Saturday, October 24, 2015

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአየር ላይ አደጋ ተረፈ

ኢሳት ዜና :- ሶስት መቶ መንገደኞችን ጭኖ ከአዲስ አበባ ተነስቶ በደብሊን አድርጎ ወደ አሜሪካ ሲጓዝ የነበረው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነው ድሪምላይን 787-8 አውሮፕላን ዛሬ ማለዳ ላይ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር በድንገት አንድ ሞተሩ አየር ላይ ቢጠፋም በአየርላንድ ዋና ከተማ ደብሊን በሰላም ማረፍ ችሏል። መንገደኞቹ ከጀርመን ፍራንክፈርት በተላከ ተቀያሪ አውሮፕላን ወደ አሜሪካ ማቅናታቸውን ሜይል ኦንላይን ዘግቧል።

ባሳለፍነው ሳምንትም ጋምቤላ ውስጥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለማረፍ ሲሞክር አደጋ አጋጥሞት በሰላም ማረፉ ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment