Tuesday, July 31, 2018

Image may contain: one or more people, people standing and outdoorበአብዲ ዒሌ ላይ የሚካሄደው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው
(ኢሳት ዲሲ–ሀምሌ 24/2010)በሶማሌ ክልል በክልሉ ፕሬዝዳንት አብዲ ዒሌ ላይ የሚካሄደው ተቃውሞ መቀጠሉ ተገለጸ።
ላለፉት 3 ወራት በመካሄድ ላይ ባለው ተቃውሞ አብዲ ዒሌ ስልጣን እንዲለቅ ተጠይቋል።
በአውበር ጂጂጋ ዞንና በአፍዴር ዞን ዛሬ የተቃውሞ ሰልፎች መደረጋቸው ታውቋል።
በርካታ ወጣቶች መታሰራቸውንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በሌላ በኩል በጋሞጎፋ ሳውላ ባላፈው ሳምንት የተካሄደውን ግጭት ተከትሎ ከ500 በላይ ሰዎች መታሰራቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።
በጣና በለስ የስኳር ፕሮጀክት ላይ በተፈጸመ ጥቃት ሶስት ሰዎች መገደላቸውም ታውቋል።

No comments:

Post a Comment