Wednesday, October 14, 2015

በአቶ ሃብታሙ አያሌው መዝገብ የተከሰሱት የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች በድጋሜ ተቀጠሩ

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሰው በ19ኛው ወንጀል ችሎት ነጻ የተባሉት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ሃብታሙ አያሌው፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ም/ል ሰብሳቢ የነበረው የሽዋስ አሰፋ፣ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ም/ል ስብሳቢና የደቡብ ተወካይ የነበረው ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም አብርሃም ሰለሞን ፣ ዛሬ ጠ/ፍርድ ቤት ቀርበው፣ በአቃቢ ህግ የተጠየቀባቸው ይግባኝ ትክክል አይደለም በማለት ለመከራከር ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ በመስጠት ጉዳዩን ሳያየው ቀርቷል።

ፍርድ ቤቱ በአቃቢ ህግ የቀረበውን ተቃውሞ መርምሮ ጥቅምት 17 ቀን 2008 ዓም ውሳኔ ይሰጣል።

No comments:

Post a Comment