Tuesday, February 14, 2017

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን ተከትሎ በምዕራብ እና አርሲ ዞን ብቻ ከ240 ሰዎች በላይ መገደላቸው ተገለጸ

ኢሳት (የካቲት 7 ፥ 2009)

የአስቸኳይ ጊዜ መታወጁን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብና አርሲ ዞን ብቻ በ20 ቀናት ውስጥ 240 ሰዎች መገደላቸውን የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ ገለጸ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀበት ከመስከረም 28/2009  እስከ ጥቅምት 18/2009 በአርሲ ነገሌ ብቻ 70 ሰዎች ሲገደሉ፣ 335 መታሰራቸውን የገለጸው የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ፣ ከዚህ በተጨማሪም በሻላ እና አጄ በተባሉ አካባቢዎች 85 ሰዎች ሲገደሉ 400 የሚሆኑት ደግሞ መታሰራቸውን ገልጿል።
የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብት ሊግ ለተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በላከው በዚሁ ባለ ዘጠኝ ገፅ ሪፖርት በኦሮሞዎች በይበልጥም በወጣቶች ላይ የተነጣጠረው ጥቃት እኤአ ከ2005 ጀምሮ ላለፉት ለ12 አመታት ተጠናክሮ መቀጠሉን ዘርዝሯል።

በሶማሌ ክልል በሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች በጊዚያዊ መጠለያ እንዲሰባሰቡ በመደረግ ላይ መሆኑን ተመድ ገለጸ

ኢሳት (የካቲት 7 ፥ 2009)

በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልል የተከሰተው የድርቅ አደጋ መባባስን ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች በጊዚያዊ መጠለያ እንዲሰባሰቡ በመደረግ ላይ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማክሰኞ አስታወቀ።
የአርብቶ አደሮችን ህይወት ለመታደግ ሲባል እየተወሰደ ባለው በዚሁ ዘመቻ አለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማትና መንግስት ለተጎጂዎቹ የምግብ አቅርቦት እንደሚያደርጉ ድርጅቱ ገልጿል።
ካለፈው ሃምሌ ወር ጀምሮ በክልሉ በተከሰተው አዲስ የድርቅ አደጋ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ለአስቸኳይ የምግብ ድጋፍ መጋለጣቸው ይታወቃል።
ከኢትዮጵያ የሶማሊ ክልል በተጨማሪ በኦሮሚያ፣ በአፋርና፣ የደቡብ ክልሎች ስር በሚገኙ በርካታ ዞኖች 5.6 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በድርቁ ጉዳት እየደረሰባቸው እንደሚገኝ የተመድ መረጃ ያመለክታል።

ኢሳት (የካቲት 7 ፥ 2009)

ኢትዮጵያ የቱርክ መንግስት የሽብርተኛ ድርጅት ነው ሲል ከፈረጀው የጉለን ንቅናቄ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ ትምህርት ቤቶችን ለቱርክ አሳልፎ ለመስጠት መወሰኑ ተቃውሞን አስነሳ።
ባለፈው ሳምንት በቱርክ ጉብኝትን ያደረጉ ፕሬዚደንት (ዶ/ር) ሙላቱ ተሾመ መንግስታቸው በኢትዮጵያ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ አምስት ትምህርት ቤቶችን ለቱርክ መንግስት ለማስተላለፍ መወሰኑ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።
ይሁንና ነጃሺ ኢትዮ-ቱርኪሽ ኢንተርናሽናል በመባል የሚጠሩትት አምስት ትምህርት ቤቶች መስራች የሆኑ ሃላፊዎች ተቋማቸው በኢትዮጵያ ህግ መሰረት የተቋቋመና ዕውቀና ተሰጥቶት የአገሪቱን ህግጋት አክብቶ የሚሰራ የትምህርት ተቋም እንጂ አሸባሪ አይደለም ሲሉ ምላሽ መስጠታቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።
በድርጅቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ የሆኑት ሌሊል አይዲን ትምህርት ቤታቸው ከቱርክ ተቋማትና ከቱርክ መንግስት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው አስታውቀዋል።

