሞና ቁጣ ማስከተሉን ማስታወስ ተችሏል። መንግስት ከእንግዲህ ፈቃድ አልሰጥም ያለ ቢሆንም፣ ከዚህ በፊት የሰጠውን ግን አልሰረዘም።
የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በበኩሉ ለውጭ ገበያ ይቀርባል ተብሎ የታሰበው የአህያ ስጋ ለሃገር ውስጥ ሊውል ይችላል የሚል ስጋት በመኖሩ በፋብሪካው ቅጥር ግቢ ቢሮ በመክፈት ቁጥጥር እንዲያደርግ አስታውቋል።
በቢሾፍቱ ከተማ የተቋቋመው ይኸው ኩባንያ ስጋውን ለቬይትናም የሚያቀርብ ሲሆን፣ የአህያ ቆዳን ደግሞ ወደ ቻይና ለመላክ እቅድ እንዳለው አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል።
በ80 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት የተቋቋመው ይኸው የቻይና ኩባንያ ለውጭ ገበያ ያቀርባል የተባለውን አህዮች ከቢሾፍቱ ከተማ ዙሪያ ካሉ ገበሬዎች ለመግዛት ማሰቡ ተነግሯል።

በሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከይዞታቸው ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009)
በሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከተጨማሪ ወታደራዊ ይዞታዎች ለቀው መውታጣቸውን የሃገሪቱ ባለስልጣናት አስታወቁ።
ቁጥራቸው ያልተገለጸው ወታደሮቹ በማዕከላዊ ሶማሊያ ከሚገኘውና ኤልቡር ተብሎ ከሚጠራ አስተዳደር ለቆ መውጣቱን የአካባቢው የክልል ባለስልጣናት ለመገናኛ ብዙሃን አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ወታደሮች ለረጅም ጊዜ ተቆጣጥረው ከቆዩት አስተዳደር በምን ምክንያት ለቀው እንደወጡ የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን፣ የሶማሊያው ታጣቂ ሃይል አልሸባብ ኤልቡርን እንደተቆጣጠረ ቪኦኤ የእንግሊዝኛው ክፍል ዘግቧል።
የኤልቡር አስተዳደር ሃላፊ የሆኑት ኑር ሃሰን ጉታሌ የኢትዮጵያ ወታደሮች አካባቢውን ለቀው እንደሚወጡ አስቀድመው የሰጡት መረጃ አለመኖሩን ገልጸዋል።
የሃገሪቱ የጸጥታ ስጋት የሆነው አልሸባብ ሰኞ ማለዳ በወታደራዊ ተሽከርካሪዎች በመታጀብ ያለምንም ግጭት አስተዳደሩን ሊቆጣጠር እንደቻሉ ጉታሌ አክለው አስረድተዋል።

በዋልድባ ገዳም አቅራቢያ በአማራና በትግራይ ሚሊሺያዎች መካከል የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከተሎ ከሁለቱም ወገን የሰው ህይወት ጠፋ

ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009)

በዋልድባ ገዳም አቅራቢያ በአማራና በትግራይ ሚሊሺያዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ከሁለቱም ወገን ታጣቂዎች ተገደሉ።
ማክሰኞ መጋቢት 26, 2009 አም ለተቀሰቀሰው ግጭት መነሻ የሆነው በዋልድባ ገዳም ለሚከበረው አመታዊ የመድሃኒያለም በዓል የሚጓዙ የአማራ ሚሊሺያዎች ትጥቅ እንዲፈቱ በመጠየቃቸው እንደሆነም መረዳት ተችሏል።
በታሪካዊው ዋልድባ አበረንታት ገዳም መጋቢት 27 ለሚከበረው አመታዊ የመድሃኒያለም የንግስ በዓል በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች ከዋዜማ ቀናት ጀምሮ ወደገዳሙ እንደሚጓዙ የእሳት ምንጮች ገልጸዋል። አሁንም በተመሳሳይ ለንግስ የሚሄዱ የአማራ ክልል ሚሊሺያዎች ትጥቅ እንዲፈቱ በትግራይ ሚሊሺያዎች ሲጠየቁ፣ የተፈጠረው ውዝግብ ወደ ግጭት አምርቷል።