Friday, December 22, 2017

በካራሚሌ ከተማ ህዝቡ ለመከላከያ ሰራዊት አገልግሎቶችን ባለመስጠት ተቃውሞውን እየገለጸ ነው።

ወታደሮቹ ወደ ከተማው ገብተው ማረፊያ ቦታ በጠየቁበት ወቅት የወረዳው ባለስልጣናት ፣ “ እናንተ በክልሉ ትዕዛዝ ስላልመጣችሁም ማረፊያ ቦታ ልንሰጣችሁ አንችልም “ በማለት ቢሮዋቸውን ቆልፈው ሲሄዱ፣ ወታደሮቹ ቢሮዎችን እየሰበሩ ገብተው ተቀምጠውባቸዋል። በድርጊቱ የተቆጣው ህዝብ ለወታደሮች ምንም አይነት አግልገሎት ላለመስጠት ቃል የገባ ሲሆን፣ ወደ ሱቆች በመሄድ ውሃ ለመግዛት ሲጠይቁ እንኳን ከፍተኛ ዋጋ ተጠይቀዋል። በህዝቡ አድማ ምንም ለማድረግ ያልቻሉት ወታደሮች ከሶስት ቀናት በፊት አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል። 
መከላከያ ከክልሉ እንዲወጣ የሚጠይቁ በርካታ የተቃውሞ ሰልፎች ዛሬም ተደርገዋል። በአምቦ፣ ጊንጪ፣ ጉደር፣ ግንደበረት፣ እና በሌሎችም የምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች የስራ ማቆም አድማ ሲደርግ ውሎአል። መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ሆነው ውለዋል። የንግድ ድርጅቶችና ባንኮችም ተዘግተዋል። የስራ ማቆም አድማው ለሚቀጥሉት 3 ቀናት ቀጥሎ እንደሚውል ታውቛል።በካራሚሌ ከተማ ህዝቡ ለመከላከያ ሰራዊት አገልግሎቶችን ባለመስጠት ተቃውሞውን እየገለጸ ነው። 

ወታደሮቹ ወደ ከተማው ገብተው ማረፊያ ቦታ በጠየቁበት ወቅት የወረዳው ባለስልጣናት ፣ “ እናንተ በክልሉ ትዕዛዝ ስላልመጣችሁም ማረፊያ ቦታ ልንሰጣችሁ አንችልም “ በማለት ቢሮዋቸውን ቆልፈው ሲሄዱ፣ ወታደሮቹ ቢሮዎችን እየሰበሩ ገብተው ተቀምጠውባቸዋል። በድርጊቱ የተቆጣው ህዝብ ለወታደሮች ምንም አይነት አግልገሎት ላለመስጠት ቃል የገባ ሲሆን፣ ወደ ሱቆች በመሄድ ውሃ ለመግዛት ሲጠይቁ እንኳን ከፍተኛ ዋጋ ተጠይቀዋል። በህዝቡ አድማ ምንም ለማድረግ ያልቻሉት ወታደሮች ከሶስት ቀናት በፊት አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል። 
መከላከያ ከክልሉ እንዲወጣ የሚጠይቁ በርካታ የተቃውሞ ሰልፎች ዛሬም ተደርገዋል። በአምቦ፣ ጊንጪ፣ ጉደር፣ ግንደበረት፣ እና በሌሎችም የምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች የስራ ማቆም አድማ ሲደርግ ውሎአል። መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ሆነው ውለዋል። የንግድ ድርጅቶችና ባንኮችም ተዘግተዋል። የስራ ማቆም አድማው ለሚቀጥሉት 3 ቀናት ቀጥሎ እንደሚውል ታውቛል።

No comments:

Post a Comment