Thursday, October 22, 2015

አስራ አምስት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ኬንያ ውስጥ ተያዙ

ጥቅምት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኬንያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሳምብሩ ምስራቃዊ ኢዞሎ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሎሲሳ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ገቡ ያላቸውን አስራ አምስት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ማሰሩን አስታውቋል።

ባለፈው እሁድ ሃያአራት፣ ሰኞ ደግሞ ስድስት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በአካባቢው በታጣቂዎች በከበባ መያዛቸውን ገልጸዋል።ስደተኞቹ በሕገወጥ መንገድ ካለምንም ሕጋዊ ፍቃድ ድንበር አቋርጠው እንደሚገቡና አስራ አምስቱ ኢዞሎ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን የጸጥታው ሹም ኪፑቺምፓ ሮቶ መናገራቸውን ኦል አፍሪካ ዘግቧል።
ገዥው ኃይል በኢትዮጵያ ኤኮኖሚያዊ ለውጥ አምጥቻለው እያለ በመገናኛ ብዙሃን ቀን ከሌት ቢናገርም፣ ሕይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው የሚወጡ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ሲጨምር እንጅ ሲቀንስ አይታይም።

No comments:

Post a Comment