Saturday, July 29, 2017

ግብር በአምባገነን አገዛዝ(Tadesse Biru Kersmo)

ስለ አምባገነን አገዛዝና ግብር ሲነሳ መጥቀስ የምወደው የእውቁ ኢኮኖክስ ማንኩር ኦልሰን Dictatorship, Democracy, and Development ነው። ከዚህ ጽሁፍ በዛ አድርጌ ልጥቀስ።
===
ዘላን ወንበዴዎች /roving bandits/ ነጥቀው ይሮጣሉ፤ መቼ እንደሚመለሱ አይታወቅም። እነዚህ ወንበዴዎች ነጥቀው በሮጡ ቁጥር የማኅበረሰቡ ሀብት የማፍራት ፍላጎት ስለሚዳከም በሚቀጥለው ዙር የሚዘርፉት ነገር እያነሰባቸው ይመጣል። ቀን ባለፈ መጠን ነጥቆ መሮጥ ራሳቸውን እንደሚጎዳቸው ይገነዘቡና ከተዘዋዋሪ ወንበዴነት ወደ ቋሚ ወንበዴነት /stationary bandit/ ይቀየራሉ። ለንጥቂያቸውም ሥርዓትና ልክ ያበጁለታል፤ ስሙን “ግብር” ይሉታል። ማኅበረሰቡንም፣ ራሳቸውንም ከሌሎች ተዘዋዋሪ ወንበዴዎች ይከላከላሉ። ይህ ሥርዓት ከሥርዓተ አልበኝነት የተሻለ፣ የቅሚያውም መጠንም አስቀድሞ የሚታወቅ ከመሆኑ ጋር ማኅበረሰቡ ለሚከፍለው ተመጣጣኝ ባይሆንም የሚያገኘው ጥቅም (ሰላምና ሌሎችም ማኅበራዊ ምርቶች) ስላሉ ምርት ይጨምራል፣ ዕድገትም ይኖራል።
ይሁን እንጂ አምባገነን ሰፋሪዎች በተደላደሉ መጠን ፍጆታቸው እየናረ መሄዱ ፈጽሞ የማይቀር ነው። ለጦር ሠራዊቱ፣ ለቤተመንግሥቱ፣ ለማሰልጠኛው፣ ለመታሰቢያ ሀውልቶች ግንባታ፣ ለአዳራሾች ግንባታ፣ ለአምባገነኖች፣ ለተከታዮቻቸውና ቤተሰቦቻቸው የክብር ልብሶችና ጌጣጌጦች፣ “ለመጠባበቂያ“፣ ..... የሚያስፈልገው ወጪ በጨመረ ቁጥር ሕዝቡ በግብር አሊያም በሌላ መንገድ እንዲከፍል ስለሚገደድ ሥርዓት በመስፈኑ ምክንያት አንሰራርቶ የነበረው የሥራ ፍላጎት እንደገና ያሽቆለቁላል። የሰፋሪ ወንበዴዎችን የሀብት ማጋበስ፣ ምቾትና እዩልኝ ፍላጎቶችን ማርካት አይቻልም።
==

Friday, July 28, 2017

የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር የአብርሃ ደስታ የክስ መዝገብ ተዘጋ 

(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 21/2009)የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አብርሃ ደስታ 8 ጊዜ በፖሊስ ተገደው ችሎት ሊቀርቡ ባለመቻላቸው ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መዝጋቱን ገልጸ። አቃቢ ህግም ሆነ ፖሊስ በውሳኔው በመስማማት ዝምታን መርጠዋል የአረና ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አብርሃ ደስታ በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ጥሪ ቢቀርብላቸውም እሳቸው ግን መምጣት አልቻሉም። ስለዚህም ፍርድ ቤቱ መዝገባቸውን መዝጋቱን አስታውቋል። አቶ አብርሃ ደስታ ፍርድ ቤቱ ሲጠራቸውም ሆነ ከወር በሗላ መዝገቡን ሲዘጋ ኢትዮጵያ ውስጥ መቀሌ ዩኒቨርስቲ በማስተማር ላይ ናቸው ። በሐምሌ ወር 2006 ከአቶ ሃብታሙ አያሌው ፣አቶ ዳንኤል ሺበሺና አቶ የሺዋስ አሰፋ ጋር በሽብር ተከ

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ከታሰሩት መካከል የአቶ አባይ ጸሃዬ ባለቤት አንዷ ናቸው ተባለ

(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 21/2009)

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ከታሰሩት መካከል የአቶ አባይ ጸሃዬ ባለቤት እንደሚገኙበት ታወቀ። ሌሎች አራት ሰዎችም ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውለዋል። የደህንነት ምንጮች እንደገለጹት የአቶ አባይ ጸሃዬ ባለቤት ወይዘሮ ሳሌም ከበደ በቁጥጥር ስር የዋሉት ለልጃቸው መልስ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ነበር። አቶ አባይ ጸሃዬ በኢትዮጵያ ሰኳር ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር እያሉ ባከነ ከተባለው 77 ቢሊየን ብር ጋር በተያየዘ ስማቸው በተደጋጋሚ ይነሳል ።

ከአቶ አባይ ጸሃዬ ጋር ከፍተኛ ቅርበትና የንግድ ሽርክና አላቸው የሚባሉት አቶ የማነ ግርማይም በቁጥጥር ስር ውለዋል። የማነ ግርማይ የባቱ ኮንስትራክሽኝ ባለቤት መሆናቸውም ታውቋል። በቀዳሚነት ከተያዙት 34 የሙስና ተጠርጣሪዎች ጋር የታሰሩት ወይዘሮ ሳሌም ከበደ የአቶ አባይ ጸሃዬ ባለቤት ሲሆኑ ከኦሞ ኩራዝ 5 የስኳር ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ መታሰራቸው ታውቋል። የባቱ ኮንስትራክሽን ባለቤት አቶ የማነ ግርማይም ከዚሁ ጋር በተያየዘ መታሰራቸው ይታወቃል።

በአምቦ ዳግም የህዝብ አመጽ ተቀሰቀሰ 

በአምቦ ዳግም የህዝብ አመጽ ተቀሰቀሰ (ኢሳት ዜና–ሐምሌ 21/2009) በአምቦ ዳግም የህዝብ አመጽ ተቀስቅሷል።የመንግስት ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት ተሰንዝሯል።ሰላም ባስ በተሰኘው የህወሃት ንብረት ላይም ህዝብ እርምጃ መውሰዱ ታውቋል። በደደርና በአለም ገና በግብር ጭማሪው ምክንያት ነጋዴዎች አድማ መምታታቸው ተገልጿል።በአማራ ክልል በሞጣ አድማው ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።በደቡብ ኢትዮጵያ የቦንጋ ነጋዴዎች መማረራቸውን ገልጸዋል።ከ1 ሺ በላይ ነጋዴዎች ፍቃዳቸውን መመለሳቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። አምቦ

Thursday, July 27, 2017

New York Times journalist says Ethiopia faces dangers due to oppression of majority


Jeffrey Gettleman
ESAT News (July 27, 2017)
New York Times journalist, who worked as the paper’s East Africa Bureau chief for a decade, says the oppression that the majority, especially Amharas and Oromos, suffer under the minority government is a danger for the future of the country.
Jeffrey Gettleman, who won the most coveted journalism award, the Pulitzer Prize in 2011 for his work focusing on East Africa, said in an exclusive interview with ESAT that building infrastructure is important but not an excuse to kill, jail and torture innocent civilians.

Ethiopia is a dictatorship and the regime knows no bounds: says a congressman


Rep. Chris Smith
Rep. Dana Rohrabacher
ESAT News (July 27, 2017)
A U.S. congressman says the murder, repression and torture that is perpetrated by the Ethiopian regime is offensive to the American values. Dana Rohrabacher, who represents California’s 48th congressional district said the regime in Ethiopia “arrogantly expects the U.S. to continue good relationships with it and perhaps expect to get some type of aid.”

Tuesday, July 25, 2017

Ethiopia: Business strikes continue amid conflicting statements by officials

ESAT News (July 25, 2017)

Strikes by businesses in Ethiopia’s capital Addis Ababa and regional towns continue for the second week despite intimidations by security forces and conflicting statements by officials.
Strikes by small businesses and vendors that began in the country’s Oromo region last week against new tax hikes have spread to the Amhara region and businesses in Addis joined the shutdown on Monday. Major business districts in the capital were closed on Tuesday despite reports that police and security forces were threatening to revoke the licenses of those who joined the strikes. Reports say that in Nefas Silk district of the capital, business owners have clashed with police who were trying to force them open their stores. Authorities put notice of violation on some shops for refusing to open for business.

በእነ መልካሙ ክንፉ የክስ መዝገብ ከወንድሙ ቦንሳ በየነ ጋር ከኦነግ ጋር ተባብራችኋል በሚል ክስ የቀረበበት አየለ በየነ ለዘጠኝ ወራት በማእከላዊ እስር ቤት መቆየቱን ጓደኞቹ ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል

(ኢሳት ዜና–ሐምሌ 18/2009) በእነ መልካሙ ክንፉ የክስ መዝገብ ከወንድሙ ቦንሳ በየነ ጋር ከኦነግ ጋር ተባብራችኋል በሚል ክስ የቀረበበት አየለ በየነ ለዘጠኝ ወራት በማእከላዊ እስር ቤት መቆየቱን ጓደኞቹ ሐምሌ 18/2009 በዋለው ችሎት ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል። የጸር ሽብር ህጉ ከሚፈቅደው ግዜ በላይ ተጨማሪ 5 ወራት በአጠቃላይ ዘጠኝ ወራት በማእከላዊ ምርመራ በእስርና በምርመራ ላይ መቆየታቸውን የገለጹት የወጣት አየለ በየነ አባሪዎቹ ህክምና ለማግኘት በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ ባለመሳካቱ ምግብ መመገብ ካቆመ ከ10 ቀናት በኋላ ተዳክሞ ወደ ህክምና ቢወሰድም ህይወቱን ማትረፍ አለመቻሉን ገልጸዋል። ትላንት ሰኞ ሐምሌ 17/2009 ሕይወቱ ያለፈው ወጣት አየለ ሆን ተብሎ ህይወቱ እንዲያልፍ መደረጉን ለችሎቱ የገለጹት አባሪዎቹ ለራሳቸውም ደህንነት እንደሚሰጉ ተናግረዋል። አውቀው ነው የገደሉት እኛንም ይገድሉናል ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል። አንደኛው ተከሳሽ መልካሙ ክንፉ እኛም ብንሆን ዋስትና የለንም ሲል ስጋቱን ገልጿል። ይህንን የሚያደረገው መንግስት ከሆነ ቁርጡን አውቀን እንሙት ሲል 4ኛው ተከሳሽ ይማም መሀመድ መጠየቁንም ከኢሳት ምንጮች መረጃ መረዳት ተችሏል። የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት የ29 አመቱ አየለ በየነ ሕይወቱ ማለፉን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ወህኒ ቤቱ እንዲያቀርብ ለሐምሌ 26/2009 ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል። ታላቅ ወንድሙን በወህኒ ያጣው 3ኛው ተከሳሽ ቦንሳ በየነ አሁንም በወህኒ ሆኖ ፍርዱን በመጠባበቅ ላይ መሆኑም ተመልክቷል።

