Thursday, October 29, 2015

በጋምቤላ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ሁለት ሰራተኞችን ገደሉ

ጥቅምት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኑዌር ዞን ዋና ከተማ ከሆነቸው ንያንግ 30 ኪሜ ራቅ ብሎ በሚገኘው የህንዱ ካራቱሪ ኩባንያ አጠገብ በሚገኘው አንዱራ የአነስተኛ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት ዙሪያ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የደቡብ ዲዛይንና ግንባታ ሲፐርቪዥን ኢንተርፕራይዝ ሰራተኛ የሆኑት ኢንጂር ሙሉጌታ ደሳለኝ እና የጋምቤላ የእርሻ ቢሮ ሰራተኛ የነበሩት ወ/ሮ ሃይማኖት ተገድለዋል። የሁለቱም ሰዎች አስከሬን ማታ ወደ አዲስ አበባ ተልኮ በሚኒሊክ ሆስፒታል ምርምራ ከተደረገበት በሁዋላ፣ የኢንጂነር ሙሉጌታ አስከሬን ወደ ነቀምት፣ የወ/ሮ ሃመልማል ደግሞ ወደ ናዝሬት ተልኳል።የአካባቢው ሰዎች እንደሚናገሩት ግድያው የተፈጸመው ከመሬት መቀራመት ጋር ተያይዞ ያካባቢው ነዋሪዎች በየጊዜው ከሚያነሱት ተቃውሞ ጋር የተያያዘ ነው።

በዚሁ ፕሮጀክት አካባቢም ከወራት በፊት ማቲያስ ዘነበ የሚባል ሰራተኛ ተገድሏል።

No comments:

Post a Comment