Wednesday, October 28, 2015

በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች የዲሽ ተጠቃሚው ቁጥር እየጨመረ ነው

ጥቅምት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወኪላችን በአዲስ አበባ የተለያዩ መንደሮች በመዘዋወር ባደረገው ቅኝት እጅግ ደሃ በሚባሉት መንደሮች ሳይቀር በዲሽ ከውጭ አገር የሚለቀቁ ስርጭቶችን የሚያየው ህዝብ ቁጥር ጨምሯል ብሎአል።

በፎቶ ግራፍ አስደግፎ በላከው መረጃ ፣ የዲሽ ቁጥር መጨመር ህዝቡ የኢሳትን የናይል ሳት ስርጭት በብዛት እየተከታተለ መሆኑን ማሳየት ብቻ ሳይሆን፣ የመንግስቱን የቴሌቪዥን ስርጭት ለመስማት ፍላጎት እንደሌለውም የሚያመለክት ነው ብሎአል።

No comments:

Post a Comment