መንግስት በኩል የሚሰጡት የተምታቱ መግልጫዎች አነጋጋሪ ሆነዋል

(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 18/2009)በመንግስት በኩል የሚሰጡት የተምታቱ መግልጫዎች አነጋጋሪ ሆነዋል።የጋቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዳይሬክተር አቶ ከበደ ጫኔ በ24 ሰአት ልዩነት ሁለት ተቃራኒ መግለጫዎችን ሰጥተዋል። እሁድ ለንባብ በበቃው ሪፖርተር ጋዜጣ የተናገሩት አቶ ከበደ ጫኔ ነጋዴው የፈለገውን የአቅሙን እንዲከፍል ውሳኔ ላይ ተደርሷል ብለዋል። በማግስቱ ይህን ሀሳባቸውን በመሻር የተተመነውን ግብር ነጋዴው የከፍላል ሲል ገልጸዋል።ተቃውሞው ወደ አጠቃላይ ህዝባዊ አመጽ የሚሸጋገር ከሆነ የግብር ተመኑ ሊሻር ይችላል የሚል ውሳኔ በመንግስት ጠረጴዛ ላይ ተቀምጦ ሁኔታዎ እየተገመገሙ እንዳሉም መረጃዎች ይጠቁማሉ። እስከዛው ነጋዴውን ነጥሎ በመምታት አስተባባሪዎችን የመለየትና የማሰር እርምጃዎች እንዲወሰዱ በህወሃት መንግስት በኩል ውሳኔ ላይ እንደተደረሰና ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑም ታውቋል። ምንም እንኳን

Monday, July 17, 2017

የአዲስ አበባ መስተዳድር ምክር ቤት ሰሞኑን ጉባኤውን አካሂዷል

(ኢሳት ዜና–ሐምሌ 10/2009)የአዲስ አበባ መስተዳድር ምክር ቤት ሰሞኑን ጉባኤውን አካሂዷል’።የከተማዋ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የ2008 በጀት ዓመት ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ አቅርቧል። ሪፖርቱ እንዳመለከተውም ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ያለ አግባብ ባክኗል።– 500 ሚሊየን የሚሆን የህዝብና የመንግስት ገንዘብ ደግሞ በወቅቱ መሰብሰብ አልተቻልም። ከዚህም ሌላ በወቅቱ ያልተወራረደ 200 ሚሊዮን ብር፣ ለማን እንደተከፈለ ማስረጃ የሌለው 257 ሚሊዮን ብር እንዲሁም አዋጅና መመሪያን ሳይከተል ለውሎ አበልና ለደመወዝ የተከፈለ ከ353 ሚሊዮን ብር በላይ በኦዲት መገኘቱን ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡ ለበጀቱ መባከን የመንግሥት የግዥ መመሪያን ተከትሎ አለመስራት፣ በመመሪያና በህግ ከተፈቀደው በላይ የውሎ አበል ክፍያን መፈፀም የሚሉት በምክንያትነት ተቀምጠዋል፡፡ ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የከተማ አስተዳደሩ ዋና ኦዲተር ወይዘሮ ፅጌወይን ካሣ፤ ብክነትና ምዝበራ በፈፀሙ አካላት ላይ ከፀረ ሙስና እና ከፖሊስ ጋር በመተባበር እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል። የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ዶክተር ታቦር ገ/መድህን በበኩላቸው፤ የኦዲት ግኝት ያለባቸው ተቋማት ተለይተው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድ ለም/ቤቱ አባላት ተናግረዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ መሥሪያ ቤቶች ያለው የግዥ መመሪያን ተከትሎ ያለመስራት ችግርና ሙስና መፍትሄ ያልተገኘላቸው ችግሮች መሆናቸው በተደጋጋሚ ሲገልጽ መቆየቱ ይታዋሳል።ዘገባውን ያገኘንው ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ነው።

በደቡብ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በሚገኘው አርባ ምንጭ ከተማ አንድ ባልሁለት ፎቅ ህንጻ ተደርምሶ 4 ሰዎች ሞቱ። 11 ሰዎች ደግሞ ቆስልዋል

(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 10/2009) በደቡብ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በሚገኘው አርባ ምንጭ ከተማ አንድ ባልሁለት ፎቅ ህንጻ ተደርምሶ 4 ሰዎች ሞቱ። 11 ሰዎች ደግሞ ቆስልዋል በተደረመሰው ሕንጻ ፍርስራሽ ስር ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መቀበራቸውንም ዥንዋ በዘገባው አመልክቷል። የከተማዋ ከንቲባ አቶ ኢዞ ኢማጎ የሕንጻው ባለቤት ደረጃውን ያልጠበቅ የህንጻ ግንባታ አካሂደዋል በሚል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል። በህንጻው ስር የተቀበሩት ሰዎች ስላሉበት ሁኔታና ሰዎቹን ለማዳን እየተደረገ ስላለው ርብርብ የተገለጸ ነገር የለም።

በደብረታቦር በሕዋሃት/ኢህአዲግ አገዛዝ የታሰሩት ባህታዊ አባ ብርሃኑ ካልተፈቱ ሕዝባዊ ተቃውሞአቸውን ለመቀጠል የከተማዋ ነዋሪዎች ተስማሙ

(ኢሳት ዜና — ሐምሌ 10/2009) በደብረታቦር በሕዋሃት/ኢህአዲግ አገዛዝ የታሰሩት ባህታዊ አባ ብርሃኑ ካልተፈቱ ሕዝባዊ ተቃውሞአቸውን ለመቀጠል የከተማዋ ነዋሪዎች ተስማሙ። የከተማዋ ከንቲባ የሕዝቡን ቁጣ በመፍራት ባህታዊው አባ ብርሃኑ ሐምሌ 12/2009 ባላቸው ቀጠሮ መሰረት ከእስር እንደሚፈቱ ማረጋግጫ ቢሰጡም የአካባቢው ነዋሪዎች የጀመሩትን ተቃውሞ እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። በደብረታቦር በኢየሱስ ደብር ቅጥር ግቢ ተራራማ ቦታ ላይ የቴሌቪዥን ታወር ነው በሚል ሲካሄድ የነበረው ግንባታም በሕዝብ ተቃውሞ እንዲቆም ተደርጓል። በታላቁ ደብር ኢየሱስ ቅጥር ግቢ በታቦተ ህጉ መውጫ ላይ ያለምእመናኑ ፈቃድ እየተገነባ ያለው ታወር የቴሌቪዥን ማሰራጫ ነው ቢባልም ላሊበላ አካባቢ ለተተከለው የራዳር የመረጃ ቋት ተጨማሪ ማስተላለፊያ መሆኑ ይነገራል። እናም ይህ ታወር ያለህዝቡና ሕዝበ ክርስቲያኑ ፈቃድ በደብሩ ውስጥ የተሰራ ስለሆነ ባህታዊው ካልተፈቱ እናፈርሰዋለን ሲሉ የአካባቢው ሰዎች ማዛታቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ባህታዊ ብርሀኑ በአገዛዙ ከታፈኑበት ጊዜ ጀምሮ ምግብ አልበላም ብለው በጾምና በጸሎት ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል። ባህታዊው የታሰሩት በሕዋሃት/ኢህአዲግ የሚመራው አገዛዝ አባ ሃይለማርያም የተባሉ የስርአቱ ደጋፊ የዞኑ ሀገረ ስብከት ተደርገው መመደባቸውን ሕዝቡ ከተቃወመ በሗላ ነው። ይህንኑ ተከትሎም በቤተክርስትያኑ አጥር ግቢ እየተገነባ ያለውን ታወር ሕዝቡ ለማፍረስ በመንቀሳቀሱ የአጋዚ ወታደሮችና የመንግስት ታጣቂዎች አካባቢውን መክበባቸው ተንግሯል። በደብረታቦር ከፍተኛ ውጥረት በመኖሩ አካባቢው በታጠቁ ፌደራሎች እየተጠበቀ ቢሆንም የሕዝቡ ተቃውሞ እያየለ በመምጣቱ የከተማው ከንቲባ ድርድርን እንደመረጡ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል። የደብረታቦር ህዝብ ባህታዊው በፍርድ ቤቱ ቀጠሮ መሰረት ሐምሌ 12/2009 ካልተፈቱ ወደ ከፍተኛ አመጽ እንደሚያመራ እየተጠበቀ ይገኛል።

ከግብር ጫናና ትመና ጋር ተያይዞ እንደገና ያገረሸው ተቃውሞ በርካታ የኦሮሚያ አካባቢዎችን እያዳረሰ ይገኛል።

(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 10/2009) ከግብር ጫናና ትመና ጋር ተያይዞ እንደገና ያገረሸው ተቃውሞ በርካታ የኦሮሚያ አካባቢዎችን እያዳረሰ ይገኛል። በሕወሃት የሚመራው አገዛዝ በተለያዩ ተሽከርካሪዎች ወደ ኦሮሚያ ተጨማሪ ወታደሮችን እየላከ መሆኑ ተነግሯል። በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው አምጽ በአምቦ ጀምሮ ጊንጪና ጀልዱ እንዲሁም ወሊሶና ቡራዩን አዳርሷል። በሻሸምኔ፣በኮፈሌና አርሲም ተመሳሳይ ሕዝባዊ ተቃዋሚዎች መኖራቸው ነው የተነገረው። በጊንጪ የስራ ማቆም አድማ ሙሉ በሙሉ እየተደረገ መሆኑ ታውቋል።የንግድ ቤቶች፣ሱቆችና ሆቴሎች ተዘግተዋል። በአምቦ ሁለት ወጣቶች በጥይት መቁሰላቸውም ተነግሯል። በኦሮሚያ በስፋት እየተከሰተ ያለው ሕዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ ወደ ሌሎች የሐገሪቱ አካባቢዎችም ተዛምቷል። በደቡብ ክልል ሳውላ ከተማ ከግብር ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ተቃውሞ ተነስቷል።–በዚሁ አካባቢ በፍርድ ቤት ትእዛዝ አንድ የወረዳው ካቢኔ አባል በመታሰሩ ይህንኑ የፈጸመው ኢኒስፔክተር ዘላለም የተባለ ፖሊስ አዛዥ በደኢህዴን ስራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ቤልጂጌ ትእዛዝ ከስራና ከሃላፊነት መነሳቱ ታውቋል። አቶ ተስፋዬ የፖሊስ አዛዡን እንዲታገድ ያደረጉት እንዴት የካቢኔ አባል በፍርድ ቤት ትእዛዝም ቢሆን ታስራልህ በሚል ነው። በግብር የተማረረውን የሳውላ ህዝብ ያስጨነቁት የወረዳው የካቢኔ አባል የወረዳው የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ሆነው በሙስና የሚታወቁ መሆናቸውን የኢሳት መነጮች ገልጸዋል። በአማራ ክልልም ከግብር ጫና ጋር በተያያዘ የባህርዳር ነጋዴዎች ፈቃዳቸውን እየመለሱ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ ጉዳይ ላይ ከግብጽ ጋር ለመተባበርና ለመደራደር ምንጊዜም ዝግጁ መሆኗን ገለጸች ።

(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 10/2009) ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ ጉዳይ ላይ ከግብጽ ጋር ለመተባበርና ለመደራደር ምንጊዜም ዝግጁ መሆኗን ገለጸች ። የግብጽ መንግስት ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ ውሀ ለመሙላት መዘጋጀቷን ተከትሎ ጉዳዩ እያሰሰበው መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል ። ይህንን ተከትሎም በኢትዮጵያ የግብጽ አምባሳደር የተመራ ቡድን አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳን በጉዳይ ላይ ማነጋገሩ ታውቋል። የግብጽ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደገለጹት የኢትዮጵያ መንግስት በኣባይ ግድብ ጉዳይ ላይም ሆነ በሁለቱ ሀገራት የትብብር ግንኙነቶች ዙሪያ ለመተባበርና ለመደራደብ ዝግጁ ነው። አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ ለግብጽ የልዑካን ቡድን እንዳረጋገጡትም ኢትዮጵያ የሌላውን ሀገር ጥቅም በሚጎዳ መልኩ የራሷን ጥቅምና እድገት አትመኝም ። አቶ ኣባ ዱላ ይህንን ቢሉም ግን የግብጽ መገናኛ ብዙሀን ኢትዮጵያ በያዝነው ሀምሌ ላይ የአባይ ግድብን በውሀ መሙላት

አንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ ነጋሽ ገብረማርያም በ93 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

(ኢሳት ዜና –ሐምሌ 10/2009) አንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ ነጋሽ ገብረማርያም በ93 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። ስርአተ ቀብራቸው ሐምሌ 11/2009 በጉርድ ሾላ ሳህሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን እንደሚፈጸም ተነግሯል። አንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ ነጋሽ ገብረማርያም የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥንን በመምራትና የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆነው አገልግለዋል። በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትና በሬዲዮ እንዲሁም በቴሌቪዥን በጋዜጠኝነት ሙያ ሲሰሩ በሙያው ዘመናዊ ትምህርት ከተማሩ የቀድሞ ጋዜጠኞች አንጋፋ እንደነበሩ የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። ጋዜጠኛ ነጋሽ ገብረማርያም ሴተኛ አዳሪዋ፣የአዛውንቶች ክበብና የድል አጥቢያ አርበኞች የተባሉ ድርሰትና ተውኔቶች ጸሃፊ ናቸው። በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት በጨርጨር አውራጃ በሀብሮ ወረዳ ልዩ ስሟ መቻራ በምትባል አካባቢ በ1917 የተወለዱት አንጋፋው ጋዜጠኛ ነጋሽ ገብረማርያም አዲስ ዘመን እልታዊ ጋዜጣ እንዲሆን በማድረግና የወሬ ነጋሪ የሚባለውን መስሪያ ቤትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዲባል ያደረጉ ባለሙያ ነበሩ። ጋዜጠኛ ነጋሽ ገብረማርያም ኤዲቶሪያል የሚለውን ርእስ አንቀጽ በሚል ከሌሎች ጋር ተማክረው የቀየሩት እሳቸው እንደነበሩም ይነገራል።

Ethiopia: Businesses shut down in protest against high tax assessment

ESAT News (July 17, 2017)
Businesses in several towns in the Oromo region of Ethiopia remained closed in protest against high taxes imposed on small business owners and vendors, which they said were assessed based on estimated sales that do not reflect their real sales.
Business owners complained that the recent assessment of taxes by authorities were arbitrary and the “estimated sales” as assessed were ten times their daily sales in some cases.

Egyptian diplomats talks to Ethiopian House Speaker on latter’s Grand Dam

ESAT News (July 17, 2017)
Egypt’s top diplomat in Addis Ababa talks to Ethiopian House Speaker on issues related to the Grand Dam being built by the latter as recent reports of water filling of the dam has worried Egyptians.
A delegation led by Egypt’s Ambassador to Ethiopia Abubakar Hefni Mahmoud met Ethiopia’s House Speaker Abadula Gemeda on Saturday. Reports coming out of Egyptian media show the country is wary of the water buildup at the dam.

Thursday, July 13, 2017

የአዲስ አበባ የግብር መክፈያ ቦታዎችም በአቤቱታ አቅራቢዎች እየተጨናነቁ ነው 

ሐምሌ ፮ ( ስድስት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባ የግብር መክፈያ ቦታዎችም በአቤቱታ አቅራቢዎች እየተጨናነቁ ነው የእለታዊ ገቢ ግብር አሰራርን በመቃወም በአምቦ ከተማ ዛሬ ተቃውሞ ሲካሄድ የዋለ ሲሆን፣ አንድ የፌደራል ፖሊስ መኪና ሲቃጠል ፣ አንድ አውቶቡስና ሌሎች የመስሪያ ቤት መኪኖችም ተሰባብረዋል። ይህን ዜና እስካጠናከርንበት በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር እስከ 11 ሰአት ድረስ በከተማዋ ተኩስ ይሰማ ነበር። ወደ ወለጋ የሚወስደው መንገድም በድንጋይ ተዘጋግቷል። በከተማዋ ያሉ አገልግሎት መስጫ ተቋማትና የንግድ ቤቶችም ተዘግተዋል። በአዲስ አበባ ደግሞ የግብር መክፈያ ቤቶች በአቤቱታ አቅራቢዎች ተጨናንቀው ታይተዋል። በየወረዳው የሚገኙ ጽ/ቤቶች በአቤቱታ አቅራቢዎች በመጨናነቃቸው ፣ ባለስልጣናቱ “የምትችሉትን ክፈሉና ሌላውን ቀስ ብላችሁ ትከፍላላችሁ” በማለት ለማረጋጋት ሙከራ ሲያደርጉ ታይተዋል። ነጋዴዎች ግን በባለስልጣኖች በኩል የሚሰጠውን መልስ የሚቀበሉት አልሆነም። በዲላ ነጋዴዎች ግብር አንከፍልም በማለት በአንድ ድምጽ እየተናገሩ ሲሆን፣ ድምጻቸውን ለማሰማት የተቃውሞ ሰልፍ ለማዘጋጀት የሚያደርጉትን ሙከራ ከንቲባው ለማጨናገፍ እየተሯሯጠ መሆኑን ወኪላችን ገልጿል።


የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ የተከሰሱበትን የሽብር ክስ ወደ ተራ ወንጀለኝት እንዲቀየር የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰነ

ኢሳት ሐምሌ-6/2009 የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ የተከሰሱበትን የሽብር ክስ ወደ ተራ ወንጀለኝት እንዲቀየር የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰነ። ፍርድ ቤቱ በሽብር ወንጀል ከተከሰሱት 22 የተቃዋሚ የፖለቲካ መረጃዎችና አባላት 17ቱ እንዲከላከሉ የጥፋተኝነት ውሳኔ አሳልፎባቸዋል። 5 ተጠርጣሪዎች ደግሞ በነጻ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤቱ ውስኗል ። ፍርድ ቤቱ በቀጥታ በሽብር ወንጀል ተሳትፈዋል ተብለው ተከሰው ከነበሩት መካከል ጎርሜሳ አያና፣ ደጀኔ ጣፋ፣ አዲሱ ቡላላ፣ አብሏታ ነጋሽ፣ ገላና ነገራ፣ ጌቱ ግርማ፣ በየነ ረዳ እና ተስፋዬ ሊበን በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ መሳተፍ ወደሚል ተቀይሮ በአዋጅ አንቀፅ 3 ወደ አንቀፅ 7 ንዑስ ቁጥር 1 ተቀይሮ ይከራከሩ ሲል ክሳቸውን አሻሽሏል። አቶ በቀለ ገርባ ላይ የቀርበው ማስረጃ የሽብር ወንጀልን የማያቋቁም ስላልሆነ ከፀረ-ሽብር አዋጅ ወጥቶ በወንጀልኛ መቅጫ ሕጉ አንቀፅ 257/ሀ/ ስር የተሰናዳ ግዙፍ ያልሆነ መሰናዳትና መገፋት ክስ ተቀይሮ እንዲከላከሉ ወስኗል። የአቶ በቀለ ገርባ የሽብር ክስ በማስረጃ የተረጋገጠ አይደለም ቀሪ ቢደረግም ለምን ወደ ወንጀል ክስ አደገና እንዲቀየር ፍርድ ቤቱ እንደወሰነ ግልጽ አይደለም ተብሏል። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ የተከሰሱበት የሽብር ክስ ቀሪ በመደሩጉ የዋስትና መብታቸውን የመጠበቅ መብት እንዲኖራቸው እንደሚያደርጉ አዲስ ስታንደርድ ዘግቧል። በኢትዮጵያ በሽብር የተከሰሰ ማንኛውም ሰው ዋስትና የመጠበቅ መብት የለውም። ይህም ሆኖ ግን አቶ በቀለ ገርባ አሁንም ጥፋተኛ የተባሉበት ወንጀል ክስ ከሕገመንግስቱ ውጭ አመፅን ቀስቅሰዋል ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን ተፃረዋል እና የእርስበርስ ጦርነት እንዲቀሰቀስ ምክንያት ሆነዋል ስለሚል ከባድ ቅጣት እንደሚያስከትልባቸው በዘገባው ተመልክቷል። በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት ከክሱ ነፃ የተደረጉት ጌቱ ግርማ፣ ጌታቸው ደረጀ፣ በየነ ፊዳ፣ ደረጀ መርባ እና ሐልቄኖ ቆንጨራ ናቸው። በሽብርተኝነት እንዲከላከሉ ከተበየነባቸው 16ቱ ተከሳሾች መካከል ደግሞ ጎርሜሳ አያኖ፣ ደጀኔ ጣፋ፣ አዲሱ ቡላላ፣ አብደታ ኔጌሳ እና ገላና ነገራ ይገኙበታል። 16ቱ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በሽብር ወንጀል ከተፈረደባቸው ከ5 እስከ 10 ዓመታት እስር እንደሚጠብቃቸው የሕግ ባለሙያዎች ይገልፃሉ። ተከሳሾቹ በሽብር ከተፈረጀው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር/ኦነግ/ ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል እንደሆነ የተወነጀሉት የአቃቤ ሕግ ሰነድ ያመለክታል። ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን የመከራከሪያ ሀሳቦችን ለማድመጥ እ/አ/አ ለነሐሴ 17/2017 መቅጠሩን አዲስ ስታንዳርድ ዘግቧል።


በአለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ የአለም ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው የጣና ሃይቅ በእምቦጭ አረም መስፋፋት ምክንያት የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል።

ኢሳት-ሐምሌ 6/)2009 በአለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ የአለም ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው የጣና ሃይቅ በእምቦጭ አረም መስፋፋት ምክንያት የመጥፋት አደጋ ተደቅኖበታል።ከዚህ ባልተናነሰ ግን በባህር ዳር ከተማና በሃይቁ ዙሪያ የሚገኙ የአገልግሎትና መንግስታዊ ተቋማት ወደ ሃይቁ የሚለቁት ፍሳሽ ችግሩን እንዳባባሰው የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ከአማራ ክልል ምክር ቤት ህንጻ ፣ ከመስተዳድሩ የዘርፉ ቢሮዎች ፣ከ3 ሺ በላይ ታሳሪዎችን ከሚይዘው ወህኒ ቤት ፣ ፖሊ ቴክኒክን ጨምሮ ከባህር ዳር ዩኒቨርስቲ የሚወጡት ፍሳሾች የሃይቁን ደህንነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዱት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ከእነዚህ መንግስታዊ ተቋማት በተጨማሪ በባህር ዳር ዙሪያ የሚገኙት የሼሕ መሃመድ አላሙዲን ንብረት የሆኑት የጣናና አቫንት ሪዞርት ሆቴል፣የወይዘሮ ትልቅ ሰው ገዳሙ ንብረት የሆነው ግራንድ ሆቴል፣የአቶ ጠብቀው ባሌ ንብረት የሆነው ፓፒረስ ሆቴል ፣ሆም ላንድ ሆቴልና ከአገልግሎት መስጫ ተቋማት የሚወጣው የመጸዳጃ ቤት እንዲሁም ሌሎች የቆሻሻ ፍሳሾች ሃይቁን ለብክለት እየዳረጉት መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸዋል። የክልሉ ኦዲተር መስሪያ ቤት ለክልሉ ምክር ቤት 6ኛ መደበኛ ጉባኤ ባቀረበው ሪፖርትም በባህር ዳር ከተማ የሚገኙ ሆቴሎች የመጸዳጃ ቤት ቆሻሻን ከፍሳሽ ማስወገጃ ቦይ ጋር በማገናኘት የጣና ሃይቅንና የአባይ ወንዝን እየበከሉ መሆኑን ይገልጻል። ባለቤቶቹ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በተደጋጋሚ ቢጠየቁም ተጫማሪ እንቅስቃሴ አለማድረጋቸውን የዋና ኦዲተሩ ሪፖርት ያመለክታል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከመንግስታዊና የአገልግሎት መስጫ ተቋማት የሚወጣው ፍሳሽ የሚይዛቸው እንደ ፎስፌትና ናይትሬት የመሳሰሉ ኬሚካሎች በጣና ሃይቅ ላይ አደጋ ለጋረጠው የእምቦጭ አረም መስፋፋት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ባለሙያዎች ይናገራሉ። የእምቦጭ አረም ከቆሻሻው የሚወጣውን ፎስፌትና ናይትሬን እየተመገበ እንደሚስፋፋ በመግልጽ በስፋቱ 350 ሺ ሄክታር ከሚሆነው አጠቃላይ የጣና ሃይቅ ገጽታ 50 ሺ ሄክታር ያህሉን በእምቦጭ አረም እንደተወረረ ባለሙያዎች አረጋግጠዋል። በዚሁም ሳቢያ የጣና ሃይቅ ሕልውና አደጋ ላይ በመውደቁ ብዙዎቹን እያሳስበ ይገኛል ።


