Friday, December 30, 2016

ዶ/ር መረራ ከእስር እንዲፈቱ የሚያስተባብር አለም ቀፍ ግብረ ሃይል ተቋቋመ

ኢሳት (ታህሳስ 21 ፥ 2009)
ነዋሪነታቸው በተለያዩ የአለማችን ሃገራት የሆነ ኢትዮጵያውያን ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር እንዲፈቱ የሚያስተባብር አለም ቀፍ ግብረ ሃይል አቋቋሙ።
ግብረ ሃይሉ እያካሄደ ያለው ይኸው አለም አቀፍ ዘመቻ አሜሪካንን ጨምሮ የአውሮፓ ህብረትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ኢትዮጵያ ለእስር የዳረገቻቸው የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞችን እንዲሁም ሌሎች አካላትን እንድትለቅ ግፊት እንደሚያደርጉ የሚጠይቅ መሆኑ ታውቋል።
የዘመቻው መጀመር አስመልክቶ መግለጫን ያወጣው ግብረ ሃይሉ በቅርቡ ተግባራዊ ተድርጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተላልፈዋል ተብለው ለእስር የተዳረጉት ዶ/ር መረራ ጉዲና ተይዘው ያሉበት ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን አስታውቀዋል።

130 ግለሰቦች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አርብ አስታወቀ

ኢሳት (ታህሳስ 21 ፥ 2009)
የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ 130 ግለሰቦች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አርብ አስታወቀ።
ለእስር ከተዳረጉት ሰዎች በተጨማሪ በስምንት ትላልቅ አክሲዮኖች በአራት ህንጻዎች በ49 ተሽከርካሪዎች፣ በ22 በመኖሪያ ቤቶችና በሁለት ፋብሪካዎች ላይ እገዳ መደረጉንም ኮሚሽኑን ዋቢ በማድረግ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰበር ዜና ዘግበዋል።
ይህንና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ለእስር የተዳረጉ የመንግስት ባለስልጣናትና ንብረት የታገደባቸውን ግለሰቦችና ተቋማት በስም ከመጥቀስ ተቆጥቧል።
በ13 ተጠርጣሪዎች ላይ የሃብት ንብረት እገዳ መጣሉን የገለጸው ኮሚሽኑ ለእስር የተዳረጉት የመንግስት ባለስልጣናት ባለሙያዎች ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሚገኝ ተመልክቷል። ከሁለት ቀን በፊት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተመሳሳይ መንገድ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 125 ግለሰቦችን ለእስር መዳረጉ ይታወሳል።
በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ውስጥ በማገልገል ላይ ነበሩ የተባሉት እነዚሁ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ላይ አስተዳደራዊ በደል ፈጽመዋል ሲል ኮሚሽኑ ይገልጻል።

በውጭ ብድር የተጀመሩ የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታቸው ሳይጠናቀቅ የብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 21 ፥ 2009)
ኢትዮጵያን ስኳር ላኪ ሃገር ያደርጋሉ ተብለው ከውጭ በተገኘ ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ግንባታቸው ከሰባት አመት በፊት የተጀመሩ ፋብሪካዎች ግንባታቸው ተስተጓጉሎ እያለ ብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ።
በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ውስጥ የሚገኘው መንግስት በበኩሉ በመገንባት ላይ ያሉትን ጨምሮ በስራ ላይ ያሉ የስኳር ፋብሪካዎች ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለመስራው መወሰኑን ይፋ አድርጓል።
መንግስት ከተለያዩ አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት በብድር ባገኘው ገንዘብ የወልቃይት፣ የኦሞ፣ ኩራዝ አንድ ሁለትና ሶስት እንዲሁም የጣና በለስ ቁጥር አንድና ሁለት ፕሮጄክቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወሳል።
ይሁንና ሃገሪቱን ከስኳር እጥረት በማላቀቅ ኢትዮጵያ ምርቷን ወደ ውጭ ሃገር በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እንድታገኝ ያደርጋሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ፋብሪካዎች አብዛኞቹ በጅምር ላይ መቅረታቸው ተመልክቷል።
ፋብሪካዎቹ በከፍተኛ የፋይናንስ እጥረት ውስጥ በመግባታቸውና የተጀመሩ ፕሮጄክቶችን ለማስጨርስ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ በማስፈለጉ ምክንያት መንግስት ነባሮቹንና አዳዲስ ግንባታዎች በሽርክና ለማካሄድ መወሰኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ፋብሪካዎቹ በአምስት አመት ውስጥ ወደ ምርት ይገባሉ ተብሎ የተጠበቁ ሲሆን፣ ግንባታቸው በ25 በመቶ ላይ የሚገኝ እንዳለም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን መረጃ ያመለክታል።

Wednesday, December 14, 2016

ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 አመታት ወደ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሃገራት ተርታ እንደማትገባ ተመድ ይፋ አደረገ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)

ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 አመታት ወደ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሃገራት ተርታ እንደማትገባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይፋ አደረገ።
የመንግስት ባለስልጣናት ሃገሪቱ በቀጣዮቹ አስር አመራት ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገራት ተርታ ትገባለች ሲሉ በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል። ይሁንና በጉዳዩ ዙሪያ ሰሞኑን ሪፖርቱን ያወጣው የድርጅቱ የንግድና የልማት ጉባዔ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ 16 ሃገራት እቅዱን እንደሚያሳኩ ቢገልጽም፣ ኢትዮጵያን ሳያካትት ቀርቷል።

ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ገቢ 400 ሚሊዮን ዶላር (ወደ አንድ ቢሊዮን ብር) አካባቢ ልታጣ እንደምትችል ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)

በኢትዮጵያ በተያዘው የፈረንጆች አመት ከቱሪዝም ገቢ 400 ሚሊዮን ዶላር (ወደ አንድ ቢሊዮን ብር) አካባቢ ልታጣ እንደምትችል ተገለጸ።
በሃገሪቱ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን አለመረጋጋት በቱሪዝም እንቅስቃሴው ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖን እያሳደረ እንደሚገኝ አፍሪካ ኒውስ መጽሄት የተለያዩ መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ረቡዕ ባቀረበው ዘገባ አስፍሯል።
በፈረጆች 2015 አም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ ወደ ሶስት ቢሊዮን ዶላር አካባቢን አግኝታ የነበረ ሲሆን፣ በ2016/2017 አም ተመሳሳይ ገቢን ለማግኘት እቅድ ተይዞ እንደነበር ለማግኘት እቅድ ተይዞ እንደነበር ታውቋል።

በአሜሪካ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ የተመራ የልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባቱ ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ባለው የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ዙሪያ ለመምከር በአሜሪካ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ የተመራ የልዑካን ቡድን ረቡዕ አዲስ አበባ መግባቱ ታውቋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሃገሪቱ ተግባራዊ የተደረገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ ዕርምጃው በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ስጋትን አሳድሯል ሲል በተደጋጋሚ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
በአዲስ አበባ የሶስት ቀን ቆይታ የሚኖረው ይኸው የልዑካን ቡድን የአሜሪካ አለኝ የምትለውን የሰብዓዊ መብት ስጋት አንስቶ ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክር ታውቋል።

የኢትዮጵያ መንግስት በጸጥታ ሃይሎች የተወሰዱ የሃይል ዕርምጃዎች ሽፋን እንዳያገኙ ድረገጾችን መዝጋቱን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ሲካሄድ ከቆየው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ መንግስት በጸጥታ ሃይሎች የተወሰዱ የሃይል ዕርምጃዎች ሽፋን እንዳያገኙ በትንሹ የ16 የመገናኛ ብዙሃንን ተቋም ድረገጾች እንዲዘጉ ማድረጉንም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ረቡዕ አዲስ ባወጣው ሪፖርት አስታወቀ።
የማህበራዊ ድረ-ገጾችን ጨምሮ የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ለመዝጋትና ለመቆጣጠር በተካሄደው በዚሁ የአፈና ዕርምጃ የተቃዋሚ ፓርቲ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች አካላት ሰለባ መሆናቸውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ኦፕን ኦብዘርባቶሪ ኦፍ ኔትዎርክ ኢንተርፊረንስ ከተሰኘ ተቋም ጋር በጋራ ያካሄደውን ጥናት አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል።
ባለፈው አመት በተለይ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎትን ለመዝጋት የተወሰደው ዕርምጃ ተግባራዊ ተደርጎ በሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወቅትም መቀጠሉን ሁለቱ አለም አቀፍ ተቋማት ገልጸዋል።

Ethiopia: Internet censorship causing severe restrictions to information

Ethiopian regime’s deadly crackdown on protesters in the last one year was accompanied by blockage of the internet and social media, according to a report by Amnesty International.
“The crackdown on protests was accompanied by increasingly severe restrictions on access to information and communications in large parts of the country by cutting off internet access, slowing down connections and blocking social media websites,” Amnesty said.
Investigations and interviews by Amnesty international also revealed that at least 800 people have been killed in the last one year of anti-government protests.
“Amnesty International’s research since the protests began revealed that security forces responded with excessive and lethal force in their efforts to quell the protests. Amnesty International interviewed at least fifty victims and witnesses of human rights abuses during the protests, twenty human rights monitors, activists and legal practitioners within Ethiopia, and also reviewed other relevant primary and secondary information on the protests and the government’s response. Based on this research, the organisation estimates that at least 800 people have been killed since the protests began.”
It said in addition to using security forces to quash protests, the Ethiopian authorities have restricted access to internet services during the protest.

