Sunday, January 17, 2016

ሰበር ዜና – በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች መኝታ እየተቃጠለ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የቀጠለው ሕዝባዊ ቁጣ እየተባባሰ በመጣበት ባሁኑ ወቅት በዛሬው ዕለት በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች መኝታ ቤት እየተቃጠለ መሆኑ ተሰማ::
ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የእሳት አደጋው አንዱን የተማሪዎች ህንፃ እያወደመው ይገኛል:: ተማሪዎች ከክፍላቸው ወጥተው እሳት አደጋውን ለማጥፋት እየተረባረቡ እንደሆነ የሚገልጹት የዓይን እማኞች እስካሁን የተጎዳ ተማሪ እንዳላዩ ገልጸዋል::
እሳት አደጋውን ያስነሳው ምክንያት እና ምን እንዳስነሳው የተረጋገጠ ነገር የለም:: ሆኖም ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን እያሰባሰበች ትገኛለች::

No comments:

Post a Comment