በአዳማ(ናዝሬት) ተቃውሞ ተቀስቅሷል

አሁን የደረሰን ዜና
በአዳማ(ናዝሬት) ተቃውሞ ተቀስቅሷል። ከግብር ጋር በተያይዘ የነጋዴው ማህበረሰብና ህብረተሰቡ የሚያሰማው ቅሬታ ወደ ተቃውሞ ተቀይሮ ቁጣ መነሳቱን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በቱሉ ቦሎም ተመሳሳይ ተቃውሞ መቀስቀሱን ለማወቅ ተችሏል።



Tuesday, July 11, 2017

በአዲስ አበባ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ተደረገ

ኢሳት ዜና (ሃምሌ 4 ,2009 ) የአዲስ አበባ አስተዳደር በመካከለኛ ገቢ ለሚኖሩ ሰዎች በገነባቸው የኮንደሚኒየም ቤቶች ላይ ያደገው የዋጋ ጭማሪ ተመዝጋቢዎችን ማስቆጣቱ ተነገረ ። አስተዳደሩ የ972 ቤቶችን እጣ ከማውጣቱ ሁለት ቀናት ቀደም ብሎ መካከለኛ ገቢ ላላቸው የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዋጋን በፊት ከታቀደው 56 በመቶ ጭማሪ አድርጓል ። ለቤቶቹ 11 ሺህ 88 ተመዝጋቢዎች የነበሩ ሲሆን ሁሉም ሙሉ በሙሉ የሚጠበቅባቸውን ክፍያ የፈጸሙ ናቸው ተብሏል ። የአዲስ አበባ አስተዳደር የቤቶች ልማትና ቁጠባ ድርጅት 972 ቤቶችን ገንብቶ ከነዋሪዎች ተቀማጭ ገንዘቡን ለሚሰበስበው ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስረክቧል ። ቤቶቹን ለመገንባት እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2013 ሲታቀድ ለባለ አንድመኝታ ቤት 228 ሺህ 900 ብር ፣ ለባለ ሁለት መኝታ ቤት 330 ሺህ ብር ፣ለባለሶስት መኝታ ቤት ደግሞ 386 ሺህ ብር በስኰር ሜትር ለማስከፈል ስምምነት ተደርሶ ነበር ። ይህም ሆኖ ግን በመሰረተ ልማት ፣ በሰራተኛ ዋጋ መጨመርና በቤቶች የዲዛይን ለውጥ ምክንያት የቤቶቹ ዋጋ ላይ በ56 በመቶ ጭማሪ መደረጉን አስተዳደሩ ይፋ አድርጓል እናም በአዲሱ ዋጋ ተመን መሰረት ለባለ ሁለት መኝታ ቤት 614 ሺህ 602 ብር ፣ ለባለ ሶስት መኝታ ቤቶች 735 ሺህ 241 ብር ፣ ለባለ አራት መኝታ ቤቶች ደግሞ 829 ሺህ 568 ብር እንዲሆን መደረጉን ፎርቹን ጋዜጣ

ለአበባ እርሻ የመሬት እጦት መኖሩን ጠ/ሚ ሃይለማሪያም ገለጹ

ኢሳት ዜና (ሀምሌ 4 ,2009 )በኢትዮጵያ የአበባ ኢንቨስትመንት በመሬት አቅርቦት እጥረት መገታቱን ጠ/ሚ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ለፓርላማ ገለጹ ። በኢህአዴግ ፓርላማ የ2010 በጀትን ለማጽደቅ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪኣም ደሳለኝ የሃገሪቱ የውጪ ንግድ እያሽቆለቆለ መሆኑን ተናግረዋል ። ችግሩን እንዲጎላ ካደረጉት ጉዳዮች መካከል በአበባ ኢንቨስትመንት ማስፋፋት ምክንያት የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ፌደራል መንግስት ያረገው ጥረት የክልል መስተዳደሮች መሬት አናቀርብም በማለታቸው ተስተጓጉሏል ሲሉ ስሞታ አቅርበዋል ። አቶ ሃይለማሪያም በገለጻቸው ለአበባ እርሻ የሚሆን መሬት ባለመገኘቱ ፌደራል መንግስት በአማራጭ መፍትሄነት ከመንግስት ልማት ድርጅት ይዞታዎች ውስጥ የሚገኙ መሬቶችን ለመጠቀም እየተገደደ መሆኑን አስታውቀዋል ። በአጠቃላይ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው የውጪ ንግድ እያሽቆለቆለ መሆኑ የሃገሪቱን የንግድ ሚዛን ጉድለት እያባባሰው መምጣቱን የአለም የገንዘብ ድርጅት ሪፖርት መግለጹ የሚታወስ ነው ። ላለፉት አስር አመታት በሃገሪቱ ገቢና ወጪ ንግድ መካከል የታየው የንግድ ሚዛን ጉድለት በአማካይ 50 ቢሊዮን ብር ነበር ።በተለይ ባለፈው አመት የነበረው የንግድ ሚዛን ጉድለት ከ87 ቢሊዮን ብር በላይ ማሻቀቡን የንግድ ሚኒስቴር ሪፖርቶች ይጠቁማሉ ። በኢትዮጵያ የአበባ ኢንቨስትመንት በአንድ ወቅት ሰሞንኛ አጀንዳ ሆኖ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ከፍተኛ ሽፋን ሲያገኝ እንደነበረ አይዘነጋም ።በአበባ ኢንቨስትመንት ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ እየተገኘ እንደሆነ ሲገለጽ ቢቆይም በኋላ ላይ ግን ምርቱን የሚወስዱ ሃገሮች ፊታቸውን በማዞራቸው ባለሃብቶቹ ማማረር መጀመራቸው ይታወሳል ። ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ የውጪ ዜጎች ሲሳተፉበት የቆዩት የአበባ ኢንቨስትመንት ጎጂ ኬሚካሎችን ስለሚጠቀም በሰራተኛ ላይ ጉዳት በማድረሱም ተቃውሞ አስነስቶ ነበር ።በኢትዮጵያ ህዝባዊ አመጽ በተቀሰቀሰ ጊዜም የአበባ ኢንቨስትመንቶች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸውም መገለጹ ይታወቃል ። ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም በፓርላማ ቀርበው የአበባ ኢንቨስትመንት የተዳከመው በመሬት እጦት ነው ቢሉም ከዘርፉ ጋር ያሉ ሌሎች በርካታ ችግሮችን ግን አላነሱም ።

የአውሮፓ ህብረት 39 የፓርላማ አባላት በኢትዮጵያ የሚፈጸመው የሰባዊ መብት ጥሰት እንዲጣራ ጥሪ አቀረቡ

ኢሳት ዜና ( ሃምሌ 4, 2009 ) የአውሮፓ ህብረት 39 የፓርላማ አባላት በኢትዮጵያ የሚፈጸመው የሰባዊ መብት ጥሰት እንዲጣራ ጥሪ አቀረቡ ። የፓርላማ አባላቱ የፈረሙት ደብዳቤ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ ያለው የሰባዊ መብት ረገጣ ሙሉ በሙሉ መጣራት ይኖርበታል ።በአገዛዙ የተቋቋመው የኢትዮጵያ የሰባዊ መብት ኮሚሽን ተካሄደ የተባለው የምርመራ ሪፖርት የገለልተኛነት ጥያቄ እንዳለበትም የፓርላማ አባላቱ ገልጸዋል ። የአውሮፓ ህብረት የ39ኙ የፓርላማ አባላት ፊርማ ያለበት ደብዳቤ የተላከው ለምክር ቤቱ የውጭ ጉዳዮች ከፍተኛ ተወካይ ለሆኑት ፌድሪካ ሞግሄርኒ መሆኑ ታውቋል ።እናም የፓርላማ አባላቱ ኢትዮጵያ በሃገሪቱ ያለው የሰባዊ አያያዝ ሁኔታ ገለልተኛ አካል እንዳያጣራ መከልከሉ በቸልታ ሊታይ አይገባም ባይ ናቸው ። ገለልተኛ አጣሪ አካል ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ሁኔታውን ካልመረመረ ባለፈው አንድ አመት በነበረው ህዝባዊ አመጽ የተገደሉትንና ደብዛቸው የጠፋ ሰዎችን ቁጥር በውል ማወቅ አይቻልም ነው ያሉት ። የፓርላማ አካላቱ እንደ አውሮፓ ህብረት ፓርላማ አባላት ገለጻ የኢትዮጵያ መንግስት ለፈጸማቸው ማናቸውም የሰባዊ መብት መተላለፍ ተጠያቂነትንና ሃላፊነትን መውሰድ ይኖርበታል ። በሰባዊ መብት ረገጣው ሴቶች መደፈራቸውና የጾታ ጥቃት መፈጸሙንም የፓርላማ አባላቱ መረጃ እንዳላቸው አረጋግጠዋል ። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከህግ ውጪ የተያዘበት መንገድና የእስር ሁኔታም በእጅጉ የሚያሳስባቸው ጉዳይ መሆኑንም 39ኙ የአውሮፓ ፓርላማ አባላት በደብዳቤቸው አጽኖት ሰጥተዋል ። ከአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ የእርዳታ ገንዘብ የምታገኘው ኢትዮጵያ የሰባዊ መብት የማታከብር ከሆነ ጉዳዩ እንደገና ሊጤንና ሃገሪቱ የምታገኘው ድጋፍ መገታት እንዳለበት የፓርላማ አባላቱ ጥሪ አቅርበዋል ። በኢትዮጵያ የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እስካሁን እንዳልተነሳና ሃገሪቱ አሁንም በውጥረት ውስጥ መሆኗንም አፍሪካ ታይምስ መግለጫውን መነሻ በማድረግ ዘገባ አቅርቧል ።

Monday, July 10, 2017

Ethiopia’s largest lake threatened by water hyacinth

ESAT News (July 10, 2017)
The ecosystem of Lake Tana, Ethiopia’s largest lake, has been threatened by the spread of water hyacinth, which experts warn could create significant damages to the fish and other aquatic life.
Besides its negative effect in hampering transportation, irrigation and hydroelectric power, it also creates a breeding ground for mosquitoes.

