Monday, October 19, 2015

በአዋሽ መልካሳ አንድ የፌደራል ፖሊስ ተገደለ

ጥቅምት ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፖሊሱ የተገደለው በከተማዋ ውስጥ ከሚገኙ ወጣቶች ጋር ተጣልቶ ነው። ፖሊሶች አንድ የግሮሰሪ ሰራተኛን ሲደበድቡ ፣ ወጣቶች በብስጭት በፌደራል ፖሊሱ ላይ እርምጃ መውሰዳቸውን ለማወቅ ተችሎአል።

በከተማዋ ከፍተኛ ግርግር መኖሩን የተናገሩት ነዋሪዎች፣ በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት ገዳዮችን ለመያዝ ጥረት እያደረጉ ነው። የከተማው ወጣቶች የፌደራል ፖሊስ አባላት ከፍተኛ የሆነ ጫና እንደሚፈጥሩባቸው ለኢሳት ገልጸው፣ አሁኑ እርምጃም በወጣቶችና በፖሊሶች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ መሄዱን ያሳያል ብለዋል። “ህዝቡ ቢናገር፣ ቢደበደብ ችግሩን የሚያይለት የለም” የሚሉት ነዋሪዎች፣ በከተማው የተሰማራው የፌደራል ፖሊስ በወጣቱ ላይ የፈለገውን የማሰቃያ ድርጊት እየፈጸመ መሆኑን ይገልጻሉ።

No comments:

Post a Comment