Tuesday, July 24, 2018

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደውን ለውጥ እንደግፋለን አሉ

(ኢሳት ዲሲ– ሐምሌ 17/2010) በዋሽንግተን ዲሲ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄደውን የለውጥ እንቅስቃሴ እንደሚደግፉ ገለጹ።
የወንጌል አማኞቹ ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማሕበራዊ መስኮች በተወጠረችባቸው ጊዚያት ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ልመና ሲያደርጉ እንደነበረ ጠቅሰው አሁንም ለተጀመረው የሰላምና የእርቅ ጉዞ የሚችሉትን ሁሉ ለማድረግ ቃል በመግባት መግለጫ አውጥተዋል።
እሁድ ዕለት በዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ጉባዔ ላይ በኢትዮጵያና በኤርትራ መሀል የተደረሰው የሰላም ስምምነት አድናቆት ተችሮታል።

No comments:

Post a Comment