Friday, December 9, 2016

የእስራዔል መንግስት በሃገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም እንዳይለግሱ ጥሎ የቆየውን እገዳ አነሳሁ አለ

ኢሳት (ኅዳር 30 ፥ 2009)
የእስራዔል መንግስት በሃገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም እንዳይለግሱ ጥሎ የቆየውን እገዳ አነሳ።
የእስራዔል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከሃገሪቱ ውጭ የተወለዱ ወይም የHIV/AIDS ስርጭት ባለባቸው ሃገራት ለአንድ አመት ያህል ቆይታ ያደረጉ ቤት-እስራዔላዊያን ደም እንዳይለግሱ ከ10 አመት በፊት እገዳ መጣሉ ይታወሳል።
ይሁንና የእስራዔል መንግስት ጥሎ የነበረው እገዳ በአግባቡ ለህዝብ ይፋ ባልተደረገበት ወቅት ማሪቭ (maiariv) የተሰኘ የሃገር ጋዜጣ ከኢትዮጵያውያን ይወሰድ የነበረ ደም ሲወገድ መቆየቱን ማጋለጡ ሃርቴዝ ጋዜጣ አርብ ዘግቧል።
የእስራዔሉ የደም ባንክ የሚቆጣጠረው ማገድ ዴቪድ አደም የተሰኘው ኩባኒያ የወሰደውን ይህንኑ ዕርምጃ ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ተከታታይ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍን ሲያደርጉ ቆይተዋል።
በተለያዩ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና በምዕራባውያን ሃገራት ዘንድ ቁጣን ቀስቅሶ የነበረው ድርጊት ለ10 አመት ያህል መነጋገሪያ ሆኖ መሰንበቱን ጋዜጣው አውስቷል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በእስር ቤት አለመኖሩ ተገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 30 ፥ 2009)
በዝዋይ እስር ቤት በእስር ላይ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በእስር ቤቱ አለመኖሩንና ያለበት ቦታ እንደማይታወቅ የጋዜጠኛውን ጉዳይ የሚከታተሉ አካላት ለኢሳት ገለጹ።
የጋዜጠኛው ቤተሰቦች በበኩላቸው የማህበራዊ ድረገጾች ባሰራጩት መረጃ ዝዋይ እስር ቤት ተመስገንን ለመጠየቅ ሁለት ቀን ቢሄዱም፣ በእስር ቤቱ ተመስገን የሚባል የመንግስት እስረኛ አናውቅም የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው አረጋግጠዋል።

Thursday, December 8, 2016

Ethiopia: Dozens desert army, join resistance forces patriotic-g7 File photo of PG7 fighters

ESAT News (December 8, 2016)

Patriotic Ginbot 7, a group fighting the Ethiopian government, said 46 soldiers have deserted the regime army and joined the resistance movement.
The soldiers, who defected after a marathon negotiations and joined Patriotic Ginbot 7, have defected with various weapons including 9 artilleries, 6 snipers and RPGs among others, according to a source on the ground with the fighters.

የአውሮፓ ሃገራት ዜጎቻቸው ወደ ሰሜን ጎንደር እንዳይጓዙ አዲስ ማሳሰቢያን አወጡ

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
በሰሜን ጎንደር የተለያዩ አካባቢዎች በመንግስትና በግንቦት ሰባት ሃይሎች መካከል የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ የአውሮፓ ሃገራት ዜጎቻቸው ወደ ስፍራው እንዳይጓዙ አዲስ ማሳሰቢያን አወጡ።
ተደጋጋሚ የጉዞ ማሳሰቢያን ሲያወጡ የነበሩት የጀርመንና የቤልጅየም መንግስታት በኢትዮጵያ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ መሻሻልን ቢያሳይም በአማራ ክልል ስር በሚገኙ ሶስት ዞኖች የጸጥታ ስጋት መኖሩን ይፋ አድርገዋል።
ለዜጎቻቸው አዲስ የጉዞ ማሳሰቢያን ያሰራጩት ሁለቱ የአውሮፓ ሃገራት በጸገዴ፣ ምዕራብና የታች አርማጭሆ የሰሜን ጎንደር አካባቢዎች ዜጎቻቸው ጉዞን ከማድረግ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
የፈረንጆች አዲስ አመት መግቢያን ምክንያት በማድረግ የጀርመንና የቤልጂየም ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ በብዛት የሚጓዙ ሲሆን፣ የሁለቱ ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሁኔታውን ከግምት ውስጥ በማስገባት የጉዞ ማስጠንቀቂያ ማሰራጨታቸውን ዘቮይስ (The Voice) የተሰኘ መፅሄት ዘግቧል።
በቅርቡ የግንቦት 7 ሃይሎች እንዲሁም ራሳቸውን ያደራጁ የነጻነት ሃይሎች በሰሜን ጎንደር ዞን ስር ከመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ጋር ግጭት ውስጥ መግባታቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ የከፋ አፈናን ከሚፈጽሙ ሃገራት መካከል ግንባር ቀደም ሃገር ተብላ ተፈረጀች

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
ኢትዮጵያ በተያዘው 2016 የፈረንጆች አም በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ የከፋ አፈናን ከሚፈጽሙ ሃገራት መካከል ግንባር ቀደም ሃገር ተብላ ተፈረጀች።
በቴክኖሎጂው አጠቃቀምና ተደራሽነት እንዲሁም ቁጥጥር ዙሪያ አመታዊ ጥናቱን ይፋ ያደረገው ፍሪደም ሃውስ የተሰኘ ተቋም ቻይና፣ ሶሪያና ኢትዮጵያ የከፋ የተባለ አፈናን ከሚፈጽሙ ሃገራት መካከል ዋነኛ መሆናቸውን ይፋ አድርጓል።
ካለፈው አመት ጀምሮ ኢንተርኔት አገልግሎት ላይ እገዳንና ቁጥጥርን ተግባራዊ አድርጋ የምትገኘው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከሚገኙ 54 ሃገራት መካከል የቴክኖሎጂው ጠላት ተደርጋ ተፈርጃለች።
በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ የኢትዮጵያ መንግስት በመደበኛውና በተጓዳኝ የኢንተርኔት አገልግሎት ላይ እገዳን ጥሎ የሚገኝ ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መውጣቱን ምክንያት በማድረግም አገልግሎቱ ታግዶ ይገኛል።

በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ኪሳራ የደረሰበት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ መግባቱ ተነገረ

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ለሃገር ውስጥና ለውጭ ባለሃብቶች መሬትን ለማቅረብ ሊያካሄድ ከነበረው ስራ ጋር በተገናኘ ያጋጠመው በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ኪሳራ አዲስ ውዝግብ መቀስቀሱ ተግለጸ።
የፌዴራልና የክልል ባለስልጣናት ለደረሰው ኪሳራ ሃላፊነቱን ማን መውሰድ እንዳለበት ለአንድ አመት ያህል ምክክርን ሲያካሄዱ ቢቆዩም ጉዳዩ ዕልባት አለማግኘቱ ታውቋል።
በጋምቤላ ክልል ብቻ ከ100 የሚበልጡ የሃገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት የሚሆን ሰፊ የእርሻ መሬት ቢሰጣቸውም የፌዴድራል ባለስልጣናት የመሬት ርክክቡ ህገወጥ ነው በማለት ባለሃብቶቹ ስራቸውን እንዲያቆሙ መወሰኑ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በበኩሉ በዚሁ ክልል ተመሳሳይ ይዞታ ላይ በርካታ ባለሃብቶች በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ብድር በመውሰድ ኪሳራ ማጋጠሙ በቅርቡ ይፋ አድርጓል።

በኢትዮጵያ የተከሰተው የዋጋ ግሽበት ከ5.6 ወደ 7 በመቶ ከፍ ማለቱን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ አጋጥሟል የተባለን የኢኮኖሚ መዳከም ተከትሎ የሃገሪቱ የዋጋ ግሽበት በተያዘው ወር ከአምስት ነጥብ ስድስት ወደሰባት በመቶ ከፍ ማለቱን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ሃሙስ አስታወቀ።
የአለም ባንክ ሃገሪቱ አጋጥሟት ያለው የውጭ ንግድ ገቢ መቀነስና የውጭ ምንዛሪ ክምችት ማሽቆልቆል በኢትዮጵያ ዋጋ ግሽበት ሊያስከትል ይችላል ሲል ማሳሰቡ ይታወሳል።
ባንኩ ሲሰጥ የቆየውን ትንበያ ተከትሎ የሃገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበትን ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በምግብ ነክ ሸቀጣሸቀጦች ላይ የዋጋ ጭማሪ በመከሰቱ ምክንያት የዋጋ ግሽበቱ ከፍ ሊል መቻሉን በሪፖርቱ አመልክቷል።

ከአውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የታሰሩት የደ/ር መረራ ጉዲናን መታሰር ተከትሎ የእሳቸው ደጋፊ ይሆናሉ የተባሉ ወጣቶች እየተለቀሙ በመያዝ ላይ ናቸው።

ኅዳር ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የታሰሩት የደ/ር መረራ ጉዲናን መታሰር ተከትሎ የእሳቸው ደጋፊ ይሆናሉ የተባሉ ወጣቶች እየተለቀሙ በመያዝ ላይ ናቸው። እስሩ እርሳቸው በተያዙ ማግስት የጀመረ ሲሆን፣ እስከዛሬ ድረስ በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ የኦሮምያ ወረዳዎች እንዲሁም በአምቦና አጎራባች ቀበሌዎች በርካታ ሰዎች ተይዘው ታስረዋል። በተመሳሳይ ዜና በደቡብ ወሎ ሃይቅ ከተማ በርካታ ወጣቶች በአዲሱ ወታደራዊ እዝ አማካኝነት መሰታሰራቸውን ለማወቅ ተችሎአል። እስካሁን በደረሰን መረጃ ከ50 ያላነሱ ወጣቶች በቁጥጥር ስር ውለዋል። በሌላ በኩል በተለያዩ መስሪያ ቤቶች በዘበኝነት ተቀጥረው ስራ የሚሰሩ የቀድሞ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንደገና መታዋቂያ እንዲያወጡና እንዲመዘገቡ እየተደረገ ነው። ሰራተኞቹ ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት ጋር አዲስ ውል እንዲፈርሙ እየተደረገ ሲሆን፣ በተለይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰሩ ሰራተኞች የጦር መሳሪያ እንዳይዙ ፣ በስራ ወቅትም ወታደሮች ካልሆኑት ጋር ተመድበው እንዲሰሩ መመሪያ ተላልፏል።

Thursday, December 1, 2016

ከሚኒስትሮች ጀምሮ እስከ ታችኛው ዕርከን ድረስ በስልጣን ላይ የሚገኙ ባለስልጣናት የህወሃት አገልጋዮች መሆናቸውን አንድ የኤምባሲ ባልደርባ ተናገሩ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
አሁን በስልጣን ላይ ባለው ስርዓት ውስጥ ከሚኒስትር ጀምሮ እስከታችኛው ዕርከን የሚሰሩ በሙሉ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ አገልጋዮች መሆናቸውን በጀርመን ፍራንክፈርት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባልደርባ የነበሩ ገለጹ። ከስርዓቱ ጋር በመቆየታቸው መጸጸታቸውንም የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ ጠይቀው ከህዝብ ጎን በመሰለፍ ለለውጥ እንደሚሰሩም አስታውቀዋል።