የአማራና ኦሮምያ ክለብ ደጋፊዎች ህውሃትን ኣወገዙ

(ኢሳት ዜና – ሃምሌ 3 , 2009 ) የኦሮምያና የአማራ እግር ኳስ ክለቦች ደጋፊዎች በባህርዳር ስታዲየም የጋራ ትብብር ባማሳየት የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ ህውሃት / አገዛዝን አወገዙ ። የባህርዳር ከተማ ክለብና የኦሮምያ ለገጣፎ እንዲሁም የአማራ ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት / አውስኮድ / ከሱሉልታ ጋር ሲጫወቱ የየክለቦቹ ደጋፊዎች በወዳጅነት መንፈስ በጋራ ሲጨፍሩ ታይተዋል:: በውድድሩ በባህርዳር ከተማና ለገጣፎ ተጫውተው 0 ለ 0 ሲለያዩ ሱሉልታ አውስኮድ ቡድን 1 ለባዶ አሸንፏል ። በዚሁም ጊዜ በባህርዳር አጼ ቴዎድሮስ ስታዲየም በተካሄዱ ጨዋታዎች የአማራና የኦሮምያ ደጋፊዎች በትብብር ስሜት ሆነው የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ / ህውሃትን /አገዛዝ አውግዘዋል ። ደጋፊዎቹ የክለባቸውን አርማና ኮከብ የሌለበት የኢትዮጵያ ባንዲራ ይዘው የኦሮሞና የአማራ ህዝብ አንድ መሆኑን የሚያሳዩ ዜማዎችን ሲያሰሙ ውለዋል ። የአማራና የኦሮምያ እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች ህብረታቸውን በወዳጅነት ስሜት በጭፈራ ሲያሳዩና ህውሃትን ሲያወግዙ በፌዴራል ፖሊሶች ከመከበባቸው ውጪ የደረሰባቸው ጉዳት የለም ። በአማራ ክልል ህዝባዊ ተቃውሞ በተቀሰቀሰበት ጊዜ የኦሮሞ ደም ፥ ደሜ ነው በማለት በጎንደርና በባህርዳር ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ነዋሪዎች ህብረታቸውንና አጋርነታቸውን ማሳየታቸው ይታወሳል ።

በአማራ ክልል ትጥቅ የማስፈታቱ ሙከራ አሁንም አልተሳካም

( ኢሳት ዜና -ሃምሌ 3 , 2009 ) በአማራ ክልል አርሶ አደሩን ትጥቅ ለማስፈታት ከሚሊሻ ሃላፊዎችና ከፖሊስ ጋር በተቀናጀ መልኩ የተጀመረው ዘመቻ ቢጠናከርም አሁንም አለመሳሳቱ ተነገረ ። በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ / ህውሃት / የሚመራው ወታደራዊ እዝ / ኮማንድ ፖስት / በመሳሪያ ምዝገባና በግብር ስም የጠራው ስብሰባ መጨናገፉም ተገልጿል ። በጎጃምና በጎንደር ድንገተኛ የቤት ለቤት ፍተሻ እየተካሄደ መሆኑንም የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል ። በጎጃም ሸበል በረንታ ወረዳ ይጠሃና ቀበሌ የሚኖሩ አርሶአደሮች በሰሜን ሸዋ ደራ እንዲሁም ደቡብ ወሎ ወግዲ የቤት ለቤት ፍተሻ ለማካሄድ ታቅዶ መክሸፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ ። በመሳሪያ ምዝገባና በግብር ስም የተጠራው ስብሰባም ከሚሊሻዎችና ከፖሊስ አካላት ሳይቀር ተቃውሞ እየገጠመው መሆኑን ለማውቅ ተችሏል ። የመሳሪያ ገፈፋውን የተቃወሙ የሚሊሻና የፖሊስ አባላት ከጸረ ሰላም ሃይሎች ጋር ትሰራላቹ በሚል ችግር እየደረሰባቸው እነደሆነም ነው የተነገረው ።ከዚሁ ጋር በተያያዘ በወረዳው ጣታና ጢሮ አካባቢዎች በዛምበራ ጫካ የሚኖሩ አርሶአደሮችን ለጦር መሳሪያችሁ ግብር ክፈሉ በማለት ለመደለል ያደረጉት ሙከራም እንዳልተሳካ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል ። በሸበል በረንታ 19 ቀበሌዎች ያሉ ካድሬዎችን በየእድ ውሃ ከተማ ሰብስበው ገበሬውን ትጥቅ ለማስፈታት እንዴት ይቻላል ሲሉ ምክክር ቢደረግም ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልተቻለ ተነገሯል ። ካድሬዎቹ ገበሬው ብሶት ስላለበት ባትነካኩት ይሻላል ማለታቸውም ተገልጿል ። በሰሜን ጎንደር አንቃሽ ወረዳ በደቡብ ጎንደር ደግሞ እብናት በጎጃም ጃዊ ወረዳ የጀመሩት በሃይል ትጥቅ የማስፈታት ዘመቻም አለመሳካቱም ታውቋል ።

ቴዎድሮስ ካሳሁን ኮንሰርት ለማዘጋጀት የመንግስትን ፈቃድ እየጠበቀ ነው

( ኢሳት ዜና – ሃምሌ 3 , 2009 ) ታውቂው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን በሚሊንየም አዳራሽ በአዲስ አመት ኮንሰርት ለማሳየት ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ፈቃድ ማስታውቂያ ክፍል ጥያቄ ቢያቀርብም ከሚመለከተው አካል ጋር ተነጋግረን ምላሽ እንሰጥሃለን መባሉ ተዘገበ ። ቴዎድሮስ ካሳሁን ጷጉሜ 5 , 2009 አ.ም ለአዲስ አመት ዋዜማ የሙዚቃ ዝግጅቱን ለማቅረብ ውል መዋዋሉን የድምጻዊው ስራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ማንጉዳይ ገልጸዋል ። ኮንሰርቱን ለማካሄድ የተስማማው አልበሙን ያከፋፈለው ኩባንያ ጆይ ኢቨንትና ፕሮሞሽን ኩባንያና ኤፕላስ ኢቨንትና ፕሮሞሽን ጋር በጥምረት ነው ። ጆይ ኢቨንት የሚሊንየም አዳራሽን ከሚያስተዳድረው አዲስ ፓርክ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ለማወቅ ተችሏል ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ሃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው የኮንሰርት ጥያቄ መቅረቡን ለሪፖርተር አረጋግጠዋል ። ነገር ግን ከሚመለከተው አካል ጋር ተነጋግረን ምላሽ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል ። በሃገሪቱ ያለው ህገ-መንግስት ግን እንዲህ አይነት ዝግጅትም ሆነ ስብሰባ እንዲሁም ሰላምዊ ሰልፍ ለማድረግ ከ48 ሰአት በፊት ቀድሞ ማሳወቅ እንጂ ፈቃድ መጠየቅን አይጠይቅም ። ምላሽም መስጠት አያስፈልገውም ። ቴዲ አፍሮ ለኮንሰርቱ 1.8 ሚሊዮን ብር እንደሚከፈለውና ለሚሊንየም ኣዳራሽ ስራው ደሞ 1.2 ሚሊዮን እንደሚከፈል ለማወቅ ተችሏል ።ቴዎድሮስ ካሳሁን ‘’ ኢትዮጵያ ‘’ የሚለው አልበሙ ከተለቀቀ በኋላ የአዲስ አበባውን ኮንሰርት አካሂዶ በሃዋሳ በጎንደርና በመቀሌ ተጨማሪ ኮንሰርቶች ለማዘጋጀት ከስምምነት ላይ መደረሱን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል ።

በምስራቅ ኣፍሪካ 27 ሚሊየን የሚጠጋ ህዝብ የምግብ እርዳታ ያስፈልፈዋል ተባለ

(ኢሳት ዜና – ሀምሌ 3/20009) የተባበሩት መንግስታት የሰብኣዊ መብት ድርጅት በምስራቅ ኣፍሪካ ከተከሰተው ከባድ ድርቅ ጋር ተያይዞ 27 ሚሊየን የሚጠጋ ህዝብ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ኣስታውቀ። እንደ ሪፖርቱ ከሆነ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ በኣፍሪካ ቀንድ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ስደተኛ ዚጎች ቁጥር ከ4 ሚሊየን በላይ ኣሻቅቧል። ከምስራቅ ኣፍሪካ ብቻ ባለፉት ስምንት ወራት 3 ሚሊየን የሚሆኑ ዜጝች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል ሲል ሪፖርቱ ኣመልክቷል። በኣካባቢው ያለው ድርቅ ፥ሰብል በወቅቱ ያለመሰብሰብ፥ የእርስ በርስ ግጭት ፥የአካባቢው ሰላም የተርጋገጠ ኣለመሆንና ተያያዥ ምክንያቶች በቀጣይም የስደተኞቹ ቁጥር እንዲያሻቅብ ምክንያት ሊሆን ይችላል ሲል ሪፖርቱ አክሏል። በኣካባቢው የሚጥለው ዝናብ ወቅቱን ኣልምጠበቅ ደግሞ ለችግሩ መባባስ ምክንያት ሆኗል። በኣሁኑ ሰኣት በምስራቅ ኣፍሪካ እየተከሰተ ያለው ሰብአዊ ቀውስ በታሪክ ከባድ በመባል ተመዝግባል ይላል ሪፖርቱ እንደ ኣለም ኣቀፉ የኣየር ንብረት ተቃም ሪፖርት ከሆነ ደግሞ በመጪው የመጸው ወቕት ይከሰታል ተብሎ በሚጠበቀው አውሎ ንፋስ ኢትዮጽያን ሰሜን ኬንያን ሶማሊያን ምእራብ ዩጋንዳን ሩዋንዳን ቡርንዲንና ሰሜን ምእራብ ደቡብ ሱዳንን ሊያጠቃ ይችላል

Friday, July 7, 2017

Ethiopia: Federal High court rejects Merea Gudina’s two requests

Bildergebnis für dr merera gudina ethiopiaESAT News (July 7, 2017)
A Federal High Court in Addis Ababa rejects request by Dr. Merera Gudina for his case to be seen separately from the bogus terrorism charges brought against two independent media abroad.
The regime brought cooked up terrorism charges against Gudina and two media outlets abroad: the Ethiopian Satellite Television and Radio (ESAT) and the Oromo Media Network (OMN). Gudina’s charges were later reduced to criminal offences of attempting to overthrow the government, violating the state of emergency and giving interviews to the media outlets banned by the regime.

