Friday, December 30, 2016

ዶ/ር መረራ ከእስር እንዲፈቱ የሚያስተባብር አለም ቀፍ ግብረ ሃይል ተቋቋመ

ኢሳት (ታህሳስ 21 ፥ 2009)
ነዋሪነታቸው በተለያዩ የአለማችን ሃገራት የሆነ ኢትዮጵያውያን ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር እንዲፈቱ የሚያስተባብር አለም ቀፍ ግብረ ሃይል አቋቋሙ።
ግብረ ሃይሉ እያካሄደ ያለው ይኸው አለም አቀፍ ዘመቻ አሜሪካንን ጨምሮ የአውሮፓ ህብረትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ኢትዮጵያ ለእስር የዳረገቻቸው የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞችን እንዲሁም ሌሎች አካላትን እንድትለቅ ግፊት እንደሚያደርጉ የሚጠይቅ መሆኑ ታውቋል።
የዘመቻው መጀመር አስመልክቶ መግለጫን ያወጣው ግብረ ሃይሉ በቅርቡ ተግባራዊ ተድርጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተላልፈዋል ተብለው ለእስር የተዳረጉት ዶ/ር መረራ ጉዲና ተይዘው ያሉበት ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን አስታውቀዋል።

130 ግለሰቦች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አርብ አስታወቀ

ኢሳት (ታህሳስ 21 ፥ 2009)
የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ 130 ግለሰቦች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አርብ አስታወቀ።
ለእስር ከተዳረጉት ሰዎች በተጨማሪ በስምንት ትላልቅ አክሲዮኖች በአራት ህንጻዎች በ49 ተሽከርካሪዎች፣ በ22 በመኖሪያ ቤቶችና በሁለት ፋብሪካዎች ላይ እገዳ መደረጉንም ኮሚሽኑን ዋቢ በማድረግ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰበር ዜና ዘግበዋል።
ይህንና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ለእስር የተዳረጉ የመንግስት ባለስልጣናትና ንብረት የታገደባቸውን ግለሰቦችና ተቋማት በስም ከመጥቀስ ተቆጥቧል።
በ13 ተጠርጣሪዎች ላይ የሃብት ንብረት እገዳ መጣሉን የገለጸው ኮሚሽኑ ለእስር የተዳረጉት የመንግስት ባለስልጣናት ባለሙያዎች ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሚገኝ ተመልክቷል። ከሁለት ቀን በፊት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተመሳሳይ መንገድ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 125 ግለሰቦችን ለእስር መዳረጉ ይታወሳል።
በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ውስጥ በማገልገል ላይ ነበሩ የተባሉት እነዚሁ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ላይ አስተዳደራዊ በደል ፈጽመዋል ሲል ኮሚሽኑ ይገልጻል።

በውጭ ብድር የተጀመሩ የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታቸው ሳይጠናቀቅ የብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 21 ፥ 2009)
ኢትዮጵያን ስኳር ላኪ ሃገር ያደርጋሉ ተብለው ከውጭ በተገኘ ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ግንባታቸው ከሰባት አመት በፊት የተጀመሩ ፋብሪካዎች ግንባታቸው ተስተጓጉሎ እያለ ብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ።
በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ውስጥ የሚገኘው መንግስት በበኩሉ በመገንባት ላይ ያሉትን ጨምሮ በስራ ላይ ያሉ የስኳር ፋብሪካዎች ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለመስራው መወሰኑን ይፋ አድርጓል።
መንግስት ከተለያዩ አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት በብድር ባገኘው ገንዘብ የወልቃይት፣ የኦሞ፣ ኩራዝ አንድ ሁለትና ሶስት እንዲሁም የጣና በለስ ቁጥር አንድና ሁለት ፕሮጄክቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወሳል።
ይሁንና ሃገሪቱን ከስኳር እጥረት በማላቀቅ ኢትዮጵያ ምርቷን ወደ ውጭ ሃገር በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እንድታገኝ ያደርጋሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ፋብሪካዎች አብዛኞቹ በጅምር ላይ መቅረታቸው ተመልክቷል።
ፋብሪካዎቹ በከፍተኛ የፋይናንስ እጥረት ውስጥ በመግባታቸውና የተጀመሩ ፕሮጄክቶችን ለማስጨርስ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ በማስፈለጉ ምክንያት መንግስት ነባሮቹንና አዳዲስ ግንባታዎች በሽርክና ለማካሄድ መወሰኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ፋብሪካዎቹ በአምስት አመት ውስጥ ወደ ምርት ይገባሉ ተብሎ የተጠበቁ ሲሆን፣ ግንባታቸው በ25 በመቶ ላይ የሚገኝ እንዳለም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን መረጃ ያመለክታል።

Wednesday, December 14, 2016

ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 አመታት ወደ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሃገራት ተርታ እንደማትገባ ተመድ ይፋ አደረገ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)

ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 አመታት ወደ መካከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሃገራት ተርታ እንደማትገባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ይፋ አደረገ።
የመንግስት ባለስልጣናት ሃገሪቱ በቀጣዮቹ አስር አመራት ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገራት ተርታ ትገባለች ሲሉ በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል። ይሁንና በጉዳዩ ዙሪያ ሰሞኑን ሪፖርቱን ያወጣው የድርጅቱ የንግድና የልማት ጉባዔ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ 16 ሃገራት እቅዱን እንደሚያሳኩ ቢገልጽም፣ ኢትዮጵያን ሳያካትት ቀርቷል።

ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ገቢ 400 ሚሊዮን ዶላር (ወደ አንድ ቢሊዮን ብር) አካባቢ ልታጣ እንደምትችል ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)

በኢትዮጵያ በተያዘው የፈረንጆች አመት ከቱሪዝም ገቢ 400 ሚሊዮን ዶላር (ወደ አንድ ቢሊዮን ብር) አካባቢ ልታጣ እንደምትችል ተገለጸ።
በሃገሪቱ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን አለመረጋጋት በቱሪዝም እንቅስቃሴው ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖን እያሳደረ እንደሚገኝ አፍሪካ ኒውስ መጽሄት የተለያዩ መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ረቡዕ ባቀረበው ዘገባ አስፍሯል።
በፈረጆች 2015 አም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ ወደ ሶስት ቢሊዮን ዶላር አካባቢን አግኝታ የነበረ ሲሆን፣ በ2016/2017 አም ተመሳሳይ ገቢን ለማግኘት እቅድ ተይዞ እንደነበር ለማግኘት እቅድ ተይዞ እንደነበር ታውቋል።

በአሜሪካ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ የተመራ የልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባቱ ተገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ባለው የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ዙሪያ ለመምከር በአሜሪካ የዴሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ የተመራ የልዑካን ቡድን ረቡዕ አዲስ አበባ መግባቱ ታውቋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሃገሪቱ ተግባራዊ የተደረገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መውጣትን ተከትሎ ዕርምጃው በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ስጋትን አሳድሯል ሲል በተደጋጋሚ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
በአዲስ አበባ የሶስት ቀን ቆይታ የሚኖረው ይኸው የልዑካን ቡድን የአሜሪካ አለኝ የምትለውን የሰብዓዊ መብት ስጋት አንስቶ ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክር ታውቋል።

የኢትዮጵያ መንግስት በጸጥታ ሃይሎች የተወሰዱ የሃይል ዕርምጃዎች ሽፋን እንዳያገኙ ድረገጾችን መዝጋቱን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ

ኢሳት (ታህሳስ 5 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ ሲካሄድ ከቆየው ህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተገናኘ መንግስት በጸጥታ ሃይሎች የተወሰዱ የሃይል ዕርምጃዎች ሽፋን እንዳያገኙ በትንሹ የ16 የመገናኛ ብዙሃንን ተቋም ድረገጾች እንዲዘጉ ማድረጉንም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ረቡዕ አዲስ ባወጣው ሪፖርት አስታወቀ።
የማህበራዊ ድረ-ገጾችን ጨምሮ የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ለመዝጋትና ለመቆጣጠር በተካሄደው በዚሁ የአፈና ዕርምጃ የተቃዋሚ ፓርቲ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች አካላት ሰለባ መሆናቸውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ኦፕን ኦብዘርባቶሪ ኦፍ ኔትዎርክ ኢንተርፊረንስ ከተሰኘ ተቋም ጋር በጋራ ያካሄደውን ጥናት አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል።
ባለፈው አመት በተለይ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎትን ለመዝጋት የተወሰደው ዕርምጃ ተግባራዊ ተደርጎ በሚገኘው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወቅትም መቀጠሉን ሁለቱ አለም አቀፍ ተቋማት ገልጸዋል።

Ethiopia: Internet censorship causing severe restrictions to information

Ethiopian regime’s deadly crackdown on protesters in the last one year was accompanied by blockage of the internet and social media, according to a report by Amnesty International.
“The crackdown on protests was accompanied by increasingly severe restrictions on access to information and communications in large parts of the country by cutting off internet access, slowing down connections and blocking social media websites,” Amnesty said.
Investigations and interviews by Amnesty international also revealed that at least 800 people have been killed in the last one year of anti-government protests.
“Amnesty International’s research since the protests began revealed that security forces responded with excessive and lethal force in their efforts to quell the protests. Amnesty International interviewed at least fifty victims and witnesses of human rights abuses during the protests, twenty human rights monitors, activists and legal practitioners within Ethiopia, and also reviewed other relevant primary and secondary information on the protests and the government’s response. Based on this research, the organisation estimates that at least 800 people have been killed since the protests began.”
It said in addition to using security forces to quash protests, the Ethiopian authorities have restricted access to internet services during the protest.

Friday, December 9, 2016

የእስራዔል መንግስት በሃገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም እንዳይለግሱ ጥሎ የቆየውን እገዳ አነሳሁ አለ

ኢሳት (ኅዳር 30 ፥ 2009)
የእስራዔል መንግስት በሃገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደም እንዳይለግሱ ጥሎ የቆየውን እገዳ አነሳ።
የእስራዔል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከሃገሪቱ ውጭ የተወለዱ ወይም የHIV/AIDS ስርጭት ባለባቸው ሃገራት ለአንድ አመት ያህል ቆይታ ያደረጉ ቤት-እስራዔላዊያን ደም እንዳይለግሱ ከ10 አመት በፊት እገዳ መጣሉ ይታወሳል።
ይሁንና የእስራዔል መንግስት ጥሎ የነበረው እገዳ በአግባቡ ለህዝብ ይፋ ባልተደረገበት ወቅት ማሪቭ (maiariv) የተሰኘ የሃገር ጋዜጣ ከኢትዮጵያውያን ይወሰድ የነበረ ደም ሲወገድ መቆየቱን ማጋለጡ ሃርቴዝ ጋዜጣ አርብ ዘግቧል።
የእስራዔሉ የደም ባንክ የሚቆጣጠረው ማገድ ዴቪድ አደም የተሰኘው ኩባኒያ የወሰደውን ይህንኑ ዕርምጃ ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ተከታታይ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍን ሲያደርጉ ቆይተዋል።
በተለያዩ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና በምዕራባውያን ሃገራት ዘንድ ቁጣን ቀስቅሶ የነበረው ድርጊት ለ10 አመት ያህል መነጋገሪያ ሆኖ መሰንበቱን ጋዜጣው አውስቷል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በእስር ቤት አለመኖሩ ተገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 30 ፥ 2009)
በዝዋይ እስር ቤት በእስር ላይ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በእስር ቤቱ አለመኖሩንና ያለበት ቦታ እንደማይታወቅ የጋዜጠኛውን ጉዳይ የሚከታተሉ አካላት ለኢሳት ገለጹ።
የጋዜጠኛው ቤተሰቦች በበኩላቸው የማህበራዊ ድረገጾች ባሰራጩት መረጃ ዝዋይ እስር ቤት ተመስገንን ለመጠየቅ ሁለት ቀን ቢሄዱም፣ በእስር ቤቱ ተመስገን የሚባል የመንግስት እስረኛ አናውቅም የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው አረጋግጠዋል።