የግልገል ጊቤ ሶስተኛ የሃይል ማመንጫ ፕሮጄክት በኬንያውያን ላይ ተፅዕኖ ማሳደር መጀመሩን ሂውማን ራይትስ ዎች ገለጸ

ኢሳት (የካቲት 7 ፥ 2009)

በቅርቡ ግንባታው የተጠናቀቀው የግልገል ጊቤ ሶስተኛ የሃይል ማመንጫ ፕሮጄክት በኬንያ የቱርካና ሃይልና በኢትዮጵያ በታችኛው የስምጥ ሸለቆ በሚኖሩ በግማሽ ሚሊዮን ነዋሪዎች ላይ ተፅዕኖ ማሳደር መጀመሩን ሂውማን ራይትስ ዎች ማክሰኞ አስታወቀ።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ የቱርክና ሃይቅ የውሃ ከፍታ መጠን ካለፈው የፈረንጆች አመት ጀምሮ በ1.5 ሜትር ቀንሶ መገኘቱን የአሜሪካ የዕርሻ መምሪያ መረጃን ዋቢ በማድረግ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መገለጫ አመልክቷል።
የሃይል ማመንጫው ስራ መጀመር እና በተጓዳኝ እየተካሄደ ያለ የመስኖ ስራ የወንዙ ውሃ መጠን እንዲቀንስ በማድረግ በዙሪያው በሚኖሩ ሰዎች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖን ሊያሳድር እንደሚችል ሂውማን ራይትስ ዎች ስጋቱን ገልጿል።

Several killed in an attack in south eastern Ethiopia

ESAT News (February 14, 2017)

ESAT’s intelligence sources say at least 20 members of the Somali special forces unit were killed in Gursum and Bombase in south eastern Ethiopia.
The attack was reportedly carried out in retaliation by armed residents in the Oromo region of southern Ethiopia where the Somali forces had reportedly carried out incursions and looting.
Weapons and ammunitions were also seized by the residents during the retaliatory attack.

Ethiopia: Rights league says 248 civilians killed in three weeks in Oromo region

ESAT News (February 14, 2017)
In a written appeal to the United Nations Human Rights Council, the League renewed “its call to the international community to act collectively in a timely and decisive manner – through all available mechanisms of the United Nations in accordance with the UN charter to stop the Ethiopian government assault on its own citizens before it is too late.”
“HRLHA calls for intervention by the international community to end human tragedy in Ethiopia,” the document addressed to the United Nations Human Rights Council said.

Tuesday, February 7, 2017

በአፋር ክልል ሰፍረው የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሁለት አርብቶ አደሮች የፈጸሙት ግድያ ውጥረት ቀሰቀሰ

ኢሳት (ጥር 30 ፥ 2009)

በአፋር ክልል ልዩ ስሙ ዞን ሶስት ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ስፍራው የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በፊት በሁለት አርብቶ አደሮች ላይ የፈጸሙት ግድያ በአካባቢው ውጥረት መቀስቀሱ ተገለጸ።
በዚሁ አካባቢ ወልጅ አልባ የሰፍሩ ወደ ስድስት ሺ አካባቢ ተቀናሽ ወታደሮች ከአርብቶ አደሮች ጋር አለመግባባት ውስጥ በመሆናቸው ተደጋጋሚ ግጭቶች በመከሰት ላይ መሆናቸውን የአፋር የሰብዓዊ መብት ድርጅት ሃላፊ የሆኑት አቶ ጋአስ አህመድ ለኢሳት አስታውቀዋል።
በዚሁ ስፍራ የሚገኙት ተቀናሽ ወታደሮች በአንድ አርብቶ አደር ላይ የፈጸሙት ድብደባ አለመግባባትን ቀስቅሶ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በከፈቱት ተኩስ ሁለቱ ሊሞቱ መቻላቸውን ሃላፊው ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስረድተዋል።

በባንክና ፋይናንስ ተቋማት ተሰማርተው የነበሩ የውጭ ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያውያን አክሲዮኖች ለጨረታ መቅረባቸው ተገለጸ



