Friday, October 16, 2015

የኔዘርላንድስ ፖሊስ አንድ በቀይ ሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ኢትዮጵያዊን አሰረ

ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ማንነታቸው ያልተገለጸው የ61 አመቱ ኢትዮጵያዊ አምሰተልፊን በምትባል ከተማ ውስጥ የተያዙ ሲሆን፣ ግለሰቡን ወደ ኢትዮጵያ ይመለሱ ወይም አይመለሱ የሚልውን ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ የ90 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ግለሰቡ በደብረማርቆስና መተከል አውራጃዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸውንና ማሰራቸውን በውጭ አገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን መረጃ መሰብሰቡን ፖሊስ አስታውቋል። በግለሰቡ ላይ ቀድም ብሎ የሞት ፍርድ ተፈርዶ የነበረ ቢሆንም፣ ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ እስር መለወጡን የጠቀሰው የፍትህ ሚኒስቴር ዘገባ፣ በፍተሻ ወቅት 2 ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት እና ወታደራዊ ዶክመንቶች መገኘታቸውን ገልጿል። ግለሰቡ የሆላንድ ዜግነት ያለው ሲሆን፣ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ነው ብሎ ካመነ የዜግነት መብቱን በማንሳት ወደ ኢትዮጵያ ሊልከው ይችላል።

No comments:

Post a Comment