Thursday, December 8, 2016

Ethiopia: Dozens desert army, join resistance forces patriotic-g7 File photo of PG7 fighters

ESAT News (December 8, 2016)

Patriotic Ginbot 7, a group fighting the Ethiopian government, said 46 soldiers have deserted the regime army and joined the resistance movement.
The soldiers, who defected after a marathon negotiations and joined Patriotic Ginbot 7, have defected with various weapons including 9 artilleries, 6 snipers and RPGs among others, according to a source on the ground with the fighters.

የአውሮፓ ሃገራት ዜጎቻቸው ወደ ሰሜን ጎንደር እንዳይጓዙ አዲስ ማሳሰቢያን አወጡ

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
በሰሜን ጎንደር የተለያዩ አካባቢዎች በመንግስትና በግንቦት ሰባት ሃይሎች መካከል የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ የአውሮፓ ሃገራት ዜጎቻቸው ወደ ስፍራው እንዳይጓዙ አዲስ ማሳሰቢያን አወጡ።
ተደጋጋሚ የጉዞ ማሳሰቢያን ሲያወጡ የነበሩት የጀርመንና የቤልጅየም መንግስታት በኢትዮጵያ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ መሻሻልን ቢያሳይም በአማራ ክልል ስር በሚገኙ ሶስት ዞኖች የጸጥታ ስጋት መኖሩን ይፋ አድርገዋል።
ለዜጎቻቸው አዲስ የጉዞ ማሳሰቢያን ያሰራጩት ሁለቱ የአውሮፓ ሃገራት በጸገዴ፣ ምዕራብና የታች አርማጭሆ የሰሜን ጎንደር አካባቢዎች ዜጎቻቸው ጉዞን ከማድረግ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
የፈረንጆች አዲስ አመት መግቢያን ምክንያት በማድረግ የጀርመንና የቤልጂየም ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ በብዛት የሚጓዙ ሲሆን፣ የሁለቱ ሃገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሁኔታውን ከግምት ውስጥ በማስገባት የጉዞ ማስጠንቀቂያ ማሰራጨታቸውን ዘቮይስ (The Voice) የተሰኘ መፅሄት ዘግቧል።
በቅርቡ የግንቦት 7 ሃይሎች እንዲሁም ራሳቸውን ያደራጁ የነጻነት ሃይሎች በሰሜን ጎንደር ዞን ስር ከመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ጋር ግጭት ውስጥ መግባታቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ የከፋ አፈናን ከሚፈጽሙ ሃገራት መካከል ግንባር ቀደም ሃገር ተብላ ተፈረጀች

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
ኢትዮጵያ በተያዘው 2016 የፈረንጆች አም በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ የከፋ አፈናን ከሚፈጽሙ ሃገራት መካከል ግንባር ቀደም ሃገር ተብላ ተፈረጀች።
በቴክኖሎጂው አጠቃቀምና ተደራሽነት እንዲሁም ቁጥጥር ዙሪያ አመታዊ ጥናቱን ይፋ ያደረገው ፍሪደም ሃውስ የተሰኘ ተቋም ቻይና፣ ሶሪያና ኢትዮጵያ የከፋ የተባለ አፈናን ከሚፈጽሙ ሃገራት መካከል ዋነኛ መሆናቸውን ይፋ አድርጓል።
ካለፈው አመት ጀምሮ ኢንተርኔት አገልግሎት ላይ እገዳንና ቁጥጥርን ተግባራዊ አድርጋ የምትገኘው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከሚገኙ 54 ሃገራት መካከል የቴክኖሎጂው ጠላት ተደርጋ ተፈርጃለች።
በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ የኢትዮጵያ መንግስት በመደበኛውና በተጓዳኝ የኢንተርኔት አገልግሎት ላይ እገዳን ጥሎ የሚገኝ ሲሆን፣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መውጣቱን ምክንያት በማድረግም አገልግሎቱ ታግዶ ይገኛል።

በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ኪሳራ የደረሰበት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ መግባቱ ተነገረ

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ለሃገር ውስጥና ለውጭ ባለሃብቶች መሬትን ለማቅረብ ሊያካሄድ ከነበረው ስራ ጋር በተገናኘ ያጋጠመው በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ኪሳራ አዲስ ውዝግብ መቀስቀሱ ተግለጸ።
የፌዴራልና የክልል ባለስልጣናት ለደረሰው ኪሳራ ሃላፊነቱን ማን መውሰድ እንዳለበት ለአንድ አመት ያህል ምክክርን ሲያካሄዱ ቢቆዩም ጉዳዩ ዕልባት አለማግኘቱ ታውቋል።
በጋምቤላ ክልል ብቻ ከ100 የሚበልጡ የሃገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ለኢንቨስትመንት የሚሆን ሰፊ የእርሻ መሬት ቢሰጣቸውም የፌዴድራል ባለስልጣናት የመሬት ርክክቡ ህገወጥ ነው በማለት ባለሃብቶቹ ስራቸውን እንዲያቆሙ መወሰኑ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በበኩሉ በዚሁ ክልል ተመሳሳይ ይዞታ ላይ በርካታ ባለሃብቶች በቢሊዮን ብር የሚቆጠር ብድር በመውሰድ ኪሳራ ማጋጠሙ በቅርቡ ይፋ አድርጓል።

በኢትዮጵያ የተከሰተው የዋጋ ግሽበት ከ5.6 ወደ 7 በመቶ ከፍ ማለቱን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ

ኢሳት (ኅዳር 29 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ አጋጥሟል የተባለን የኢኮኖሚ መዳከም ተከትሎ የሃገሪቱ የዋጋ ግሽበት በተያዘው ወር ከአምስት ነጥብ ስድስት ወደሰባት በመቶ ከፍ ማለቱን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ሃሙስ አስታወቀ።
የአለም ባንክ ሃገሪቱ አጋጥሟት ያለው የውጭ ንግድ ገቢ መቀነስና የውጭ ምንዛሪ ክምችት ማሽቆልቆል በኢትዮጵያ ዋጋ ግሽበት ሊያስከትል ይችላል ሲል ማሳሰቡ ይታወሳል።
ባንኩ ሲሰጥ የቆየውን ትንበያ ተከትሎ የሃገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበትን ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በምግብ ነክ ሸቀጣሸቀጦች ላይ የዋጋ ጭማሪ በመከሰቱ ምክንያት የዋጋ ግሽበቱ ከፍ ሊል መቻሉን በሪፖርቱ አመልክቷል።

ከአውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የታሰሩት የደ/ር መረራ ጉዲናን መታሰር ተከትሎ የእሳቸው ደጋፊ ይሆናሉ የተባሉ ወጣቶች እየተለቀሙ በመያዝ ላይ ናቸው።

ኅዳር ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአውሮፓ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የታሰሩት የደ/ር መረራ ጉዲናን መታሰር ተከትሎ የእሳቸው ደጋፊ ይሆናሉ የተባሉ ወጣቶች እየተለቀሙ በመያዝ ላይ ናቸው። እስሩ እርሳቸው በተያዙ ማግስት የጀመረ ሲሆን፣ እስከዛሬ ድረስ በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ የኦሮምያ ወረዳዎች እንዲሁም በአምቦና አጎራባች ቀበሌዎች በርካታ ሰዎች ተይዘው ታስረዋል። በተመሳሳይ ዜና በደቡብ ወሎ ሃይቅ ከተማ በርካታ ወጣቶች በአዲሱ ወታደራዊ እዝ አማካኝነት መሰታሰራቸውን ለማወቅ ተችሎአል። እስካሁን በደረሰን መረጃ ከ50 ያላነሱ ወጣቶች በቁጥጥር ስር ውለዋል። በሌላ በኩል በተለያዩ መስሪያ ቤቶች በዘበኝነት ተቀጥረው ስራ የሚሰሩ የቀድሞ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንደገና መታዋቂያ እንዲያወጡና እንዲመዘገቡ እየተደረገ ነው። ሰራተኞቹ ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት ጋር አዲስ ውል እንዲፈርሙ እየተደረገ ሲሆን፣ በተለይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰሩ ሰራተኞች የጦር መሳሪያ እንዳይዙ ፣ በስራ ወቅትም ወታደሮች ካልሆኑት ጋር ተመድበው እንዲሰሩ መመሪያ ተላልፏል።

