Tuesday, July 24, 2018

በወለጋ ደምቢዶሎ አንዲት ነፍሰጡር ተገደሉ

(ኢሳት ዲሲ– ሐምሌ 17/2010) በወለጋ ደምቢዶሎ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት አንዲት ነፍሰጡር ተገደሉ።
ቁጥራቸው ለጊዜው በውል ያልታወቁ ሰዎችም ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል።
በባሌ ጎባ የተከሰተው ግጭት ዛሬም መቀጠሉን የገልጹት ነዋሪዎች መንግስት በአስቸኳይ ይድረስልን ሲሉ ጥሪ አድርገዋል።
በባቢሌ በጭናክሰን ውጥረቱ መባባሱን ያገነኘው መረጃ ያመልክታል።
በተያያዘ ዜናም በደሴ ባልታወቁ ሃይሎች በተፈጸመ የስለት መሳሪያ ጥቃት በርካታ ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ታውቋል።

No comments:

Post a Comment