Tuesday, July 24, 2018

በቃሊቲ ማረሚያ ቤት አምጽ ተቀሰቀሰ

(ኢሳት ዲሲ– ሐምሌ 17/2010) በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከትላንት ሌሊት ጀምሮ አምጽ መቀስቀሱ ተሰማ።
በጥይትና በአስለቃሽ ጢስ በርካታ እስረኞች ተጎድተዋል።
በዞን አራት የሚገኙ እስረኞች እንፈታ የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውን ተከትሎ የተጀመረው አመጽ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከፍተኛ ውጥረት ማንገሱን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
በአከባቢው መንገዶች መዘጋታቸው ተገልጿል።
እስረኞች የድረሱልን ጩሀት እያሰሙ መሆኑም ታውቋል።በተመሳሳይ በደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት በተቀሰቀሰ አመጽ ቤቶች መቃጠላቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በአርባምንጭ እስር ቤት ውስጥም ተቃውሞ ተነስቷል። በርካታ እስረኞች ተጎድተው ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ታውቋል።

No comments:

Post a Comment