Tuesday, July 31, 2018

በሶማሊ ክልል ተቃውሞ ቀጥሎ ዋለ

( ኢሳት ዜና ሃምሌ 24 ቀን 2010 ዓ/ም )ትናንት በራሶም ወረዳ የተጀመረው ተቃውሞ ዛሬ በአፍዴራ ዞን ቀጥሎ ውሎአል። በአፍዴራ ዞን በሙሉ ሰላማዊ ሰልፍ መደረጉን ለክልሉ ተወላጆች መብት መከበር የሚታገለው አቶ ጀማል ድሪሬ ገልጸዋል። የራሶም ወረዳ ተወላጆች የአብዲ አሌን ባለስልጣናት ማስወጣታቸውንና አስተዳደሩን መቆጣጠራቸውን አቶ ጀማል ገልጸዋል። በቅርቡ ዶ/ር አብይ ምሁራንን ሰብስበው ባናገሩበት ወቅት ፣ በክልሉ ያለውን ተቃውሞ በጎሳ መነጽር ለማየት መቻላቸው እንዳሳዘናቸው አቶ ጀማል አክለው ገልጸዋል። አቶ አብዲ ኢሌ የክልሉን ወረዳዎች ከ52 ወደ 99 ወረዳዎች ከፍ ማድረጉ ታውቋል። አብዲ ኢሌ በክልሉ የተነሳበትን ተቃውሞ ለማብረድ ለተለያዩ ጎሳ አባላት ወረዳ እየሰነሸነ መስጠቱን የገለጹት አቶ ጀማል፣ አከላሉም ብዙ ችግሮች ያሉበት መሆኑን ገልጸዋል። ወረዳዎች ሲከለሉ ባህላዊ አሰራርን የጣሱና ግጭት ለመፍጠር ተብለው የተዘጋጁ መሆኑን አቶ ጀማል አክለው

No comments:

Post a Comment