ኢሳት (ጥር 30 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ሃገር ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያውያን በባንክ እና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት ውስጥ የአክሲዮን ድርሻ እንዳይኖራቸው ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ በርካታ ባንኮች በትውልደ ኢትዮጵያውያኑ ስር የነበሩ አክሲዮኖች ለጨረታ አቀረቡ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በተለያዩ ባንኮች ውስጥ አክሲዮን የነበራቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን እስከ ህዳር ወር መጨረሻ ድረስ የያዙትን አክሲዮን እንዲመልሱ ማሳሰቢያን አውጥቶ እንደነበር ይታወሳል።
የጊዜ ገደቡን መጠናቀቅ ተከትሎም አዋሽ ባንክ በበርካታ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ስር የነበሩ 21ሺ 52 አክሲዮኖችን ለጨረታ ያቀረበ ሲሆን፣ ጨረታው በቀጣዩ ሳምንት እንደሚካሄድ አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል።
የንብ ባንክ በበኩሉ ወደ ስምንት ሺ አካባቢ የሚጠጉ አክሲዮኖችን በተመሳሳይ መልኩ ለጨረታ ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆኑ ታውቋል። ይሁንና በባንኩ አክሲዮን ገዝተው የነበሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የአክሲዮን ሰርቲፊኬታቸውን መመለስ በነበራባቸው የጊዜ ገደብ ሳይመልሱ መቅረታቸውን ጋዜጣው አስነብቧል።

የዘንድሮው የሰሜን አሜሪካ የስፖርት ፌስቲቫል በዋሽንግተን ሲያትል ከተማ እንደሚካሄድ ተገለጸ

ኢሳት (ጥር 30 ፥ 2009)
በየአመቱ በሰሜን አሜሪካ በደማቅ ሁኔታ የሚከበረው የዘንድሮው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል የፊታችን ሃምሌ በዚሁ በአሜሪካ ዋሽንግተን ግዛት ሲያትል ከተማ እንደሚካሄድ መወሰኑን አዘጋጆች አስታወቁ።
ለ34ኛ ጊዜ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በማሰባሰብ የሚካሄደው ይኸው አመታዊ በዓል በፈረንጆቹ ከሃምሌ 2 እስከ 8 2017 ድረስ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
የባለፈው አመት ዝግጅት በካናዳ ቶሮንቶ ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፣ የዘንድሮውን በዓል ለማስተናገድ የቴክሳስ ግዛት ጥያቄ አቅርቦ እንደነበርም ለመረዳት ተችሏል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሌሎች ሃገራት ያልተከፈለው ገንዘብ በስራው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ገለጸ

ኢሳት (ጥር 30 ፥ 2009)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከናጀሪያ ግብፅና ሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ያልተከፈለው ከ200 ሚሊዮን ዶላር በላይ በስራው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን የድርጅቱ ሃላፊዎች ገለጹ።
አየር መንገዱ ለነዚህ ሃገራት በተለያዩ ጊዜያት የአየር ትኬትና ሌሎች የትራንስፖርት አገልግሎቶች ሲሰጥ ቢቆይም ለአገልግሎቱ ክፍያ ሳይፈጸምለት በርካታ ጊዜያት መቆጠሩን ሮይተርስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑትን አቶ ተወልደ ገብረማሪያምን ዋቢ በማድረግ ማክሰኞ ዘግቧል።
አየር መንገዱ የተለያዩ አገልግሎትን ሲሰጣቸው የቆዩት ሃገራት የውጭ ምንዛሪ እጥረት አጋጥሟቸው በመገኘቱ ምክንያት ክፍያውን ሊፈጽሙ እንዳልቻሉ ሃላፊው ለዜና አውታሩ አስረድተዋል።

Ethiopia: Security forces killed two in Afar

ESAT News (February 7, 2017)

Security forces killed two in Afar after the locals confronted the forces in an attempt to free one of their own, who was beaten and abducted by the forces.