የዶ/ር መረራ ጉዲና መታሰር በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት ዶ/ር መረራ ጉዲናን ለእስር መዳረጉን በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሃሙስ ገለጸ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) አመራር በቁጥጥር ስር መዋላቸው ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ የተካሄደ አፈና ነው ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ሃላፊ የሆኑት ሚቼሌ ካጋሪ አስታውቀዋል።
መንግስት የወሰደው ዕርምጃም በሃገሪቱ ያለውን ውጥረት እንደሚያባብሰው ያሳሰቡት ተወካዮዋ እርምጃው በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ ለሚከታተሉ አለም አቀፍ አካላት ጥሪን ያስተጋባ ነው ሲሉ አክለው ገልጸዋል።

ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲመቻች ጥሪ ቀረበ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባላት ህብረቱ ለእስር በተዳረጉት ዶ/ር መረራ ጉዲና ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹ ጥሪ ማቅረባቸውን ዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ ሃሙስ ዘገበ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር መረራ በኢትዮጵያ ተደንግጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መመሪያን ተላልፈው ተገኝተዋል በሚል ረቡዕ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
የፓርቲው አመራር ዶ/ር መረራ ከአንድ ሳምንት በፊት የአውሮፓ ህብረት ዋና መቀመጫ በሚገኝበት ብራሰልስ ተገኝተው ከህብረቱ የፓርላማ አባላት ጋር ውይይት ማካሄዳቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በሽያጭ በማቅረብ ላይ ነው ተባለ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት ለጎረቤት ደቡብ ሱዳን የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በሽያጭ በማቅረብ ላይ መሆኑን የሃገሪቱ አንድ የመገናኛ ብዙሃን ተቋም በብቸኝነት አግንቼዋለሁ ያለውን ሚስጢራዊ መረጃ ዋቢ በማድረግ አጋለጠ።

ባለፉት 10 ወራት ብቻ ወደ 90ሺ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በስደት የመን መግባታቸውን ተመድ ገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
ባለፉት 10 ወራቶች ብቻ ወደ 90ሺ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በስደት የመን መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን አስታወቀ።
ጦርነት ዕልባት ወዳላገኘባት የመን የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ስጋት እንዳደረሰባት የገለጸው ድርጅቱ ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ከ70ሺ የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን ወደ ሃገሪቱ ገብተው እንደነበር አውስቷል።

Friday, November 25, 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በወያኔ ጦር ላይ በተለያዩ ቦታዎች በተደጋጋሚ ጥቃት መፈፀሙን በመቀጠል ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ታወቀ፡፡

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)

የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ነበልባል የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ህዳር 10 ቀን 2009 ዓ.ም ለሊት ጎንደር ዳንሻ ከተማ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በተባለ ቦታ ሰፍሮ ከሚገኝ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ላይ በፈፀመው ድንገተኛ ማጥቃት ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ አጥቅቶ ተሰውሯል፡፡ በወሰደው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃም 15 የወያኔ ቅጥረኛ ወታደሮችን በመግደል ቁጥራቸው ያልታወቀ ደግሞ ማቁሰሉን አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ከስፍራው ባደረሰን ዘገባ አስታውቋል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ጥቃቱን በመቀጠል ህዳር 13 ቀን 2009 ዓ.ም በአብደራፊ ከተማ ዙሪያ በህወሓት መከላከያ ሰራዊት ላይ ተመሳሳይ የደፈጣ ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን ባደረገው ሰፊ የማጥቃት እርምጃም 25 በመግደልና 17 በማቁሰል በቅጥረኛው የህወሓት ጦር ላይ ጠንካራ ክንዱን በማሳረፍ የበላይነትን ተጎናፅፎ የህወሓት ቅጥረኛ ወታደሮችን እንቅስቃሴ በመግታት መበታተን እንደቻለ ሪፖረተራችን አክሎ ገልጿል፡፡
ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት እየፈፀመ ያለውን ቆራጥ ተጋድሎ ጥቃቱ በሚፈፀምበት ቦታ ሁሉ ሙሉ በሙሉ የህዝብን ድጋፍ እያገኘ ሲሆን የቆመለትን አላማ ከግብ ለማድረስ ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ ትንሳኤ እስኪሆን ድረስም ጀግኖች የአርበኞች ግንቦት 7 ነበልባል ሰራዊት ወደፊት በመግፋት በተግባር የኢትዮጵያ አለኝታነታቸውን እያስመሰከሩ ይገኛሉ፡፡

Tuesday, November 22, 2016

Ethiopia: Amharas in Benishangul face displacement

ESAT News (November 22, 2016)
Amharas who have resettled and called it home in Benishangul Gumuz region since 30 years ago during the former Ethiopian regime have said  they are facing harassment and threat of displacement from their land.
The Amharas, who settled in Benishangul in a resettlement program in the former government are being threatened by authorities to leave the region, according to a source who spoke on the phone with ESAT.
Hundreds of Amharas in Asosa have been displaced after authorities gave their land to developers, forcing them to migrate to towns and other areas.
Meanwhile, security forces have detained several youth in Benishangul Gumuz following the martial law declared in October, sources told ESAT.
An estimated 80,000 Amharas live in Benishangul Gumuz region in western Ethiopia.

Monday, November 21, 2016

ማዕበል ከፋሲል የኔአለም

የትኛውም ለህዝብ ነጻነት የሚታገል ድርጅት ከውስጥም ከውጪም ማዕበል ያጋጥመዋል። በማዕ በል ሳይመታ ለውጤት የበቃ ድርጅት በታሪክ ያለ አይመስለኝም፤ ማዕበል የአንድ ድርጅት ተፈጥሮአዊ ባህሪው ነው ማለትም ይቻላል። የትኛውም ድርጅት ማዕበል እንዳይነሳ ማድረግ አይችልም፣ ውስጣዊ ማእበል እንዳይነሳ ማድረግ ቢችል እንኳን ውጫዊ ማዕበሉን በፍጹም ማስቀረት አይችልም። ትልቁ ነገር ድርጅቱ ማእበሉን እንዴት በጥበብ ያልፈዋል የሚለውን ጥያቄ መመለሱ ላይ ነው። ማእበል ለአንድ ድርጅት አወንታዊ ወይም አሉታዊ ነገሮችን ይዞ ይመጣል። አንዳንድ ድርጅቶች የተነሳባቸውን ማእበል በጥበብ ማለፍ ያቅታቸውና ይጠፋሉ ( የማእበል አሉታዊ ጎኑ መሆኑ ነው)፣ ሌሎቹ ደግሞ ማእበሉን ማለፍ ብቻ ሳይሆን ከማእበሉ ትምህርት ወስደውበት ተጠናክረው ይወጣሉ ( የማእበል አወንታዊ ጎኑ ነው)።

Thursday, November 17, 2016

CPJ renews calls to Ethiopian regime to release all journalists

Ethiopia should immediately release all journalists detained amid an intensifying crackdown on the media, the Committee to Protect Journalists said on Thursday.
In recent weeks, Ethiopian authorities have jailed Getachew Worku, newspaper editor, as well as two members of the award-winning Zone 9 bloggers’ collective, which has faced continuous legal harassment on terrorism and incitement charges.
A fourth journalist has been missing for a week; his family fears he is in state custody, CPJ said in a state
“Silencing those who criticize the government’s handling of protests will not bring stability,” CPJ Africa Program Coordinator Angela Quintal said from New York. “The constant pressure on Zone 9 bloggers with repeated arrests and court appearances is clearly designed to intimidate the remaining independent journalists in Ethiopia.”

የአርበኞች ግንቦት7 ሃይል ከህወሃት/ኢህአዴግ ወታደሮች ጋር በቀብትያ ሁመራ እና አጎራባች ቀበሌዎች እየተዋጋ ነው

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአርበኞች ግንቦት7 የሰሜን ጎንደር አስተባባሪ እንደገለጹት፣ አባሎቻቸው በሰሜን ጎንደር በተለያዩ አካባቢዎች ለወራት ሲደራጁና ሲያደራጁ ከቆዩ በሁዋላ፣ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ወታደራዊ ጥቃት በመፈጸም ላይ ናቸው። በተለይ ከትናንት ጀምሮ በቃፍታ ሁመራ እና በአከር አካባቢ ከፍተኛ ውጊያ እያካሄደ መሆኑንም ተናግረዋል።

በአባይ ግድብ አካባቢ ያለው የስራ እንቅስቃሴ መዳከሙን ጋዜጠኞች ገለጹ ።

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ‹‹ በአባይ ግድብ ላይ ያለው እንቅስቃሴ ቆሟል የሚል ወሬ በስፋት እየተወራ ነውና ወሬውን አክሽፉ!” ተብለው ለጉብኝት የተላኩት ጋዜጠኞች ምንም አይነት የስራ እንቅስቃሴ ባለማየታቸው የሚወራው ትክክል መሆኑን አረጋጋጥው መመለሳቸውን ለኢሳት ገለጹ።
ሰሞኑን ወደ አባይ ግድብ የተላከው የ መንግስት ጋዜጠኞች ቡድን ለጉብኝት በቆየበት አንድ ቀን፤ ምንም አይነት ስራ ሲሰራ አለመመልከቱን ገልጿል፡፡ ‹‹ ለአንድም ደቂቃ ስራው አይስተጓጎልም ›› የተባለለት ይህ የግድብ ስራ አልፎ አልፎ ከሚንቀሳቀሱ ተሸከርካሪዎች በስተቀር ምንም አይነት የስራ እንቅስቃሴም ሆነ ሰራተኞችን አለመመልከቱንና ስራው ተስተጓጉሏል የሚለው እውነት መሆኑን የቡድኑ አባላት ተናግረዋል።

በሶማሊያ ክልል በኮሌራ ወረሽኝ 35 ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በምስራቅ ኢትዮጵያ ኦጋዴን አካባቢዎች በኮሌራ በሽታ 35 ሰዎች መሞታቸውንና ድርቁን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊ ቀውስ እየተፈጠረ መሆኑን የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት አስታወቀ። በድርቁ ምክንያት እንስሳት እየሞቱ ነው። የምግብ እጥረት ተጠቂ የሆኑት የኦጋዴን ነዋሪዎች አፋጣኝ እርዳታ ካላገኙ አደጋው የከፋ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።

በኢንተርኔት አፈና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች ።

ኅዳር ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በዜጎቻቸው ላይ አፈና በማድረግ የመረጃ እቀባ ከሚያደርጉ አገራት ውስጥ ቻይና፣ ሶሪያ እና ኢራንን በመከተል ኢትዮጵያ በዓለም አራተኛ፣ በአፍሪካ ደግሞ በአንደኝኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ፍሪደም ሃውስ አስታውቋል። በኢንተርኔት ስርጭት ሁዋላ ቀር የሆነችው ኢትዮጵያ በኢንተርኔት ተጠቃሚ ዜጎቿ ላይ በምታደርገው እቀባዎችና አፈናዎች ግን ቀዳሚ ሆናለች ብሎአል።

ዮናታን ተስፋዬ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት እንደሚታሰር ታውቋል

ፌስቡክ ላይ በጻፋቸው ፅሁፎች ምክንያት የሽብር ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በፍ/ቤት እየታየ የሚገኘውና በእስር ቂሊንጦ ያለው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ በሚገኝበት እስር ቤት ውስጥ ከአርብ ህዳር 2/2009 ዓ.ም ጀምሮ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት ታስሮ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለዚህ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የዳረገው ህዳር 2/2009 ዓ.ም የፍርድ ቤት ቀጠሮ የነበራቸው እነ አቶ በቀለ ገርባ ወደ ፍርድ ቤት አንሄድም በሚል ከቂሊንጦ እስር ቤት አስተዳደር ጋር አለመግባባት ፈጥረው ድብደባ ሲደርስባቸው አቶ ዮናታን ‹‹ለምን ትደበድቧቸዋላችሁ፤ በመግባባት ቢሆን አይሻልም ወይ›› በሚል ለግልግል ጣልቃ መግባቱን ተከትሎ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋዬ በተለይ አብሮት የታሰረው አቶ አዲሱ ቡላላ ላይ ድብደባ ሲደርስበት ‹‹ተው አትደባደቡ›› በማለቱ ‹‹ምን አገባህ›› ተብሎ በራሱም ላይ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞበት ከዚያ ወዲህ በሰንሰለት ለመታሰር እንደተዳረገ ታውቋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ ሰንሰለቱ የሚፈታለት ቤተሰቦቹ ሊጎበኙት ሲጠራ ብቻ እንደሆነም የመረጃው ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ አቶ ዮናታን መከላከያ ማስረጃዎችን ለማድመጥ ለህዳር 19/2009 ዓ.ም ተለዋጭ የፍ/ቤት ቀጠሮ ላይ እንደሚገኝ ይታወሳል፡፡

Wednesday, November 16, 2016

በቆላ ቃብቲያ ኹመራ ከፍተኛ ጦርነት ተቀስቅሷል

zehabesha
 ዛሬ ኅዳር 7 ቀን 2009 ዓ.ም ከቀኑ 11.00 አካባቢ ጀምሮ የወያኔ ጦር ከአማራ ገበሬዎች ላይ ጦርነት ከፍቷል። በአካባቢው የጎበዝ አለቆች የሚመራው የአማራ ገበሬዎች ጦር በአጋዚ ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ለማጥቃት የሄደው የወያኔ አጋዚ ጦር ከምልሻዎች እርዳታ መጠየቁን ሰምተናል።

Monday, October 31, 2016

በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ ለተጨማሪ 6 ወራት ስጋት ሆኖ እንደሚቀጥል ተገለጸ


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ እኤአ እስከ 2017 አጋማሽ ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ድርጅት (UNOCHA) ዛሬ ሰኞ ባወጣው ሪፖርት አስታወቀ።
ድርቁ አርብቶ አደር በሆኑ በደቡብና በምስራቅ የአገሪቷ አካባቢዎች ማለትም በባሌ፣ ጉጂና፣ ቦረና ዞኖች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል። ግጦሽ እና የውሃ አቅርቦት እየቀነሰ በመምጣቱ የቀንድ ከብቶች አካላቸው በተጎሳቆለ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ይኸው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ድርጅት (UNOCHA) ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

አዲስ የተመሰረተው የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ እድገትና ብልጽግናን የሚያመጣ የፌዴራል ስርዓት መገንባት ዋነኛ አላማው መሆኑን አስታወቀ


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
በአራት የፖለቲካ ድርጅቶች የተመሰረተው የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ እድገትና ብልጽግናን የሚያመጣ የፌዴራል ስርዓት መገንባት ዋነኛ አላማው መሆኑን አስታወቀ።
በሃገራዊ ንቅናቄው የምስረታው ስነስርዓት ላይ ያወጣው የጋራ መግለጫ እንደሚያመለክተው ብሄር ብሄረሰቦች መብታቸው የተከበረባትና ሉዓላዊነቷ የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን መመስረት የህብረቱ ዋነኛ ዓላም መሆኑ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ በኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ በአርበኞች ግንቦት ሰባት፣ በአፋር ህዝብ ፓርቲ፣ እና በሲዳማ ህዝቦች ዴሞክራሲያው ንቅናቄ የተፈጠረ ህብረት መሆኑን በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ተገልጿል።

ሲራጅ ፈርጌሳ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ተከትሎ የታሰሩትን ሰዎች ቁጥር ለመግለጽ ፈቃደኛ አይደሉም


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ የተደነገገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ የታሰሩ ሰዎችን ቁጥር ለመግለጽ የመከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈርጌሳ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተዘገበ።
የኮማንድ ፖስቱ ዋና ጸሃፊ ተደርገው የተሰየሙት የመከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈርጌሳ ዕሁድ በሰጡት መግለጫ፣ 2ሺህ ሰዎች ምክር ተሰጥቷቸው ተለቀዋል ቢሉም የታሰሩትን ቁጥር ለመገለጽ ግን ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተመልክቷል።

በኢትዮጵያ በሶስት ሳምንት ጊዜ ውስጥ አንድ ሺህ ያህል ሰው መገደሉን የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ አስታወቀ


ኢሳት (ጥቅምት 21 ፥ 2009)
ለአንድ አመት ያህል በዘለቀውና በኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል በቀጠለው ግድያ በሶስት ሳምንት ጊዜ ውስጥ አንድ ሺህ ያህል ሰው መገደሉን የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ አስታወቀ።
ድርጅቱ ዕሁድ ጥቅምት 20 ቀን 2009 እንዳስታወቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ የተገደሉት ሰዎች ቁጥር 1ሺ ሲደርስ 40ሺ ሰዎች ደግሞ ታስረዋል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በኦሮሚያ ክልል ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ አባብሶታል በማለት ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ጥሪ ያቀረበው የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ፣ በሶስት ሳምንት ውስጥ የተገደሉት ሰዎች 1ሺ ሰዎች ስለመድረሳቸው ያገኘውን መረጃ ለማረጋገጥ መቸገሩን የገለጸ ሲሆን፣ ይህም የግንኙነት መስመሮች በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሙሉ በሙሉ በመቋረጣቸው የተከተለ መሆኑን አስረድቷል። የግንኙነት መስመሮቹ መቋረጥ በኦሮሚያን በአማራ ክልሎች እየተካሄደ ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ ለመደበቅ እንደሆነም አመልክቷል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል ከተካሄደውና 1ሺህ ሰዎች ከተገደሉበት ዕርምጃ የ248 ሟቾች አድራሻን በመግለጫው ያመለከተው የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ፣ ከ40 ሺህ ያህል እስረኞች የ3ሺህ 708ቱን አድራሻ አመልክቷል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጆችን ተከትሎ በተካሄደው የመንግስት ሃይሎች ዕርምጃ፣ በሻላና አጄ ብቻ 85 እንዲሁም በአርሲ ነገርሌ 70 ሰዎች መገደላቸውን አስፍሯል።
የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ ይህንን የሰብዓዊ መብት ሪፖርት ለተባበሩት መንግስታት የጸጥታ ም/ቤት፣ ለመንግስታቱ ማህበር የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና ለአፍሪካ ህብረት አስታውቋል።

ሶማሊያ የሚገኙ በርካታ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ትእዛዝ አንቀበልም በማለት ገሚሶቹ ሲጠፉ ሌሎች ወደ ኢትዮጵያ አንመለስም አሉ

ጥቅምት ፳፩ (ሃያ አንድ ቀን ፳፻ / ኢሳት ዜና :- የኢሳት የወታደራዊ የደህንነት ምንጮች እንደገለጹት በሶማሊያ በአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ስም ያልታቀፉትና ላለፉት 4 አመታት ከአልሸባብ ጋር ሲዋጉ ከነበሩት ወታደሮች መካከል በመቶዎች የሚቆጠሩት ትእዛዝ አንቀበልም በማለት አምጸው ከቀዩ በሁዋላ ከ70 ያላናሱት የጦር መሳሪያዎቻቸውን ሸጠው ባህር ተሻግረው ወደ አረብ አገራት ሰያቀኑ፣ ቀሪዎቹ ወደ አገሩ ከተመለሰው ጦር ጋር አብረን አንጓዝም በማለት ወደ ተለያዩ አካባቢዎች መበታተናቸውን ገልጸዋል።

አመጹ ለወራት የዘለቀ መሆኑን የገለጹት ምንጮች፣ ወታደሮች ከሚያነሱዋቸው ጥያቄዎች መካከል ዘረኝነትና የክፍያ መቋረጥ ዋነኞቹ ናቸው። በአመጹ ውስጥ የተሳተፉት ወደ ኢትዮጵያ እንደመለሱ ለማግባባት ሙከራ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም ወደ አገራቸው ሲመለሱ ከፍተኛ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በመግለጽ ማግባባቱን ሳይቀበሉት ቀርተዋል።

Ethiopia: unrest causing tourism crisis

ESAT News (October 31, 2016)
Ethiopian tourism minister contradicted the official narrative on the non effect of the state of emergency by admitting that the industry has been seriously derailed following the marshall law.
The minister, Ayisha Mohammed, said addressing a meeting that deliberated on the struggling industry that not only the number of tourists has decreased drastically following the state of emergency but those tourists who are in the country already have faced problems at check points, banks and Internet access which has been blocked by the regime.

