Thursday, December 14, 2017

የጥበቃ ሰራተኞች እየተማረሩ ነው

በአገሪቱ የሚታየውን ውጥረት ተከትሎ በተለያዩ ተቋማት በጥበቃ ላይ የተሰማሩ የመከላከያ አባላት፣ ፖሊሶችና የጥበቃ ሰራተኞች ያለ እረፍት ጥበቃ እንዲያካሂዱ መታዘዛቸውን ተከትሎ ተቃውሞው ማሰማት ጀምረዋል።
የጥበቃ ሰራተኞች “ ደፍርሶ በጠራ” የሚል አስተያየቶች እየሰጡ ሲሆን፣ ትእዛዝ ለመቀበል አሻፈረን እያሉ ነው። በተለይ የመከላከያ አባላት ጥያቄዎችን እያነሱ መገኘታቸው ለወታደራዊ አዛዦች ራስ ምታት እየሆነ መምጣቱን ምንጮች ገልጸዋል።
በተለይ የአማራና የኦሮሞ ብሄር የመከላከያ ሰራዊት አባላት አጋዚ የተባለው ጦር በህዝብ ላይ የሚፈጽመውን ጥቃት እየተቃወሙ በመምጣታቸው በስምሪት ስም ተቃውሞ ሊያስተባብሩ ይችላሉ የተባሉት ወታደሮች እየተለ ወደተለያዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ ጥበቃ እየተደረገባቸው ነው።

No comments:

Post a Comment