Ethiopia: Regime forces launch artillery attack against resistance forces

 ESAT News (February 7, 2017)

Reports reaching from north Gondar say Ethiopian regime forces have used heavy artillery on Monday after armed groups fighting the regime have broken out of an ambush killing four.
Sources who spoke to ESAT on the phone from north Gondar say the attempted ambush by the regime forces took place in Belesa while the forces fighting the regime, who call themselves freedom forces, were gathering for a meeting.

Monday, February 6, 2017

በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል ድንበር ላይ በተከሰተው ግጭት የመንግስት አካላት እንደተሳተፉበት ተገለጸ

ኢሳት (ጥር 29 ፥ 2009)

የኦሮሚያ ክልል ከሶማሌ ክልል ጋር በሚዋሰንበት ድንበር በቅርቡ ለሰዎች ሞት ምክንያት በሆነው ግጭት የመንግስት አካላት ተሳታፊ መሆናቸውን የኦሮሚያ ክልል መንግስት ገለጸ።
የኦሮሚያ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) በፌዴራልና በሶማሌ ክልል አስተዳደር ድጋፍ የሚደረግላቸው የመንግስት ታጣቂዎች በኦሮሞ ብሄር ተወላጆች ላይ ግድያና ዘረፋን እየፈጸሙ ናቸው ሲል ባለፈው ሳምንት መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
በአካባቢው በመንግስት ታጣቂዎች እየተፈጸመ ያለው ዕርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን ያስታወቀው ፓርቲው ድርጊቱ የኦሮሚያ ክልል ይዞታን በሃይል ለመውሰድ የታለመ እንደነበርም አመልክቷል።

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ6 አየር ሃይል አባላት ላይ የእስራት ቅጣት አስተላለፈ

ኢሳት (ጥር 29 ፥ 2009)

የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ ሲያቀኑ በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉ ስድስት የአየር ሃይል አባላት ላይ ከሶስት እስከ 10 አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት አስተላለፈ።
ከሳሽ አቃቤ ህግ በሰኔ 2007 አም ተከሳሾቹ የአየር ሃይልን በመክዳት ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ጋር ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ ሊያመሩ ሲሉ ባህር ዳር እና ጎንደር ከተሞች ላይ እንደተያዙ በክሱ አመልክቶ እንደነበር ይታወሳል።
የቀድሞው የአየር ሃይል አባላት ህገመንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል የማፍረስ አላማ ይዘው በሽብር ድርጅት ውስጥ አባላት በመሆንና በሽብር ድርጊት ተግባር ላይ ለመሳተፍ በማሰባቸው የሚል ክስን አቅርቦ እንደነበርም በወቅቱ መዘገባችን አይዘነጋም።

የቅዱስ ላሊበላ አቢያተ-ክርስቲያናት አስተዳደሪ ቆሞስ አባ ወልደተንሳይ አባተ በመንግስት ጣልቃገብነት ከሃገር መሰደዳቸውን ገለጹ

ኢሳት (ጥር 29 ፥ 2009)

የታሪካዊው ቅዱስ ላሊበላ አቢያተ-ክርስቲያናት አስተዳደር የነበሩት ቆሞስ አባ ወልደተንሳይ አባተ በመንግስት ጣልቃገብነት ከሃገር መሰደዳቸውን ገለጹ። የላሊበላ አብያተክርስቲያናት ሰበካ ጉባዔ በመንግስት ባለስልጣናትና በብአዴን ካድሬዎች ቁጥጥር ስር መውደቁንም ለኢሳት በሰጡት ቃለምልልስ አመልክተዋል።
ወልቃይት የትግራይ ነው በሚል ለህዝቡ እንዲያስተምሩ ግፊት ይደረግባቸው እንደነበርም አመልክተዋል። በመጨረሻም ምክንያቱ ባልታወቀና ባልተገለጸ መንገድ በስፍራቸው ሌላ ሰው ተሹሞ መገኘቱን ገልጸዋል።

በአዲስ አባባ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጄክት የፋይናንስ ችግር ገጠመው

ኢሳት (ጥር 29 ፥ 2009)

በአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪዎችን የቤት ችግር ይቀርፋሉ ተብለው ግንባታቸው የተጀመረ የጋራ መኖሪያ ቤት ፕሮጄክቶች የፋይናንስ ችግር እንዳጋጠማቸው ተገለጸ።
የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኮንትራክተሮችና እቃ አቅራቢዎች ለሰሩት ስራ ክፍያ እየተከፈላቸው ባለመሆኑ ችግር ውስጥ እንደሚገኙና ስራቸውንም ማከናወን የማይችሉበት ደረጃ ላይ እየደረሱ መሆኑን እንዳስታወቁ ሪፖርተር ጋዜጣ በእሁድ እትሙ ዘግቧል።
የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር በበኩሉ በ20/80 እና በ40/60 ቤቶች ግንባታ ላይ የተፈጠረው መስተጓጎል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ አሰራር በመጀመሩ ምክንያት ነው ሲል ምላሽን ሰጥቷል።

Ethiopia: Official says gov’t has a hand in conflict between Somali, Oromo

ESAT News (February 6, 2017)

An official with the Oromo Regional State accused the government of having a hand in the recent killings and cattle raiding by the Somali Region Special Forces against the Oromo people in East Hararghe, Bale and Borena.
Head of the regional communication bureau, Addisu Arega told local media that government bodies had a role in the incursions, looting and killings by the Somali Region Special Forces against the Oromos.

Ethiopia: Former air force officers sentenced to prison terms

ESAT News (February 6, 2017)

A court in Addis Ababa sentenced six former officers with the Ethiopian air force to prison terms ranging from 3 to 6 years convicting them of terrorism and other charges.
The charge brought by the regime says the officers were caught in Bahir Dar and Gondar three years ago while heading to Eritrea to join Patriotic Ginbot 7, an armed group operating from Eritrea. The charge

Ethiopia: Agency predicts low rainfall in drought stricken areas

ESAT News (February 6, 2017)

The UN Office for the Coordination of Humanitarian Affairs, quoting
Meteorological sources said climate outlook for belg 2017 season (mid-February to May), shows below normal rainfall  in the southern and south-eastern parts of the country.
Belg is the main rainy season for the pastoralist and agro‐pastoralist communities in the lowlands of southern and south-eastern Ethiopia, including southern Somali region, the lowlands of Borena, Guji and Bale zones and  other southern Ethiopian regions; and it’s the second major rainy season for Afar region.

Friday, February 3, 2017

የኢትዮጵያ መንግስት የ26.5 ቢሊዮን ብር ቦንድ ሽያጭ አጸደቀ



ኢሳት (ጥር 2009)

የኢትዮጵያ መንግስት ያጋጠመውን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ የ26.5 ቢሊዮን ብር ቦንድ ሽያጭ እንዲካሄድ ያቀረበው ጥያቄ ረቡዕ በፓርላማ ጸደቀ።
የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች በበኩላቸው ሊካሄድ የታሰበው የቦንድ ሽያጭ የሃገሪቱን አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ሊያባብስ ይችላል ሲሉ ስጋታቸውም ገልጸዋል። በፓርላማ የጸደቀው ይኸው አዋጅ መንግስት ከተለያዩ አካላት ወለድ የሚከፈልበት የቦንድ ሽያጭ እንዲያከናውን ይሁንታ መስጠቱ ታውቋል።
የአዋጁ መፅደቅን ተከትሎ መንግስት ከተለያዩ አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት በረጅም ጊዜ የሚከፈል የ26.5 ቢሊዮን ብር የቦንድ ሽያጭ ያካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
ሊካሄድ የተወሰነው የቦንድ ሽያጭ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ካፒታል ለማሳደግ ያለመ እንደሆነ የመንግስት ባለስልጣናት ቢገልጹም የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ዕርምጃ ሃገሪቱ ያጋጠማትን የበጀትና የፋይናንስ እጥረት ለመታደግ እንደሆነ አስረድተዋል።

ለእስር የተዳረጉ ጋዜጠኞች ይፈጸምብናል ያሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰት አስመልክቶ ለተመድ ደብዳቤ ጻፉ

