Tuesday, July 24, 2018

አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የእውቅና ሽልማት ተበረከተለት

(ኢሳት ዲሲ– ሐምሌ 17/2010) አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ በኢትዮጵያና በኤርትራ መሀል ለተደረሰው የሰላም ስምምነት ላበረከተው አስተዋጾ የእውቅና ሽልማት ተበረከተለት።
በዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የኤርትራውያን ፌስቲቫል ላይ ተገኝተው የእውቅና ሽልማቱን የተረከቡት የንቅናቄው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ናቸው።
በፌስቲቫሉ ላይ የሁለቱ ሀገራትንና የአፍሪካውን ቀንድ ሰላም የተመለከተ ጉባዔ ተካሄዷል። በምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎችም ቀርበዋል።

No comments:

Post a Comment