U.S. Embassy complains of Ethiopia Internet shutdown

ESAT News (October 31, 2016)
The United States Embassy in Addis Ababa said the shutdown of Internet by the Ethiopian regime has severely affected its activities.
Responding to complaints by Ethiopians, who are having difficulty in communicating with the Embassy due to the blockage of the Internet and social media, the Embassy said it shared the frustrations of the public. “We share your frustration, as the restrictions severely affect our activities as well.”

Tuesday, October 25, 2016

አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት ህትመት ማቋረጡን አስታወቀ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሃገሪቱ በሚታተሙ የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ በማሳደሩ ምክንያት ህትመት ለማቆም መገደዱን አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት ይፋ አደረገ።
ከአስር አመት በፊት በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተመዝግቦ በወር አንድ ጊዜ ለህትመት ይበቃ የነበረው መጽሄቱ በመንግስት የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስራውን እንዳይቀጥል ማድረጉን የመጽሄቱ መስራችና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጸዳለ ለማ ለዜና ክፍላችን አስታውቃለች።
በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሲታተም የቆየው አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት በተለይ በኦሮሚያ ክልል ሲካሄድ የቆየውን ህዝባዊ ተቃውሞ ስፊ ዘገባን በመስጠት ሲዘግብ መቆየቱ ይታወሳል።
ይሁንና መጽሄቱን ተግባራዊ ተደርጎ በሚገኘው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ስራውን መቀጠል እንዳልቻለና የማይቻል አስቸጋሪ ደረጃ ውስጥ መግባቱን አዘጋጇ አስረድታለች።
የመንግስት ማተሚያ ቤቶች የህትመት ውጤታቸውን ለማሳተም ወደ ድርጅቱ ሲሄዱ ከኮማንድ ፖስቱ ፈቃድ እንዲያመጡ ይጠይቁ እንደነበር ህትመቱን ለማቆም የተገደደው የአዲስ ስታንዳርድ መጽሄቱ አዘጋጆች ገልጻለች።
መንግስት በማተሚያ ቤት በኩል እየፈጸመ ካለው ወከባ በተጨማሪ የህትመት ውጤቶችን የሚሸጡ ግለሰቦችንና የንግድ ድርጅቶች ጋዜጦችንና መጽሄቶችን ለመረከብ ፍራቻ አድሮባቸው እንደሚገኝም ታውቋል።
መጽሄቱ በአዋጁ ምክንያት ከህትመት ሲወጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን የተለያዩ አበይት ጉዳዮችን ግን በኦንላይን ህትመቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
የዚሁ አዋጅ መውጣት ተከትሎ በሃገሪቱ የሚታተሙ የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች ጋዜጦችን ማሳተም አስቸጋሪ እየሆነባቸው መምጣቱን ሲገልፁ መቆየታቸው ይታወሳል። ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው አዋጅ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በማንኛውም አካል ላይ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ስልጣንን ሰጥቷል።
ያለ-ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የቤት ለቤት ፍተሻ እንዲካሄድ የደነገገው አዋጁ፣ በመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች ላይ ቁጥጥር እንዲካሄድ ውሳኔን አስተላልፏል።
የአዋጁ መውጣትን ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲቋረጥ የተደረገ ሲሆን ሰዎች ለሚሰጧቸው አስተያየቶች ተጠያቂ እንደሚሆኑም ተደንግጓል። የጋዜጠኛ መብት ተማጋች ድርጅቶች አዋጁ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን አፍኖ እንደሚገኝ በመግለጽ ላይ ናቸው።
መቀመጫውን በዚህ በአሜሪካ ያደረገው ኮሚቴ ቱ ፕሮቴክት ጆርናሊስት (CPJ) ኢትዮጵያ በአለማችን በመገናኛ ብዙሃን ላይ አፈና ከሚያካሄዱ 10 ዋነኛ ሃገራት መካከል አንዷ መሆኗን ይገልጻል።
በሃገሪቱ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሁሉንም የመረጃ መለዋወጫ መንገዶች በመዝጋት ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንን አደጋ ውስጥ ከቶ እንደሚገኝ ሰኞ ባወጣው መግለጫ አስተውቋል።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአሜሪካ ህግ አውጪ አካል በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የውሳኔ ሃሳብ እንዲያጸድቅ አለም-አቀፍ ዘመቻ በማካሄድ ላይ መሆኑን ገለጸ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
የአሜሪካ ህግ አውጪ አካል የሃገሪቱ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የውሳኔ ሃሳብ እንድያጸድቅ እያካሄደ ያለው እንቅስቃሴ ተቀባይነት እንዲያገኝ አለም አቀፍ ዘመቻ በማካሄድ ላይ መሆኑን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ።
አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ የዘመቻው አካል የሆነና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር መድረክ ሰኞ በዚህ በአሜሪካ ኒው ዮርክ ከተማ መካሄዱ ታውቋል።
በሃገሪቱ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ በኒው ዮርክ ከተማ በተካሄደው የውይይት መድረክ በርካታ አለም አቀፍ ተቋማትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ግለሰቦች ተሳታፊ መሆናቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገልጿል።

ኢትዮጵያን የሚጎበኙ የውጭ ሃገር ቱሪስቶች ቁጥር በመቀነስ ላይ ነው ተባለ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ ሃገሪቱን የሚጎበኙ የውጭ ሃገር ቱሪስቶች ቁጥር በመቀነስ ላይ መሆኑ ተገልጸ።
መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉት ዲፕሎማቶች ከመዲናይቱ 40 ኪሎሜርት ርቀው እንዳይሄዱ የተቀመጠው እገዳ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጭ ሃገር ዜጎች ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩ ታውቋል።
መንግስት ዲፕሎማቶቹ ከመዲናይቱ 40 ኪሎሜርት ርቀው ሲሄዱ ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ ያለባቸው ለደህንነታቸው ነው ሲል መግለጹ ይታወሳል።

በኢትዮጵያ መንግስት የተፈጸመ የኢንተርኔት የስለላ ተግባር ክስ መቀጠል ይገባዋል ሲል አንድ ድርጅት ገለጸ

ኢሳት (ጥቅምት 15 ፥ 2009)
በአንድ አሜሪካዊ ዜጋ ላይ በኢትዮጵያ መንግስት የተፈጸመ የኢንተርኔት የስለላ ተግባር ክስ መቀጠል ይገባዋል ሲል ጉዳዩን በመከታተል ላይ የሚገኘው ድርጅት ይግባኝ አቀረበ።
ኤሌክትሮኒክስ ፍሮንቲየር ፋውንዴሽን የተሰኘውና የስለላ ድርጊቱ የተፈጸመባቸውን አቶ ኪዳኔን ጉዳይ በመከታተል ላይ የሚገኘው ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስት ለፈጸመው የስለላ ድርጊት ተጠያቂ መሆን ይገባዋል ሲል ይግባኙን ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ለሚገኝ የይግባኝ ፍርድ ቤት አቅርቧል።

Wednesday, October 19, 2016

UK foreign secretary refuse to address the case of Andargachew Tsige

ESAT News (October 19, 2016)

UK’s Foreign Secretary, Boris Johnson, has on Tuesday refused to answer questions in the House of Commons about the case of Andargachew ‘Andy’ Tsege, a British father of three who is held on Ethiopia’s death row, Reprieve, an organization following the case of Andy said in a release.

Tuesday, October 18, 2016

State of emergency is militarized response: rights researcher

ESAT News (October 18, 2016)
A senior researcher with Human Rights Watch says the state of emergency declared by the TPLF regime in Ethiopia meant a militarized response that will have a counterproductive effect in the long term stability of Ethiopia.
Felix Horne, senior researcher for the Horn of Africa with HRW also said that by declaring the state of emergency, the regime showed that it is not willing to take steps for change. “It is a message that they are not willing to open up the political space. They are not willing to address many of the grievance. It is a very worrying development,” Horne said in an exclusive interview with ESAT.

Saturday, October 15, 2016

የአርበኞችግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መግለጫ

የአርበኞች ግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2009 ዓ.ም. አካሂዶ በወቅቱ የአገራችን ሁኔታዎች ተነጋግሮ ውሳኔዎችን አሳልፏል፤ ሠራዊቱንም አነጋግሯል።

Monday, October 10, 2016

በኢትዮጵያ የተከሰተው አለመረጋጋት በኢንቨስትመት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ተባለ

ኢሳት (መስከረም 30 ፥ 2008)
በኢትዮጵያ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አለመረጋጋት በሃገሪቱ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩንና ለውጭ ባለሃብቶች ስጋር መፍጠሩን አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትና ባለሙያዎች ገለጹ።
ይኸው በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች እየተካሄደ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ በኢትዮጵያ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ በሚደረገው ጥረት ላይ ሁለገብ የሆኑ መሰናክሎች እንደፈጠረ ብሪታኒያ ለንደን ከተማ በሚገኘው ብሉምበርግ ኢንተሊጀንሲ አለም አቀፍ የምጣኔ ሃብት ባለሙያ ማርክ ቦህሉንድ ለብሉምበርግ አስረድተዋል።
ባለፈው ሳምንት በቢሾፍቱ ከተማ የደረሰውን ዕልቂት ተከትሎ በተለያዩ የኦሮሚያ የክልል ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞዎች ሲካሂዱ የነበረ ሲሆን፣ በዚሁ ድርጊት 11 ፋብሪካዎች መውደማቸው ይፋ ተደርጓል።

የአውሮፓ ህብረት የማሻሻያ እርምጃዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጠየቀ

ኢሳት (መስከረም 30 ፥ 2008)
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ በሃገሪቱ የማሻሻያ ዕርምጃዎችን ተግባራዊ እንዲደረጉ ሰኞ ጠየቀ።
በወቅታዊ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በተያዘው ወር ሁለተኛ መግለጫውን ያወጣው ህብረቱ ሁሉንም ወገኖች የሚያሳትፍ የማሻሻያ ዕርምጃ እንዲወሰድ ማሳሰቡን ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ታይምስ ጋዜጣ ህብረቱን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።
ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ ስላለው አለመረጋጋት ስጋቱን ገልጾ የነበረውን የኢትዮጵያ የልማት አጋር የሆነው የአውሮፓ ህብረት በሃገሪቱ በተለይ በኦሮሚያ ክልል ለወራት የዘለቀው ህዝባዊ ተቃውሞ አሳስቦት እንደሚገኝ አመልክቷል።

