Sunday, July 15, 2018

እስካሁን የባከነውን ጊዜ ለማካካስ እንሰራለን- ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ተለያይተው በነበሩበት ወቅት የተቃጠለውን ጊዜ ለማካካስ እንሰራለን አሉ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ይህን ያሉት በሚሊኒየም አዳራሽ በተዘጋጀ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግስት የሰላም ማብሰሪያ መድረክ ላይ ነው።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በዚሁ ወቅት፥ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ አንድ ህዝቦች ናቸው ማንም ሀይል ሊነጣጥለን አይችልም ብለዋል።
ከዚህ በኋላ ባለው ጊዜም አብረን ወደ ፊት ለመራመድ ቆርጠን ተነስተናል ሲሉም ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment