Saturday, December 12, 2015

በሰሜን ጎንደር መተማ ላይ እየሆነ ያለው ይህ ነው። በአጋዚ ዘረኛ ጦር የተገደሉ አማሮች!!!

በተጨማሪም ለጉልበት ስራ በመተማ በኩል ወደ ሱዳን የገቡ ኢትዮጲያዊያን ወጣቶች በጥይት ተጨፈጨፉ!!

ለማሽላ ቆረጣ በአንድ ሱዳናዊ ባለሃብት አማካኝነት ወደ ሱዳን ከገቡ የጉልበት ሰራተኞች መካከል ከ100 በላይ የሚሆኑት ኢትዮጲያዊያን ወጣቶች በሱዳን መከላከያ ሰራዊት በጂምላ መጨፍጨፋቸውን የአርበኞች ግንቦት ፯ ድምፅ የራዲዮ ዜና ምንጮች ገለጹ፡
፡ምጮቻችን አያይዘው እንደገለፁት በገፍ የተጨፈጨፉት ኢትዮጲያውያን አስከሬኖቻቸው አለመቀበሩን እና በየቦታው ወድቆ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡የሱዳን መከላከያ ሰራዊት ኢትዮጲያዊያኑን በገፍ የጨፈጨፈበት ምክኒያት እስካሁን በውል አልታወቀም፡፡
ይሁንና የኢትዮጲያዊያኑን በገፍ መጨፍጨፍ የወያኔ ኢህአዴግባለስልጣናት ቢሰሙም ለግድያው ትኩረት አለመስጠታቸው ታውቋል፡፡እዲያውም ይባስ ተብሎ የሰሜን ጎንድር ዞን ገዢ አቶ ግዛት አብየ ሟቾቹ በህገወጥ መንገድ ድንበር ጥሰው የገቡ ናቸው በማለት ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው እየተገለፀ ነው፡፡
ቢሆንም ግን መተማ እና አካባቢዋ ውጥረት ነግሷል፡፡ የወያኔ ባለስልጣናት የኢትዮጲያን መሬት ለሱዳን አሳልፈው ለመስጠት ሽርጉድ እያሉ በሚገኝበት ዋዜማ የጅምላ ግድያው መፈፀሙ የአካባቢውን ህዝብ ይበልጥ እንዳስቆጣው ለማውቅ ተችሏል፡፡

No comments:

Post a Comment