Tuesday, January 5, 2016

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለአለም የጤና ድርጅት መሪነት ሊወዳደሩ ነው

ታኀሳስ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሚኒስትሩ የውጭ ጉዳይ ስልጣናቸውን በመልቀቅ ለአለም የጤና ድርጅት መሪነት ሊወዳደሩ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ታውቋል። ዶ/ር ቴዎድሮስ ሰሞኑን ወደ ጄኔቫ የሚመጡ ሲሆን፣ ለመመረጥ የቅስቀሳ ( ሎቢ) ስራ ይሰራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የድርጅቱ ሰራተኞች ዶ/ር ቴዎድሮስ የንጹሃን ዜጎችን ደም በማፍሰስ የሚወነጀለው የህወሃት/ኢህአዴግ አንዱ ከፍተኛ መሪ በመሆናቸው ኢትዮጵያውያን ተቃውሞዋቸውን ፊርማ በማሰባሰብና ለድርጅቱ ደብዳቤ በመጻፍ እንዲገልጹ ጥሪ አቅርበዋል።

No comments:

Post a Comment