ኢሳት (ጥር 2009)

የአስችኳይ ጊዜ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ ለእስር የተዳረጉ ጋዜጠኞች ይፈጸምብናል ያሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰት አስመልክቶ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ደብዳቤ ጻፉ።
ከወራት በፊት ለእስር የተዳረጉት ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩና አናኒያ ሶሪ ለእስር በተዳረጉ ጊዜ በሽብርተኛ ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አድርጋችኋል ቢባሉም እስካሁን ድረስ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ አለመቻላቸውን በደብዳቤያቸው ማስፈራቸውን አዲስ ስታንዳርድ መጽሄት ዘግቧል።
በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር በዋሉ ጊዜ ከቤተሰብ ጋር እንዳይገኛኑ ተደርገው ለብቻቸው ለሶስት ቀን በጨለማ ክፍል እንዲቆዩ ተደርገው እንደነበር ጋዜጠኞቹ በጽሁፋቸው አውስተዋል።

በሶማሊያ የሚገኙ ኢትዮጵያ ወታደራዊ ሃላፊዎች በጦር መሳሪያ ንግድና በሌሎች የሙስና ወንጀሎች ውስጥ ተሰማርተው እንደሚገኙ ተገለጸ

ኢሳት (ጥር 2009)

በሶማሊያ ተሰርቶ በሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በወታደራዊ አመራርነት የተቀመጡ ሃላፊዎች በጦር መሳሪያ ንግድና ሌሎች የሙስና ወንጀሎች ውስጥ ተሰማርተው መገኘታቸውን የሃገሪቱ መገኛኛ ብዙሃን ሃሙስ ዘገቡ።
ለበርካታ አመታት በሶማሊያ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሰራዊት በሃላፊነት በማገልገል ላይ ያሉ ሃይሌ ገብሬ በዚህ ህገወጥ ድርጊት በመሰማራት ከፍተኛ ንብረት በማካበት ላይ መሆናቸውን ሱና ታይምስ የተሰኘ ጋዜጣ የአመራሩን ፎቶ በማስደገፍ ለንባብ አብቅቷል።
በቅፅል ስማቸው በሶማሊውያን ዘንድ ጀኔራል ገብሬ በሚል መጠሪያ የሚታወቁት እኝሁ ወታደራዊ መኮንን ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመመሳጠር የጸጥታ ድጋፍ የሚለግስን ገንዘብ እየመዘበሩ እንደሚገኝ ጋዜጣው ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የሃይሌ ገብሬ የቅርብ ባልደርቦች ዋቢ በማድረግ ለንባብ አብቅቷል።

Ethiopian military officer in Somalia accused of selling arms, massive corruption

ESAT News (February 2, 2017)

An investigative report by a Somali website accused a high ranking  Ethiopian officer in Somalia of arm sales to rival factions and collecting bribes from Somali politicians who want come to power.
Waagacusub media described Haile Gebre as “the most corrupt military officer” who became extremely wealthy from huge sums of money that he is getting from opportunistic Somali politicians who want to buy the sympathy of Addis Ababa.
Waagacusub media quote one of officer Gabre’s juniors, who remained anonymous for fear of reprisal as saying that “Gebre was corrupted by Somali politicians and he in turn corrupted Ethiopian senior officials so they would condone his wrongdoing.”

A U.S. Court of Appeals hears arguments in a case against wiretapping of an American by the Ethiopian regime

ESAT News (February 2, 2017)
A DC Circuit Court for the U.S. Court of Appeals today heard arguments on a wiretapping case brought against the Ethiopian regime by an Ethiopian American in Maryland.
Few years ago, the Ethiopian regime had infected the computer of Mr. Kidane with secret spyware, wiretapping his private Skype calls, and monitoring his entire family’s every use of the computer for a period of months.
With the help of the Electronic Frontier Foundation (EFF) and Citizen Lab, Mr. Kidane found that the Ethiopian regime used a notorious surveillance malware known as FinSpy, illegally wiretapped and invaded the privacy of Mr. Kidane, a U.S. citizen on U.S. soil, according to a statement by EFF.