በደቡብ ጎንደር የተጀመረው ትጥቅ የማስፈታት ዘመቻ ከሸፈ

(ኢሳት ዜና – ሰኔ 30 2009) በደቡብ ጎንደር እብናት ወረዳ የህውሃት አጋዚ ጦር የገበሬውን ትጥቅ ለማስፈታት ያደረገው ሙከራ መክሸፉ ተነገረ ። በሰሜን ጎንደር የተጀመረው ገበሬውን ትጥቅ የመፍታት ዘመቻ ወደ ደቡብ ጎንደር ተሻግሯል ።የኢሳት መንጮች እንደገለጹት በደቡብ ጎንደር እብናት ወረዳ ባሉ ቀበሌዎች ትጥቅ ለማስፈታት የአጋዚ ጦር በከፈተው ተኩስ 3 ሰዎች ቆስለዋል ። በእብናት ወረዳ ሰፍሮ የነበረው የህውሃት አጋዚ ጦር በሚንጦች ፣ መልዛ ፣ ጨጨወ አቦ ፣ እና ወፍጮማ በተባሉ አካባቢዎች ዘምቶ በታጠቁ ገበሬዎች ጥቃት ደርሶበታል ተብሏል ። በዚሁ ጥቃት የተበሳጨው የህውሃት ጦር አዛውንቶችን ህጻናትንና ሴቶችን እየደበደበ ወደ እስር ቤት እያስገባቸው መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸዋል ። በሰሜን ጎንደር የተጀመረውን የትጥቅ ትግል ማስቆም ያልቻለው የህውሃት ጦር ሶስት ስልቶችን በመከተል በህዝቡ ላይ ጫና እያደረገ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል ። የህውሃት አጋዚ ጦር በስሜን ደቡብ ጎንደር ህዝቡን ትጥቅ ለማስፈታት የሚጠቀምባቸው ሶስቱ ስልቶችና ዘዴዎች የሃይማኖት መሪዎች እንዲገዝቱ መላክ ፣ በገንዘብና በማባበያ መደለልና የሃይል እርምጃ መውሰድ የሚሉ ናቸው ። በአማራ ክልል ህዝቡን ትጥቅ ለማስፈታት የተጀመረው ዘመቻ ሊሳካ ያልቻለው የእካባቢው ህብረተሰብ ከሁሉም በፊት ጦር መሳሪያ የነጻነቱ ዋስትና አድርጎ ስለሚወስድ ነው ተብሏል ። በሰሜንና ደቡብ ጎንደር ያሉ የነጻነት ታጋዮች በጎበዝ አለቃ እየተመሩ አካባቢውን እስካሁን ተቆጣጥረውት ይገኛሉ ። የግንቦት ሰባት አርበኞች የተለያዩ ጥቃቶችን በመፈጸም አገዛዙን እያዳከሙ እንደሚገኙም በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል ።

የኢትዮጵያ ፓርላማ ከ320 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

(ኢሳት ዜና - ሰኔ 30 2009) 
የኢትዮጵያ ፓርላማ የቀረበለትን ከ320 ቢሊዮን ብር በላይ አመታዊ በጀት አጸደቀ ።
ይህ በጀር ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸርበ17 በመቶ ብልጫ ያለው ቢሆንም የበጀት ጉድለቱ ግን የአጠቃላይ መጠኑ 1/3ኛ መሆኑን ለምወቅ ተችሏል ። ከካፒታል በጀት ከ1114 ቢሊዮን ብር በላይ ሲመደብ ለአጠቃላይ የወጪ በጀት ደግሞ 81.8 ቢሊዮን ብር ተመድቧል ።የ100 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት ያለበት የመንግስት አመታዊ በጀት ከብድር እና እርዳታ ይገኛል ጠብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል ።ዋናው ገቢ ግን ከግብርና ከሃገር ውስጥ የሚሰበሰብ ነው ተብሏል ።በበጀት እቅዱ ላይ የቀረበው መረጃ እንደሚያመለክተው ለልማት የሚውለው ገንዘብ ሲቀንስ ለመከላከያና ለጦር መሳሪያ የሚወጣው ግን ጨምሯል ።በዚሁም መሰረት የመከላከያ በጀቱ አምና 11 ቢሊዮን ብር እንዲሆን ተደርጓል ።የልማት ፕሮጀክት በጀቱ ደግሞ አምና 12 ቢሊዮን የነበረው ዘንድሮ ወደ 7 ቢሊዮን ብር እንዲወርድ ተደርጓል ተብሏል ። ኢትዮጵያ ያለባት የብድር ጫና ከ5 መቶ ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱና ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር በ35 ቢሊዮን ብር መጨመሩ መገለጹ ይታወሳል ። ከውጭ ንግድ ገቢ ኢትዮጵያ የምታገኘው ገቢ ደግሞ ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር በ5 ቢሊዮን ቀንሷል ። ከፍተኛ የገንዘብ ግሽበት ባለባት ኢትዮጵያ የእዳ ጫናውና የውጪ ምንዛሪ እጥረት በሃገሪቱ የኢኮኖሚ ሁኔታ ላይ ችግር እየፈጠረ መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ ። 

Thursday, July 6, 2017

የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ አርነት ግምባር / ጋህዴአግ/ የኦህዴድን የግዛት ማስፋፋት ጥያቄን እንደሚያወግዝ አስታወቀ

ኢሳት ዜና ሰኔ 29 2009
የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት / ኦህዴድ / ከጋምቤላ ክልል ጋር በተያያዘ እያካሄደ ያለውን ማስፋፋት ጥያቄ እንደሚያወግዝ የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ አርነት ግምባር / ጋህዴአግ / ባወጣው መግለጫ አስታወቀ ። በአሁኑ ጊዜ የኦሮሞም ሆነ የጋምቤላ ህዝብ አንገብጋቢ ጥያቄ የግዛት መስፋፋት አለመሆኑን ጋህዴአግ ገልጿል ። የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ አርነት ግንባር /ጋህዴአግ/ በመግለጫው እንዳለው ህውሃት መራሹ ገዢ ግምባር ለዘመናት በሰላምና በመቻቻል አብሮ የኖረውን ህዝብ እርስ በእርስ እንዲጋጭ በማድረግ የአብሮነት ማህበራዊ እሴትን በመናድ ላይ ይገኛል ። በተለይም በቅርቡ በጋምቤላ አካባቢ የኦህዲድ መልክተኞችን በመላክ የድንበር ማስፋፊያ ጥያቄ መቅረቡ የዚሁ ደባ ማሳያ ነው ብሏል ። ጋህዴአግ በመግለጫው ይህም የተደረገው የኦሮሞ እና የጋምቤላ ህዝብን ሆነ ብሎ ለማጋጨት ስለሆነ በእጅጉ እናወግዘዋለን ሲል ግንባሩ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል ። እንደመግለጫው የኦሮሞም ሆን የጋምቤላ ህዝብ የወቅቱ ጥያቄ የፍትህ ፥ የዲሞክራሲ እና የነጻነት እንጂ የተሰፋፊነትና የድንበር አይደለም ። እናም የሁለቱ ክልልሎች ህዝቦች የኦህዴድን የግዛት መስፋፋት ጥያቄ እንዳይቀበሉትና እንዲታገሉት የጋምቤላ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ አርነት ግንባር /ጋህዴአግ / ጥሪ አቅርቧል ። የሁለቱም ክልሎች ህዝብ በመተማመን በእኩልነትና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ ድርጅቱ አጥብቆ እንደሚሰራም አስታውቋል ።

በአዲስ አበባ ጎርፍ ባስከተለው ዶፍ ዝናብ 5 ሰዎች ሞቱ

ኢሳት ዜና ሰኔ 29, 2009
በአዲስ አበባ ባለፉት ሁለት ቀናት ከፍተኛ ጎርፍ ባስከተለው ዶፍ ዝናብ 5 ሰዎች መሞታቸውን የአደጋ መከላከል ባለስልጣናት አስታወቁ ። በከተማዋ በስተደቡብ ጫፍ ላይ አንድን ወንዝ በመሻገር ላይ የነበሩ 4 ሰዎች በጎርፍ መወሰዳቸውን የአዲስ አበባ የእሳት አደጋ መከላከል ቢሮ ቃል አቀባይ አቶ ንጋቱ ማሞ መግለጻቸውን ዘገባዎች አመልክተዋል ። የቱርኩ የዜና ወኪል አናዱሉ ከአዲስ አበባ እንደዘገበው እስከሁን የሁለት ሰዎች አስከሬን ሲገኝ አባትና ልጅ በጎርፍ ተወስደው የደረሱበት አልታወቀም ። በአዲስ አበበ ጃክሮስ አካባቢ አንዲት ሴት ድልድይ ስትሻገር አዳልጧት ወደ ወንዝ በመግባቷ በውሃው መወሰዷንም ለማረጋገጥ ተችሏል ። በጎርፉ ሳቢያ 7 ሰዎች በተደረገላቸው እገዛ ከሞት ማምለጣቸውም ተዘግቧል ። በአዲስ አበባ ካለፈው ግንቦት ወዲህ በረዶ ቀላቅሎ የሚጥለው ዝናብ በከተማዋ ከፍተኛ ስጋት መደቀኑንና በዚህም ሳቢያ ነዋሪዎቿን ለሞት እየዳረገ መሆኑን የአናዱሉስ ዘገባ ያመለክታል ። በዝናቡ ሳቢያ ከፍተኛ ንብረት መውደሙንም ዘገባው ጨምሮ ገልጿል ።

ዩኤንድፒ የአፍሪካ ዳይሬክተር አቶ ተናኘወርቅ ጌቱ የጓደግኛቸውን ልጅ ካለውድድር ቀጠሩ

ኢሳት ዜና – ሰኔ 29, 2009
የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ስራ አስፈጻሚ አባል እና የጠቅላይ ሚንስትሩ ሃይለማሪያም ደሳለኝ አማካሪ አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ ሴት ልጅ በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም ( ዩኤንድፒ ) በአባቷ እገዛ ያለውድድር እንድትቀጠር መደረጉን አንድ አለም አቀፍ የፕሬስ ተቋም አጋለጠ ። ኢንተር ሲቲ ፕሬስ የተሰኘውና በተባበሩት መንግስታት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የሚሰራው የሚድያ ተቋም እንዳለው የአምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ ጓደኛ የሆኑትና የዩኤንዲፒ የአፍሪካ ዳይሬክተር አቶ ተናኘወርቅ ጌቱ ሳሌም ብርሃኔ የተባለችን ሴት ልጅ ያለምንም ውድድር እና ህጋዊ አሰራር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንድትቀጠር ትእዛዝ ሰጥተዋል ። እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2013 በዩኤንዲፒ ያለምንም ውድድር እንድትቀጠር የተደረገችው የአምባሳደር ብርሃኔ ገብረክርስቶስ ልጅ እንደገና የመዋቅር ለውጥ በተደረገበት በ2016 ጊዜም ከፍተኛ የደረጃ እድገት እንድታገኝ መደረጉን ኢንተር ሲቲ ፕሬስ አጋልጧል ። እንደገናም በ2017 ምንም አይነት የስራ ውድድር ማስታወቂያ ሳይወጣ ወደ ቋሚ የኮንትራት ውል ተሸጋግራ በደረጃ ላይ ደረጃ ፤ በእድገት ላይ እድገት እንደተጨመረላት በዘገባው ተገልጿል ። ሳሌም ብርሃኔ በዚህ ሁኔታ ተጠቃሚ መሆኗን በሚመለከት ኢንተር ፕሬስ ሲቲ ለዩኤንዲፒ ማብራሪያ እንዲሰጠው ጥያቄ ቢያቀርብም እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ አለማግኘቱን

Wednesday, July 5, 2017

በወላይታ ሲዳማ ዞን የተነሳው የመሬት ይገባኛል ጥያቄ ወደ ግጭት እንዳያመራ መንግስት እጁን ከጉዳዩ እንዲሰብስብ ጥሪ ቀረበ


ሰኔ 28/2009

በወላይታ ሲዳማ ዞን የተነሳው የመሬት ይገባኛል ጥያቄ ወደ ግጭት እንዳያመራ መንግስት እጁን ከጉዳዩ እንዲሰብስብና በሃገር ሽማግሌዎች እንዲፈታ ጥሪ ቀረበ ።

