Wednesday, October 21, 2015

እንግሊዝ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጉዳይ ቅደሚያ እንድትሰጥ በድጋሜ ተጠየቀች

 ኢሳት ዜና :-በእስር ላይ የሚገኙትን የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ህገወጥ እስር አስመልክቶ የእንግሊዝ ባለስልጣናት ነገ በሚጀመረው የኢትዮጵያና የእንግሊዝ የንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ ላይ ሊያነሱት እንደሚገባ አቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ የሚከታተለው ሪፕሪቭ የተባለው ተቋም ጠይቋል።

የንግድ እና የኢንቨስትመንት ስብሰባው ከፍተኛ ቦታ የተሰጠው እንደመሆኑ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ግራንት ሻፕስ ለኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጉዳይ ማንሳት ይኖርባቸዋል ብሎአል። ሪፐርቭ አቶ አንዳርጋቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ እየጠየቀ ባለበት ሁኔታ፣ የእንግሊዝ ባለስልጣናት ግን ስለ አማካሪና ስለህግ ሂደት ያወራሉ በማለት ተችቷል። እንግሊዝ የነገውን አጋጣሚ በመጠቀም አቶ አንዳርጋቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ መጠየቅ አለባት ሲል ድርጅቱ አክሎ ገልጿል።

No comments:

Post a Comment