“የቢሾፍቱ እልቂት ከደረሰ በሁዋላ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በአጋዚ ወታደሮች ተገድለዋል”

መስከረም ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያውያንንና የአለምን ህዝብ ድንጋጤ ውስጥ የከተተው የቢሾፍቱ እልቂት ከተከሰተ በሁዋላ የተነሱ ህዝባዊ ንቅናቄዎችን ለማፈን የአጋዚ ወታደሮች በወሰዱት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መገደላቸውን ከተለያዩ አካባቢዎች የኢሳት ወኪሎች ያሰባሱበዋቸው መረጃዎች አመልክተዋል።
ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ በተካሄደባቸው በምስራቅ ሸዋና በምዕራብ አርሲ እልቂቱ ከፍተኛ እንደነበር ወኪሎቻችን ገልጸዋል።

ዢው ፓርቲ ከወጣቶች ጋር እርቅ ለመፍጠር ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ ተደረገ

መስከረም ፴ (ሠላሳ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአማራ ክልል በባህርዳር ዙሪያ ወረዳ አንዳሳ በሚባለው አካባቢ ከጎበዝ አለቆች ጋር እርቅ መፍጠር እንፈልጋለን በሚል ገዢው ፓርቲ ያቀረበውን ጥያቄ ወጣቶች ውድቅ አደረጉት። ወጣቶቹ፣ ማንኛውም ሰው፣ ፖሊስም ሆነ ወታደር ረብሻ ቢፈጥር እርምጃ እንወስዳለን በማለት የተማማሉ ሲሆን፣ አካባቢያችንን ከእንግዲህ እኛ የመረጥናቸው እንጅ እናንተ የምትመርጡት አያስተዳድረውም በማለት በፖሊሶች እና በአመራሮች ላይ ድንጋይ በትኖ አባሯቸዋል።
ሰባት አሚት በሚባለው አካባቢ ደግሞ የቀበሌ አመራሮችን ለመምረጥ የተደረገው ሙከራ ከሽፏል። የአካባቢ ካድሬዎች ምርጫ እናስደርጋለን ብለው ቢሄዱም ህዝቡ ፈቃደኛ ሳይሆን የቀረ ሲሆን፣ የቀበሌውን ቁልፍ በመቀየር ቀበሌውን በእጁ አስገብቷል።

አቶ አንዳርጋቸውን ጽጌን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ ሪፕሪቭ የተሰኘው ተቋም ገለጸ

ኢሳት (መስከረም 30 ፥ 2008)
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ በእስር ላይ የሚገኙ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞችን ደህንነት አድጋ ውስጥ እንደከተተ አንድ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም ሰኞ አስታወቀ።
መቀመጫውን በብሪታኒያ ያደረገው ሪፕሪቭ ተቋም የሃገሪቱ መንግስት በኢትዮጵያ ያለውን ወቅታዊ ጉዳይ ግምት ውስጥ በመክተት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲያመቻችና ይፋዊ ጥያቄን እንዲያቀርብ አስቧል።

Wednesday, October 5, 2016

U.S. Embassy confirms the death of American in Ethiopia

ESAT News (October 5, 2016)
The Embassy of the United States of America in Addis Ababa confirmed on Wednesday that an American was killed in Holeta, 26 miles west of the capital when a van she was travelling was struck by a stone thrown by unknown assailants.
The Embassy said the cause of death was head injury by a rock thrown by unknown assailants. ESAT broke the story Tuesday quoting credible hospital sources.

Tuesday, October 4, 2016

በአዲስ አበባ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተገለጸ

ኢሳት (መስከረም 24 ፥ 2009)
የእሬቻ ዕልቂትን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በመዛመት ላይ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ ማክሰኞ በመዲናይቱ አዲስ አበባ መቀስቀሱን እማኞች ለኢሳት ገለጹ።
በከተማዋ አንዳንድ አካባቢዎች ረፋድ ላይ የተጀመረው ተቃውሞ በአየር ጤና ብስራተ-ገብርዔል አካባቢ ተዛምቶ ማምሸቱ ታውቋል። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ በስም ያልገለጧቸው ሃይሎች ሁከት ለመፍጠር ጥረት አድርገዋል ሲል ማክሰኞ ምሽት ድርጊቱን አረጋግጧል።
በመዲናይቱ አዲስ አበባ የተስተዋለውን ይህንኑ ተቃውሞ ተከትሎ የአለም አቀፍ ድርጅት ሰራተኞች ከስራ መውጫ ሰዓታቸው አስቀድመው ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ መደረጉም ታውቋል።
ማክሰኞች ምሽት በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች በርካታ የጸጥታ ሃይሎች መሰማራታቸውንና ነዋሪዎች በጊዜ ወደ ቤት ለመግባት ጥረት ሲያደርጉ መታየቱንም እማኞች አክለው ገልጸዋል።

Monday, October 3, 2016

ከእሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ የተገደሉ ሰዎችን ድርጊት በማውገዝ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች ተቃውሞዎች ተካሄዱ

ኢሳት (መስከረም 23: 2009)
በቢሾፍቱ ከተማ ዕሁድ ከእሬቻ በዓል አከባበር ጋር በተገናኘ የተገደሉ ሰዎችን ድርጊት በማውገዝ በተለያዩ የኦሮሚያ የክልል ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። 
በሃዘን ድባብ ውስጥ በምትገኘው የደብረዘይት ከተማ እንዲሁም ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው የአምቦ ከተሞችና በምስራቅ አርሲ ዞን ከእሁድ ጀምሮ ህዝቡ ተቃውሞን እያሰማን እንደሚገኝ ነዋሪዎችን ለኢሳት አስታውቀዋል። 
በምስራቅ አርሲ ዞን ስር በሚገኙ የገጠር ከተሞች እንዲሁም በሻሸመኔና አጎራባች ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞው በመካሄድ ላይ ሲሆን የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ተቃውሞውን ለመቆጣጠር የሃይል ዕርምጃን እየወሰዱ እንደሆነ ታውቋል። 

በቢሾፍቱ ከተማ በእሬቻ በዓል ላይ የሞቱ ተጨማሪ አስከሬኖች መገኘታቸው ተገለጸ

ኢሳት (መስከረም 23: 2009)
በቢሾፍቱ ከተማ ዕሁድ ከእሬቻ በዓል አከባበር ጋር በተገናኘ የሞቱ ሰዎች ተጨማሪ አስከሬን ሰኞ ጠዋት መገኘቱን እማኞች ለኢሳት ገለጹ። 
የቤተሰብ አባሎቻቸውን ያጡ በርካታ ሰዎች በሆራ ሃይቅ ዙሪያ በመሰባሰብ በሞት የተለዩ ሰዎችን በመፈለግ ላይ ሲሆኑ በትንሹ የ10 ሰዎች አስከሬን ከ24 ሰዓት በኋላ መገኘቱን የከተማዋ ነዋሪዎች አስታውቀዋል። 
የቢሾፍቱ ከተማ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ባይሳ በበኩላቸው፣ አደጋው በደረሰ ማግስት ሰኞ ጠዋት ብቻ ሆስፒታሉ የአንድ ሰው አስከሬን መረከቡን ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል። 
ይሁንና የከተማዋ ነዋሪዎችና እማኞች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የገቡበት ያልታወቁ ሰዎችን ለማፈላለግ አሁንም ድረስ በበዓሉ አከባበር ስፍራ በለቅሶ እና በሃዘን ውስጥ መሆናቸውን አስረድተዋል። 

በቢሾፍቱ ሰኞ ረፋድ ድረስ 23 አስከሬኖች መገኘታቸው እማኞች ገለጹ

ኢሳት (መስከረም 23: 2009)
ሰኞ ረፋድ ድረስ ተጨማሪ 23 አስከሬን በእሬቻ በዓል አከባበር ስፍራ በነበረ ጉድጓድ ውስጥ መውታጣቸውን እማኞች ለዜና ክፍላችን አስታውቀዋል። 
ለደህንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የበዓሉ ታዳሚዎች ዕሁድ ምሽት ጀምሮ የሞቹ ሰዎችን ለማፈላለግ እየተካሄደ ባለው ዘመቻ በአጠቃላይ ተጨማሪ የ26 ሰዎች አስከሬን መገኘቱን ገልጸዋል። 
መንግስት ድርጊቱን ለመሰፋፈን ጥረት በማድረግ ላይ በመሆኑ እማኝነታችንን መስጠት እንፈልጋለን ያሉት ግለሰቦች በስፍራው የነበረው ጉድጓድ በአግባቡ አለመታጠሩና አለመጠናቀቁ ጥያቄ እንደፈጠረባቸው አክለው ገልጸዋል። 

Entire Oromo region flares up in violent protest following the Ireecha massacre

ESAT News (October 3, 2016)
From Borena in the south to Sendafa, and Aweday in the east to Wolega, the entire Oromo region of Ethiopia erupted in protest on Monday with people venting their anger in burning government plated vehicles and offices. People in all major towns in the region took to the streets on Monday in protest for the killing of hundreds of festival goers in Bishoftu, who were celebrating the annual Ireecha, a religious festival to welcome spring.

Sunday, October 2, 2016

የቢሾፍቱው እልቂት የህወሓት መቀበሪያ ጉድጓድ ቁፋሮ ነው!!!

መስከረም 22 ቀን 2009 ዓ.ም.
ከአርበኞች ግንቦት 7
ዛሬ መስከረም 22 ቀን 2009 ዓም ዓመታዊ ባህላዊ የእሬቻ በዓል ለማክበር በሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ከተማ የሚገኝ ሀይቅ ዳር ተሰባስቦ ነበር። በበዓሉ ትውፊት መሠረት ለፈጣሪ ምሥጋና ለማቅረብ ብዙዎች ቄጠማ፣ ለምለም ሳርና አበባዎችን ይዘው ነበር። ሕዝቡ አጋጣሚውን በመጠቀም የህወሓት አገዛዝ በክልሉና በመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚያደሰውን በደል ለመቃወም የተቃውሞ ድምጾችን አሰማ፤ የተቃውሞ ምልክቶችን አሳየ።
ሕዝባዊ ተቃውሞ ባጋጠመው ጊዜ ሁሉ የሚሸበረው የህወሓት አገዛዝ ለሰላማዊ ተቃውሞ የሰጠው ምላሽ እንደተለመደው ጥይት ነበር። ሕዝብ በማንኛውም ቦታ ተቃውሞ የማቅረብ መብት አለው። በየትኛውም ዓለም ሕዝባዊ በዓላት ዓይነተኛ የተቃውሞ ማቅረቢያ ቦታዎች ናቸው። ተቃውሞው የቀረበበት ድባድ በጣም ሰላማዊየነበረ በመሆኑ የተለየ ጥበቃ ሊሰጠው ሲገባ የአገዛዙ ምላሽ ግን ከተለመደው የባሰ ሆነ። በታንኮች ላይ ከተጠመዱ መትረሶች ተኩሰው በርካታ ሰው መፍጀታቸው አልበቃ ሲላቸው በሄሊኮፕሮች ላይ በተጠመዱ መትረሶች ሕዝቡን ፈጁ። የሞተውና የቆሰው ሕዝብ ብዛት ምን ያህል እንደሆነ መናገር ለጊዜው አይቻልም፤ ያም ሆኖ ግን ሟቶች በመቶዎች ቁስለኞች ደግሞ በሺዎች ነው የሚቆጠሩት።

በህዝባችን የነጻነት ተጋድሎ እየኮራን ለመጨረሻው ድል ታጥቀን እንነሳ!



በኦሮምያ እና በአማራ የተለያዩ ከተሞች የሚካሄደው የነጻነት ትግል በእጅጉ አስደማሚ ነው። ባለፉት ሳምንታት በጎንደርና በባህርዳር ለስድስት ቀናት እንዲሁም በተለያዩ የሰሜን ጎንደርና የምዕራብ ጎጃም ከተሞች የተደረገው የስራ ማቆም አድማ በአገራችን የቅርብ ጊዜ ታሪክ ያልታየ ወደር የለሽ ተግባር ነው።
ህዝቡ የስራ ማቆም አድማ ያደረገው የሚበላውና የሚጠጣው ተርፎት እንዳልሆነ ይታወቃል። እንዲያውም በአገሪቱ የሰፈነው አስከፊ ድህነትና የኑሮ ውድነት እንኳንስ ስራ ተፈትቶ፣ 24 ሰአታት ቢሰራም የሚቋቋሙት እንዳልሆነ እናውቃለን። ነገር ግን ህዝቡ፣ ረሃቡንና ጥማቱን ለሳምንታት ችሎ የአድማውን ጥሪ ተግባራዊ አድርጓል። ይህ ምን ይነግረናል? በቅድሚያ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንዳልነው ህዝቡ በዚህ ዘረኛና አፋኝ አገዛዝ መንገሽገሹን ያሳየበት ነው፤ “ልማቱ ተስፋፍቷል፣ ህዝቡም የደስታና የምቾች ኑሮ መኖር ጀምሯል” እያሉ በድህነቱና በብሶቱ ሲሳለቁበት ለቆዩት እውነተኛ ኑሮውን አሳይቷቸዋል። ይህንኑ ፕሮፓጋንዳ አምነው በመቀበል ወሬውን ሲያራግቡ ለነበሩ የአገር ውስጥና የውጭ የአገዛዙ ጠበቃዎች ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል ። እንዲሁም አገዛዙን ለማስወገድ ህዝቡ ማንኛውንም አይነት መስዋትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ያሳየበት ነው። ረሃብና ጥማቱን ችሎ ከውስጡ የተጣበቀውን አለቅት ለማስወገድ መወሰኑን አሳይቷል። “ሩጥ ስንለው የሚሮጥ፣ ተቀመጥ ስንለው የሚቀመጥ ህዝብ ፈጥረናል” በማለት ሲሳለቁበት በነበረቡት ገዢዎች ላይ እየጠራ ተሳልቆባቸዋል። ከእንግዲህም እሱ በፈለገው እንጅ እነሱ በፈለጉት መንገድ እንደማይገዛላቸው ነግሯቸዋል።

በዛሬው የኢሬቻ በዓል በተፈጠረው ግጭት በመቶዎች የሚቆጠር ህይወት መጥፋቱን ኦፌኮ አስታወቀ

1451በዛሬው ዕለት በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ኃይቅ ለመከበር በዝግጅት ላይ የነበረውና ከኦሮሞ ክብረ በዓሎች አንዱ የሆነው ኢሬቻ በዓል መንግሥትን በተቃወሙ ወጣቶችና በመንግሥት ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ተቋርጦ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አስታወቀ። የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፤ ፓርቲያቸው ባጠናቀረው መረጃ ሰዎች በተኩስ፣ በአስለቃሽ ጭስ እና በመረጋገጥ ሕይወታቸው እንዳለፈ ነው። 
በርካታ የቆሰሉ ሰዎች አሁንም በሆስፒታል እንደሚገኙ አክለው የተናገሩት ዶ/ር መረራ የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ተናግረዋል።

Hundreds dead at Ireecha celebrations


ESAT News (October 2, 2016)
Hundreds of festival goers have reportedly been killed on Sunday in the town of Bishoftu, the site of the annual Ireecha celebrations, an important religious festival by the people of Oromo in welcoming spring. Fana broadcasting, one of the organs of the ruling party reported that 52 people died in a stampede.

Friday, September 30, 2016

በጎንደርና ባህርዳር ከተሞች የንግድ ቤቶች መታሸጋቸው ተቃውሞ አስነሳ

ኢሳት (መስከረም 20 ፥ 2009)
በቅርቡ በጎንደርና ባህር ዳር ከተሞች በስራ ማቆም አድማ ተሳትፋችኋል የተባሉ የንግድ ድርጅቶችን ለማሸግ በንግድ ቢሮ እየተካሄደ ያለው የማሸግ ዕርምጃ ነዋሪዎችን ማስቆጣቱ ታወቀ። 
በተለይ ከአንድ ሳምንት በፊት ለሶስተኛ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ ውስጥ በቆየችው የጎንደር ከተማ በርካታ ሱቆች እየታሸጉ መሆናቸውን እማኞች ማስረጃዎችን በማስደገፍ ለኢሳት አስረድተዋል። 
ይሁንና የከተማው የንግድ ቢሮ የንግድ ድርጅቶቹን ለማሸግ እየወሰደ ያለው እርምጃ በነዋሪዎች ዘንድ ቁጣን እንደቀሰቀሰ ለደህንነታቸው ሲሉ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ እማኞች ገልጸዋል። 
ሆቴሎችና ሻይ ቤቱን በዚሁ የማሸግ እርምጃ ዋነኛ ኢላማ መሆናቸውን የተናገሩት የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ድርጊቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ ተጨማሪ ህዝባዊ ተቃወሞ ሊቀሰቀስ እንደሚችል ለኢሳት መረጃን ያደረሱ አካላት አስታውቀዋል። 

በቤኒሻንጉል ጊዛን ወደ 300 የሚጠጉ ነዋሪዎች ለደህንነታቸው ሲሉ ጫካ መግባታቸው ተነገረ

ኢሳት (መስከረም 20 ፥ 2009)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጊዛን ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የተቀሰቀሰውን ግጭት እልባት አለማግኘቱን ተከትሎ ወደ 300 የሚጠጉ ነዋሪዎች ለደህንነታቸው ሲሉ ጫካ መግባታቸውን እማኞች አርብ ለኢሳት ገለጡ። 
በነዋሪዎችና ከትግራይ ክልል መጥተው ሰፍረዋል በተባሉ 1ሺ አካባቢ ሰዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት በትንሹ ስምንት ከሚሆኑ የመንግስት የጸጥታ አባላት ግድያ ምክንያት መሆኑን ሃሙስ መዘገባችን ይታወሳል። 
ድርጊቱ እልባት ሳያገኝ ለሶስተኛ ቀን መቀጠሉን የተናገሩት የሸርቆሌ ከተማ አካባቢ ነዋሪዎች ግጭቱን ተከትሎ ወደ 300 የሚጠጉ ነዋሪዎች ህይወታቸውን ለማትረፍ ሲሉ ወደ ጫካ መሰደዳቸውን አስረድተዋል። 

ፖሊስ የተመድ ሰራተኞች የእሬቻን በዓልን ለመከታተል ወደ ቢሾፍቱ እንዳይጓዙ አሳሰበ

ኢሳት (መስከረም 20 ፥ 2009)
የፊታችን ዕሁድ በደብረ ዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ የሚከበረውን የእሬቻ በዓል አከባባር ምክንያት በማድረግ የተባበሩት መንግስታት የደህንነትና የጸጥታ መምሪያ ሰራተኞች ወደ ከተማዋ እንዳይጓዙ አሳሰበ። 
መምሪያው ለሰራተኞቹ ባሰራጨው ማሳሰቢያ ተለይቶ የታወቀ የደህንነት ስጋት ባይኖርም፣ የድርጅቱ ሰራተኞች ቅዳሜ እኩለ ቀን ጀምሮ እስከ ሰኞ ድረስ የግል ጉዞን ጨምሮ ከማንኛውም እንቅስቃሴ እንዲታቀቡ ጠይቋል። 
በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ህዝባዊ ተቃውሞዎች ሲካሄዱ መሰንበታቸውን ያወሳው የተመድ የጸጥታና የደህንነት መምሪያ፣ የድርጅቱ ሰራተኞች ራሳቸውን ከማንኛውም ህዝባዊ ስብሰባዎች እንዲያርቁ አክሎ አሳስቧል። 
በክልሉ ለወራት የዘለቀውን ተቃውሞ ተከትሎ አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲን ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማትና ኤምባሲዎች ሰራተኞቻቸው ወደ አካባቢው በሚያደርጉት ጉዞ ላይ የጥንቃቄ እርምጃን እንዲወስዱ ሲያሳስቡ መቆየታቸው ይታወሳል።

በቢሾፍቱ ከተማ ከፍተኛ የጸጥታ ቁጥጥር እየተደረገ ነው

ኢሳት (መስከረም 20 ፥ 2009)
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ከነገ በስቲያ እሁድ በበሾፍቱ ከተማ ለሚከበረው የእሬቻ በዓል ልዩ ሃይል ተመድቦ የጸጥታ ቁጥጥር በመደረግ ላይ መሆኑን አርብ አስታወቀ። 
የከተማዋ ነዋሪዎች የፌዴራልና የክልል የጸጥታ አባላት ከመቼውም ጊዜ በላይ በመሰማራት ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ በተለያዩ ስፍራዎች ፍተሻ በመካሄድ ላይ መሆናቸውን ረቡዕ ለኢሳት መግለጻቸው ይታወሳል። 
የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አርብ ባወጣው መግለጫ በከተማ የበዓሉ አከባበር በሰላም እንዲስተናገድ ለማድረግ ታስቦ ልዩ ሃይል መመደቡንና ከነዋሪዎች ጋር በጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር መካሄዱን አመልክቷል። 

Tensions remain high in Benishangul

ESAT News (September 30, 2016)
At least 300 people have taken refuge in a jungle in Benishangul Giumuz region in western Ethiopia following clashes with regime’s army officials, who settled in the region to carry out gold exploration.
Eight security forces have reportedly been killed on Wednesday following clashes with the local people in an area known as Sherkolle.

Security tightens ahead of Ireecha celebrations on Sunday

ESAT News (September 30, 2016)
There is huge presence of federal and regional security forces in and around Debre Zeit, a.k.a Bishoftu, 25 miles from the capital Addis Ababa, ahead of Ireecha celebrations on Sunday. Ireecha is an important annual celebration by the people of Oromo, the largest ethnic group in Ethiopia.
The United Nations Department of Safety and Security (UNDSS) office in Addis Ababa meanwhile advised its staff to stay away from large gatherings and to avoid Debre Zeit this weekend.
Vehicles and passengers entering the town are being searched and the administration of the town has informed local media that there was a boost up in security in and around Debre Zeit.

Thursday, September 29, 2016

ተጨማሪ መረጃዎች ስለ “ደህንነቱ|” መሥሪያ ቤት [ታደሰ ብሩ]

“ስለ ‘ደህንነቱ’ መሥሪያ ቤት ከማውቀው በጥቂቱ” በሚለው አጭር መጣጥፍ ላይ በርከት ያሉ የውስጥ መልዕክቶች ደርሰውኛል። በበጎም ይሁን በክፉ የፃፋችሁልኝ ሁሉ አመሰግናለሁ፤ በግልም አመሰግኛቸዋለሁ።
ከተላኩልኝ አስተያየቶች በተለይ አንዱ ትኩረቴን ስቦታል። በውስጡ ተረብ ያለበት ሆኖ “የፃፍከው በአጠቃላይ ጉዳዮች ላይ ነው፤ ‘ከማውቀው በጥቂቱ’ አልክ እንጂ ከአጠቃላይ ጉዳዮች ያለፈ የምታውቀው ዝርዝር ነገር የለም፤ ቢኖርህ ኖሮ ለነገ የምታቆይበት ምክንያት አይኖርህም ነበር፤ ቢያንስ ደጋፊዎችህን ለማስጠንቀቅ ሁለት ሶስት ስሞችን ትጠራ ነበር” የሚል ነው የመልዕክቱ ይዘት ነበር። አስተያየት ሰጪው እልህ ውስጥ ሊያስገናኝ የፈለገ ይመስላል። እኔ በቀላሉ እልህ ውስጥ የምገባ ሰው አይደለሁም፤ ሆኖም ቆም ብዬ እንዳስብበት አደረገኝ።
ስለ ህወሓት መሥሪያ ቤት ተጨማሪ ነገሮችን መናገር ህወሓትን ለማሸነፍና በምትኩ ነፃነት፣ ፍትህ፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈባት አገር ለመመሥረት ለምናደርገው ትግል ምን ያህል ይጠቅማል? ተጨማሪ ነገር ብጽፍ በዚህ እኩይ መሥሪያ ቤት ያሉ ቅን ሰዎችን ይጠቅማል ወይስ ይጎዳል? የሚለውን እንዳስብበት አደረኝ። በእኔ ስሌት ከጉዳቱ ጥቅሞ በልጦ ስላገኘሁት እነሆ ተጨማሪ ነገሮች ማለት ፈለግሁ።

Ethiopia: The Myth of a Stable and Reliable Partner Under the Minority TPLF Regime [By Neamin Zeleke]

“I want the superiority of one ethnic group to end” – Ethiopia’s Olympic Silver medalist Feyisa Lilesa on Al Jazeera
“Those who make peaceful revolution impossible will make violent revolution inevitable.” – John F. KennedyNeamin Zeleke -- Satenaw

In the first installment ofthis series, the myth of a strong military under the TPLF/EPRDF regime was examined. This sequel article discusses the manifold policies and measures taken by the ruling TPLF/EPRDF’s and their consequences for peace and stability in Ethiopia and the sub region.
A myth promoting the minority TPLF regime as a reliable and stable partner in the Horn of Africa has been circulating for years among Western policy makers, think tank analysts and academics, especially in the US, UK, and other western countries. This should not come as a surprise: since 9/11, the primary preoccupation of western foreign and security policymakers has been fighting global terrorism.

በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) የሚከበረውን የእሬቻ በዓልን አስመልክቶ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት መሰማራቱ ተገለጸ

ኢሳት (መስከረም 19 ፥ 2008)

የፊታችን ዕሁድ በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ ለሚከበረው አመታዊው የእሬቻ በዓል አከባባር በሚል ቁጥር ከፍተኛ የሆነ የፌዴራል የክልል የጸጥታ ሃሎች በከተማዋ መሰማራታቸውን እማኞች ለኢሳት ገለጹ።
የበዓሉ አከባበር ዝግጅትን ተከትሎ ወደ ከተማ በሚገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ፍተሻ በመደረግ ላይ መሆኑም ታውቋል።
በኦሮሚያ ክልል ከወራት በፊት የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ተከትሎ በቢሾፍቱ ከተማ ዙሪያዋ ባሉ የገጠር ወረዳዎች ህዝባዊ ትዕይንቶች ሲካሄዱ የንበረ ሲሆን፣ በእሬቻ በዓል አከባበር ወቅትም ተቃውሞ ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት ባለመኖሩ የጸጥታ ቁጥጥር በመደረግ ላይ መሆኑን ነዋሪዎች አስረድተዋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በተቀሰቀሰ ግጭት 8 የጸጥታ ሃይሎች ተገደሉ

ኢሳት (መስከረም 19 ፥ 2008)

በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ሰርቀሌ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በነዋሪዎችና በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት በትንሹ 8 የጸጥታ ሃይሎች መገደላቸውን እማኞች ለኢሳት ገለጹ።
የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች የተገደሉት በስፍራው ወርቅ ለማውጣት በሚል በቅርቡ ከ1ሺ በላይ የትግራይ ተወላጆች መስፈራቸውን ተከትሎ በተቀሰቀሰ አለመግባባት መሆኑ ተነግሯል። በዚሁ ግጭት ከተገደሉት የጸጥታ ሃይሎች በተጨማሪ ከ20-30 የሚደርሱ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው የቤኒሻንጉል ህዝብ ንቅናቄ አመራሮች ለኢሳት ገልጸዋል።

ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች የማዕረግ ዕድገት ተሰጣቸው ተባለ

ኢሳት (መስከረም 19 ፥ 2008)

ከ30 የሚበልጡ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ሃሙስ የሌተናል፣ የሜጀርና፣ የብርጋዴር ጀነራልነት ማዕረግ እንደተሰጣቸው መንግስት አስታወቀ።
በሃገሪቱ ፕሬዜዳንት ሙላቱ ተሾመ የማዕረግ እድገት ተሰጥቷቸዋል ከተባሉት ወታደራዊ መኮንኖች መካከል የሜጀር ጄነራልነት ማዕረግ የነበራቸው ገብራት አየለ ቢጫ በብቸኝነት የሌተናል ጀኔራልነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል።
በብርጋዴር ጀነራልነት ሲያገለግሉ ነበር የተባሉ 12 ወታደራዊ መኮንኖች ደግሞ የሜጀር ጀኔራልነት ሹመትን ያገኙ ሲሆን፣ 25 ኮሎኔሎች እንዲሁ የብርጋዴር ጄኔራልነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል።

በቃሊቲ በሚገኙ እስረኞች ላይ የሚደረገው ጫና መቀጠሉ ተነገረ

ኢሳት (መስከረም 19 ፥ 2008)

በቃሊቲ ወህኒ ቤት በሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች ላይ የሚፈደረገው ጫና እና ማሰቃየት መቀጠሉ ታወቀ። የ18 ዓመታት እስራት ተፈርዶበት ላለፉት 5 አመታት በዚህ ወህኒ ቤት በሚገኘው በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ላይ በእስር ቤቱ ሃላፊዎች የሚፈጸመው ጥቃት መቀጠሉን እንዲሁም የማበሳጨት ዕርምጃዎች መጨመራቸውን መረዳት ተችሏል።
በቅድሚያ የጻፋቸውን ማስታወሻዎች፣ በኋላም ማናቸውንም የጽህፈት መሳሪያና ባዶ ወረቀቶች ጭምር የነጠቁት የእስር ቤቱ አዛዦች የተለያዩ ቁሳቁሶች እንዳወደሙበትም በቅርቡ ከእስር ቤት የወጣ ግለሰብ ለኢሳት አብራርቷል።

Wednesday, September 28, 2016

የኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የዋስትና መብት ጥያቄ በፖሊስ ተቃውሞ እየቀረበበት ነው ተባለ

ኢሳት (መስከረም 17 ፥ 2009)

ከወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ ጋር በተገናኘ በቅርቡ ለእስር የተዳረጉት ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ማክሰኞ ፍርድ ቤት መቅረባቸውንና ለከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ያቀረቡት የዋስትና መብት ጥያቄ በፖሊስ ተቃውሞ እንደቀረበበት እማኞች ለኢሳት ገለጹ።
በኮሚቴ አባሉ ላይ ምርመራን እያካሄደ መሆኑን ለችሎት ያስታወቀው ፖሊስ፣ ኮሎኔል ደመቀን በሽብርተኛ ወንጀል ድርጊት የሚጠረጥራቸው በመሆኑ ያቀረቡት የዋስትና መብት ተቀባይነት እንዳያገኝ ተቃውሞ አቅርቧል።