በሰሜን አሜሪካ የወላይታ ተወላጆችና ወዳጆች ማህበር በውዝግቡ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ የወላይታ ህዝብ የሲዳማን ህዝብ ጨምሮ ከሁለቱ ጎረቤቶቹ ጋር በሰላምና በፍቅር መኖርን በማስታወስ አሁን የገጠመንም ችግር ከሲዳማ ህዝብ ጋር በመነጋገር እንዲፈታው ያለውን እምነት ገልጿል ። የውዝግቡ መነሻ የሆነውንና አሁን በወላይታ ዞን የሚገኘውን ቦታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ በመስጠት የውዝግቡን አነሳስ የሚዳስሰው መግለጫ ሁለቱም ወገኖች የግዛት ይገባኛል ጥያቄ አንስተው እንደማያውቁም አስታውሰው አሁን የተፈጠረውም ችግር የተከተለው በመንግስት አካላት ጣልቃ ገብነት እንደሆነም አመልክተዋል ።

በአባያ ሀይቅና በብላቴ ወንዝ አዋሳኝ የሆነው “ጨከሬ ‘ የተባለው ቦታ ዛሬ የውዝግብ መነሻ ሆኖ መገኘቱን የሚዘረዝረው የወላይታ ተወላጅና ወዳጆች ማህበር በመንግስት አካላት ጣልቃ ገብነት በሁለቱ ብሄረሰቢች መካከል ግጭት ሊከተል እንደሚችል ስጋቱን በመግለጽ መንግስት እጁን እንዲሰበስብ ጥሪ አድርጓል ። “ይህ ጉዳይ በጥንቃቄ ካልተያዘ በአካባቢው የማያባራ ግጭት ሊፈጠር እንደሚችልና አላስፈላጊ መናቆር ብሎም ደም መፋሰስ ሊያስከትል እንደሚችል አያጠራጥርም “ በማለት ስጋቱን የሚገልጸው የወላይታ ተወላጅና ወዳጆች ማህበር ችግሮችን በጋራ የመፍታት የዳበረ ልምድ ያላቸው ሁለቱ ብሄረሰቦች በራሰቸው እንዲጨርሱት እድል እንዲሰጣቸው ጠይቋል ።

ከወላይታና ሲዳማ ብሄረሰቦች የተውጣጡ የሃረር ሽማግሌዎች ምሁራናን ታዋቂ ግለሰቦች ያካተተ አካል እንደሚመሰረትና ለችግሩ እልባት እንዲሰጥ ምእሕበሩ ጥሪውን አቅርቧል ።


የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ሬድዮ የተመሰረተበት 7ኛ ዓመት በቴነሲ ግዛት ናሽቪል ከተማ ተከበረ

ሰኔ 28/2009

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ሬድዮ የተመሰረተበት 7ኛ ዓመት በቴነሲ ግዛት ናሽቪል ከተማ ተከበረ ። በከተማዋ የሚገኙ የኢሳት ደጋፌዎች በተገኙበትና በሳምንቱ መጨረሻ በተካሄደው መድረክ ኢሳትንና የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮችን የተመለከቱ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ውይይትም ተካሂዷል ።

የናሽቪል የኢሳት ኮሚቴ ባዘጋጀውና ቅዳሜ ጁላይ 2/20/17 በተካሄደው ዝግጅት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እንዲሁም ኮሜዲያን ክበበው ገዳ የተገኙ ሲሆን ከአጎራባቿ ከተማ ሜንፈስ የመጡ የኢሳት ደጋፊዎችና በዝግጅቱ

Tuesday, July 4, 2017

ብአዴን ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካና ርእዮተአለም ብልሽት አጋጥሞታል።

ሰኔ ፳፯ ( ሃያ ሰባት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- “ ብአዴን ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካና ርእዮተአለም ብልሽት አጋጥሞታል። በ40 እና 50 አመታት ጊዜ ውስጥ የበለጸገ አገር የሚፈጥር መስመር ሆኖ እያለ፣ ይህንን መስመር በብቃት ባለማወቃችን ምክንያት ይህን መስመር እየተከላከልነው አይደለም” የሚሉት ባለስልጣኑ፣ በእኛ የአመለካከትና የአስተሳሰብ ብልሽት ምክንያት ከመስመራችን በተጻጻሪ ለቆሙ ሃይሎች አቅም ሆነን እንታያለን ሲሉ በተሃድሶ ስብሰባ ላይ ምሬታቸውን ይገልጻሉ። ለአስተሳሰባችን መበላሸት ማሳያ ከሆኑት ምክንያቶች መካከል በክረምት ወራት የገጠመን ከፍተኛ ትርምስ አንዱ ነው የሚሉት ባለስልጣኑ፣ የደርግን ስርዓት አንኮታኩተው የጣሉትን ህወሃትን ከኢህአዴግ ጋር ለማጣላት፣ ህወሃትን በብአዴን ላይ ለማነሳሳትና ከፍተኛ ግጭት ለመፍጠር ጸረ ሰላም ሃይሉ ሃይሉን አሟጦ ሲሰራ ቆይቷል ይላሉ። “ይህ የተጠነሰሰው ሴራ ባግባቡ ያልገባው የእኔ

የኪነጥበብ ሙያተኞች በሽብርተኝነት ተከሰሱ

ኢሳት ሰኔ 27/2009
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት 5 አርቲስቶችን እና ተባባሪዎች ያላቸውን የሽብርና የወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል።
ሴና ሰለሞን፣ ኢፋ ገመቹ፣ ሃይሉ ነጮ፣ አሊያድ በቀለ እና ኤልያስ ክፍሉ የተባሉ አርቲስቶችና በግል ስራ እንደሚተዳደሩ የተገለጹ ቀነኒ ታምሩ እና ሞይቡሊ ምስጋኑ የቀረበባቸው ክስ ሁከትና አመጽ የሚያነሳሱ ዜናዎችን በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋ አዘጋጅተው በድምጽ በመቅረጽ ማሰራጨታቸው፤ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ስለ አገሪቱ ፖለቲካዊ ሁኔታ ቃለ-መጠይቅ በማድረግ ማሰራጨታቸው፤ ሁከትና አመጽን የሚያነሳሱና ሙዚቃዎችን በማዘጋጀት ከኦነግ ባንራና ወታደሮች በማቀናበር በዩቲዩብ ላይ በመጫናቸው እንደሆነ የክስ መዝገባቸው አመላክቷል።

የህዉሃት/ ኢህ አዴግ መንግስት 120 የሱማሊያ እስረኞችን ለሱማሊያ መንግስት ማስረከቡ ተገለጸ

ኢሳት ሰኔ 27/2009
የህዉሃት/ ኢህ አዴግ መንግስት 120 የሱማሊያ እስረኞችን ለሱማሊያ መንግስት ማስረከቡ ተገለጸ። 29ኛውን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ እየተካፈሉ ያሉት የሱማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀሰን አሊ በቲውተር ገጻቸው የመረጃውን ትክክለኛነት አረጋግጠዋል።
የሱማሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃሰን አሊ ሰኞ እለት እንደገለጹት ከሆነ ሃገራቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በገባችው ስምምነት መሰረት 120 የሱማሊያ እስረኞችን ተረክባለች። እስከ ኣስር አመት እና ከዚያ በላይ መታሰራቸው የተገለጸው እስረኞች በምን መመዘኛ ሁኔታ እንደተለቀቁ፤ እንዲሁም የኢህአዴግ መንግስት በአጸፋው ምን ሊያገኝ እንደሚችል የተገለጸ ነገር አለመኖሩ ለማወቅ ተችሏል።
በሜሪካ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከመጣ በኋላ ኢትዮጵያ በሱማሊያ ያላት ሚና እየቀነሰ በመሄዱ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የአለም አቀፍ ትኩረት ለመሳብ ጥረት እየተደረገ መሆኑ በኢሳት መዘገቡ የሚታወስ ነው።

ለቤት ግንባታ በአለም አቀፍ ጨረታ የተመዘገቡ የውጭ አገር ኩባንያዎች ወደ ስራ አለመግባታቸው ተገለጸ

ኢሳት ሰኔ 27/2009
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ለቤት ግንባታ ባወጣው አለም አቀፍ ጨረታ 28 የሚጠጉ ደረጃ አንድ የውጭ ኮንትራክተሮች ተወዳድረው የተመረጡ ቢሆንም አንዳቸውም ወደ ስራ መግባት እንዳልቻሉ የኢሳት ምንጮች ገለጹ።
ከዛሬ ሁለት አመት በፊት የኮንስትራክሽን ሚኒስትሩና የአዲስ አበባ ከንቲባ የሆኑት አቶ ድሪባ ኩማ በሰጡት የጋራ መግለጫ የውጭ ኮንትራክተሮችን በመኖሪያ ግንባታ ዘርፍ ለማሳተፍ ቅድመ-ዝግጅቱ የተጠናቀቀ መሆኑን ገልጸው በጥቂት ቀናት ወደ ስራ ይገባሉ ቢሉም ባልተገለጸ ምክንያት መግለጫው ተፈጻሚ መሆን እንዳልቻለ ለማወቅ ተችሏል።
በአለም አቀፍ ጨረታ የተመዘገቡት የውጭ ሀገር ኩባንያዎች እንዲቀሩ የተደረገው በገንዘብ እጥረት መሆኑን የገለጹት የኢሳት ምንጮች የህዉሓት መራሹ መንግስት ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ብቻ በበጀት ያልተደገፈን እቅድ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

ህወሃት መራሹ መንግስት ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚያስተላልፈውን የቴሌቪዥና የራዲዮ ስርጭት ሙሉ በሙሉ ለማፈን የሚያደርገው እንቅስቃሴ ለማክሽፈፍ ነጻነት ናፋቂ ኢትዮጵያውያን በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀናጅተው እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ ቀረበ

ኢሳት ሰኔ 27/2009
ህወሃት መራሹ መንግስት ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚያስተላልፈውን የቴሌቪዥና የራዲዮ ስርጭት ሙሉ በሙሉ ለማፈን የሚያደርገው እንቅስቃሴ ለማክሽፈፍ ነጻነት ናፋቂ ኢትዮጵያውያን በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀናጅተው እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ ቀረበ።
የኢሳት ዋና ዳይሬክተር አበበ ገላው ጉዳዩን በማስመልከት ለኢሳት በሰጠው መግለጫ አንዳስገነዘበው ህወሃት መራሹ መንግስት በከባድ ፈተና ውስጥ ባለበት በዚህ ወቅት ከመቶ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መድቦ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑ ገልጿል።
የህውሃት/ ኢህአዴግ አገዛዙ የስለላና የአፈና መረብ በሆነው ኢንሳ በተባለው ድርጅት አማካኝነት በቅርቡ

Monday, July 3, 2017

በህገወጥ መንገድ ወደ ታንዛኒያ የገቡ 45 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በበቆሎ ማሳ ውስጥ ተደብቀው መያዛቸውን የታንዛኒያ ባለስልጣናት አስታወቁ።

