Monday, July 23, 2018

በጅግጅጋ ወጣቶች በአብዲ ኢሌ አገዛዝ ላይ ተቃውሞ አደረጉ

(ኢሳት ዜና ሃምሌ 16 ቀን 2010 ዓ/ም ) ወጣቶቹ ተቃውሞዋቸውን ያሰሙት የአብዲ ኢሌን ፍጹማዊ አገዛዝ በመቃወም እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች ተጠርጥረው የተሳሩ ዜጎች እንዲፈቱ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ እስር ቤቶች እንዲዘጉ ለመጠየቅ ነው። ወጣቶቹ ተቃውሞአቸውን በሚያሰሙበት ወቅት አብዲ አሌ ወታደሮቹን ልኮ ጥቃት እንደሚፈጸምባቸው ማድረጉን አቶ አሊ አብዲ ሃሰን ከጅግጅጋ ገልጸዋል። በጥቃቱ እስካሁን የደረሰውን ጉዳት ለማወወቅ ባይቻልም፣ ብዙ ወጣቶች እንደቆሰሉ የሚደርስን መረጃ ያመለክታል። አዲስ አበባ የሚገኙ የሶማሊ ክልል አገር ሽማግሌዎች ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ሙሃመድ አሊ ጣሂር ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment