Thursday, October 15, 2015

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪዎች በፈጠሩት ችግሮች የኦሞና የቱርካና ሃይቅ የመድረቅ አደጋ ከፊታቸው ተጋርጧል ተባለ

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኙት የቱርካና ሃይቅና የኦሞ ወንዝ ኢትዮጵያ በምትከተለው የኢንዱስትሪ ዘመቻ ምክንያት የመድረቅ እና የአየር ንብረት መዛባት አደጋን ማስከተሉንና በዚህም ለውጥ ሳቢያ የአካባቢው ነዋሪዎች ስጋት ውስጥ መሆናቸውን ሂውማንራይትስ ወች በጥናት ሪፖርቱ አመልቷል።

በሰሜናዊ ምዕራብ ኬንያ በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ የሚገኘው የቱርካና ሃይቅ በዓለማችን በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ከሚገኙት ታላላቅ ሃይቆች አንዱ ሲሆን ዘጠና በመቶ የሚሆነውን ውሃ ከኦሞ ወንዝ ያገኛል። ኢትዮጵያ ግድቦችን በመስራት የውሃውን ፍሰቱን በማቆሟ ምክንያት በኦሞ ሸለቆ ውስጥ የሚኖሩ አርብቶ አደር ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያንን ጨምሮ በአካባቢው የአየር ንብረት ላይ መዛባት ስለሚያስከትል ነዋሪዎቹ ለችግር ተጋልጠዋል።
ወንዙን ለሸንኮራ አገዳ ምርት ለመጠቀም መታሰቡ የአርብቶ አደሩን የወደፊት ዕጣ ፈንታና ዝርያቸው አናሳ የሆኑትን ዜጎች በህልውና ስጋት ውስጥ እንዲወድቁ አድርጓቸዋል። የተባበሩት መንግስታትን ጨምሮ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የኢትዮጵያ መንግስት የአካባቢውን ነዋሪዎች ያማከለ የልማት ዕቅድ ተግባራዊ እንዲያደርግ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

No comments:

Post a Comment