ሰኔ ፳፮ ( ሃያ ስድስት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በህገወጥ መንገድ ወደ ታንዛኒያ የገቡ 45 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በበቆሎ ማሳ ውስጥ ተደብቀው መያዛቸውን የታንዛኒያ ባለስልጣናት አስታወቁ። ኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ካለምንም ሕጋዊ ሰነድ ወደ ታንዛኒያ ሲገቡ መያዛቸውን የታንጋ ክፍለሃገር የስደተኞች ጉዳይ ዋና ሃላፊ የሆኑት ክሪስፒን ኒጎያኒ ገልጸዋል። ባለስልጣኑኑ እንዳሉት ስደተኞቹ በሰሜናዊ ምስራቅ ታንዛኒያ በሚኪንጋ አውራጃ በኬኒያ እና ታንዛኒያ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሆሮሆሮ ላይ በቁጥጥር ሥር ውለዋል። አክለውም ኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች በእርሻ ማሳ ውስጥ ተደብቀው ከታንዛኒያ ወደ ማላዊ ድንበር የሚያሸጋግራቸውን ሰው በመጠበቅ ላይ እያሉ መያዛቸውን እና በሕገወጥ አዘዋዋሪዎች አማካኝነት ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊገቡ እንደነበርም አስታውቀዋል። ሕገወጥ ስደተኞችን በማዘዋወር ተግባር ላይ የተሰማሩ ታንዛኒያዊያን መኖራቸውንም ባልስልጣኑ አውስተው ኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞችን በበቆሎ ማሳ ውስጥ ሲያዙ በርሃብ ደክመው መዛላቸውንም ባልስልጣኑ አክለው ገልጸዋል። በሕገወጥ መንገድ ወደ ታንዛኒያ በመግባታቸው ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ እና ታንዛኒያ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት የሚሞክሩ ሕገወጥ ስደተኞች መተላለፊያ አገር እየሆነች መምጣትዋን ዥንዋ ዘግቧል።

በሽብርና በሌሎችም ወንጀሎች ተከሰው በእስር ቤት እያሉ እንደገና ቂሊንጦን አቃጥለዋል በሚል ክስ ከቀረበባቸው ወጣቶች መካከል፣ የተወሰኑት ዝዋይ እስር ቤት ተወስደው ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው እንደሚገኙ ምንጮች ገልጸዋል።

ሰኔ ፳፮ ( ሃያ ስድስት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሽብርና በሌሎችም ወንጀሎች ተከሰው በእስር ቤት እያሉ እንደገና ቂሊንጦን አቃጥለዋል በሚል ክስ ከቀረበባቸው ወጣቶች መካከል፣ የተወሰኑት ዝዋይ እስር ቤት ተወስደው ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው እንደሚገኙ ምንጮች ገልጸዋል። እስረኞች ፍርድ ቤት ላይ ተቃውሞ በማሰማት፣ እንዲሁም የእስር ቤቱን አስተዳደር ፊት ለፊት በመጋፈጥ ይታወቁ ነበር። በተለይ አዲስ ክስ በሀሰት ከተመሰረተባቸው በኋላና ክሱን ለመመስረትም ከፍተኛ ድብደባ ከተፈጸመባቸው በኋላ በድፍረት ፍርድ ቤት ላይ አቤቱታቸውን በማቅረብ፣ የእስር ቤቱን አስተዳደር ሲጋፈጡ ቆይተዋል። በእነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ የሽብር ክስ ከተመሰረተባቸው 38ቱ እስረኞች በተጨማሪ በተለያዩ ወንጀሎች የተከሰሱት 121 ተከሳሾች ፍርድ ቤት አንቀርብም እስከማለት ደርሰዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ አቤቱታቸውን አልቀበል በማለቱ፣ ዳኞችን የሕወሓት ኢህአዴግ ወኪሎች በማለት በግልጽ የተቹ ሲሆን፣ የ121 ሰዎች መዝገብ ተቀይሮ በ20 ሰዎች እንዲከፋፈል ከተደረገ በሁዋላ ደግሞ እስረኞቹ ፍርድ ቤት አንሄድም በማለት ተቃውሞ አሰምተዋል። ወጣቶቹን ለመወንጀል ሰበብ ሲፈልግ የነበረው ቂሊንጦ እስር ቤት፣ ከሁለት ሳምንት በፊት እስረኞቹ እርስበርስ ተጣልተዋል በሚል የተወሰኑትን ወደ ዝዋይ ወስዷል፡፡ እስረኞች ለሁለት ቀናት ያክል ቀንና ሌሊት እጃቸው የፊጥኝ ታስረው በደል ተፈጽሞባቸዋል። ደቡብ ክልል እየተባለ በሚጠራው የዝዋይ እስር ቤት ክፍል ውስጥ ፣ በሮቹ የማይከፈቱ ሲሆን እስረኞች ሌት ተቀን ይደበደባሉ፣ ከአቅማቸው በላይ የሆነ ስፖርት እንዲሰሩ እየተደረጉም ይቀጣሉ። ከቤተሰብ ጋር መገናኘትም አይችሉም፡፡ እነዚሁ እስረኞች በዚህ ክፍል ውስጥ ታስረው በተመሳሳይ ሁኔታ ቅጣት እየተፈጸመባቸው እንደሚገኙ የእስር ቤቱ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ስቃይ የሚፈጸምባቸው እስረኞች ማንነት ተለይቶ እንዳይታወቅ ለማድረግ በቂሊንጦ ዞን 5 የሚገኙ እስረኞች በቤተሰብ እንዳይጠየቁ ተከልክለዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ከአማራ ክልል የተያዙ በርካታ ዜጎች ክስ እየተመሰረተባቸው ነው። በክልሉ የተነሳውን ህዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴ ተከትሎ ፣ የተያዙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሰሞኑን የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸዋል። ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ ከ120 በላይ ከአማራ ክልል የተያዙ ሰዎች ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን፣ አብዛኞቹ ክሳቸው ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር የተያያዘ ነው።

ከበየዳና ደባርቅ አካባቢ ተነስተው ዘመነ ወርቅ በተባለው የተከዜ ሰው ሰራሽ ሃይቅ አካባቢ እንዲሰፍሩ የተደረጉት ነዋሪዎች የክልሉ መንግስት ምንም ዓይነት መሰረተ ልማት ሳያሟላ እንድንሰፍር በማድረጉ ከፍተኛ ችግር ላይ ጥሎናል ብለዋል።

ሰኔ ፳፮ ( ሃያ ስድስት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከበየዳና ደባርቅ አካባቢ ተነስተው ዘመነ ወርቅ በተባለው የተከዜ ሰው ሰራሽ ሃይቅ አካባቢ እንዲሰፍሩ የተደረጉት ነዋሪዎች የክልሉ መንግስት ምንም ዓይነት መሰረተ ልማት ሳያሟላ እንድንሰፍር በማድረጉ ከፍተኛ ችግር ላይ ጥሎናል ብለዋል። በ2008 ዓም. ከ1400 አባወራ በላይ ወደ አካባቢው እንዲሰፍር ቢደረገም በአጎራባች ክልሎች እንደሚካሄደው ሰፈራ የመሰረተ ልማት ተቋማት ሳይገነቡ በደፈናው ወደ ቦታው መወሰዳቸው የይምሰል አሰራር በመሆኑ አብዛኛዎቹ ሰፋሪዎች ሃብትና ንብረታቸውን በመተው አካባቢውን ለቀው ለመሄድ መገደዳቸውን ገልጸዋል፡፡ በአካባቢው ምንም ዓይነት ትምህርት ቤት ባለመኖሩ ከዘጠና በላይ ተማሪዎች ዓመቱን ሙሉ ያለትምህርት ማሳለፋቸው የገዥው መንግስት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ ግፍ እየፈጸመበት መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ እምነታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተከዜ ሰው ሰራሽ ሐይቅ አካባቢ ምንም ዓይነት ንጹህ የመጠጥ ውሃ ያልተዘጋጀ መሆኑን የሚገለጹት ሰፋሪዎች፣ በድንገተኛም ሆነ በተለያዩ በሽታዎች ለሚጠቁ ታካሚዎች ምንም ዓይነት ህክምና ሊሰጥ የሚችል የጤና ተቋም በአቅራቢያው አለመገኘቱ ብዙዎች በህመም እንዲሰቃዩና አካባቢውን አልምተው እንዳይጠቀሙ ሆን ተብሎ የተሰራባቸው ግፍ መሆኑን ቅሬታ አቅራቢዎች ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ የአካባቢ ጥበቃ ቦታውን ያስረከበ ሲሆንና ማዘጋጃ ቤቱም ቦታውን በፕላኑ መሰረት እንዳስረከበ የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢ፣ ከተማዋ ምንም አይነት የኤሌትሪክ አገልግሎት አለማግኘቷ ትልቅ ችግር ፈጥሮባቸዋል። በከተማዋ ምንም ዓይነት የጸጥታ አስከባሪ ሃይል ባለመኖሩ ለሌባና ዘራፊዎች በመጋለጥ በመማረር ላይ መሆናቸውን የገለጹት የከተማዋ ሃይል አመራር ኃላፊ፣ አንድን ከተማ ለመጠበቅ ይጠቀሙበት የነበረው አንድ መሳሪያ ብቻ መሆኑ ህዝቡ ከሚመጣበት ዘራፊ ለመከላከል የሚያስችል አቅም እንዳይኖረው ሆን ተብሎ የታቀደ እንደሆነ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡

እዳ አለባቸው የሚባሉ ነጋዴዎች በባንክ ያስመቀጡትን ገንዘባቸውን እንዳያወጡ እገዳ እየተጣለባቸው መሆኑን ነጋዴዎች ገልጸዋል

ሰኔ ፳፮ ( ሃያ ስድስት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- እዳ አለባቸው የሚባሉ ነጋዴዎች በባንክ ያስመቀጡትን ገንዘባቸውን እንዳያወጡ እገዳ እየተጣለባቸው መሆኑን ነጋዴዎች ገልጸዋል። ከፍተኛ ገንዘብ ለመሰብሰብ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ያለው ገዢው ፓርቲ፣ ነጋዴዎች ከገቢያቸው ጋር ያልተመጣጣነ ግብር እንዲከፍሉ በማድረጉ በተለያዩ አገራት የሚገኙ ነጋዴዎች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው። “ የሌለንን ገቢ እንዳለን አድርጎ የሚጣለው ግብር” በኑሮአችን ላይ ችግር እየፈጠሩ ነው የሚሉት ነጋዴዎች፣ ብዙዎች የንግድ ፈቀዳቸውን ለመመለስ እየተገደድን ነው ይላሉ። በአዲስ አበባ ነጋዴዎች አቤቱታቸውን የሚሰማላቸው በመጣታቸው እየተቸገሩ ነው። የኢህአዴግ ካድሬዎች በበኩላቸው ነጋዴዎች ግብራቸውን ከከፈሉ በሁዋላ መከራከር እንደሚችሉ ለማሰማመን እየሞከሩ ነው። ይሁን እንጅ ነጋዴዎች፣ አጠቃላይ የግብር አጣጣል ዘዴው ካልተቀየረ በስተቀር በአቤቱታ ብቻ አይፈታም ይላሉ። በደቡብ ክልል በከምባታ ጠንባሮ ዞን ዱራሜ ከተማ ላይ ብዙ ነጋዴዎች በተጠላባቸው የተጋነነ ግብር ቁጣቸውን መግለጻቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ነጋዴዎቹ ባልሰራነው ስራና ባላገኘነው ገቢ እንዴት ከፍተኛ ግብር ይጣልብናል በማለት አቤቱታ ቢያቀርቡም ፣ ተገቢውን መልስ የሚመልስላቸው አካል አላገኙም። አንዳንድ ነጋዴዎች ግብር አልከፈላችሁም በሚል በባንክ ያስቀመጡትን ገንዘብ እንዳያንቀሳቅሱ መታገዳቸውንም ተናግረዋል። የግብር እዳ ያለባቸው ነጋዴዎች የባንክ ገንዘባቸውን እንዳያንቀሳቅሱ እግዱን የጣለው ክፍል ማን እንደሆነ በግልጽ ባልተገለጸበት ሁኔታ ባንኮች ገንዘብ ማገዳቸው ህገወጥ መሆኑንም ነጋዴዎች ተናግረዋል። በአማራ ክልልም እንዲሁ ነጋዴዎች ተመሳሳይ ቅሬታ እያቀረቡ ነው።