Monday, December 21, 2015

ሰበር ዜና በኦጋዴን ነጻ አዉጭ በአርበኞች ግንቦት 7 እና በጥምር ሐይሎች በሁለት አቅጣጫዎች ከፍተኛ ጦርነት ተቀሰቀሰ

በኦጋዴን ነጻ አዉጭ በርበኞች ግንቦት 7 እና በጥምር ሐይሎች በሁለት አቅጣጫዎች ከፍተኛ ጦርነት ተቆስቁሶ ነገር ግን የመጨረሻ የማጥቃት እርምጃ ለመዉሰድ ታግደናል እየተደበደብን ነዉ፤፤
ይላል የወያኔ መንግስት የሰሜኑ እና የምስራቁ እዝ።

ዛሬ ለሊት ከ23፡00 ሰአት ጀምሮ በሰሜን ጎንደር ልዩ ኮዱ 13.274645/ 37. 878478 በሰሜን ኦጋዴን ጋላዲ ጠረፍ አካባቢ ከባድ ዉጊያ ገጥሞናል በተለይ ሰራዊታችን በአየር ሐይሉ ላይ ምንም እምነት የለዉም፤፤
ዞሮ ሁሉ ሊደበድበን ይችላል ቃኘዉ አየር ሐይል በረራዎችም እያመጡ ያለዉ መረጃ ምንም የትም የማያደርስ ነዉ።
በየ ወቅቱ በሚቆሰቆሱ ግጭቶች ጉዳት እየደረሰብን ነዉ።
ከመከላከያ መሳሪያ ግምጃ ቤት የመጡልን መሳሪያዎች ያረጁና ከፍተኛ እድሳት ይፈልጋሉ።
ከፍተኛ ተጠሪነቱ ለመአከላዊ መንግስት የሆነ ሐይል ተቋቁሞብን እርስ በእርሳችን መግባባት አቅቶናል፤፤
የመሳሰሉት የዛሬዉ የወያኔን መከላከያ ቢሮ ደህንነትን ያጨናነነቀ ጩህት ነዉ፡፡
መከላከያ ሰራዊቱ ጥቃት ወይም ወረራ ለማድረግ ከፍተኛ ሰራዊት እያከማቸባቸዉ በሚገኙት በሰሜኑ አካባቢዎች አለመረጋጋት ነግሰዋል፤፤
በትናንትናዉ እለት አንድ ጓድ መሪ 9 የሰራዊት አባላትን ከመመሪያ ዉጭ ይዞ በመንቀሳቀሱ እርሱን ለመከተል ፍለጋ ላይ የነበረ አነስተኛ የጦር ክፍል የኤርትራን ቄጠና አልፎ በመሄዱ ተደምስሷል።
ኤርትራም ሰራዊቷን በኢትዮጵያ ቦርደሮች ላይ አጠራቅማለች ዉጥረቱ እጅግ ተባብሶ መቀጠሉን ከስፍራዉ የደረሰን መረጃ አመለከተ!!! ጉድሽ ወያኔ

No comments:

Post a Comment