Thursday, October 29, 2015

በሰቆጣ ከፍተኛ የውሃ ችግር ተፈጥሯል

ጥቅምት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነዋሪዎች እንደሚሉት ከድርቁ ጋር ተያይዞ የውሃ ችግሩ በመባባሱ ፣ ህዝቡ ውሃ ለማግኘት በእጅጉ ተቸግሯል።

የውሃ ችግሩ በመባባሱና በየአካባቢው የሚታየው የውሃ ጀሪካም ብዛት ” ሳምንቱን ” ቢጫው ሳምንት” አስብሎታል በማለት ነዋሪዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የውሃ ችግሩ ከሰቆጣ በተጨማሪ በተለያዩ አገሪቱ ክፍሎች ይታያል።
በሌላ በኩል ደግሞ ክልሉን እመራዋለሁ የሚለው ብአዴን ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በማውጣት በአሉን ለማክበር እንቅስቃሴ ላይ ነው። ከዚሁ በአል ጋር ተያይዞ ለብአዴን ገንዘብ አናዋጣም ያሉ ነጋዴዎች ክትትል እየተደረገባቸው ነው።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አብዴን አባላት እንደገለጹት፣ያለፍላጎታቸው መዋጮ እንዲያወጡ ተጠይቀው ፈቃደኛ ያልሆኑ ነጋዴዎች፣ ፋይላቸው ወደ ገቢዎች ቢሮ እየተላለፈና ክትትል እየተደረገባቸው ነው። በነጋዴዎቹ ላይ የሃሰት ወንጀል በማዘጋጀት የበቀል እርምጃ ለመውሰድ ተብሎ እየተሰራ መሆኑን ነጋዴዎች ይገልጻሉ። አባላቱ እንደሚሉት የአብዴን አባላት ወደ አንዳንድ ነጋዴዎች ቤት በመሄድ ገንዘብ ሲቀበሉ ደረሰኝ አይሰጡም።

No comments:

Post a Comment