Thursday, December 3, 2015

በጎንደር ዩንቨርስቲ ከፍተኛ ተቃውሞ በተማሪዎች ተነስቷል::

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – የጎንደርን ህዝባዊ አመፅ የቋራ ገበሬዎች እና የጎንደር ዮኒቨርስቲ ተማሪዎች ተቀላቀሉ። ዛሬ ከሰአት በሃላ ጀምሮ የቆራ ገበሬዎች የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግሬ ይጠቀምባቸዉ የነበሩትን የእርሻ መሳሪያ በማዉደም አመፁን ተቀላቅለዋል።በተያያዘ ዜና ከሸዲ ተነስቶ ወደ ጎንደር በማምራት ላይ የነበረ ሚኒባስ ነጋዴ ባህር ላይ በጥይት ተመትቶ ሰዎች መሞታቸዉ ከአካባቢዉ የመጡ ታማኝ ምንጮቾ ጠቁመዋል። መላዋ ጎንደር የስጋት ቀጠና ሁናለች።ጎንደር ዩኒቨርስቲ ማራኪ ካምፓስ ጎን የከባድ መሳሪያ ተኩስ ከተማዋን እያናወጣት ነዉ።

የጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ወያኔ ሌባ ፣ወያኔ ሌባ፣ ይለያል ዘንድሮ በማለት ድምጽ እያሰሙ ሲሆን በርካታ ቁጥር ያላቸው የፌድራል ፖሊስ ወደ ግቢው በመግባት ላይ ናቸው::አንገረብ አካባቢ የሚገኝ እስር ቤት እየነደደ ነው። ፒያሳ ማንም ነዋሪ አይንቀሳቀስም። ዩኒፎርም የለበሱ ትግርኛ ብቻ የሚናገሩ የልዩ ጦር አባላት ብቻ ይታያሉ;በተለምዶ ዘይት መጭመቂያ በሚባለው18 መስጊድ ኮሌጂ አካባቢ እስረኞችን ፍለጋ በሚል ቤት ለቤት ፍተሻ የሚደረግ ሲሆን ፣ህዝቡን የማንገላታት እና ፣በቤት ውስጥ የተገኜን ውድ ንብረት ከየት አመጣኽው በሚል የመቀማት ስራ እየተፈፀመበት ነው።
የጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ወያኔ ሌባ ፣ወያኔ ሌባ፣ ይለያል ዘንድሮ በማለት ድምጽ እያሰሙ ሲሆን በርካታ ቁጥር ያላቸው የፌድራል ፖሊስ ወደ ግቢው በመግባት ላይ ናቸው::አንገረብ አካባቢ የሚገኝ እስር ቤት እየነደደ ነው። ፒያሳ ማንም ነዋሪ አይንቀሳቀስም። ዩኒፎርም የለበሱ ትግርኛ ብቻ የሚናገሩ የልዩ ጦር አባላት ብቻ ይታያሉ;በተለምዶ ዘይት መጭመቂያ በሚባለው18 መስጊድ ኮሌጂ አካባቢ እስረኞችን ፍለጋ በሚል ቤት ለቤት ፍተሻ የሚደረግ ሲሆን ፣ህዝቡን የማንገላታት እና ፣በቤት ውስጥ የተገኜን ውድ ንብረት ከየት አመጣኽው በሚል የመቀማት ስራ እየተፈፀመበት ነው።

No comments:

Post a Comment