Friday, July 27, 2018

በአወዳይ አንድ ታጣቂ የነበረ ግለሰብ 3 ሰዎችን ገደሎ 5 ሰዎችን ደግሞ አቆሰለ

( ኢሳት ዜና ሃምሌ 20 ቀን 2010 ዓ/ም )ሃሙስ እለት ከአስተዳደር ጥበቃ ስራ የተባረረው ከድር ኢብራሂም የተባለው ታጣቂ በህዝቡ ላይ ጥይት በመተኮስ 3 ሰዎችን ወዲያውኑ ሲገድል 5 ሰዎች ደግሞ ቆስለው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል። ህዝቡ በወሰደው እርምጃም ሰውዬው በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሉ ታውቋል። ግለሰቡ ከስራ ከተሰናበተ በሁዋላ ታጥቆት የነበረውን የጦር መሳሪያ አለማስረከቡን ወኪላችን ገልጿል።

No comments:

Post a Comment