Thursday, December 1, 2016

ከሚኒስትሮች ጀምሮ እስከ ታችኛው ዕርከን ድረስ በስልጣን ላይ የሚገኙ ባለስልጣናት የህወሃት አገልጋዮች መሆናቸውን አንድ የኤምባሲ ባልደርባ ተናገሩ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
አሁን በስልጣን ላይ ባለው ስርዓት ውስጥ ከሚኒስትር ጀምሮ እስከታችኛው ዕርከን የሚሰሩ በሙሉ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ አገልጋዮች መሆናቸውን በጀርመን ፍራንክፈርት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባልደርባ የነበሩ ገለጹ። ከስርዓቱ ጋር በመቆየታቸው መጸጸታቸውንም የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ ጠይቀው ከህዝብ ጎን በመሰለፍ ለለውጥ እንደሚሰሩም አስታውቀዋል።

የዶ/ር መረራ ጉዲና መታሰር በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት ዶ/ር መረራ ጉዲናን ለእስር መዳረጉን በሃገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ አለመረጋጋት ሊወስደው እንደሚችል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሃሙስ ገለጸ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) አመራር በቁጥጥር ስር መዋላቸው ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ የተካሄደ አፈና ነው ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ሃላፊ የሆኑት ሚቼሌ ካጋሪ አስታውቀዋል።
መንግስት የወሰደው ዕርምጃም በሃገሪቱ ያለውን ውጥረት እንደሚያባብሰው ያሳሰቡት ተወካዮዋ እርምጃው በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ ለሚከታተሉ አለም አቀፍ አካላት ጥሪን ያስተጋባ ነው ሲሉ አክለው ገልጸዋል።

ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲመቻች ጥሪ ቀረበ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባላት ህብረቱ ለእስር በተዳረጉት ዶ/ር መረራ ጉዲና ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ እንዲያመቻቹ ጥሪ ማቅረባቸውን ዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ ሃሙስ ዘገበ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር መረራ በኢትዮጵያ ተደንግጎ የሚገኘውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መመሪያን ተላልፈው ተገኝተዋል በሚል ረቡዕ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
የፓርቲው አመራር ዶ/ር መረራ ከአንድ ሳምንት በፊት የአውሮፓ ህብረት ዋና መቀመጫ በሚገኝበት ብራሰልስ ተገኝተው ከህብረቱ የፓርላማ አባላት ጋር ውይይት ማካሄዳቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በሽያጭ በማቅረብ ላይ ነው ተባለ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
የኢትዮጵያ መንግስት ለጎረቤት ደቡብ ሱዳን የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በሽያጭ በማቅረብ ላይ መሆኑን የሃገሪቱ አንድ የመገናኛ ብዙሃን ተቋም በብቸኝነት አግንቼዋለሁ ያለውን ሚስጢራዊ መረጃ ዋቢ በማድረግ አጋለጠ።

ባለፉት 10 ወራት ብቻ ወደ 90ሺ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በስደት የመን መግባታቸውን ተመድ ገለጸ

ኢሳት (ኅዳር 22 ፥ 2009)
ባለፉት 10 ወራቶች ብቻ ወደ 90ሺ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በስደት የመን መግባታቸውን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን አስታወቀ።
ጦርነት ዕልባት ወዳላገኘባት የመን የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ስጋት እንዳደረሰባት የገለጸው ድርጅቱ ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ከ70ሺ የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን ወደ ሃገሪቱ ገብተው እንደነበር አውስቷል።