Wednesday, January 13, 2016

የወያኔ ሰራዊት እርስ በእርሱ ተታኮሱ ከፍተኛም ጉዳት ደረሰ ተባለ

የመላዉ ኢትዮጵያ ህዝቦች ጠላት የሆነዉ እራሱን የትግራይ ነጻ አዉጭ ብሎ የሚጠራዉ የግፈኞች ስብስብ የሆነዉ ጎጠኛዉ ወያኔ በተለያዩ ከተሞች በዉትድርና ላይ ተሰማርተው የነበሩ የኦሮሞና የአማራ እንዲሁም የተለያየ ብሔር ያላቸዉን አባላት እና አርባ ምንጭ ላይ ከአሜሪካ ሰራዊት ጋር የነበረዉን መጠነኛ ብርጌድ በትግራይ ክልል ራማ ላይ በአንድነት አሰባስቦ! በካድሬዎቹ አማካኝነት፡
በኦሮሚያ ክልል ላይ የተነሳዉ ንቅናቄ የሚመራዉ በሽብርተኛ ሐይሎች በተለይም በኦነግና ! በርበኞች ግንቦት 7 ! ነዉ።
ዋነኛ አላማዉም ኢትዮጵያን አጥፍቶ ስልጣን በእጁ ማስገባት ብቻ ነዉ! 
ስለዚህም ይህን እንቅስቃሴ በማያዳግም እርምጃ መምታት አላማችን ነዉ!!


በሚል ዲስኩር ወር የዘለቀ ንትርክ እንደነበረ ምንጮች ሲገልጹ።
ከተለያዩ ክፍሎች የተዉጣጣዉ ሰራዊት በበኩሉ እኛ ከዚሁ ህዝብ ነዉ የወጣነዉ!
ለምን ወደዚህ ተነጥለንስ እንድንመጣ ተደረግን@!
ለምንስ ህዝባችን ላይ የማያዳግም እርምጃ እንድንወስድ ታግባቡናላችሁ!
በማለታቸዉ አለመግባባት የተፈጠረ ሲሆን በትናንትናው እለት በአንድ የአማራ ብሔር ተወላጅ ከፍተኛ መኮንን ትእዛዝ መሰረት 98 የሚደርሱ ልዩ ስልጡን ሐይሎች ከዚሁ ስብስብ ከሰራዊቱ በመነጠል እና ከራማ በመነሳት የወያኔን ወታደራዊ ቀለበት ቦርደር ጥበቃ ደምስሰዉ 23 ያህሉን በመግደል እና 13 በማቁሰል አስቸጋሪና ከባድ ዳገታማ ተራራ ወደ ሆነዉ አዲ በቕዩ በመገስገስ ላይ ሳሉ በድጋሚ ከተከታተላቸዉ የወያኔ ሐይል ጋር ተፋልመዉ ከ70 በላዩ በአዲቛላ ወደ ጎረቤት ሐገር በሰላም አልፈዉ መግባታቸዉ ከስፍራዉ እየተነገረ ነዉ።
ዛሬ በደረሰን መረጃ መሰረት ከወያኔ በኩል በአጠቃላይ 54 ቅጥረኞች መደመሰሳቸዉን ከስፍራዉ የደረሰን ምንጭ የወታደራዊ መረጃዉን ተነርተርሶ የገለጸ ሲሆን ድንበር ዘለል የእርስ በእርሱ ዉጊያ የፈጠረዉ ድባብ ዛሬም በራማ አካባቢ የሰፈረዉን ሰራዊት እንዳስደነበረዉ ለመረዳት ተችሏል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

No comments:

Post a Comment