Thursday, October 22, 2015

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሎሚ መፅሄት ማኔጂንግ ደይሬክተር ላይ የ 18 አመት እስር በየነበት !!


የሎሚ መፅሄት ማኔጂንግ ዳይሬክተርና ባለቤት የሆነው ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ ላይ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ 18 አመት እስራትና የ 100 ሺህ ብር ቅጣት ሲበየንበት በመፅሄቱ አሳታሚ ድርጅት ላይ ደግሞ የ 200 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት በዛሬው ዕለት በሌሉበት ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስተላልፎል!
ከ 800 ሺህ ብር በላይ ታክስ በማጭበርበርና በሌሎች 14 ክሶች ጥፋተኛ የተባለው የሎሚ መጽሄት ዋና ስራ አስኪያጅ በ 18 ዓመት ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ ተወሰነ.
በመጽሔታቸው በወጡ ጽሁፎች ድርጅቱና ሥራ አስኪያጆቹ ሐሰተኛ ወሬ አትሞ በማውጣትና ሕዝብን በማነሳሳት ወንጀል ‘በሚሉ ሁለት ክሶች ሰኔ 6 ቀን 2006 ዓ.ም በኢትዮጵያ ፍትሕ ሚኒስቴር መከሰሳቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤት ቆመውም ነበር.

No comments:

Post a Comment