Thursday, February 4, 2016

ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በማላዊ እስር ቤት ውስጥ በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ተገለፀ

ጥር ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሕገወጥ መንገድ  ድንበር ተሻግረው ወደ ማላዊ ገብተዋል ተብለው በአገሪቱ ፍርድ ቤት ቀርበው እስር የተፈረደባቸው ኢዮጵያዊያን ስደተኞች በእስር ቤቱ ውስጥ ሰብዓዊ መብታቸው ተጥሶ አስከፊ በሆነ አያያዝ በደል እየተፈጸመባቸው እንደሆነ ሴቭ አወር ሳውል SOS የተባለ ግብረሰናይ ድርጅት አስታወቀ።

በእስር ቤቱ ውስጥ ካሉት 2 ሽህ 532 አጠቃላይ ታራሚዎች መካከል 569 የሚሆኑት የውጭ አገር ዜጎች ሲሆኑ ከነኝህ ውስጥ 230ው ኢትዮጵያዊያን  ናቸው። ስደተኞቹ በተጨናነቀ ክፍል ውስጥ ታጭቀው የጤና እክሎች የደረሱባቸው ሲሆን የምግልብ አቅርቦቱ በቂና ያልተመጣጠነ አየለም ሲል ድርጅቱ አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ አመልክቷል።
የአገሪቱ የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊ  የእስር ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን ስደተኞችን ወደ ትውልድ አገራቸው ለመመለስ መንግስታቸው የበጀት ችግር እናለበት አስታውቀው ከየዓለም አቀፉ ስደተኞች ድርጅት አይኦኤም ጋር በመተባበር የመለሱ ስራ መዘግየቱን አስታውቀዋል። ለዚህም በምክንያትነት ያቀረቡት ሰተኞቹ ምንም ዓይነት ሕጋዊ ማንነታቸውን የሚገልጽ ፓስፓርትም ሆነ የይለፍ ወረቀት አለመያዛቸው እነሆነ አበክረው ገልጸዋል።
በአስከፊ ሰቆቃ ውስጥ ያሉትን ኢትዮጵያዊያን ወጣት ስደተኞች ለመታደግ የኢትዮጵያ መንግስት ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አለማድረጉን ኒያሳ ታይም አክሎ ዘግ

No comments:

Post a Comment