Thursday, December 24, 2015

የዞን 9 ጦማሪያን በአቃቤሕግ ይግባኝ ተጠየቀባቸው

ታኀሳስ ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በነሶልያና መዝገብ ከሽብር ነፃ የተባሉት አምስት ተከሳሾች ላይ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ያቀረበው ይግባኝ ያስቀርባል በሚል ለታኅሣሥ 20 ቀን 2008 እንዲቀርቡ ተብለዋል።
መጥሪያው የደረሰው የበፍቃዱ ኃይሉ ሰነድ እንደሚያሳየው ይግባኝ የተባለባቸው በሌለችበት የተከሰሰችው ሶልያና ሽመልስ እና በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አጥናፉ ብርሀኔ እንዲሁም አቤል ዋበላ ናቸው። በፍቃዱ ኃይሉ የተቀየረለትን ‘አመጽ የማነሳሳት’ የወንጀል አንቀጽ ለመከላከል ለጥር 30, 2008 መቀጠሩ ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment