Thursday, October 15, 2015

በሁመራ ከ500 በላይ የሞተር አሽከርካሪዎች ስራ እንዲያቆሙ ታዘዙ

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሞተር ሳይክል ሰዎችን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ህይወታቸውን የሚመሩ 500 ያክል ወጣቶች ስራ እንዲያቆሙ በመታዘዛቸው ችግር ላይ መውደቃቸውን ተናግረዋል።

ሰራተኞቹ በድንገት አቁሙ በመባላቸው፣ ቤተሰቦቻቸውን ለማስተዳደር ተቸግረዋል። መንግስት አማራጭ ስራ ሳይፈጥር በድንገት ስራ አቁሙ ማለቱ ተገቢ አይደለም በሚል ወጣቶቹ ያስነሱትን ተቃውሞ ተከትሎ የወረዳው ባለስልጣናት ተጨማሪ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥተዋል።
አንድ ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ ወጣት እንዳለው ሞተረኞች ለጸረ ሳላም ሃይሎች የተለያዩ መሳሪያዎችን ያቀብላሉ በሚል ምክንያት ለመቅጣት ታስቦ የተደረገ ነው ብሎአል።
ከተማው በቂ የትራንስፖርት አገልግሎት ሳይኖረው፣ የህዝቡን የትራንሰፖርት አግልግሎት ችግር በመቅረፍ ላይ እያለን መበረታታት ሲገባን፣ ስራ አቁሙ መባላችን ተገቢ አይደለም በማለት ወጣቶች ተቃውሞአቸውን ለኢሳት ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment